ru
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Открыть в Telegram
2 485
Подписчики
Нет данных24 часа
-157 дней
-5230 день
Архив постов
በኢትዮጵያ ከነሐሴ 2015 በፊት በነበሩት አራት ወራቶች የቤንዚን ዋጋ 69 ብር ከ52 ሳንቲም ነበር። ከአንድ ወር በፊት በተደረገ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ክለሳ፤ የቤንዚን ዋጋ በአምስት
በኢትዮጵያ ከነሐሴ 2015 በፊት በነበሩት አራት ወራቶች የቤንዚን ዋጋ 69 ብር ከ52 ሳንቲም ነበር። ከአንድ ወር በፊት በተደረገ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ክለሳ፤ የቤንዚን ዋጋ በአምስት ብር ገደማ ጨምሯል። ከትላንት ለሊት መስከረም 18፤ 2016 ጀምሮ ደግሞ የዚህ የነዳጅ ምርት የመሸጫ ዋጋ ወደ 77 ብር ከ65 ሳንቲም ከፍ ብሏል። “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው አሽከርካሪዎች፤ ባለፉት ሁለት ወራት በድምሩ 8 ብር ከ13 ሳንቲም የተመዘገበበት የቤንዚን ዋጋ ጭማሪ፤ ኑሯቸውን እንዳከበደባቸው ተናግረዋል። አሽከርካሪዎቹ፤ መንግስት “የነዳጅ ዋጋ ቅነሳ አሊያም ድጎማ ሊያደርግ ይገባል” የሚል አቋማቸውንም አንጸባርቀዋል። 🔴 በአዲስ አበባ ያሉ አሽከርካሪዎች የነዳጅ ዋጋ ጭማሪን በተመለከተ የሰጡትን አስተያየት ይህን ሊንክ ተጭነው ይመልከቱ፦ https://youtu.be/ROhLxabAIwA @EthiopiaInsiderNews

ቪዲዮ:- በሰሜን አውሮፓዊቷ ሀገር ላቲቪያ መዲና ሪጋ በመጪው እሁድ በሚካሄደው የዓለም የጎዳና ውድድር ላይ ለሚካፈሉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ትላንት ምሽት ይፋዊ አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል። የዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ስፖርት አስተዳዳሪ አካል በአዲስ ቅርጽ ያዘጋጀው ይህ ውድድር፤ ከዚህ ቀደም ከነበረው ግማሽ ማራቶን በተጨማሪ የአንድ ማይል እና የአምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫዎችን ያካተተ ነው። ከ90 ሀገራት የተውጣጡ ሯጮች በሚፎካከሩበት በዚህ ውድድር ላይ 13 ሴት እና ወንድ አትሌቶች ኢትዮጵያን ይወክላሉ። በውድድሩ የማሸነፍ ግምት ከተሰጣቸው አትሌቶች መካከል፤ ከአንድ ወር በፊት በሀንጋሪ ቡዳፔስት በተከናወነው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ1,500 ሜትር ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ያመጣችው ድርቤ ወልተጂ ትገኝበታለች። ድርቤ በአንድ ማይል ውድድር ከኬንያዊቷ ፌይዝ ብርቱ ፉክክር ይጠብቃታል። እንደ 21 ዓመቷ ድርቤ ሁሉ የሀገሯ ልጅ ፍሬወይኒ ኃይሉም በርቀቱ ከፍተኛ ግምት ከተሰጣቸው ዝርዝር ውስጥ ተካትታለች። ድርቤ እና ፍሬወይኒ በትላንትው ዕለት ቦሌ አደይ አበባ ስቴድየም አጠገብ በሚገኘው የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ተገኝተው የማጠቃለያ የጋራ ልምምድ ሲሰሩ ታይተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) * የኢትዮጵያ የአትሌቲክስ ብሔራዊ ቡድን ለሪጋው ውድድር ስላደረገው ዝግጅት እና በአሸኛኘት ስነ ስርዓቱ ላይ የተላለፉ መልዕክቶችን ሙሉ ቪዲዮ ለመመልከት ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://youtu.be/RPlvn6pP94M

ቪዲዮ፦ በኬንያ አስተናጋጅነት የተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ከትላንት በስቲያ ረቡዕ ተጠናቅቋል። ሰላሳ ሺህ ገደማ ተሳታፊዎች ታድመውታል በተባለለት በዚህ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ፣ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ እና የግብርና ሚኒስትር ዶ/ር ግርማ አመንቴን ጨምሮ 45 ገደማ በሆኑ ልዑካን ተወክላለች። የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በቦርድ ሰብሳቢነት የሚመሩትን “Alliance for a Green Revolution in Africa” የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅትን በመወከል በጉባኤው የተገኙ ሲሆን ንግግር የማድረግ ዕድልም አግኝተዋል። አቶ ኃይለማርያም በኬንያ ናይሮቢ ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን በተመለከተ ከዚህ ቀደም የነበራት እንቅቃሴ ላይ “ክፍተት እየተፈጠረ መምጣቱን” ተናግረው ነበር። ባለፈው ዓመት በተካሄደው ዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ጉባኤ፤ COP 27 ላይ ኢትዮጵያ የነበራትን “በጣም ደካማ visibility” በማሳያነት ያነሱት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር፤ ለዚህም እንደ አንድ ምክንያት የጠቀሱት ዘርፉን የሚከታተለው አካል ራሱን ችሎ አለመቋቋሙን ነው። “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” በጉዳዩ ላይ ያነጋገረቻቸው የጉባኤው ተሳታፊዎች የፕላን እና ልማት ሚኒስትሯ ዶ/ር ፍጹም እና የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታሁን ጋረደው ይህንን ሀሳብ ተቃውመውታል። * * ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ሁለቱ ባለስልጣናት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የሰጡትን ሙሉ ማብራሪያ ይህን ሊንክ ተጭነው ይመልከቱ፦ https://youtu.be/A76imry90aI

