ru
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Открыть в Telegram
2 485
Подписчики
Нет данных24 часа
-157 дней
-5230 дней
Архив постов
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተወሰኑ ተቋማት አገልግሎቶችን ለግል ተቋማት በውክልና አስተላልፎ ሊያሰራ ነው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ያሉ መስሪያ ቤቶች፤ የተወሰኑ ስራዎቻቸውን በውክልና
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተወሰኑ ተቋማት አገልግሎቶችን ለግል ተቋማት በውክልና አስተላልፎ ሊያሰራ ነው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ያሉ መስሪያ ቤቶች፤ የተወሰኑ ስራዎቻቸውን በውክልና ለግል ተቋማት አስተላልፈው (outsource) ሊያሰሩ ነው። በዚህ አሰራር ምክንያት ከስራቸው የሚነሱ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞችን ወደ ሌሎች መስሪያ ቤቶች ለማዘዋወር እና “በሚፈልጉበት የስራ መስክ” እንዲሰማሩ ለመደገፍ መታሰቡም ተገልጿል። አዲሱን አሰራር ተግባራዊ የማድረግ ሂደትን እየመራ ያለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ነው። በከተማ አስተዳደሩ ስር ያሉ መስሪያ ቤቶችን የአገልግሎት አሰጣጥ የመከታተል ኃላፊነት ያለበት ይህ ቢሮ፤ አዳዲስ አሰራሮችን የመዘርጋት ስልጣንም በአዋጅ ተሰጥቶታል። ቢሮው የተወሰኑ የመንግስት ስራዎችን ወደ ግል ተቋማት የማስተላለፍ እቅዱን በተመለከተ፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ካሉ መስሪያ ቤቶች ጋር ዛሬ ሰኞ ግንቦት 21፤ 2015 ዓ.ም ውይይት አድርጓል። ይህንን አሰራር በቅድሚያ እንዲጀምሩ በጥናቱ የተለዩ የከተማ አስተዳደሩ 5 መስሪያ ቤቶች እና 6 ሆስፒታሎች መሆናቸው በዛሬው ውይይት ላይ ተጠቅሷል። በቅድሚያ ወደ ተግባር ይገባሉ የተባሉት የንግድ፣ ትራንስፖርት፣ ገቢዎች እንዲሁም የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮዎች እና የአሽከርካሪ፣ ተሽከርካሪ ፈቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን ናቸው። የየካቲት 12፣ ጥሩነሽ ቤጂንግ፣ ዳግማዊ ሚኒሊክ፣ ዘውዲቱ፣ ጋንዲ መታሰቢያ እና ራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታሎች የተወሰኑ አገልግሎታቸውን ለግል አካላት ከሚያስተላልፉት ውስጥ ተመድበዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11062/ @EthiopiaInsiderNews

ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ለማምለጥ በተደረገ ሙከራ፤ ቢያንስ አምስት ታራሚዎች ቆስለው መያዛቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ በአዲስ አበባ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የሚገኙ የተወሰኑ ታራሚዎች ትላንት ለሊት ለማምለጥ
ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ለማምለጥ በተደረገ ሙከራ፤ ቢያንስ አምስት ታራሚዎች ቆስለው መያዛቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ በአዲስ አበባ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የሚገኙ የተወሰኑ ታራሚዎች ትላንት ለሊት ለማምለጥ ባደረጉት ሙከራ፤ አንድ እስረኛ ሲገደል ቢያንስ አምስቱ መቁሰላቸውን እና አንዱ ሳያይዝ መቅረቱን የአይን እማኞች እና የአካባቢ ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ከቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የማምለጥ ሙከራ መደረጉን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያረጋገጠው የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ግን ያመለጠ እስረኛ “የለም” ብሏል። ከአስር ዓመት እና ከዚያ በላይ የተፈረደባቸው እስረኞችን ከሚያስተናግደው ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት የማምለጥ ሙከራ የተደረገው፤ ለዛሬ አጥቢያ ትላንት ረቡዕ ግንቦት 16፤ 2015 ለሊት አስር ሰዓት ገደማ መሆኑን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው አንድ የአይን እማኝ እና አምስት የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። የማምለጥ ሙከራውን ያደረጉት እስረኞች ብዛት 11 መሆኑን ከማረሚያ ቤት ፖሊሶች መስማታቸውን ነዋሪዎቹ አክለዋል። እንደ ነዋሪዎቹ ገለጻ እስረኞቹ ከማረሚያ ቤቱ አምልጠው መውጣታቸውን ተከትሎ፤ በትንሹ ለአንድ ሰዓት ያህል የቆየ ተኩስ በአካባቢው ሲሰማ ቆይቷል። ድርጊቱ በተፈጸመበት ሰዓት በስራ ምክንያት በአካባቢው እንደነበሩ የተናገሩ አንድ የዓይን እማኝ በበኩላቸው፤ ተኩሱ ይበልጥ ጎልቶ ይሰማ የነበረው በማረሚያ ቤቱ መግቢያ ላይ ባለው አስፓልት መንገድ ላይ እና ተሻግሮ ባሉት አካባቢዎች እንደነበር አስረድተዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11039/ @EthiopiaInsiderNews

በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በተቀሰቀሰ ግጭት አምስት ሰዎች መገደላቸው ተነገረ በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች ነዋሪዎች መካከል በተከሰተ ግጭት አምስት ሰዎች መገደላቸውን
በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በተቀሰቀሰ ግጭት አምስት ሰዎች መገደላቸው ተነገረ በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች ነዋሪዎች መካከል በተከሰተ ግጭት አምስት ሰዎች መገደላቸውን የልዩ ወረዳው አስተዳደር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታወቀ። በግጭቱ ጉዳት የደረሰባቸው ሰባት ሰዎች ደግሞ በህክምና ላይ መሆናቸውን አስተዳደሩ ገልጿል። የኑዌር፣ አኝዋ እና ኮሞ ብሔረሰቦች መኖሪያ በሆነው ኢታንግ ልዩ ወረዳ ግጭት የተቀሰቀሰው፤ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እሁድ ግንቦት 13፤ 2015 መሆኑን የልዩ ወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኡቦንግ ጊሎ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በዚሁ ዕለት ጠዋት ጀልባ በመቅዘፍ ላይ የነበረ አንድ የሚሊሺያ አባል በጥይት ተመትቶ መገደሉ፤ በልዩ ወረዳው ለተነሳው ግጭት መነሻ ምክንያት መሆኑንም አስረድተዋል። ጥቃት የተፈጸመበትን የሚሊሺያ አባል ሁኔታ ለመመልከት ወደ ስፍራው የሄዱ የአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ተኩስ ከተከፈተ በኋላ ሁኔታው ወደ ግጭት ማምራቱን አቶ ኡቦንግ ገልጸዋል። ተኩሱን የከፈቱት “ደፈጣ ላይ” የነበሩ ታጣቂዎች መሆናቸውን የጠቀሱት ዋና አስተዳዳሪው፤ ይህን ጥቃት ተከትሎ የአኝዋ እና ኑዌር ብሔረሰቦች መኖሪያ በሆኑ ቀበሌዎች መካከል “ውጊያ” መጀመሩን አብራርተዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11031/ @EthiopiaInsiderNews

በ37 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በተካሄደ የኦዲት ምርመራ፤ “ምንም ጉድለት” ያልተገኘባቸው ሁለቱ ብቻ መሆናቸው ተገለጸ የ2013 ሂሳባቸው ኦዲት ከተደረጉ 37 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ “ምንም
በ37 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በተካሄደ የኦዲት ምርመራ፤ “ምንም ጉድለት” ያልተገኘባቸው ሁለቱ ብቻ መሆናቸው ተገለጸ የ2013 ሂሳባቸው ኦዲት ከተደረጉ 37 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ “ምንም ጉድለት ያልተገኘባቸው” ሁለቱ ብቻ እንደሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። ሚኒስቴሩ ኦዲት ከተደረጉት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ 48.6 በመቶው “ተቀባይነት የሚያሳጣ” ደረጃ ላይ እንደሆኑ ተረጋግጧል ብሏል። የትምህርት ሚኒስቴር ይህንን ያስታወቀው ትላንት ማክሰኞ ግንቦት 15፤ 2015 በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው። በዚህ ስብሰባ ላይ በቀረበው የሚኒስቴሩ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከተነሱ ጉዳዮች ውስጥ፤ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎችን የተመለከተው ይገኝበታል። ዩኒቨርስቲዎቹ ዘንድሮ ያስተናገዷቸውን ተማሪዎች ብዛት፣ በፓርላማ ለመጽደቅ በሂደት ላይ ያለው የዩኒቨርስቲዎች ራስ ገዝ አስተዳደር አዋጅ እና በዚህ ዓመት የሚጀመረው የተማሪዎች መውጫ ፈተና በሪፖርቱ የተጠቀሱ ጉዳዮች ናቸው። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ያላቸው የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓትም በዚሁ ሪፖርት ተካትቷል። ሪፖርቱን ለተወካዮች ምክር ቤት አባላት በንባብ ያቀረቡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፤ ተቋማቱ በዚህ ረገድ ያሉበት ደረጃ የፌደራል ዋና ኦዲተር ካደረገው የ2013 ዓ.ም የሂሳብ ኦዲት በኋላ ለመለየት መቻሉን አስታውቀዋል። እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ ኦዲት ከተከናወነባቸው 37 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ 18 ያህሉ “ተቀባይነት የሚያሳጣ” የኦዲት ጉድለት ተገኝቶባቸዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11028/ @EthiopiaInsiderNews

#BerhanuNega #Education በኢትዮጵያ ካሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ “ከፍተኛ” የሚባለውን ደረጃ ያሟሉ፤ አራት ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ በኢትዮጵያ በአጠቃላይ የትምህርት ዘ
#BerhanuNega #Education በኢትዮጵያ ካሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ “ከፍተኛ” የሚባለውን ደረጃ ያሟሉ፤ አራት ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ በኢትዮጵያ በአጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ካሉ 47 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተፈላጊውን “ከፍተኛ ደረጃ” የሚያሟሉት አራቱ ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ወላጆች፣ የቀድሞ ተማሪዎች እና መምህራንን የሚያሳትፍ፤ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ያለመ ሀገር አቀፍ የትምህርት ዘመቻ በአንድ ወር ተኩል ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል። የትምህርት ሚኒስቴር ይህንን ያስታወቀው ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 15፤ 2015 በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው። ሪፖርቱን ለፓርላማ አባላት ያቀረቡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአጽንኦት ካነሷቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ፤ የትምህርት ቤቶችን ጥራት የሚመለከት ነው። እርሳቸው የሚመሩት መስሪያ ቤት በሀገሪቱ አጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ባሉ 47 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ግምገማ ማድረጉን የተናገሩት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ በተገኘው ውጤት ላይ ተመስርቶ ትምህርት ቤቶቹ በአራት ደረጃዎች እንደተመደቡ ገልጸዋል። ግምገማው የተደረገው፤ ትምህርት ቤቶች በሚጠቀሟቸው ግብዓቶች፣ በመማር ማስተማር ሂደቶቻቸው እንዲሁም ተማሪዎቻቸው በሚያስመዘግቧቸው ውጤቶች ላይ እንደነበር አመልክተዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11020/ @EthiopiaInsiderNews

