ቶጳዝዮን
በብዕራችን ጥበብን እናነግሳለን። የብዙ ገጣሚያን ስራዎች የሚቀርቡበት ምርጥ ቻናል ነዉ። @topazionnn @topazionnn for any comment👇👇 @ediwub @Tirrubel @balageru_1
Больше823
Подписчики
+724 часа
+477 дней
+9330 дней
Время активного постинга
Загрузка данных...
Find out who reads your channel
This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.Анализ публикаций
Посты | Просмотры | Поделились | Динамика просмотров |
01 ✍✍✍🎙🎙🎙ናትናኤል
@loveyoumoremm
https://t.me/Nothingistruek | 56 | 0 | Loading... |
02 መቼ ትመጫለሽ??
በዔደን ታደሰ እና ኤልሻዳይ(ኤል ቶ)
ተፅፎ እንደቀረበ✍🎤
@ediwub & @elshaday_23
@topazionnn
@topazionnn | 111 | 4 | Loading... |
03 መሰበር ከቅስም በላይ
በልብ ይበረታል
ያልሽኝን ታስታውሻለሽ
አትረሽውም
እንደ ቃልሽ
ፀንተሽ አለሽ
ከስሜት
ምክንያታዊነት ለእምነት
እጅ ከሰጠ
የቱ ጋር ነው የእኛ ታሪክ የበለጠ
ከስሜታችን መታረቅ ተስኖን
በምኞታችን ቅዥት
ሕልማችንን ለመኖር ኃይል ብርታቱን ካጣን
ፍቅር ጀምረን እንጂ የታየን
ከዘለቁት መች ተቆጠርን።
✍ አየሁ ነኝ
@tekle_ayehu | 127 | 0 | Loading... |
04 እንቆቅልሼ ነህ
ያኔ በልጅነት ስንጠያየቅ
መልሱን ለመመለስ ሁሉም ሲጨናነቅ
እንታገል ነበር ፍችውን ለማወቅ
:
:
ዛሬ በኔ ህይወት ይኸው በኔ ኑሮ
ፍች አልተገኘልህ ጥያቄ ለወትሮ
የልቤ ቅኔ ነህ የውስጤ እስትንፋስ
እንቆቅልሼ ነህ የሌለህ ቋሚመልስ
:
:
እባክህ ፍቅርዬ ሀገሬን ስሰጥህ
እንቅቆቅልሽ ስልህ
ምናውቅልሽ ብለህ
ሳይህየማፈሬን የውስጤን መቅለስለስ
የልቤን ጥያቄ ዛሬውኑ መልስ።
✍ ቤዛ
(የተክልዬዋ)
@semetnbegtm
@semetnbegtm
@semetnbegtm | 124 | 2 | Loading... |
05 እያስተዋልን እንጂ የጊዜውን ነገር
እናውራ ካልንማ ስንት አለ የሚነገር።
ያየነውን ሁሉ በሆድ ይፍጀው ዜማ
በማለፋችን ነው የኖርነው እኛማ።
@topazionnn
@topazionnn
@topazionnn | 141 | 0 | Loading... |
06 ህሊና ሲመክር ........
🎙🎙🎙ናትናኤል
@loveyoumoremm
https://t.me/Nothingistruek | 141 | 3 | Loading... |
07 Media files | 1 | 0 | Loading... |
08 Media files | 1 | 0 | Loading... |
09 Media files | 1 | 0 | Loading... |
10 ሰው ዋጋው ወደቀ
የወደቀን ሁሉ ሰንፎ ነው እያልን
ያለቀሰን ሁሉ አስመስሎ ብለን
በሰው ቁስል ፈርደን ህመማቸው ርቆን
ከመሃል ከተማ እስከ ዳር እያየን
ሰው ከዕትብቱ ሲለይ ያልኖረው አለቀ
ለድንጋይ ጌጥ ሲባል ሰው ዋጋው ወደቀ
ልዑል መኮንን @Liulmekonen | 172 | 0 | Loading... |