ዛሬ በናይሮቢ በጸደቀው የአየር ንብረትን በተመለከተው ስምምነት ላይ ኢትዮጵያ ማሻሻያ እንዲደረግ የጠየቀችባቸው ጉዳዮች ምንድን ናቸው? የአፍሪካ ሀገራት ዛሬ ጷግሜ 1፤ 2013 በተጠናቀቀው የመጀመሪያው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ላይ ሀገራት “የናይሮቢ ዲክላሬሽን” ስምምነትን ተቀብለዋል፡፡ የአፍሪካ ሀገራት “በሙሉ ድምጽ እና ድጋፍ” ተቀብለውታል የተባለው ይህ ስምምነት የአህጉሪቱ አቋም ሆኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እና ኮንፈረንሶች ላይ የሚቀርብ ነው፡፡ ስምምነቱ የአየር ንብረትን ለመከላከል እና ለመቋቋም የአፍሪካ ሀገራት የሚተገብሯቸውን የፖሊሲ ማሻሻያዎች የያዘ እንዲሁም በኢኮኖሚ ያደጉ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ሊወስዷቸው የሚገቡ እርምጃዎችን ያስቀመጠ ነው፡፡ የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ በተጀመረበት ሰኞ ዕለት ለአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ስለ ስምምነቱ ዝርዝር ገለጻ ተደርጓል፡፡ በዚህ ገለጻ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የተገኙት የፕላን እና ልማት ሚኒስትሯ ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ከሀገራቸው አቋም አንጻር “ቢስተካከሉ” ባሏቸው ጉዳዮች ላይ አስተያየት ሰጥተው ነበር፡፡ በዛሬው ዕለት ደግሞ የሀገራት መሪዎች እና ተወካዮች በተገኙበት በ“ናይሮቢ ዲክላሬሽን” ላይ በዝግ ውይይት ተካሂዷል፡፡ ሀገራቱ ስምምነቱን እንደተቀበሉት ከመገለጹ ከአንድ ሰዓት ገደማ በፊት “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታሁን ጋረደው፤ ኢትዮጵያ በሁለት ጉዳዮች ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ ጥያቄ ማቅረቧን ገልጸዋል፡፡ 🔵 ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት 👉 https://youtu.be/n1rJb--OpaA @EthiopiaInsiderNews

35 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሀገር አቀፍ የሰላም መድረክ እንዲመቻች ጥሪ አቀረቡ ሰላሳ አምስት ሀገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሁሉንም የማህበረሰብ አካላት የሚያሳትፍ ሀገር አቀፍ የሰላ
35 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሀገር አቀፍ የሰላም መድረክ እንዲመቻች ጥሪ አቀረቡ ሰላሳ አምስት ሀገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሁሉንም የማህበረሰብ አካላት የሚያሳትፍ ሀገር አቀፍ የሰላም መድረክ እንዲመቻች ጥሪ አቀረቡ። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶቹ በዚህ ዓመት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተስተዋሉ “አዳዲስ እና ነባር ግጭቶች በመጪው ዓመትም ተባብሰው እንዳይቀጥሉ” ያላቸውን ስጋትም ገልጸዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ይህን የገለጹት ዛሬ ረቡዕ ጷጉሜ 1፤ 2015 ባቀረቡት “የአዲስ ዓመት የሰላም ጥሪ” ነው። ድርጅቶቹ መጪው 2016 ዓ.ም. “የዜጎችን መሰረታዊ የሰብዓዊ መብቶች እና ነጻነቶችን የሚያጣብቡ ግጭቶች የሚቀጥሉበት እንዳይሆን በማሰብ” አስር ጥሪዎችን ማቅረባቸውን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባው ካፒታል ሆቴል በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ድርጅቶቹ በቀዳሚነት ያቀረቡት ጥሪ “ሁሉንም የማህበረሰብ አካላት የሚያሳትፍ ሀገር አቀፍ የሰላም መድረክ (የሰላም ኮንቬንሽን)” እንዲመቻች የሚጠይቅ ነው። በድርጅቶቹ የተጠየቀው የሰላም መድረክ ዋና ዓላማ “ወደ ነውጥ ሊያድጉ የሚችሉ ውጥረቶችን ለመከላከል እና መልስ እንዲገኝላቸው ለማስቻል” መሆኑን የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) የተሰኘው የሲቪል ማህብረሰብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር አቶ በፍቃዱ ኃይሉ በመግለጫው ላይ ተናግረዋል። በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚከሰቱ ግጭቶች መንስኤ ቀድሞ እንደሚታይ የጠቆሙት የካርድ ዋና ዳይሬክተር፤ “በሰላማዊ መንገድ እየተፈቱ ያሉ ግጭቶች ዘላቂ እና አስተማማኝ ሰላማዊ ሁኔታ እንዲገነባላቸው” ማስቻል ሌላኛው የሰላም መድረኮቹ ዓላማ ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11969/ @EthiopiaInsiderNews