#SugarFactories #Privatization ለሽያጭ የቀረቡ የመንግስት የስኳር ፋብሪካዎችን ወደ ግል ማዛወር የሚፈልጉ ኩባንያዎች ምክረ ሃሳባቸውን እንዲያቀርቡ ተጠየቁ የኢትዮጵያ መንግስት በስሩ
#SugarFactories #Privatization ለሽያጭ የቀረቡ የመንግስት የስኳር ፋብሪካዎችን ወደ ግል ማዛወር የሚፈልጉ ኩባንያዎች ምክረ ሃሳባቸውን እንዲያቀርቡ ተጠየቁ የኢትዮጵያ መንግስት በስሩ ያሉ ስምንት የስኳር ፋብሪካዎችን ወደ ግል ማዛወር ለሚሹ ገዢዎች ምክረ ሃሳባቸውን (proposal) እንዲያቀርቡ ጋበዘ። ለሽያጭ ከቀረቡት መካከል የአርጆ ዴዴሳ፣ ከሰም፣ ጣና በለስ እና ተንዳሆ የስኳር ፋብሪካዎች ይገኙበታል። በመንግስት እጅ ከሚገኙት ከእነዚህ ስምንት ፋብሪካዎች ውስጥ አራቱ በኦሞ ኩራዝ የስኳር ፕሮጀክት ስር የሚገኙ ናቸው። እነዚህን የስኳር ፋብሪካዎች መግዛት የሚሹ የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ምክረ ሃሳቦቻቸውን ከዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 15፤ 2015 ጀምሮ እንዲያስገቡ ግብዣ ቀርቦላቸዋል። የገንዘብ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የተሰኘው መንግስታዊ ተቋም በጋራ ባወጡት መግለጫ፤ ዛሬ ይፋ የሆነው ሂደት “መንግስት ወደ ተወዳዳሪ የገበያ መዋቅር ለመሸጋገር እና በስኳር ዘርፍ ያለውን የግሉን ዘርፍ ዕድገት ለማጠናከር የሚያደርገው ጥረት ወሳኝ ምዕራፍ” እንደሆነ አስታውቀዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11017/ @EthiopiaInsiderNews

የሀገሬ ቴሌቪዥን ሥራ አስኪያጅና ዕውቁ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መምህር ብርሃኑ አድማስ ዛሬ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓም በፀጥታ ኀይሎች ከቢሯቸው መወሰዳቸውን ዋዜማ ከአይን እማኞች ሰም
የሀገሬ ቴሌቪዥን ሥራ አስኪያጅና ዕውቁ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መምህር ብርሃኑ አድማስ ዛሬ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓም በፀጥታ ኀይሎች ከቢሯቸው መወሰዳቸውን ዋዜማ ከአይን እማኞች ሰምታለች። መ/ር ብርሃኑ የተወሰዱት "ለጥያቄ ትፈለጋለህ" ተብለው መሆኑንም ሰምተናል። ዘገባው የዋዜማ ራዲዮ ነው። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news

#Balderas #GeneralAssembly ባልደራስ ዛሬ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ፤ ወደ ሀገር አቀፍ ፓርቲነት ለማደግ የቀረበለትን ውሳኔ አጸደቀ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ወደ ሀገር አቀፍ
#Balderas #GeneralAssembly ባልደራስ ዛሬ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ፤ ወደ ሀገር አቀፍ ፓርቲነት ለማደግ የቀረበለትን ውሳኔ አጸደቀ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ወደ ሀገር አቀፍ ፓርቲነት ለማደግ ዛሬ እሁድ ግንቦት 13፤ 2015 ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ወሰነ። በዛሬው የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ፤ ባልደራስን በምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ አምሃ ዳኘው በፕሬዝዳንትነት ተመርጠዋል። ባልደራስ ከምስረታ ጉባኤው በኋላ ባካሄደው የዛሬው የመጀመሪያ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ፤ የፓርቲውን የወደፊት አቅጣጫ በሚወስኑ ዋነኛ ጉዳዮች ላይ ውሳኔዎች ተላልፈዋል። ለፓርቲው አዲስ ፕሬዝዳንት መሾም፤ በጠቅላላ ጉባኤው ቅድሚያ ውሳኔ የተሰጠበት ጉዳይ ነው። ባልደራስ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመምረጥ የወሰነው፤ ፓርቲውን ከምስረታው ጀምሮ በፕሬዝዳንትነት የመሩት አቶ እስክንድር ነጋ ባለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ ራሳቸውን ከኃላፊነት በማግለላቸው ምክንያት ነው። አቶ እስክንድርን ለመተካት በዛሬው ጠቅላላ ጉባኤ ከቀረቡ ሶስት ዕጩዎች መካከል፤ የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አምሃ ዳኘው ይገኙበታል። ለፕሬዝዳትነት ለመወዳደር የቀረቡት ሌሎች ዕጩዎች፤ የፓርቲው ብሔራዊ ምክር ቤት ጸሀፊ ዶ/ር በቃሉ አጥናፉ እና የፓርቲው የህግ ክፍል ኃላፊ የሆኑት አቶ ሳምሶን ገረመው ናቸው። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11005/ @EthiopiaInsiderNews

#G7Summit #Ethiopia የቡድን ሰባት ሀገራት፤ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ለፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ ትግበራ ቁርጠኛ እንዲሆኑ ጥሪ አቀረቡ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት
#G7Summit #Ethiopia የቡድን ሰባት ሀገራት፤ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ለፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ ትግበራ ቁርጠኛ እንዲሆኑ ጥሪ አቀረቡ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በደቡብ አፍሪካ ለተፈረመው ግጭት የማቆም ስምምነት ሙሉ ትግበራ ቁርጠኛ እንዲሆኑ የቡድን ሰባት መሪዎች ጉባኤ ጥሪ አቀረበ። በኢንዱስትሪ የበለጸጉት ሰባት አገራት መሪዎች ትላንት ቅዳሜ ግንቦት 12፤ 2015 ባወጡት መግለጫ በፕሪቶሪያ ግጭት የማቆም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ “የተገኙትን መልካም ለውጦች” በአዎንታ እንደሚቀበሉ አስታውቀዋል። የአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን እና የፈረንሳዩ አቻቸው ኤማኑዌል ማክሮን ጨምሮ የቡድን ሰባት መሪዎች፤ ባለፈው ጥቅምት ወር በፕሪቶሪያ ከተማ የተፈረመውን ስምምነት በተመለከተ ጠቅለል ያለ አቋማቸውን የገለጹት በጃፓን ሂሮሺማ ባካሄዱት ጉባኤ ባወጡት መግለጫ ነው። መሪዎቹ በዚሁ ጉባኤያቸው ዋነኛ ትኩረታቸውን ያደረጉት ዩክሬን፣ ሩሲያ እና ቻይናን ለተመለከቱ ጉዳዮች ቢሆንም ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካን በተመለከተ ያላቸውን አቋም ጭምር አንጸባርቀዋል። በኢንዱስትሪ የበለጸጉት ሀገራት መሪዎች፤ በኢትዮጵያ ጎረቤት ሱዳን ስድስተኛ ሳምንቱን ያስቆጠረውን ጦርነት እንዲሁም የአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት ጉዳይን በመግለጫቸው ትኩረት ሰጥተው አንስተዋል። የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ “ቅድሚያ ለሚሰጧቸው ማሻሻያዎች” እና በአልሸባብ ላይ ለጀመሩት ዘመቻ ዓለም አቀፍ ድጋፍ እንዲደረግም ጥሪ አቅርበዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11000/ @EthiopianInsider1

#G7Summit #Ethiopia የቡድን ሰባት ሀገራት፤ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ለፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ ትግበራ ቁርጠኛ እንዲሆኑ ጥሪ አቀረቡ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት
#G7Summit #Ethiopia የቡድን ሰባት ሀገራት፤ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ለፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ ትግበራ ቁርጠኛ እንዲሆኑ ጥሪ አቀረቡ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በደቡብ አፍሪካ ለተፈረመው ግጭት የማቆም ስምምነት ሙሉ ትግበራ ቁርጠኛ እንዲሆኑ የቡድን ሰባት መሪዎች ጉባኤ ጥሪ አቀረበ። በኢንዱስትሪ የበለጸጉት ሰባት አገራት መሪዎች ትላንት ቅዳሜ ግንቦት 12፤ 2015 ባወጡት መግለጫ በፕሪቶሪያ ግጭት የማቆም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ “የተገኙትን መልካም ለውጦች” በአዎንታ እንደሚቀበሉ አስታውቀዋል። የአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን እና የፈረንሳዩ አቻቸው ኤማኑዌል ማክሮን ጨምሮ የቡድን ሰባት መሪዎች፤ ባለፈው ጥቅምት ወር በፕሪቶሪያ ከተማ የተፈረመውን ስምምነት በተመለከተ ጠቅለል ያለ አቋማቸውን የገለጹት በጃፓን ሂሮሺማ ባካሄዱት ጉባኤ ባወጡት መግለጫ ነው። መሪዎቹ በዚሁ ጉባኤያቸው ዋነኛ ትኩረታቸውን ያደረጉት ዩክሬን፣ ሩሲያ እና ቻይናን ለተመለከቱ ጉዳዮች ቢሆንም ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካን በተመለከተ ያላቸውን አቋም ጭምር አንጸባርቀዋል። በኢንዱስትሪ የበለጸጉት ሀገራት መሪዎች፤ በኢትዮጵያ ጎረቤት ሱዳን ስድስተኛ ሳምንቱን ያስቆጠረውን ጦርነት እንዲሁም የአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት ጉዳይን በመግለጫቸው ትኩረት ሰጥተው አንስተዋል። የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ “ቅድሚያ ለሚሰጧቸው ማሻሻያዎች” እና በአልሸባብ ላይ ለጀመሩት ዘመቻ ዓለም አቀፍ ድጋፍ እንዲደረግም ጥሪ አቅርበዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11000/ @EthiopiaInsiderNews

#TemesgenDesalegn ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ ተወሰደ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ቅዳሜ ምሽት ሁለት ሰዓት ገደማ ግንቦት 12፤ 2015 ከመኖሪያ ቤቱ በጸጥታ ኃይሎች
#TemesgenDesalegn ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ ተወሰደ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ቅዳሜ ምሽት ሁለት ሰዓት ገደማ ግንቦት 12፤ 2015 ከመኖሪያ ቤቱ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ መወሰዱን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ተመስገንን የወሰዱት በሁለት ፒክ አፕ ተጨነው የመጡ እና የፖሊስ ደንብ ልብስ የለበሱ የጸጥታ ኃይሎች መሆናቸውን ገልጸዋል። እስከ ምሽት ድረስ ከቅርብ ጓደኞቹ ጋር የነበረው ተመስገን፤ በአዲስ አበባ ጃንሜዳ አካባቢ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በሚገባበት ወቅት፤ የግቢ ዙሪያው በጸጥታ ኃይሎች ተከብቦ ማግኘቱን የዓይን እማኞቹ ተናግረዋል። እንደ እማኞቹ እና ቤተሰቦቹ ከሆነ፤ ተመስገን የተወሰደበትን ቦታ እስከ ምሽት አራት ሰዓት ድረስ ማወቅ አልተቻለም። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