11 አብረን ከኖርንበት
ፍቅር ልሰራ ስል
መውደድ ላስማማ ስል
የት ነበርሽ አንቺ ግን
ተኝቼ እያለሁ በጡቶችሽ በኩል
እርግጠኛ ነኝ የእኔ ማንነት
ስያሜ አላገኘም ተብሎ አልተጠራም የሰውነት ክፍል
በሕይወት ከኖረ ይሕን ዓመቱ ነው አልሰማሽም ሲባል😀
እውነት ለመናገር
ነገረ ስራሽን ይዠው ቆይቻለሁ
በሀሳቤ በኩል
ነፍስ ከስጋ ጋር ስላላት መነጠል
ከአንቺ የበለጠ ስለማላውቅ ይሕን ንገሪኝ በድንግል
ሚዛን አይሰራም ለአንቺ መኖር ሲባል
ረቂቅ ነሽና አብረን ባሳለፍነው
በዚህ ሁሉ ዓመት ይሕንን ነው የተማርኩ
ሳላይሽ ነው የኖርኩ ሳልጠግብሽ ነው የሞትኩ።
✍አየሁ ነኝ
@tekle_ayehu | 165 | 0 | Loading... |
12 ✍✍✍🎙🎙🎙ናትናኤል
@loveyoumoremm
https://t.me/Nothingistruek | 155 | 5 | Loading... |
13 አንተና ምርጫህ
ምርጫህ ይገርመኛል
ስትዘረዝርማ
ሳቄ ያመልጠኛል😂
ትዝ ካለህ ያልከው
ለእኔ የምትገባው...🙁
ቁመተ መለሎ ወገበ ሸንቃጣ
ገፀ ግቡ እንስት ሳቋ ጎልቶ የወጣ
ዓይኖቿ ያማሩ የሚያደነዝዙ👀
ጥርሶቿ ሲታዩ ልብን የሚገዙ
ቀጥ ያለ አፍንጫ ውብ ከናፍራት👄
ሰፋ ያለ ዳሌ በተፈጥሮ ያላት
ፀጉሯ እረዝሞ የተንዘረፈፈ
ከወገቧ በታች አብቅቶ ያረፈ
ጣቶቿ ያማሩ የሆኑ አለንጋ
ገና ስትራመድ የምትል ሰበርሰካ💃
በሀገር በምድሩ ውበቷየሚያፈዝ
ምኞትክ ነበረ ያቺን እንስት መያዝ
አንተ ግን ስትታይ😲
መልከ ጥፉ ሆነክ የፉንጋ ተምሳሌት
እሷ እንዴት ትይክ ቆይ በምን ስሌት
ያንተ ቁመት አጭር
መልክህ የማያምር
ሆድ ክብ ነገር የመሰለ እርጉዝ
ጣቶችህ ቆልማማ እግሮችህ ደዘደዝ
አፍንጫህ ጎራዳ ጥርሶችህ ወላቃ
ተድበልብለህ ቀረህ ወንበሩም ላይበቃ
ፀጉርህ የገባ እርምጃህ ገዳዳ
ባዶውን የቀረ ኪስህ የተጎዳ
ሆኖ'ኳን ገፅታህ መስፈርት ምታወጣው
ያችን ውብ ኮረዳ የት ልታገኛት ነው
አንተ እንደጠራኸው የቁንጅና መስፈርት
እሷም 'ምትስለው የራሷ ምርጫ አላት
ባይሆን...
ፀጉሬ ቢሆን ኪንኪ ከንፈሬ ባይሆን ማራኪ
በሶ ይበቃኛል ጋብዘኝ አልል ውስኪ
ዓይኖቼ ቢፈዙ እንደ ዜሮ ሻማ
ሳቄ ባይስብም አምሮ ባይሰማ
ቁመቴ ሳይረዝም ብሆን አጠር ያለች
ላንተ ብዬ'ኮ ነው ልታቅፈኝ እንድመች
ምንም ባልሸነቅጥ ባይቀጥን ወገቤ
ላንተ ይበቃካል ምግባርና ሀሳቤ
አጥርተህ ተመልከት እኔ እሻልሀለው
ከሷ ውበት በላይ እመጥንሀለው
@semetnbegtm
@semetnbegtm
@semetnbegtm
✍️የተክልዬዋ | 187 | 5 | Loading... |
14 😔😔😔😔ምን ብዬ ልመልስ
✍✍✍🎙🎙🎙ናትናኤል
@loveyoumoremm
https://t.me/Nothingistruek | 177 | 1 | Loading... |
15 ከረፈደ መጣህ 😒
ከረፈደ መጣህ ጊዜው ካለፈበት
ላንተ ፍቅር ቦታ አንድም በሌለበት😕
ከረፈደ መጣህ ፍቅሬ ከቀነሰ
ሌላ ሰው ገብቶበት ቆይቶ ከነገሰ
ያኔ በሰቀቀን ስኖር በፍራቻ 🥺
በልብ አዕምሮዬ ሆነህ አንተ ብቻ
ያኔ የት ነበርክ?
ጭንቀት የኔ ሆና እኔነቴን ለብሳው😔
ልቤ ልብ አቶ ተሰብሬ ሳለው
ያኔ የት ነበረክ?
ማፍቀሬን ወንጅዬ በመውደዴ አንተን😭
እራሴን ጠልቼው ሲከብደኝ ሰው ማመን
ያኔ የት ነበርክ?