የፎቶ ዘገባ፦ በናይሮቢ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ላይ ከተገኙ 19 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች መካከል 13ቱ በዛሬው የጉባኤው ውሎ ላይ ንግግሮችን አድርገዋል። በጉባኤው ላይ ለመገ
+4
የፎቶ ዘገባ፦ በናይሮቢ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ላይ ከተገኙ 19 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች መካከል 13ቱ በዛሬው የጉባኤው ውሎ ላይ ንግግሮችን አድርገዋል። በጉባኤው ላይ ለመገኘት ትላንት ከሰዓት ናይሮቢ የደረሱት ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ፤ የከባቢ አየር ለውጥን በተመለከተ ሀገራቸው ያላትን አቋም ለታዳሚዎች ያስደመጡት የ10 ሀገራት መሪዎች ንግግር ካደረጉ በኋላ ነበር። እርሳቸውን ቀድመው የመናገር ዕድል ካገኙ መሪዎች መካከል የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ፣ የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ እና የጋናው ፕሬዝዳንት ናና አኩፎ ኦዶ ይገኙበታል። ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ በዛሬው ንግግራቸው ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ለውጥ ምክንያት እያጋጠማት ስላለው ድርቅ እና የአፍሪካ ሀገራት በጉዳዩ ላይ መያዝ ስላለባቸው ወጥ አቋም አንስተዋል። የኢትዮጵያ መንግስት የከባቢ አየር ለውጥን ለመከላከል እና ለመቋቋም በተለያዩ ዘርፎች ላይ ፕሮጀክቶችን መተግበሩን የጠቀሱት ፕሬዝዳንቷ፤ ሀገሪቱ ተጨማሪ ፕሮግራሞችን እውን ለማድረግ “ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ድጋፍ” እንደሚያስፈልጋት አስረድተዋል። እነዚህን ፕሮግራሞች ለመደገፍ ቃል የገቡ አጋር አካላትም ቃላቸውን እንዲያከብሩ ጠይቀዋል። “የባለብዙ ወገን ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት፤ በማደግ ላይ ባሉ ሀገሮች እና በዋነኛነት በአፍሪካ ትከሻ ላይ የተከማቸን ታሪካዊ ዕዳ ከማባባስ ይልቅ ዓላማቸውን የሚመጥን ከፍ ያለ ማሻሻያ እንዲያደርጉ አጥብቀን እናሳስባለን” ሲሉም ፕሬዝዳንቷ ተደምጠዋል። የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ፤ የከባቢ አየር ለውጥን ለመከላከል እና ለመቋቋም የሚያስፈልገውን ገንዘብ የኢትዮጵያ መንግስት ከሀገር ውስጥ ምንጮች ለመሸፈን እንቅስቃሴ መጀመሩን አስታውቀው ትላንት አስታውቀው ነበር። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ አማራጮች ላይ ሊደረጉ ከታቀዱ የምክክር መድረኮች ውስጥ አራቱ በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይካሄዱ መቅረታቸው ተገለጸ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ 50 ገደማ ከተሞች የሽግግር ፍትህ የ
በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ አማራጮች ላይ ሊደረጉ ከታቀዱ የምክክር መድረኮች ውስጥ አራቱ በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይካሄዱ መቅረታቸው ተገለጸ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ 50 ገደማ ከተሞች የሽግግር ፍትህ የፖሊሲ አማራጮችን በተመለከተ ግብዓት ሲያሰባስብ የቆየው የባለሙያዎች ቡድን፤ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት አራት የምክክር መድረኮችን ሳያካሄድ መቅረቱን አስታወቀ። የባለሙያዎች ቡድኑ ረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሰነዱን በመጪው ዓመት ጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ ለማጠናቀቅ ማቀዱንም ገልጿል። የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሰነድ የሚያዘጋጀው፣ አስራ አራት አባላት ያሉበት የባለሙያዎች ቡድን በፍትህ ሚኒስቴር አማካኝነት የተቋቋመው ባለፈው ህዳር ወር ውስጥ ነበር። የባለሙያዎች ቡድኑ የሽግግር ፍትህ የፖሊሲ አማራጮች ላይ የሚያደርጋቸውን ምክክሮች የሚመራበት ፍኖተ ካርታ አዘጋጅቶ ወደ ውይይት የገባው ከአራት ወራት በፊት ነው። በአዳማ ከተማ የተጀመረው የምክክር መድረክ፤ 46 ከተሞችን አካልሎ በነሐሴ ወር መጀመሪያ በአዲግራት ከተማ በተካሄደ ውይይት መጠናቀቁን የባለሙያዎች ቡድኑ ዛሬ ማክሰኞ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። ቡድኑ በአጠቃላይ ሊያካሄዳቸው አቅዷቸው የነበሩ የምክክር መድረኮች ብዛት 59 ቢሆኑም፤ በጸጥታ ችግር ምክንያት አራት ያህሉን መሰረዙን የባለሙያዎች ቡድን አባል የሆኑት ዶ/ር ማርሸት ታደሰ በመግለጫው ላይ ተናግረዋል። 🔵 ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11957/ @EthiopiaInsiderNews

በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ መድረኮች ላይ “ክፍተት እየተፈጠረብን ነው” – የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ እና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይን በ
በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ መድረኮች ላይ “ክፍተት እየተፈጠረብን ነው” – የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ እና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይን በተመለከተ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላት የቀደመ እንቅስቃሴ ላይ “ክፍተት እየተፈጠረ መምጣቱን” የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ተናገሩ። የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የአካባቢ ጥበቃ እና የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ስር መደረጉ ቀርቶ ራሱን ችሎ በተቋቋመ መስሪያ ቤት መመራት ይገባዋል ብለዋል። በኬንያ መዲና ናይሮቢ ዛሬ ሰኞ በተጀመረው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት አቶ ኃይለማርያም፤ “የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ ከፍ ብሎ መታየት አለበት የሚል እምነት አለኝ” ሲሉ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። በእነዚህ ዘርፎች ኢትዮጵያ አሁን ያላት አደረጃጀት ላይ “የሚቀራት ነገር እንዳለ ይታያል” ያሉት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር፤ የአካባቢ፣ የአየር ንብረት እና የደን ጉዳዮችን የሚከታተል ራሱን የቻለ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ያላት ኬንያ በዚህ ረገድ የተሻለች መሆኗን መስክረዋል። “ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ visibility በጣም ደካማ ነው። በዚህ መድረክም ታያለህ። ባለፈው በCOP 27 ላይም አይተናል” ሲሉ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተናገሩት አቶ ኃይለማርያም፤ ዘርፉን የሚከታተለው አካል ከፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ስር ወጥቶ “ይህንን ስራ ብቻ በሚከታተል አካል” መመራት እንዳለበት ምክረ ሃሳባቸውን ለግሰዋል። 🔵ለሙሉ ዘገባው፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11955/ 🔵 በቪዲዮ ለመመልከት፦ https://www.youtube.com/watch?v=7C5atRzfvhE

በአየር ንብረት ጉዳይ ላይ የሚመክር የመጀመሪያው አህጉር አቀፍ ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀመረ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴን ጨምሮ ከ20 ገደማ በላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እንደሚገኙበት የሚጠበቀ
በአየር ንብረት ጉዳይ ላይ የሚመክር የመጀመሪያው አህጉር አቀፍ ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀመረ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴን ጨምሮ ከ20 ገደማ በላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እንደሚገኙበት የሚጠበቀው የመጀመሪያው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ፤ ዛሬ ሰኞ ነሐሴ 29 በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ መካሄድ ጀመረ። በዚህ ጉባኤ ላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና ለመቋቋም ስለሚወስዷቸው እርምጃዎች ቃል የሚገቡበት “የናይሮቢ ስምምነት” ይፋ ይደረጋል ተብሏል። ኬንያ እና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በጋራ ያዘጋጁት የአየር ንብረትን የተመለከተው ይህ ጉባኤ፤ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ሲዘጋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ለሶስት ቀናት የሚቆየው ጉባኤ በኬንያታ አለም አቀፍ የስብሰባ ማዕከል ዛሬ ሲከፈት የኬንያው ፕሬዝዳንን ዊሊያም ሩቶ ባደረጉት ንግግር፤ “አፍሪካ ለከባቢ አየር ለውጥ ያደጉ ሀገራትን ከመውቀስ ባለፈ ያላት አቅም ላይ ትኩረት በማድረግ እርምጃዎችን መውሰድ ላይ ማተኮር ይገባታል” ብለዋል። የአየር ንብረት ለውጥን ለሚከላከሉ ቴክኖሎጂዎች የሚውሉ ጥሬ እቃዎች አፍሪካ ውስጥ እንደሚገኙ የጠቀሱት የኬንያው ፕሬዝዳንት፤ የአፍሪካ ሀገራት እነዚህን የተፈጥሮ ሀብቶች እሴት በመጨመር ጥቅም ላይ ማዋል እና ለዓለም ገበያ ማቅረብ እንዳለባቸው ተናግረዋል። ዛሬ ጠዋት በተካሄደው የመክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ተገኝተዋል። አቶ ኃይለማርያም በጉባኤው የተገኙት በቦርድ ሰብሳቢነት የሚመሩትን የአፍሪካን የግብርና አሰራር ለማሻሻል የሚሰራውን “Alliance for a Green Revolution in Africa” የተሰኘውን መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በመወከል ነው። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11943/