#BalderasParty ጠቅላላ ጉባኤውን እንዳያደርግ ተከልክሎ የነበረው ባልደራስ ፓርቲ፤ በመጪው እሁድ ስብሰባውን ሊያካሄድ ነው ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ፤ ከሁለት ወራት በፊት በክልከላ
#BalderasParty ጠቅላላ ጉባኤውን እንዳያደርግ ተከልክሎ የነበረው ባልደራስ ፓርቲ፤ በመጪው እሁድ ስብሰባውን ሊያካሄድ ነው ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ፤ ከሁለት ወራት በፊት በክልከላ ሳቢያ ተደናቅፎ የነበረውን የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባውን ከነገ በስቲያ እሁድ ግንቦት 13፤ 2015 ሊያካሄድ ነው። የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ በድጋሚ እንዳይስተጓጎል፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስብሰባው ከሚደረግበት ሆቴል ጋር ውል የመግባት እና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማሳወቅ ስራ እንዳከናወነ ተገልጿል። ከሶስት ዓመት በፊት የተመሰረተው ባልደራስ ፓርቲ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ሊያደርግ የነበረው፤ ባለፈው መጋቢት ወር መጀመሪያ ላይ ነበር። በዕለቱ የፓርቲው አባላት ጠቅላላ ጉባኤው ይካሄድበታል በተባለው ጋምቤላ ሆቴል ቢሰባሰቡም፤ ሆቴሉ ስብሰባውን ማስተናገድ እንደማይችል ማስታወቁ ይታወሳል። ከዚህ በኋላ ፓርቲው በሚያዝያ 22፤ 2015 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤውን ለማድረግ በድጋሚ ቀጠሮ ይዞ እንደነበር የባልደራስ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አምሃ ዳኘው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ፓርቲው ለዚህ ስብሰባው ዝግጅት እያደረገ ባለበት ሰዓት፤ ራሳቸው ምክትል ፕሬዝዳንቱ በመታሰራቸው ምክንያት የታቀደው ጠቅላላ ጉባኤ መስተጓጎሉን አቶ አምሃ አስረድተዋል። እርሳቸው ከእስር ከተፈቱ በኋላ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ በድጋሚ ዝግጅት መጀመሩን የገለጹት የባልደራስ ምክትል ፕሬዝዳንት፤ ይህ ዝግጅት ተጠናቅቆ በመጪው እሁድ ጉባኤውን በኢትዮጵያ ሆቴል ለማካሄድ ቀጠሮ መያዙን አስታውቀዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10985/ @EthiopiaInsiderNews

#NationalDialogue የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ከህብረተሰቡ የሚቀርቡ የምክክር አጀንዳዎችን ከዛሬ ጀምሮ መቀበል እንደጀመረ አስታወቀ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ የህ
#NationalDialogue የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ከህብረተሰቡ የሚቀርቡ የምክክር አጀንዳዎችን ከዛሬ ጀምሮ መቀበል እንደጀመረ አስታወቀ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚላኩለትን የምክክር አጀንዳዎች ከዛሬ ጀምሮ መቀበል እንደጀመረ አስታወቀ። ኮሚሽኑ በሀገራዊ ምክክሩ ላይ የሚሳተፉ ግለሰቦችን የመለየት ስራን፤ በ4 ክልሎች እና በ1 የከተማ አስተዳደር ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ እንደሚያከናውንም ገልጿል። የምክክር ኮሚሽኑ ዛሬ አርብ ግንቦት 11፤ 2015 በጽህፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ተሳታፊዎችን የመለየት ስራ የሚጀመረው በጋምቤላ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና ሀረሪ ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እንደሆነ ይፋ አድርጓል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ፤ በአራቱ ክልሎች እና በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባሉ ሁሉም ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ “የተለዩ የህብረተሰብ ክፍሎች” “ይወክሉኛል” የሚሏቸውን ተሳታፊዎች እንዲመርጡ እንደሚደረግ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። ኮሚሽኑ ከተሳታፊዎች የመለየት ስራ ጎን ለጎን በቀጣዩ ሳምንት በዋናነት የሚያከናውነው ስራ “አጀንዳዎች ማሰባሰብ” መሆኑን ዋና ኮሚሽነሩ ገልጸዋል። በሀገራዊ ምክክሩ ላይ ሊቀርቡ ይገባሉ የሚባሉ አጀንዳዎች “በቀጥታ ከህዝቡ” የሚሰበሰቡ መሆኑን ያስታወሱት ፕሮፌሰር መስፍን፤ ፍላጎቱ ያላቸው ሰዎች “በኢሜል፣ በአካል ወደ ኮሚሽኑ በመምጣት እና በፖስታ” አጀንዳዎችን ማቅረብ እንደሚችሉ አስታውቀዋል። ኮሚሽኑ በእንደዚህ አይነት መልኩ የሚመጡ አጀንዳዎችን ከዛሬ ጀምሮ መቀበል እንደሚጀምር ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ሂሩት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10976/ @EthiopiaInsiderNews