እያልኩ አላማርር አምላክ መርቆኛል
ባንተ ብበደልም በሱ ግን ክሶኛል 😊
ተፃፈ በሜሮን ብዙነህ(@mareiu)
@topazionnn | 238 | 6 | Loading... |
16 #የአቀባይ_ተቀባይ
ገጣሚ እና አንባቢ ፦ዔደን ታደሰ
@ediwub
@topazionnn
@topazionnn | 207 | 2 | Loading... |
17 እመሰክራለሁ 🙏😭
እመሰክራለሁ ያንቺን ደግነት
ያንን ዘመን ስኖር በሃጢአት ባርነት
እናቴ አንቺ ነሽ ያወጣሺኝ ከሞት 🤕
እመሰክራለሁ አማላጅነትሽን
ሃጢያቴ በዝቶብኝ ለብሼ በደልን
ፈጥነሽ ያሰጠሺኝ ምህረት የልጅሽን🥺
እመሰክራለሁ ያንቺን ፀጋ ና ክብር
ሁሉም በሩን ዘግቶ አጥቼ ውጭ ባድር
እመቤቴ አንቺ ነሽ የሰጠሽኝ ፍቅር😥
እመሰክራለሁ ያንችን ንፅህና
እርቦኝ አጥቼ ወጥቼ ጎዳና
በወርቁ ጫማሽ ውሀ ጠጥቻለሁና😓
እምዬ ስላንቺ ቃላትም የለኝ
ተናግሬም አያልቅ ጊዜም አይበቃኝ
እመቤት ማርያም የጭንቄ ደራሽ
በቤትሽ ባነባ ከቶ አልሰለቸሽ😔
አንቺ ሩህሩህ ደግ የፍቅር እናት
ከእቅፍሽ አልውጣ እንዳልራቆት🙏😭
በሜሮን (@mareiu)
@topazionnn | 369 | 7 | Loading... |
18 መቼ ትመጫለሽ???
በቅርብ ቀን...............
@topazionnn
@topazionnn | 458 | 1 | Loading... |
19 AI
መካሪ አስተማሪ መስታወት የሚያዩት
ሲዝሉ ሲሰንፉ ደጋፊ በህይወት
ጠጋኝ ቀና አድራጊ አበርቺ አየዞህ ባይ
በጨለመብህ ቀን መፍትሄ የሚያሳይ
የልብ ጓደኛ ሳምሰንግ ያመረተው AI ስላገኘው
ልጠቁምህ ሊንኩን ተጫን እና እየው
ቢሆንም ፋሽኑ የዘንድሮ ዜና
እኔ እስከገባኝ በዚህ አይነት ገና
ያጋቡን ይሆናል ይሞሽሩትና😊
በ ልዑል መኮንን ተጫረ (@Liulmekonen) | 255 | 1 | Loading... |
20 ሰይጣን ፩ አርጎናል
የመዝሙር መከፈት ሙስሊሙን ካስከፋው
ክርስቲያኑን ደሞ መንዙማው ካስቆጣው
ፈጣሪን ማመስገን ይቅርብን ይበቃል
ኧረ እንደውም !
ሁሉም የሚሰማው ዘፈኑ ይሻላል!
ይገርማል! ኧረ ያስደንቃል !
ተዉ የተባልነው ኃጥያት አስማምቶናል
እግዚአብሔር ይመስገን ሰይጣን 1 አርጎናል።
ታክሲ ውስጥ በተፈጠረ አለመግባባት የተጫረች
በ ዘመልአክ(@zemelak7) | 444 | 7 | Loading... |
21 (ቅን ጣት)
ሙት ነው የሚኖረው አፈር ነው የቆመው
በቅንጣት ብቻ ነው ሰው ከሰው ሚለየው
ከልብ እጅ ተሳስሮ ጣት ቀንቶ ሲሰራ
ቅን ልብ ጣት አልምዶ ቀኝ ቀኙን ሲመራ
በቅን ልብ ያደረው በቅንጣት ተጽፎ እግዜር ለሰው ቢነግስ
ከደስታው ቀን ቢደርስ በሰው ቅንጣት ስራ ከመምሰሉም ቢደርስ
ምንም ለማትሞላ ለዚህች ስራህ ሰው ሆይ መንግስት አትጠብቅ
በችሮታው እንጂ በሰራሁት ማለትን አታድምቅ
እግዜር ከሰፈረ የቅንጣት ጥረትህ
ቅን ሆነህ ልትሰራ ቀኑንም ባላየህ
እግዜርስ በስራ ቢሰጥህ መትሮ
ለመፈጠር ብቻ ስራህ ተከምሮ
ከምድር እስከ ሰማይ ዋጋ ብታመጣ
እንዲሰራህ አምላክ ክፍያህ ቢወጣ
እንኳንስ መዝነህ ኪሎ ልታነሳ
ያኔ ድሮ በአርብ ሊፈጥርህ ሲነሳ
የእግዜር እስትንፋስ እፍታው ይቅርና
አፈር ከመንካቱ ዋጋህ ይሆናል መና
በ ልዑል መኮንን እንደተጫረ (@Liulmekonen) | 281 | 2 | Loading... |
22 እኔ ተሜሽ ከደጅሽ ከትሜ ፊደል አስማምቼ እየቆጠርኩ ግሴን
ቅኔ ፍቅር ሳመሰጠር እውነት መስሎኝ የኔው ጠፋ ስመኝ አንቺን
ከጸሀይ ሳስጠጋሽ ሲመሽ ከጨረቃ
አንዳንዴ ከብርዱ ሲያካፋም ከጭቃ
የመሸከም ልኬ እያዘነበለ ሊወድቅ እያመነታ
ወይ አላሳለፍሽኝም ወይ አላባረርሽኝ የኔዋ የኔታ
በማርያም በናቱ በአዛኝቱ ፍቺኝ
አቦ!