ኢሰመኮ እስከ አሁን ስላደረገው ክትትል፣ ግኝቶች፣ ተግዳሮት እና ምክረ ሐሳቦች ነሐሴ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ ጋር የተወያየ ሲሆን፤ ስለ አጠቃላይ ሁኔታው፣ የሰብአዊ መብቶች አከባበርና ዘላቂ ሰላማዊ መፍትሔ ሐሳቦች ከልዩ ልዩ ባለድርሻ አካላት ጋር የሚያደርገውን ውይይትና ምክክር የሚቀጥል መሆኑን ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ገልጸዋል፡፡ @

ኢሰመኮ ስለእነክርስቲያን ታደለ እስር!... #Ethiopia | በአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጅ አተገባበር ጋር ተያይዞ በአዋሽ አርባ እና በተለያዩ መደበኛ ባልሆኑ ቦታዎች ተይዘው የሚገኙ ሰዎችን በተመለከተ ... የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ጨምሮ 5 የኮሚሽኑ ባለሙያዎች የሚገኙበት ቡድን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት በቁጥጥር ሥር ውለው አዋሽ አርባ አካባቢ በሚገኘው የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የምዕራብ ዕዝ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ ውስጥ ተይዘው የሚገኙትን ታሳሪዎች ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ጎብኝቷል። እነዚህ ታሳሪዎች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ዮሐንስ ቧያለው፣ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር ካሳ ተሻገር፤ እንዲሁም ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ አባይ ዘውዱ፣ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ፤ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባል አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ አቶ በለጠ ጌትነት፤ እና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ውስጥ በኃላፊነት ይሠሩ የነበሩት አቶ ከፋለ እሱባለውን ጨምሮ በአጠቃላይ 53 ወንድ እስረኞች ሲሆኑ፤ ከአዲስ አበባ ከተማና ከአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎች በተለያየ ጊዜ ተይዘው ከነሐሴ 15 ቀን እስከ ነሐሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ወደ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ የሚገኝ ጊዜያዊ/መደበኛ ያልሆነ ማቆያ ጣቢያ የተወሰዱ ናቸው፡፡ ኮሚሽኑ በተለመደው አሠራሩ መሠረት ታሳሪዎቹን ለብቻቸው አነጋግሯል፣ ቦታውን ጎብኝቷል እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸውን የፖሊስ ኃላፊዎች አነጋግሯል፡፡ የፖሊስ ኃላፊዎች ለኮሚሽኑ እንደገለጹት ታሳሪዎችን ወደዚህ ጊዜያዊ ማቆያ ጣቢያ ማምጣት ያስፈለገው አዲስ አበባ የሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ማቆያ ጣቢያ ላይ ከፍተኛ መጣበብ በመፈጠሩ መሆኑን፣ የአዋሽ አርባ አካባቢ ከፍተኛ ሙቀት ያለበት አካባቢ ስለሆነ በተቻለ መጠን በግቢው ውስጥ ካሉት ቤቶች ውስጥ የተሻለ በሆነው ሰፊ አዳራሽ ውስጥ የመኝታ አልጋ ተዘጋጅቶ ታሳሪዎቹ በአንድ ላይ አብረው የተያዙ መሆኑን፣ ነፋስ ለመቀበል መንቀሳቀስ እንደሚቻል፣ በካምፑ በኩል ቁርስ፣ ምሳ እና እራት ተዘጋጅቶ እንደሚቀርብ፣ አስቸኳይ የሕክምና ዕርዳታ በካምፑ በኩል ሊሰጥ እንደሚችል፣ ከዚህ በላይ ለሆነ የሕክምና አገልግሎት ወደ ሆስፒታልም መውሰድ እንደሚቻል፤ ለምሳሌ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያለው ወደ አዲስ አበባ ለሕክምና ተወስደው የህክምና አገልግሎት አግኝተው መመለሳቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም የቤተሰብ ጉብኝት ሊመቻች እንደሚችል ሆኖም ከቦታው ርቀት አንጻር አብዛኛዎቹ ታሳሪዎች ቤተሰብ እንዳይጉላላ ጉብኝቱን እንደማይፈልጉ መግለጻቸውንና ይልቁን በስልክ ለመነጋገር እንዲችሉ መጠየቃቸውንና ይህም ዝግጅቱ እየተጠናቀቀ ስለሆነ በቅርቡ በስልክ ለመነጋገር እንዲችሉ እንደሚደረግ፣ ቃላቸውን ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆኑ የተወሰኑ ታሳሪዎች ቢኖሩም የምርመራ ሥራውን በአፋጣኝ ለማጠናቀቅ ፖሊስ የተቻለውን ጥረት እያደረገ መሆኑንና አጠቃላይ አያያዛቸው የሰብአዊ መብቶችን ያከበረ እንዲሆን ፖሊስ ዐቅም በፈቀደው መጠን ሁሉ የተቻለውን ጥረት እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በአንጻሩ እጅግ አብዛኛዎቹ ታሳሪዎች ብሔራቸው አማራ፣ እምነታቸው ኦርቶዶክስ ክርስቲያን መሆኑንና ለእስር የተዳረጉት በብሔር ማንነታቸው ብቻ መሆኑን እንደሚያምኑ፣ ከፊሎቹ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተያዙበትና ቤታቸው በተበረበረበት ወቅት በራሳቸውና በቤተሰብ አባል ላይ ድብደባ፣ ብሔር ተኮር ስድብ፣ ማጉላላት፣ ዛቻና ማስፈራራት እንደደረሰባቸው ሆኖም በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ከሆኑ በኋላ የተፈጸመ ድብደባ ወይም አካላዊ ጥቃት አለመኖሩን፣ ከፊሎቹ በተለይም ከአማራ ክልል ተይዘው የመጡ ሰዎች ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ ቤተሰቦቻቸው የት እንዳሉ እንኳን እንደማያውቁ አስረድተዋል። አክለውም የአዋሽ አርባ አካባቢ እጅግ ከፍተኛ ሙቀት ያለው በመሆኑና ከአካባቢው የአየር ጠባይ እንዲሁም ቦታው የወታደራዊ ካምፕ እንጂ መደበኛ የተጠርጣሪዎች ማቆያ ስፍራ ስላልሆነ ለጤንነታቸው፣ ለደኅንነታቸውና ለሕይወታቸው ሥጋት እንዳላቸው፣ አልባሳትን ጨምሮ ከቤተሰብ የሚፈልጉትን አቅርቦት ለማግኘት እንዳልቻሉ፣ ከፊሎቹ በሥራቸውም ሆነ በግል ሕይወታቸው ፈጽሞ በፖለቲካ ነክ ጉዳይ ተሳትፎ እንደሌሉና እንዴት ለእስር እንደበቁ መገረማቸውንና መደንገጣቸውን ገልጸዋል። ኮሚሽኑም ከፖሊስ ኃፊዎች ጋር ባደረገው ውይይት በእስር ወቅት ተፈጽመዋል ስለተባሉ የሥነ ምግባር ጥሰቶች ተገቢው ማጣራት እንዲደረግ፣ ታሳሪዎቹ ከቤተሰብ ለሚፈልጉት አቅርቦት አዲስ አበባ በሚገኘው የፖሊስ ቢሮ አማካኝነት እንዲመቻች፣ ከቤተሰብ መገናኛ ስልክና ጉብኝት ለሚፈልጉም በአፋጣኝ እንደሚመቻች መግባባት ላይ ተደርሷል። ኢሰመኮ በተቋቋመበት አዋጅ ቁጥር 210/1992 (በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 እንደተሻሻለው) አንቀጽ 6/12 መሠረት በአስቸኳይ ጊዜ ወቅት ሰብአዊ መብቶችን የመከታተል ተግባርና ኃላፊነት ያለበት መሆኑን እና በአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታም ውስጥ ቢሆን የጸጥታ እና የፍትሕ አካላት በሰብአዊ መብቶች እና ሕገ መንግሥታዊ መርሖች እንዲመሩ፣ በማናቸውም ሁኔታ ሊገደቡ የማይችሉ መብቶች ሊከበሩ እንደሚገባ፤ እንዲሁም ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አፈጻጸም ጋር የሚወሰዱ ማናቸውም እርምጃዎች የጥብቅ አስፈላጊነትን፣ የተመጣጣኝነትን፣ ከአድሎ ነጻ የመሆንን እና የሕጋዊነትን መርሖች ጨምሮ በሰብአዊ መብቶች መርሖች እና ድንጋጌዎች ሊመሩ እንደሚገባ በማስታወስ፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በላከው ምክረ ሐሳብ፣ እንዲሁም ይፋ ባደረጋቸው ሰነዶች ማሳሰቡ የሚታወስ ነው። በተለይም ሰዎችን ከአስገድዶ መሰወር፣ እገታ፣ አፈና ወይም ባልታወቁ ቦታዎች (unacknowledged detentions) እንዳይታሰሩ የሚደረጉ ጥበቃዎች እንዲሁም ነጻና ገለልተኛ በሆነ ፍርድ ቤት የመዳኘትና ፍትሕ የማግኘት መብት በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት በማናቸውም ጊዜ ቢሆን ሊታገዱ የማይችሉ መብቶች መሆናቸውን ማሳሰቡም ይታወቃል። ኮሚሽኑ አዋጅ ቁጥር 6/2015 ተግባር ላይ ከዋለበት ከሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ የሚደርሱትን አቤቱታዎች እና ጥቆማዎች ከመመርመር፣ መረጃዎችን እና ማስረጃዎችን ከማሰባሰብ በተጨማሪ፣ ተጎጂዎችን፣ የተጎጂ ቤተሰቦችን፣ ምስክሮችን እና ሌሎች የመረጃ ምንጮችን፣ እንዲሁም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድን ኃላፊዎችን ጨምሮ ከሚመለከታቸው የጸጥታ አካላት ጋር በመነጋገር እና የውትወታ ሥራ በመሥራት ከአዋጁ አፈጻጸም ጋር የተያያዙ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን በተመለከተ ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛል። በዚሁም መሠረት፣ በኮማንድ ፖስቱ ትዕዛዝ መታሰራቸው ከተገለጸው ታሳሪዎች በተጨማሪ በዚሁ የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ዐውድ በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ፤ በአማራ ክልል ደብረ ታቦር፣ ባሕር ዳር እና ጎንደር ከተሞችን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች፤ በኦሮሚያ ክልል በአዳማ፣ በቢሾፍቱ፣ በገላን እና በሸገር እንዲሁም ሌሎች ከተሞች፣ መደበኛ ያልሆኑ ቦታዎች ተይዘው ስለነበሩ ሰዎች፣ ከፊሎቹ የተለቀቁ ቢሆንም ይህ ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ እስከሆነበት ጊዜ ድረስ በእስር ላይ ስለሚገኙ ሰዎችና ከእነዚህም መካከል የኤርትራ ፍልሰተኞችን (migrants) ጨምሮ ኮሚሽኑ ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት በመጪው ሰኞ በሚያካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ በተሰናባቹ አቶ ጸጋዬ ቱኬ ምትክ አዲስ ከንቲባ ሊሾም ነው የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት በመጪው ሰኞ ነሐሴ 29፤ 2015 በሚያካሄደው አ
የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት በመጪው ሰኞ በሚያካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ በተሰናባቹ አቶ ጸጋዬ ቱኬ ምትክ አዲስ ከንቲባ ሊሾም ነው የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት በመጪው ሰኞ ነሐሴ 29፤ 2015 በሚያካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የከተማዋን ከንቲባ ጨምሮ የካቢኔ አባላትን ሹመት ሊሰጥ ነው። የከተማዋ ምክር ቤት ሹመቶችን የሚሰጠው፤ የሲዳማ ክልል ካደረገው ግምገማ በኋላ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችም እንዲነሱ መወሰኑን ተከትሎ ነው። የሲዳማ ክልል ከአንድ ሳምንት በፊት ካካሄደው የፓርቲ እና የመንግስት አፈጻጸም ግምገማ በኋላ፤ “ብልሹ አሰራር ፈጽመዋል” ያላቸውን 10 ከፍተኛ አመራሮችን ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቆ ነበር። በዚህ ግምገማ ከስልጣናቸው እንዲነሱ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ባለስልጣናት መካከል ሰባቱ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ተመድበው የሚሰሩ ከፍተኛ አመራሮች መሆናቸውን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያገኘችው ዝርዝር ያመለክታል። ከእነዚህ የከተማይቱ አስተዳደር አመራሮች ውስጥ በስልጣን ከፍተኛውን ቦታ የያዙት፤ ለሶስት ዓመታት ገደማ ሀዋሳን በከንቲባነት የመሩት አቶ ጸጋዬ ቱኬ ናቸው። አቶ ጸጋዬ እና ሌሎች ስድስት የካቢኔያቸው አባላት ከስልጣን ከተነሱ በኋላ ባሉት ሳምንታት፤ የከተማዋን የስራ እንቅስቃሴ ሲመሩ የቆዩት የሀዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሱ አሩሳ ናቸው ተብሏል። 🔵 ለዝርዝሩ 👉 https://ethiopiainsider.com/2023/11939/ @EthiopiaInsiderNews