#YilkalKefale #Amhara የአማራ ክልል ከዚህ ቀደም የሚያነሳቸው “የማንነት እና የወሰን፣ የተዛባ ትርክት፣ የህገ መንግስት ማሻሻል፣ ዜጎች በየትኛውም አካባቢ መብታቸው ተጠብቆ መኖርን” የተ
#YilkalKefale #Amhara የአማራ ክልል ከዚህ ቀደም የሚያነሳቸው “የማንነት እና የወሰን፣ የተዛባ ትርክት፣ የህገ መንግስት ማሻሻል፣ ዜጎች በየትኛውም አካባቢ መብታቸው ተጠብቆ መኖርን” የተመለከቱ ጥያቄዎች፤ “በውል እንደገና መመርመር እና መፈተሽ” እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ተናገሩ። ርዕሰ መስተዳድሩ ለእነዚህ ጥያቄዎች “መውጫ መንገድ ማስቀመጥ ይገባል” ብለዋል። ዶ/ር ይልቃል ይህን ያሉት፤ የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች የተካፈሉበት ኮንፈረንስ ዛሬ ሐሙስ ግንቦት 10፤ 2015 በባህር ዳር ከተማ በተጀመረበት ወቅት ባሰሙት ንግግር ነው። “በአማራ ክልል ያደሩ፣ የነበሩ እና ትግል እየተካሄደባቸው ያሉ ጥያቄዎች አሉ” ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ገዢው ብልጽግና ፓርቲ የክልሉን ህዝብ ጥያቄዎች ለማስመለስ “በሂደት ላይ የሚገኝ” መሆኑን ለኮንፍረንሱ ተሳታፊዎች ገልጸዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

#Metema #Sudan #Refugees በሱዳን ግጭት ለተሰደዱ ሰዎች፤ በምዕራብ ጎንደር ዞን በ56 ሄክታር መሬት ላይ ቋሚ የመጠለያ ጣቢያ ሊገነባ ነው በሱዳን እየተካሄደ ባለው የእርስ በእርስ ግጭት
#Metema #Sudan #Refugees በሱዳን ግጭት ለተሰደዱ ሰዎች፤ በምዕራብ ጎንደር ዞን በ56 ሄክታር መሬት ላይ ቋሚ የመጠለያ ጣቢያ ሊገነባ ነው በሱዳን እየተካሄደ ባለው የእርስ በእርስ ግጭት ሳቢያ፤ በየዕለቱ ከ800 በላይ ሰዎች በአማራ ክልል መተማ ዮሃንስ ከተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ መሆኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን አስታወቀ። ለስደተኞቹ በዞኑ ስር ባለ 56 ሄክታር መሬት ላይ ቋሚ የመጠለያ ጣቢያ ሊገነባ መሆኑም ተገልጿል። ከተቀሰቀሰ አንድ ወር ያለፈውን የሱዳን ግጭት በመሸሽ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ያሉት፤ በአማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ጋምቤላ ክልሎች በኩል አድርገው መሆኑን የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ትላንት ረቡዕ ግንቦት 9 ባወጣው መግለጫ አስታውቆ ነበር። ስደተኞችን በቀዳሚነት ማስተናገድ በጀመረው የአማራ ክልል መተማ ወረዳ በኩል፤ ካለፈው ሚያዝያ ወር ጀምሮ ከ22 ሺህ በላይ ስደተኞች ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸውን የምዕራብ ጎንደር ዞን የአደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አበባው በዛብህ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የምዕራብ ጎንደር ዞን እስካሁን ድረስ የ66 ሀገራት ዜግነት ያላቸውን ስደተኞች መቀበሉን የጠቆሙት ኃላፊው፤ ወደ መተማ የሚገቡትን ሰዎች በሁለት ምድብ ከፍሎ ሲያስተናግድ መቆየቱን አስረድተዋል። በመጀመሪያው ምድብ የተቀመጡት በሱዳን ውስጥ ይኖሩ የነበሩት ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ፤ ዞኑ “ከስደት ተመላሾች” በሚል አግባብ ማስተናገዱን ገልጸዋል። ሱዳናውያን ጨምሮ የሌሎች ሀገራት ዜጎች ደግሞ “ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች” በሚለው ሁለተኛ ምድብ አቀባበል ሲደረግላቸው መቆየቱን አብራርተዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10964/ @EthiopiaInsiderNews

#Sidama #SNNPR #SouthWestEthiopia #Budget የፌደራል መንግስት “ደመወዝ የመክፈል ጫና ውስጥ ለገቡ” ክልሎች፤ ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ማበደሩን የገንዘብ ሚኒስትሩ ተናገሩ የ
#Sidama #SNNPR #SouthWestEthiopia #Budget የፌደራል መንግስት “ደመወዝ የመክፈል ጫና ውስጥ ለገቡ” ክልሎች፤ ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ማበደሩን የገንዘብ ሚኒስትሩ ተናገሩ የክልል መንግስታት ላጋጠማቸው የበጀት እጥረት፤ የፌደራል መንግስት ብድር መስጠት እንጂ ቀጥታ ድጋፍ ማድረግ እንደማይችል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ። የፌደራል መንግስት “ደመወዝ የመክፈል ጫና ውስጥ ለገቡ” ክልሎች፤ ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ማበደሩንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል። የገንዘብ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት፤ ትላንት ረቡዕ ግንቦት 9፤ 2015 ከተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ላይ ነው። የሚመሩት የሚኒስቴር መስሪያ ቤትን የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ለማቅረብ በፓርላማ ለተገኙት አቶ አህመድ ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል፤ ክልሎች የገጠማቸውን የበጀት እጥረት የተመለከተው አንዱ ነበር። ለዚህ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ሚኒስትሩ አቶ አህመድ፤ “ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንዳንድ ክልሎች ደመወዝ የመክፈል ጫና” ውስጥ መግባታቸውን አረጋግጠዋል። ይህ ችግር በተለይም በአዲስ ክልሎች ውስጥ የሚታይ ቢሆንም “አንዳንድ ነባር ክልሎችም ጭምር” ተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን አንስተዋል። ሚኒስትሩ “ደመወዝ የመክፈል ጫና ውስጥ ገብተዋል” በሚል የጠቀሷቸው፤ ደቡብ፣ ሲዳማ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎችን ነው። የሶማሌ እና አፋር ክልሎችም ተመሳሳይ ችግር እንዳጋጠማቸው በገንዘብ ሚኒስቴር የትሬዠሪ ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ነጠሩ ወንድወሰን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10956/ @EthiopiaInsiderNews