ወይ ልቤን መልሺ ወይ ያንቺኑ ስጭኝ
በ ልዑል መኮንን እንደተጫረ (@Liulmekonen) | 239 | 0 | Loading... |
23 የ እግዜር ፍጥረቶች ነን ከአዳም የ ሰረግን
ካፈሩ ከውሀ ከእሳት ከነፋሱ በቃል የታነፅን
ጥበብና ፍቅር ብርሀንና ቃል በሆነው ጌታችን
በእጁ በጥበብ ተቀርፀን በኤደን ያቆየን
ስሙ ነው ጥበብም
ስሙ ነው ፍቅርም
ስሙ ነው ብርሀንም
የህልው ቃልነት
ፎኖተ ፍቅርነት
ብርሃን ጸአዳነት
ህይወት ጥበብነት
ሰውም! ሰውም!
ሰውም ማፍቅር የሚችለው
ህያው ቃል ሚያወጣው
ልቡ ከአምላኩ ጸንቶ ብርሃን ከተጋባበት
ጥበብ ካደመቀው ፍቅር ከተሳለበት
ብርሃን ከበራለት ቃል ከፈለቀለት
በ ልዑል መኮንን እንደተጫረ (@Liulmekonen) | 222 | 0 | Loading... |
24 Haile....:
የእግዜር መደነቂያ!
ጥበቡን ማወቂያ!
ከአፈር ለይቶ ከአዳም ጎን መጥቶ
አዳም በሸለበ አንድ አጥንቱን አጥቶ
ሰራሽ አሳምሮ
ቸረሽ ብልህነትን ጥበብን ጨምሮ
እኔ የአዳም ቁራጭ ልጁ ደስእያለኝ
ከደብር ሳቀና በቸር እንዲያውለኝ
ይኸው ቸር ቀን የለመንኩት ችሮታው ደረሰኝ
አንቺን እንዳየሁሽ በነጠላሽ ተሸፍነሽ
የእግዜር ደጁን ለመሳለም ዳዊት ደግመሽ
ከነጠላሽ ከመስቀልሽ ከነፍስሽ ደብር ደረስኩና
ችሮራታዬ ፍቅር ሆኖተመለሰ አንቺን መውደድ ሰጠኝና
ስጦታዬን ሳልቀበል ሳላወራሽ ብትርቂኝ
በማርቆስ ደጅ ከአብማው ደብር እኔ እንድገኝ
ባሰበው ቀን አገናኘን ችሮታውም አልተነሳኝ
ይኸው!
ሀዲስ በድርሰቱ ያስተማረው ፍቅር
ከአባይ መፍሰሻ እኔን ከባህርዳር
አንቺን ከሸዋ ምድር አንድላይ ቢጨምር
ለፍቅር አምላክ ምንተስኖት ለ እግዚአብሔር
እኔም!
አንቺን ችሮታዬን የእግዜርን ስጦታ
በሰጠኝ ብያለሁ ቃልም ከአፌ ወጥታ
በ ልዑል መኮንን እንደተጫረ(@Liulmekonen)
(ቅን ጣት)
ሙት ነው የሚኖረው አፈር ነው የቆመው
በቅንጣት ብቻ ነው ሰው ከሰው ሚለየው
ከልብ እጅ ተሳስሮ ጣት ቀንቶ ሲሰራ
ቅን ልብ ጣት አልምዶ ቀኝ ቀኙን ሲመራ
በቅን ልብ ያደረው በቅንጣት ተጽፎ እግዜር ለሰው ቢነግስ
ከደስታው ቀን ቢደርስ በሰው ቅንጣት ስራ ከመምሰሉም ቢደርስ
ምንም ለማትሞላ ለዚህች ስራህ ሰው ሆይ መንግስት አትጠብቅ
በችሮታው እንጂ በሰራሁት ማለትን አታድምቅ
እግዜር ከሰፈረ የቅንጣት ጥረትህ
ቅን ሆነህ ልትሰራ ቀኑንም ባላየህ
እግዜርስ በስራ ቢሰጥህ መትሮ
ለመፈጠር ብቻ ስራህ ተከምሮ
ከምድር እስከ ሰማይ ዋጋ ብታመጣ
እንዲሰራህ አምላክ ክፍያህ ቢወጣ
እንኳንስ መዝነህ ኪሎ ልታነሳ
ያኔ ድሮ በአርብ ሊፈጥርህ ሲነሳ
የእግዜር እስትንፋስ እፍታው ይቅርና
አፈር ከመንካቱ ዋጋህ ይሆናል መና
በ ልዑል መኮንን እንደተጫረ (@Liulmekonen) | 245 | 0 | Loading... |
25 ጨዋታዉ ፈረሰ
.