የሶማሌ ክልል ካቢኔ የሀገር ሽማግሌዎች እና የጎሳ መሪዎች ጉባኤ እንዲቋቋም ውሳኔ አሳለፈ የሶማሌ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት 114 አባላት ያሉት የሀገር ሽማግሌዎች እና የጎሳ መሪዎች ጉባኤ እንዲቋ
የሶማሌ ክልል ካቢኔ የሀገር ሽማግሌዎች እና የጎሳ መሪዎች ጉባኤ እንዲቋቋም ውሳኔ አሳለፈ የሶማሌ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት 114 አባላት ያሉት የሀገር ሽማግሌዎች እና የጎሳ መሪዎች ጉባኤ እንዲቋቋም ውሳኔ አሳለፈ። የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ትላንት ማክሰኞ ነሐሴ 23፤ 2015 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፤ የጉባኤውን ስልጣን እና ኃላፊነት የሚዘረዝረውን አዋጅ ለክልሉ ምክር ቤት መርቷል። የጉባኤው አባላት የሚሆኑ የሀገር ሽማግሌዎች እና የጎሳ መሪዎች ዋነኛ ስራቸው “የማማከር ስራ” መሆኑን የሶማሌ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዲቃድር ረሺድ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። “በአንዳንድ አዳዲስ የሰፈራ ፕሮግራሞች ግጭት ስለሚከሰቱ፤ በግጭት ዙሪያ፣ በጎሳ ግጭት ዙሪያ፣ በልማት ዙሪያ የሚያማክሩን ይሆናል” ሲሉ የቢሮው ኃላፊው አስረድተዋል። የጉባኤው አባላት በመሆን የሚመረጡት የሀገር ሽማግሌዎች የተለያዩ የጎሳ ማህበረሰብ ቅንርጫፎችን የሚወክሉ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ አብዲቃድር፤ “ከአዋጁ መጽደቅ በኋላ በሚወጣ መመሪያ የአባላት ምርጫ በግልጽ የሚቀመጥ ይሆናል” ብለዋል። በዚህ መመሪያ መሰረት የሚመረጡት የጉባኤው አባላት በሚያደርጉት ስብሰባ፤ የጉባኤውን ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር እንደሚመርጡም አመልክተዋል። የጉባኤው ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር በበኩላቸው፤ በአዋጁ በተቀመጠላቸው ስልጣን መሰረት “አስፈላጊ የሆኑ ሹመቶችን” እንደሚሰጡ የቢሮ ኃላፊው አክለዋል። 🔵 ለዝርዝሩ 👉https://ethiopiainsider.com/2023/11934/ @EthiopiaInsiderNews

የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የቀረበባቸውን ክስ እንዲከላከሉ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ብይን ሰጠ የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ) በዐቃ
የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የቀረበባቸውን ክስ እንዲከላከሉ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ብይን ሰጠ የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ) በዐቃቤ ህግ የቀረበባቸውን ክስ እንዲከላከሉ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ብይን ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ዛሬ ሰኞ ነሐሴ 22፤ 2015 በነበረው የችሎት ውሎ ከቀድሞው የክልል ርዕሰ መስተዳድር ጋር በአንድ መዝገብ ከተከሰሱ ግለሰቦች መካከል 16 ተከሳሾችን በነጻ ማሰናበቱን የአቶ አብዲ ጠበቃ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የአቶ አብዲን ጉዳይ ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ችሎት፤ ለዛሬ ቀጠሮ ይዞ የነበረው ዐቃቤ ህግ ባቀረበው ክስ ላይ ብይን ለመስጠት ነበር። በዚህም መሰረት ጉዳያቸው በችሎቱ እየታየ ካሉት 42 ተከሳሾች ውስጥ 26 የሚሆኑት በዐቃቤ ህግ የቀረበባቸውን ክስ እንዲከላከሉ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል። በዐቃቤ ህግ የቀረበባቸውን ክስ እንዲከላከሉ ከተባሉት ተከሳሾች መካከል፤ የሶማሌ ክልልን ለስምንት ዓመት ያስተዳደሩት አቶ አብዲ መሐመድ ይገኙበታል። “አብዲ ኢሌ” በሚለው ቅጽል ስማቸው የሚታወቁት የቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር እንዲከላከሉ የተበየነባቸው፤ “የጦር መሳሪያ ይዞ በማመጽ፣ ወይም የእርስ በርስ ጦርነት በማስነሳት በመንግስት ላይ የሚደረግ ወንጀልን” ፈጽመዋል በሚል በዐቃቤ ህግ የቀረበባቸውን ዋና ክስ መሆኑን ጠበቃቸው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11927/ @EthiopiaInsiderNews

አዲሱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ማናቸው? አቶ አረጋ ከበደ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሆነው እስከተሾሙበት ዕለት ድረስ የአማራ ክልል የስራ ፈጠራና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ ሆነው በማገልገል ላይ
አዲሱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ማናቸው? አቶ አረጋ ከበደ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሆነው እስከተሾሙበት ዕለት ድረስ የአማራ ክልል የስራ ፈጠራና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ። የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በልማት አስተዳደር የሰሩት አቶ አረጋ፤ ወደ ክልል የኃላፊነት ቦታ የመጡት፤ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ረዳት የህዝብ ተሳትፎ አማካሪ በመሆን ነው። ከዚያ በመቀጠልም የክልሉ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ሆነው አገልግለዋል። ከአራት ዓመታት በፊት በክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት ላይ ከተፈጸመው ጥቃት በኋላ አቶ አረጋ፤ የክልሉን ሚሊሺያ ጽህፈት ቤት በኃላፊነት እንዲመሩ ተሹመዋል። ነገር ግን በዚህ የኃላፊነት ቦታ ላይ የቆዩት ለአንድ ዓመት ያህል ብቻ ነው። በሐምሌ 2012 የክልሉ ቴክኒክ ሙያ እና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ኃላፊ በመሆን፤ የወቅቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህን ካቢኔ ተቀላቅለዋል። አቶ አረጋ ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ በኋላ በአማራ ክልል አዲስ መንግስት ሲመሰረት፤ የክልሉ የስራ ፈጠራ እና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል። አቶ አረጋ ወደ ክልል ኃላፊነት ከመምጣታቸው በፊት፤ በምስራቅ ጎጃም ዞን በወረዳ እና በዞን አመራርነት ሰርተዋል። አዲሱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር የምስራቅ ጎጃም ዞንን በምክትል አስተዳዳሪ እና በዋና አስተዳዳሪነት መርተዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11916/ @EthiopiaInsiderNews