ከውጭ የልማት አጋሮች ዘንድሮ ለማግኘት ታቅዶ የነበረው 7.7 ቢሊዮን ብር፤ እስካሁን “ፈሰስ አለመደረጉን” የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ የፌደራል መንግስት በተያዘው በጀት ዓመት ከውጭ ቀጥታ የበጀት
ከውጭ የልማት አጋሮች ዘንድሮ ለማግኘት ታቅዶ የነበረው 7.7 ቢሊዮን ብር፤ እስካሁን “ፈሰስ አለመደረጉን” የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ የፌደራል መንግስት በተያዘው በጀት ዓመት ከውጭ ቀጥታ የበጀት ድጋፍ 7.7 ቢሊዮን ብር ለማግኘት ቢያቅድም፤ እስካሁን “ፈሰስ አለመደረጉን” የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሶስት ሚሊዮን ዜጎች በጦርነት እና ግጭት ሳቢያ “ወደ ከፋ ድህነት” መግባታቸውን በጥናት ማረጋገጡንም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል። የገንዘብ ሚኒስቴር ይህን ያስታወቀው የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን፤ ለተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 9፤ 2015 ባቀረበበት ወቅት ነው። በገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ በቀረበው የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ከተነሱ ጉዳዮች ውስጥ የመንግስትን ገቢ የሚመለከተው ይገኝበታል። የፌደራል መንግስት በተያዘው በጀት ዓመት፤ ከታክስ፣ ታክስ ካልሆኑ እና ከውጭ ቀጥተኛ የበጀት ድጋፍ 446.5 ቢሊዮን ብር ለማግኘት አቅዶ እንደነበር በሚኒስቴሩ ሪፖርት ላይ ተጠቅሷል። ከዚህ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው የታክስ ገቢ ሲሆን፤ ከዚህም 400.2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ነበር። በዘንድሮው በጀት ዓመት መጀመሪያ ላይ በተያዘው በዚህ እቅድ፤ “ከውጭ የልማት አጋሮች የሚመጣ ቀጥተኛ የበጀት ድጋፍ” በሚል ታሳቢ ተደርጎ የነበረው 7.7 ቢሊዮን ብር ነበር። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10951/ @EthiopianInsider1

#Bishoftu #Police በቢሾፍቱ ከተማ ባለ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት አራት ፖሊሶች ተገደሉ ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ገደማ ላይ በምትገኘው የቢሾፍቱ ከተማ “ማንነታቸ
#Bishoftu #Police በቢሾፍቱ ከተማ ባለ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት አራት ፖሊሶች ተገደሉ ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ገደማ ላይ በምትገኘው የቢሾፍቱ ከተማ “ማንነታቸው ያልታወቁ” ታጣቂዎች ትላንት እሁድ ግንቦት 6፤ 2015 ለሊት በፖሊስ ጣቢያ ላይ በከፈቱት ጥቃት፤ አራት የኦሮሚያ ፖሊስ አባላት ተገደሉ። በጥቃቱ ጉዳት የደረሰበት አንድ የፖሊስ አባል፤ አዲስ አበባ ወደሚገኘው የፖሊስ ሆስፒታል ተወስዶ በህክምና ላይ መሆኑን የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ምንጮች ገልጸዋል። በቢሾፍቱ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ስር በሚገኘው የክፍለ ከተማ ሶስት ፖሊስ ጽህፈት ቤት ላይ ታጣቂዎች ተኩስ የከፈቱት፤ ሌሊት ስድስት ሰዓት ገደማ ላይ መሆኑን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው ሶስት የአካባቢው ነዋሪዎች አስረድተዋል። በከተማዋ መግቢያ ላይ “ሰንሻይን” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው በዚሁ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ጥቃቱን የፈጸሙት ታጣቂዎች፤ “ማንነታቸው የማይታወቅ” መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በዚሁ አካባቢ የሚኖሩ አንድ የዓይን እማኝ፤ በትላትናው ዕለት እኩለ ለሊት ገደማ በታጣቂዎቹ እና በፖሊስ አባላቱ መካከል “ከፍተኛ ድምጽ” ያለው የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር ገልጸዋል። የተኩስ ልውውጡ ለአንድ ሰዓት ገደማ ያህል የቆየ እንደነበርም ተናግረዋል። ሌላው የአካባቢው ነዋሪ በበኩላቸው፤ በፖሊስ ጣቢያው ፊት ለፊት በሚገኘው “ያቱ ሆቴል” ተረኛ የነበሩ የጥበቃ ሰራተኞች ላይ ጭምር ተኩስ ተከፍቶባቸው ነበር ብለዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10940/ @EthiopiaInsiderNews