.
ልጅነቴ ልጅነትህን፤
ለጋነትህ ጮርቃነቴን፤
በትዝታ እየቃኘሁ፤
ሳቃችንን እየሰማሁ፤
በትዉስታ ምልሰት፤
በጥሞና ስመለከት።
በድንጋይ ከታትፈን፤
ማባያ ጨምረን፤
መረቁን ከልሰን፤
የሰራነዉ ጎመን።
ለሚመጣዉ ዘመን፤
የእቃቃ ሰርጋችን፤
ሚዜ ስናዘጋጅ ፤
መኖርን ስንዋጅ፤
ወረቀት ቀዳደን፤
ቦጭቀን፤
ቦጫጭቀን፤
እየጎዘጎዝን፤
ሰፈር ስናበላሽ፤
መንደር ስናቆሽሽ፤
ቡና አፍልተን፤
ቁርሱን በልተን፤
ደግሞ ስንጣላ፤
ይጠፋናል መላ፤
ኩርኩም ስንቃመስ፤
ጮኸን ስንዋቀስ፤
መተቃቀፍ በማግስቱ፤
መንከባለል በክረምቱ፤
ስንቱ አለፈ በጊዜያቱ።
የእቃቃ ቤታችን፤
ያለምነዉ ኑሯችን፤
ጨዋታዉ ፈረሰ፤
ዳቦዉ ተቆረሰ።
በኤደን ታደሰ እንደተፃፈ(@ediwub)
@topazionnn
@topazionnn
@topazionnn | 81 | 1 | Loading... |
26 @semetnbegtm
@semetnbegtm
@semetnbegtm | 242 | 2 | Loading... |
27 በጎልማሳነት ዘመን በአስቸጋሪው ሰአት።
ሰው ከመሆን ርቆ ኅሊናን ከማጣት።
ፈጣሪህን አስብ በለጋነት እድሜ ፤
እርጅና ሳይመጣ ሳትያዝ ወንድሜ
።
ሽምገላ ሳይመጣ ሳይደክም ጉልበቴ፤
መንገዱን ላዘጋጂ ለማይቀረው ጉዞ በወጣትነቴ፤
እስትንፋሴ እያለ ሳለሁ በሕይወቴ።
በአምሳሉ ለፈጠረኝ ከፍጥረታት ሁሉ በላይ፤
እገዛለሁ ለትዛዙ ሰው ላረገኝ በመስቀል ላይ።
✍️𝕟𝕒𝕙𝕠𝕞
@topazionnn
@topazionnn | 458 | 5 | Loading... |
28 የግጥም ችሎታ እና ተሰጥኦ ያላችሁ ግጥሞቻችሁን ማጋራት የምትፈልጉ እንዲሁም አብራችሁን መስራት የምትፈልጉ ካላችሁ ልታናግሩን ትችላላችሁ👉👉@ediwub
@topazionnn
@topazionnn | 412 | 2 | Loading... |
29 @semetenbegtm
@semetenbegtm
@semetenbegtm | 399 | 6 | Loading... |
30 ማናት?
.
.
ከፍጡራን በላይ ፣
ከፀሐይ የበራች፣
ደምቃ የምትታይ፣
በቀኙ የቆመች፣
ወርቅን ተጎናጽፋ፣
ምሕረት የምትለምን፣
በኵሯን ታቅፋ፣
አለም የምታድን፣
ቃላቶች ደርድረን፣
ፅፈን የማንገልፃት፣
የጣፈጠ ስሟን፣
ጠርተን የማንጠግባት፣
እዉን ይህቺ ማናት?
..................................