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በመጪዎቹ ሶስት ዓመታት “በአማካይ 8.3 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል”- ዶ/ር ፍጹም አሰፋ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት በአማካይ 8.3 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በመጪዎቹ ሶስት ዓመታት “በአማካይ 8.3 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል”- ዶ/ር ፍጹም አሰፋ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት በአማካይ 8.3 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በዚህ ዓመት በ9.2 በመቶ ያድጋል በሚል እቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፤ ከሶስት ዓመት በኋላም በዚህ የእድገት መጠን ደረጃ ላይ እንደማይደርስ የፌደራል መንግስት ይፋ ያደረገው ሰነድ አመልክቷል። የፌደራል መንግስት የልማት እቅድ ሲያዘጋጅ የረጅም ጊዜውን በአስር ዓመት እና የመካከለኛ ጊዜውን ደግሞ በሶስት ዓመት ይከፋፈላል። በዚህ አሰራር መሰረት የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት፤ ከ2013 ዓ.ም እስከ 2015 ድረስ የቆየ የመጀመሪያውን የመካከለኛ ጊዜ እቅድ አዘጋጅቶ እስከተጠናቀቀው በጀት ዓመት መጨረሻ ድረስ ሲተገብር ቆይቷል። በዚህ እቅድ የመጀመሪያ ዓመት፤ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ 8.5 በመቶ እድገት ያስመዘግባል ተብሎ እቅድ ተይዞ ነበር። በ2014 ዓ.ም ወደ 8.7 በመቶ ከፍ እንደሚል የተገመተው የእድገት ምጣኔ፤ በዘንድሮው ዓመት ወደ 9.2 በመቶ እንደሚመነደግ በፌደራል መንግስት የእቅድ ሰነድ ላይ ሰፍሯል። ሆኖም ይህ እቅድ በተከታታይ ሶስት ዓመታት አለመሳካቱ ባለፉት ቀናት በተደረገ “የመካከለኛ ጊዜ አፈጻጸም” ግምገማ ላይ ይፋ ተደርጓል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11907/ @EthiopiaInsiderNews

በሀዋሳ ከተማ ያሉ የንግድ ተቋማት በአንድ ወር ውስጥ የደህንነት ካሜራ እንዲገጥሙ የሚያስገድድ መመሪያ ወጣ የሲዳማ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ የንግድ ተቋማት በአንድ ወር ጊዜ
በሀዋሳ ከተማ ያሉ የንግድ ተቋማት በአንድ ወር ውስጥ የደህንነት ካሜራ እንዲገጥሙ የሚያስገድድ መመሪያ ወጣ የሲዳማ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ የንግድ ተቋማት በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የደህንነት ካሜራ እንዲገጥሙ የሚያስገድድ መመሪያ አወጣ። መመሪያውን ተግባራዊ የማያደርጉ የንግድ ተቋማት ባለቤቶች ላይ የእስር አሊያም የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ቢሮው መመሪያውን ይፋ ያደረገው፤ ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 17፤ 2015 በሀዋሳ ከተማ ከሚገኙ የንግድ ተቋማት ባለቤቶች ጋር ባካሄደው ውይይት ላይ ነው። የሲዳማ ክልል ዋና ከተማ በሆነችው ሀዋሳ የሚገኙ የንግድ ተቋማት፤ የደህንነት ካሜራ እንዲገጥሙ የሚስገድደው መመሪያ የወጣው በሁለት ምክንያቶች ነው ተብሏል። በሀዋሳ ከተማ በሚገኙ አንዳንድ ድርጅቶች ፊት ለፊት “የሞተር ሳይክል ስርቆቶች” በተደጋጋሚ እንደሚፈጸሙ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተናገሩት የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ፤ ይህንን ድርጊት እና በድርጅቶቹ ውስጥ በሀሰተኛ የገንዘብ ኖት የሚደረጉ ግብይቶችን “ለመቆጣጠር” መመሪያው መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በአዲሱ መመሪያ መሰረት በከተማይቱ የሚገኙ የንግድ ተቋማት በድርጅታቸው ውስጥ እና ወደ ውጭ የሚመለከቱ የደህንነት ካሜራዎችን መግጠም ይኖርባቸዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11900/ @EthiopiaInsiderNews

የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ዛሬ ባደረገዉ ስብሰባ ያለፉትን ሃያ ቀናት የሥራ እንቅስቃሴዎቹን ገምግሟል፡፡ ዛሬ ባደረገዉ ግምገማ በሁለተኛዉ እና በሦስተኛው ዙር ወታደራዊ ኦፕሬሽን በተወሰዱ ርምጃዎች አብዛኞቹ የአማራ ክልል ዞኖች ወደ መደበኛ ሁኔታ መመለሳቸውን አረጋግጧል፡፡ በአማራ ክልል ባሕር ዳርን ጨምሮ የዞንና የወረዳ ከተሞችን በመቆጣጣር፣ እሥረኞችን በማስለቀቅ፣ ለዝርፊያ እንዲመቸዉ ቁልፍ መሠረተ ልማቶችን በማውደምና በአማራ ክልል ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በነፍጥ እና በመንጋ በመናድ እኩይ ፖለቲካዊ ፍላጎቱን ለማሳካት ያለመዉ ጽንፈኛና ዘራፊ ኃይል ፍላጎትና ድርጊት ማክሸፉን ዕዙ በግምገማዉ አረጋግጧል፡፡የአማራ ክልልንም ከዝርፊያ፣ ወድመትና የመፍረስ አደጋ መታደግ መቻሉን አይቷል፡፡ በመሆኑም የክልሉን ዞኖች ከባሕር ዳር ከተማ ጋር የሚያገናኙትን ጨምሮ ክልሉን ከአዲስ አበባ ጋር የሚያገናኙና ተዘግተዉ የነበሩ ዋና ዋና መንገዶችና መሥመሮች ተከፍተዋል፡፡ አብዛኞቹ መሥመሮች ለትራስፖርትና ለመደበኛ እንቅስቃሴ ክፍት እንዲሆኑ ተደርገዋል፡፡ ሁሉም የመንግሥትና የግል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የተሟላ መደበኛ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል፡፡ ሕዝቡ ለመከላከያ ሠራዊት እያሳየ ያለው አቀባበል፣ የስንቅና የማበረታቻ ድጋፍ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን ዕዙ በግምገማዉ አረጋግጧል፡፡ በተለያዩ አካባቢዎች በኪስ ቦታዎች እየተሰበሰቡና በቡድን እየተደራጁ መንገድና ሱቆችን ለመዘጋት፣ ዝርፊያና በመሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመፈጸም፣ የተዛቡና የተሳሳቱ መረጃዎችን በማሰራጨት ህብረተሰቡን ለመደናገር ቢሞክሩም እንደልተሳካላቸዉ ዕዙ አይቷል፡፡ የተጀመረዉን ሰላምና መረጋገት ይበልጥ ለማጽናትና አስተማማኝ ለማድረግ ወታደራዊ ኦፕሬሽኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ዕዙ ጥብቅ መመሪያ ሰጥቷል፡፡ ከዘራፊና ጽንፈኛ ኃይሎች በጸዱ አካባቢዎች የድርጊቱ ዋና ዋና ተዋናዮች በሕግ ቁጥጥር ሥር እንዲዉሉ እየተደረገ መሆኑንም አረጋግጧል፡፡ ከአንዳንድ ኪስ ቦታዎች በቀር ሰላማዊ ሁኔታዉና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የፈጠረለትን አጋጣሚ በመጠቀም አርሶ አደሩ ወደ መኸር አዝመራ ሥራው መመለሱንና የግብርና ግብአቶች ወደየአካባቢዎቹ እየተጓጓዙ መሆኑን ዕዙ አረጋግጧል፡፡ ዕዙ ክልሉ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲመለስ ላደረጉ የጸጥታ አካላት፣ ለሕዝቡና በየደረጃዉ ላሉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የቀጠናና በስራቸዉ ላሉ የኮማንድ ፖስት መምሪያ አባላት በዚህ አጋጣሚ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡ መላዉ የክልሉ ሕዝብ ከጸጥታ ኃይሎች ጎን በመሰለፍ ሰላምና መረጋጋት ለመፍጠር ያደረገዉን አኩሪ ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥል ዕዙ ጥሪዉን ያቀርባል፡፡ ነሐሴ 17 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ @ethiopianinsider1

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ በመጪው ዓመት ጥር ወር ዋናውን ኮንፍረንስ ለማካሄድ “የሚቻለውን ጥረት እያደረግኩ ነው” አለ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመጪው ዓመት ጥር ወር ላይ ዋናውን የምክክ
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ በመጪው ዓመት ጥር ወር ዋናውን ኮንፍረንስ ለማካሄድ “የሚቻለውን ጥረት እያደረግኩ ነው” አለ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመጪው ዓመት ጥር ወር ላይ ዋናውን የምክክር ጉባኤ ለመጥራት “የሚቻለውን ጥረት” እያደረገ መሆኑን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ከነገ ነሐሴ 18፤ 2015 ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የጉባኤውን ተሳታፊዎች መለየት እንደሚጀምርም ይፋ አድርጓል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ይህን ይፋ ያደረገው፤ ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 17 በዋና ጽህፈት ቤቱ እየሰጠ ባለው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። ባለፈው ዓመት ታህሳስ ወር ላይ በአዋጅ የተቋቋመው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ እስካሁን ድረስ በአምስት ክልሎች እና አንድ ከተማ አስተዳደር የጉባኤ ተሳታፊዎች ልየታን አከናውኗል። ኮሚሽኑ የጉባኤ ተሳታፊዎችን የለየባቸው አካባቢዎች፤ በሐረሪ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ ናቸው። በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የተገኙት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ፤ “እስከ ጥር ድረስ ዋናውን ሀገራዊ ምክክር ኮንፍረንስ ለመጥራት የሚቻለንን ጥረት እያደረግን ነው” ብለዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) [በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ይታከልበታል] @EthiopiaInsiderNews

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን በውድድር እና በቅደመ ክፍያ ለመቀበል የሚከተለው አካሄድ ምን ይመስላል? አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የሚቀበልበት መንገድ “በጣም
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን በውድድር እና በቅደመ ክፍያ ለመቀበል የሚከተለው አካሄድ ምን ይመስላል? አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የሚቀበልበት መንገድ “በጣም ተገድቦ” እንደነበር ያስታወሱት የተቋሙ ፕሬዝዳንት ፕ/ር ጣሰው ወልደሃና፤ የራስ ገዝ ትግበራው በዚህ ረገድ ለውጥ እንደሚያመጣ ተናግረዋል። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በየዓመቱ 7 ሺህ ገደማ አዳዲስ ተማሪዎችን እንደሚቀበል ከዩኒቨርስቲው የተገኘ መረጃ ያመለክታል። መደበኛ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲው የሚገቡት፤ ልክ እንደሌሎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ሁሉ የትምህርት ሚኒስቴር በሚያደርገው ምደባ ነው። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ራስ ገዝነትን መተግበር ከሚጀምርበት ከቀጣዩ 2016 የትምህርት ዘመን አንስቶ ግን የቅደመ ምረቃ ተማሪዎች የሚገቡበት ይህ አሰራር እንደሚቀር ፕሮፌሰር ጣሰው አስታውቀዋል። “ከ2016 ጀምሮ ዩኒቨርስቲው የመቁረጫ ነጥቡን ያለፉ ተማሪዎችን አወዳድሮ፣ የዩኒቨርስቲ ተልዕኮዬን ያሳኩልኛል የሚላቸውን ተማሪዎች ተቀብሎ ያስተምራል” ሲሉ ፕሮፌሰር ጣሰው ዩኒቨርስቲው የሚከተለውን አዲስ አሰራር ገልጸዋል። አንጋፋው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የቅደመ ምረቃ ተማሪዎችን የሚያወዳድረው፤ ዩኒቨርስቲውን ከመቀላቀላቸው በፊት በሚሰጥ የመግቢያ ፈተና መሆኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ማቲዮስ ኢንሰርሙ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ዩኒቨርስቲው እነዚህን የቅደመ ምረቃ ተማሪዎችን አወዳድሮ የሚያስገባው መንግስት በሚመድብለት በጀት እንደሆነ የገለጹት ዶ/ር ማቲዮስ፤ ከዚህ ውጪ ደግሞ ክፍያ እየፈጸሙ በዩኒቨርስቲው የሚማሩ ተማሪዎች እንደሚኖሩ አስረድተዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11881/