በአዲስ አበባ የቤት ግብር ከሚከፍሉ 183 ሺህ ገደማ መኖሪያ ቤቶች የሚገኘው ዓመታዊ ገቢ፤ 47.7 ሚሊዮን ብር መሆኑን ከከተማይቱ ፋይናንስ ቢሮ የተገኘ መረጃ ያመለክታል። ግብር ከሚከፈልባቸው ከእነ
በአዲስ አበባ የቤት ግብር ከሚከፍሉ 183 ሺህ ገደማ መኖሪያ ቤቶች የሚገኘው ዓመታዊ ገቢ፤ 47.7 ሚሊዮን ብር መሆኑን ከከተማይቱ ፋይናንስ ቢሮ የተገኘ መረጃ ያመለክታል። ግብር ከሚከፈልባቸው ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ 12 በመቶው የሚከፍሉት “ከ10 ብር በታች” መሆኑን የሚገልጹት በአዲስ አበባ ከተማ ፋይናንስ ቢሮ የንብረት ታክስ ጊዜያዊ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት አስተባባሪ አቶ አስማማው ሙሉጌታ፤ 46 በመቶው ደግሞ “ከመቶ ብር በታች” መሆኑን በአጽንኦት ጠቅሰዋል። 2,500 ያህል ቤቶች ከ1 ብር በታች እንደሚከፍሉ በተጨማሪነት ያነሱት አስተባባሪው፤ “ለዓመታዊ ግብር ከ1 ብር በታች ማለት በጣም በጣም ዝቅተኛ ነው። አሁን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። ምክንያታዊም አይደለም” ሲሉ አሁን የተደረገውን ማሻሻያው አስፈላጊነት አስገንዝበዋል። የፌደራል መንግስት የንብረት ታክስ (property tax) አዋጅ ገና እያዘጋጀ ቢሆንም፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ግን እስከዚያው ድረስ በቀድሞው አዋጅ ላይ ተመስርቶ ከቤት ግብር የሚያገኘውን ገቢ ለማሳደግ ጥናት ማድረጉን አስተባባሪው ገልጸዋል። በዚህ ጥናት በአዲስ አበባ የሚገኙ ቤቶች በቦታ ደረጃቸው፣ በተገነቡበት ቁስ እና በአገልግሎት አይነታቸው ተከፋፍለው፤ አዲስ ወርሃዊ የኪራይ ዋጋ እንደተተመነላቸው አቶ አስማማው አስታውቀዋል። የአዲስ አበባ የፋይናንስ ቢሮ ባለፈው ሚያዝያ ወር ባወጣው “የጥናት ውጤት ውሳኔ” መሰረት፤ ቤቶች ያረፉባቸውን ቦታዎች ታሳቢ በማድረግ በአራት የተለያዩ ደረጃዎች ይከፋፈላሉ። በጥናቱ ከፍ ያለ የኪራይ ዋጋ ተመን የተገመተላቸው “ደረጃ አንድ” ላይ የሚመደቡ ቦታዎች፤ ከዋና መስመር ያላቸው ርቀት እና የተሟላላቸው መሰረተ ልማት ታሳቢ ተደርጎላቸዋል። ዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10930/

#ሰሞነኛጉዳዮች በአዲስ አበባ ተግባራዊ ሊደረግ የታቀደው የቤት ግብር ማሻሻያ ምን ዝርዝር ይዟል? አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባወጣው አዲስ የቤት ግብር ማሻሻያ መሰረት የቤት ባለቤቶች የሚጠበቅባቸ
#ሰሞነኛጉዳዮች በአዲስ አበባ ተግባራዊ ሊደረግ የታቀደው የቤት ግብር ማሻሻያ ምን ዝርዝር ይዟል? አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባወጣው አዲስ የቤት ግብር ማሻሻያ መሰረት የቤት ባለቤቶች የሚጠበቅባቸውን ክፍያ እንዲፈጽሙ፤ በሶስት መቶ ሺህ ገደማ ቤቶች ላይ የግብር ግመታ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። ቤቶቹን የመለየት እና ግብር የመገመት ሂደት ከተጠናቀቀ በኋላ፤ ኮንዶሚኒየም ቤቶችን ጨምሮ ከዚህ ቀደም የቤት ግብር የማይከፈልባቸው ቤቶች ክፍያ እንዲፈጽሙ እንደሚያደርግ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ገልጿል። በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ የእነዚህ ቤቶች ባለቤቶች ሊከፍሉ የሚገባውን የቤት ግብር የመለየት ስራ እያከናወነ ያለው፤ የከተማዋ የመሬት ይዞታ ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ ነው። በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ የመሬት ይዞታዎችን መረጃ በዲጂታል እና በወረቀት የመያዝ ኃላፊነት በአዋጅ የተጣለበት ኤጀንሲው፤ የሰበሰባቸውን መረጃዎች ጥቅም ላይ የማዋል ስልጣንም ተሰጥቶታል። በዚህም መሰረት ኤጀንሲው እስካሁን ድረስ 147 ሺህ ይዞታዎች ላይ የማረጋገጥ ስራ አከናውኖ፤ መረጃቸውን በዲጂታል መንገድ መያዙን የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ግፋወሰን ዴሲሳ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ኤጀንሲው በራሱ ካደረጋቸው ማረጋገጫዎች ባሻገር “የባለቤትነት መብት የተመዘገበላቸው” የሪል ስቴት እና ኮንዶሚኒየም ቤቶችን መረጃ መያዙን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ይህም በተቋሙ የመረጃ ቋት ውስጥ ያሉ የቤት ይዞታዎችን ቁጥር 363 ሺህ እንደሚያደርሰው አመልክተዋል። ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10930/ @EthiopiaInsiderNews