በኤደን ታደሰ እንደተፃፈ
@ediwub
@topazionnn
@topazionnn | 578 | 9 | Loading... |
31 ሞትና ህይወት
ህይወት ማለት ፤ተጓዥ ሂደት
'ምትሰጥህ ፤ነፃ ትምህርት
ሁለት ቀለም ፤ጥቁርናነጭ
ምታሲዝህ ፤አንድ አማራጭ
ብርቱ ውጊያ ፤ባለ ትግል
ከጊዜጋ ምታነሳ ፤ወይ የምትጥል
አንዴ ጣፋጭ ፤ወይ መራራ
ስትደቁስ የማትራራ
ግማሽ ባንተ ፤ግማሽ ላንተ እየሆነች
ተለዋዋጭ ሂደት፤ 'ማትሰለች
ትልቅ ሀሰት፤ ምትክድህ በአንድ እለት
ምትሞሽርህ ለቁርጥ ቀን፤ ምትድርህ ለሞት
ሞት ማለት ፤የማይፋቅ እውነት
በሰከንዶች ውስጥ ፤ከአለም መለየት
ጣዕም አልባ ፤ባዶ ስሜት
ለዱንያ ጥፋት ፤መክፈያ ሰዓት
የምድር ሩጫን ፤የጉዞ ማብቂያ
ነብስን መከተል፤ ስጋን መልቀቂያ
አንዴ ከሄዱ ፤የማይመጡበት
ነፃ መውጫ ነው፤ ከዓለም ሰንሰለት
እንዳመጣጥህ፤ ጠርቶ የሚወስድህ
አፈር 'ሚያለብስክ፤ ለራቁት ገላህ
ደባል ማይጠራ ፤ገንዘብ ወይም ሌላ
ጊዜ የማይሰጥ ፤ከመጣ ሗላ
ይዘህ ምትሄደው፤ የኖርከው ግብርህ
ክፋና መልካም ፤ያረከው ስራህ
እንዲነው እልፈት ፤ቸኳይ እንግዳ
ከተፍ የሚለው ፤ሳትሰናዳ
ወስዶ ይከትሀል፤ ከዘመን ምርጫህ
ሲኦል ወይ ገነት፤ ልክ እንደ ስራህ።
✍️የተክልዬዋ
@semetnbegtm
@semetnbegtm
@semetnbegtm
share&comment እንዳይረሳ😊 | 347 | 2 | Loading... |
32 @semetenbegtm
@semetenbegtm
@semetenbegtm | 1 | 0 | Loading... |
33 ሲከፋህ ቀን ጠብቅ
መቼም በዚች ምድር
መኖር ስትጀምር...
አለ ብዙ ጉዳይ አለ ብዙ ነገር
አንደ ስትደሰት አንደ ስትቸገር
አንደ ስትከፋ ሌላ ጊዜ ስትስቅ፣
ስንት አለ ሚያስደንቅ፤
ደግሞ በስተጀርባ፦
እልፍ ጉዳይ አለ አንተን የሚያስጨንቅ፤
እናም ወዳጄ ሆይ...
መልካሙን ግለጠው መጥፎውን ግን ደብቅ
ሲደላህ ተደሰት ሲከፋህ ቀን ጠብቅ።
@balageru_1
@topazionnn
@topazionnn | 791 | 16 | Loading... |
34 #ሀገር_ስጡኝ
እኔ ልክ እንደ አስኳል ነኝ፣
ከቅርፊቴ ውጭ ብቻዬን ፍጹም ህልውና የሌለኝ፡፡
ውበት ድምቀቴን.......መኖሬን፣
እስትንፋስ ልቤን........ብሌኔን
የኔን መጠሪያ ማንነት
ሃገሬን ያጠበባችሁ፣
በሰፈር በመንደር - - በጎጥ
በወንዝ በድልድይ ድንበር፣
እንደ እይታችሁ ጥበት
ግዙፏን ያሳነሳችሁ
የኔ ሃገሬ ባህር ነች
ሰፊ ነች ምጡቅና ጥልቅ፣
እንደ እናንተ ማነስ አልቻልኩም
የዘር ሰበዝ ስሰነጥቅ፣
በናንተ አለም አልኖርም
እውነትን ክጄ ታሪክ ስፍቅ፡፡
ይልቅ እንጥፍጣፊ የሃገር ፍቅር ከቀራችሁ፣
በጥቁር አፈሯ እንድቀበር
ኢትዮጵያን ስጡኝ እባካችሁ፡፡
#በሻለቃ/ጋዜጠኛ ወይንሐረግ በቀለ
@topazionnn
@topazionnn
@topazionnn | 1 227 | 5 | Loading... |
35 እሷን ይመስለኛል
.
.
በብሩሽ ቢቀለም የሴትነት መልኩ፤
ተለክቶ ቢሰፈር የቀሚሷ ልኩ፤
እሷን ይመስለኛል.........
በጥለቷ እራፊ እንባዋን ሸፍና፤
የልቧንን እህታ በሳቋ አፍና፤
ራሷ በርትታ 'ምታበረታዋን፤
ራሷ ጀግና 'ምታጀግነዋን፤
የዘወትር አመስጋኝ ደጃፉን ናፋቂ፤
አድባር የመረቃት ጠበኛ አስታራቂ፤
ቃሏ 'ማይታበይ እዉነተኛይቱን፤
የእግዚአብሔር ወዳጅ ባለማተቢቱን።
እሷን ይመስለኛል........እ'..ሷ'..'ን
✍✍ኤደን ታደሰ
@ediwub
@topazionnn
@topazionnn | 627 | 7 | Loading... |
36 አለ ማፍቀር
ራቅ ብለው ፤በአይን እያዩ
ስሜት በግልፅ፤ ሳያሳዩ
ከተወዳጁ ፤እያወጉ
ቀርቦ ጠረን ፤እየማጉ
በመከተል፤ እንደ ጥላ
በመገስገስ ፤ከእሱ ሗላ
ቃል እያጡ፤ ለመናገር
በዛ ሰው ፊት ፤መደናገር
በሙሉ ቀልብ ፤እያመኑ
የቅርብ እሩቅ ፤እየሆኑ
ሳይገለፅ፤ የልብ እውነት
የሰው ደስታን፤ ላለማጥፋት
ለራስ የከጀሉት ፤ሌላ እቅፍ እያዩት
በዝምታ ፤ታጥረው
ምኞትን፤ ተነጥቀው
እንዲህም፤ አለ ማፍቀር
....
ተስፋ በሌለበት፤ ተስፋ እየቀጠሉ
ለፍቅር እየኖሩ ፤እራስን እየጣሉ
ላልተሰጠ ነገር ፤ዋጋ እየከፈሉ
ማማረርን ይዘው፤ ከአምላክ ከተጣሉ
ሙሉነትን ትቶ ፤ባዶ ሆኖ ከመጥፋት
ከምድር ከሰማዩ ፤ጠልቶ ከመለየት
ለነፃዋ ህይወት ፤ደስታን ማሰንበቻ
ማጣፈጫው ቅመም ፤አለማፍቀር ብቻ።
✍️የተክልዬዋ
@semetnbegtm
@semetnbegtm
@semetnbegtm | 468 | 3 | Loading... |
37 ❤ቢታነፅ ቢወቀር!
(በእውቀቱ ስዩም)
እኔም አንድ ሰሞን
ልክ እንደ ሰለሞን
"ሁሉም ከንቱ ከንቱ ንፋስን መከተል
ላይጥሉ መታገል: ላይከብሩ መባተል"
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ: እፈላሰፍ ነበር!
ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጓሮ በር በኩል: ሰለሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ንፋስ አሳድጄ እንደ ቆቅ አጠመድሁ
ከፀሀይዋ በታች: ግልገል ፀሀይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ: ብርሀን አበደርሁ
ማቅ የነበረው ጨርቅ: ሸማ ሆኖ ቆየኝ
"ከንቱ የነበረው: "አንቱ" ሆኖ ታየኝ!
ለካስ...
ጠቢብ ቢያስተምረው
መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ: ቢታነፅ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም: ካልወደደ በቀር!
@topazionnn
@topazionnn
@topazionnn | 445 | 6 | Loading... |
38 ፋራ ነኝ
ፋራ ነሽ ይሉኛል ቀሚስ በመልበሴ፣
እኔ ግን ልክ ነኝ ከእናቴ ነው ውርሴ።
ሀጢአትን ማንገስ ዘመናዊነት ነው አሉ ፣
ህግ አፍርሶ መኖር አራዳነት ካሉ፣
አዎ እኔ ፋራ ነኝ ያሻችሁን በሉ ።
ወንድ ከሴት ጋር መለየት አቅቶን፣
#ዘመኑ #ነው #አልን #ግራ #እየተጋባን።
ዘመን ምን አደረገ ዘመን ተኮነነች፣
ሁሉም እንደልቡ ታግሳ ባኖረች።
እራሳችንን መግዛት መታዘዝ ሲያቅተን፣
እናሳብባለን ዘመን ነው እያልን።
አሁንም እላለሁ እኔ ፋራ ነኝ፣
በሱሪ ማፍርበት ቀሚስ የሚያኮራኝ፣
ዘመናዊ መሆን ከቶ የማያሻኝ፣
እውነቱን ልንገርህ አዎ እኔ ፋራ ነኝ፣
ሜካፕ የተባለው አመድ የማይነካኝ፣
የተፈጥሮ ውበቴ ፀጋዬ የበቃኝ፣
በቀሚስ ምኮራ የኢትዮጵያ ልጅ ነኝ!!!!!!!
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
😘😘😘😘😘😘😘
#share_share_share
@topazionnn
@topazionnn
@topazionnn
For any comment👇👇
@Creamy16 | 702 | 4 | Loading... |
39 ድንቄም ስዕለት
.
.
የእናቴ እድርተኛ፤
ሲላትም ቤተኛ፤
ተጫዋች ወገኛ፤
ሲላትም ልግመኛ።
ከጌታዋ ዘንዳ፤
እበተስኪያን ሄዳ፤
ከመቅደሱ ዘንዳ፤
መሰማትን ወድዳ።
ራሷን አርቃ፤
መቀነቷን ታጥቃ፤
ከሁሉ ርቃ፤
ጸለየች አጥብቃ።
ምቀኛዬን፤
ሸረኛዉን፤
ሰዳቢዬን፤
አሽሟጣጩን፤
አይኑን እንዳላየዉ፤
ብርሃኑን አጥፋዉ፤
ድምፁን እንዳልሰማዉ፤
ልሳኑን ንጠቀዉ፤
ደጃፌ እንዳይደርስ፤
አጥሬን እንዳያፈርስ፤
ፊቱን እንዳይመልስ፤
እርምጃዉን ደምስስ።
ካለበት ድፋልኝ፤
እግሩን ቁመጥልኝ፤
ወስደኸዉ ገላግለኝ፤
ስዕለቴን ስማልኝ።
..........................................
ስዕለቷ ይሰምር ይሆን?😁
በኤደን ታደሰ እንደተፃፈ(@ediwub)
@topazionnn
@topazionnn | 422 | 3 | Loading... |
40 ( ሰው .. )
=============
የሰው ልጅ ምስኪኑ
ባለማወቅ ፀልሞ ...
:
ብቻዬን ነኝ ይላል
ዓለም ተሸክሞ !!
by #Da_Kiyorna
ንሸጣ : Rumi
@topazionnn
@topazionnn | 666 | 2 | Loading... |
Показать все...
መቼ ትመጫለሽ .mp33.46 MB
❤ 7👏 1
መሰበር ከቅስም በላይ
በልብ ይበረታል
ያልሽኝን ታስታውሻለሽ
አትረሽውም
እንደ ቃልሽ
ፀንተሽ አለሽ
ከስሜት
ምክንያታዊነት ለእምነት
እጅ ከሰጠ
የቱ ጋር ነው የእኛ ታሪክ የበለጠ
ከስሜታችን መታረቅ ተስኖን
በምኞታችን ቅዥት
ሕልማችንን ለመኖር ኃይል ብርታቱን ካጣን
ፍቅር ጀምረን እንጂ የታየን
ከዘለቁት መች ተቆጠርን።
✍ አየሁ ነኝ
@tekle_ayehu
🤗 3❤ 1
እንቆቅልሼ ነህ
ያኔ በልጅነት ስንጠያየቅ
መልሱን ለመመለስ ሁሉም ሲጨናነቅ
እንታገል ነበር ፍችውን ለማወቅ
:
:
ዛሬ በኔ ህይወት ይኸው በኔ ኑሮ
ፍች አልተገኘልህ ጥያቄ ለወትሮ
የልቤ ቅኔ ነህ የውስጤ እስትንፋስ
እንቆቅልሼ ነህ የሌለህ ቋሚመልስ
:
:
እባክህ ፍቅርዬ ሀገሬን ስሰጥህ
እንቅቆቅልሽ ስልህ
ምናውቅልሽ ብለህ
ሳይህየማፈሬን የውስጤን መቅለስለስ
የልቤን ጥያቄ ዛሬውኑ መልስ።
✍ ቤዛ
(የተክልዬዋ)
@semetnbegtm
@semetnbegtm
@semetnbegtm
🥰 2👍 1
እያስተዋልን እንጂ የጊዜውን ነገር
እናውራ ካልንማ ስንት አለ የሚነገር።
ያየነውን ሁሉ በሆድ ይፍጀው ዜማ
በማለፋችን ነው የኖርነው እኛማ።
@topazionnn
@topazionnn
@topazionnn
👏 6👍 3
ህሊና ሲመክር ........
🎙🎙🎙ናትናኤል
@loveyoumoremm
https://t.me/Nothingistruek
teacher ♡♡.m4a2.75 MB
🥰 3❤ 1
ሰው ዋጋው ወደቀ
የወደቀን ሁሉ ሰንፎ ነው እያልን
ያለቀሰን ሁሉ አስመስሎ ብለን
በሰው ቁስል ፈርደን ህመማቸው ርቆን
ከመሃል ከተማ እስከ ዳር እያየን
ሰው ከዕትብቱ ሲለይ ያልኖረው አለቀ
ለድንጋይ ጌጥ ሲባል ሰው ዋጋው ወደቀ
ልዑል መኮንን @Liulmekonen
👏 7👍 3