2 485
Подписчики
Нет данных24 часа
-157 дней
-5230 дней
Архив постов
2 485
የተረጋገጠ የምርጫ ውጤት (ከምርጫ ቦርድ የዛሬ መግለጫ የተገኘ)
1. ደቡብ ክልል አንጋጫ 2 ምርጫ ክልል (ለፓርላማ )
- አራት ፖርቲዎች (ኢዜማ፣ ኢህአፓ፣ ኢሶዴፓ፣ ብልጽግና) ተወዳድረዋል
- ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል
2. ደቡብ ክልል አንጋጫ 1 ምርጫ ክልል (ለፓርላማ)
- 59 ምርጫ ጣቢያዎች አሉት
- ሶስት ፓርቲዎች (ኢዜማ፤ ኢሶዴፓ፣ ብልጽግና) እና አንድ የግል ዕጩ ተወዳድረዋል
- ብልጽግና አሸንፏል
3. ደቡብ ክልል ዳሰነች ምርጫ ክልል (ለፓርላማ)
- 44 ምርጫ ጣቢያዎች አሉት
- በምርጫ ክልሉ የተወዳደረው ብልጽግና ብቻ ነው
- ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል
4. ደቡብ ክልል እነሞርና ኤነር 2 ምርጫ ክልል (ለክልል ምክር ቤት)
- ሶስት የክልል ምክር ቤት መቀመጫ አለው
- ብልጽግና፣ ኢዜማ እና ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ተወዳድረዋል
- ሶስቱንም መቀመጫዎች ያሸነፈው ብልጽግና ፓርቲ ነው
5. ደቡብ ክልል ኢስራ ቶጫ ምርጫ ክልል (ለፓርላማ)
- ኢሶዴፓ፣ ኢዜማ፣ አዲስ ትውልድ እና ብልጽግና ተወዳድረዋል
- ብልጽግና አሸንፏል
6. ደቡብ ክልል ቀዲዳ ጋሜላ 1 ምርጫ ክልል (ለፓርላማ)
- ብልጽግና፣ ኢሶዴፓ፤ ኅብር ኢትዮጵያ እና ኢዜማ ተወዳድረዋል
- ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል
7. ደቡብ ክልል ቀዲዳ ጋሜላ 2 ምርጫ ክልል (ለፓርላማ)
- ኢህአፓ፣ብልጽግና፣ ኢሶዴፓ፤ ኅብር ኢትዮጵያ እና ኢዜማ ተወዳድረዋል
- ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል
8. ደቡብ ክልል ናኦ ልዩ ምርጫ ክልል (ለፓርላማ)
- ኢዜማ እና ብልጽግና ፓርቲዎች ተወዳድረዋል
- ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል
9. ደቡብ ክልል ሸይ ቤንች ምርጫ ክልል (ለፓርላማ)
- ኢዜማ እና ብልጽግና ተወዳድረዋል
- ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል
10. ደቡብ ክልል ጸማይ ልዩ ምርጫ ክልል (ለፓርላማ)
- ኢዜማና ብልጽግና ተወዳድረዋል
- ብልጽግና አሸንፏል
11. ደቡብ ክልል ወናጎ 2 ምርጫ ክልል (ለፓርላማ)
- የጌዲዮ ህዝብ ዴሞክራሲዊ ድርጅት፣ ኢዜማ እና ብልጽግና ተወዳድረዋል
- ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል
12. ደቡብ ክልል አንጋጫ 2 ምርጫ ክልል (ለክልል ምክር ቤት)
- ሶስት የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች አሉት
- ኢሶዴፓ፣ ኢዜማ፣ብልጽግና እና ኢህአፓ ተወዳድረዋል
- ሶስቱንም የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች ብልጽግና አሸንፏል
13. ደቡብ ክልል ቡሳ ምርጫ ክልል (ለክልል ምክር ቤት)
- አንድ የክልል ምክር ቤት መቀመጫ አለው
- ኢዜማ፣ ብልጽግና እና መኢአድ ተወዳድረዋል
- ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል
14. ደቡብ ክልል ኮንተብ 03 ምርጫ ክልል (ለክልል ምክር ቤት)
- ሶስት መቀመጫዎች አሉት
- እናት፣ኢዜማ፣ኢሶዴፓ እና ብልጽግና ተወዳድረዋል
- ሶስቱንም መቀመጫዎች ብልጽግና አሸንፏል
15. ደቡብ ክልል ሸይ ቤንች ምርጫ ክልል
- ኢዜማ እና ብልጽግና ተወዳድረዋል
- ብልጽግና ፓርቲ አሸንፏል
16. ደቡብ ክልል ዘይሴ ልዩ ምርጫ ክልል (ለክልል ምክር ቤት)
- አንድ መቀመጫ አለው
- አዲስ ትውልድ፤ ነጻነት እና እኩልነት፣ ኢዜማ ብልጽግና እና ተወዳድረዋል
- ኢዜማ አሸንፏል
[በ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" የተጠናቀረ]
2 485
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጸጥታ ችግር ምክንያት ወደ መቐለ የሚያደርገውን በረራ ላልተወሰነ ጊዜ አቋረጠ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በትግራይ እንደገና ባገረሸው ውጊያ ምክንያት ወደ መቐለ የሚያደረገውን የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት አቋረጠ። አየር መንገዱ በረራውን ያቋረጠው ከማክሰኞ ሰኔ 15 ጠዋት ጀምሮ እንደሆነ የድርጅቱ እና የጉዞ ወኪል ሰራተኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
በትላንትናው እና በዛሬው ዕለት ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ፤ ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ በረራ የነበራቸው መንገደኞች ከጉዟቸው መስተጓጎላቸውን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ከተጓዦቹ አረጋግጣለች። ለተጓዦቹ በረራ መሰረዙ የሚነገራቸው አየር ማረፊያ ከደረሱ በኋላ እንደሆነ በመቐለ አየር ማረፊያ የሚሰሩ አንድ ባለሙያ ገልጸዋል።
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት፤ የመጨረሻው በረራ የተደረገው 53 ተሳፋሪዎችን ጭኖ ከመቐለ አሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ ወደ አዲስ አበባ ማክሰኞ ከምሽቱ 12 ጉዞውን ባደረገው አውሮፕላን ነው። በማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨ ተንቀሳቃሽ ምስል በእሳት የተያያዘ አንድ አውሮፕላን ወደ መሬት ሲወርድ አሳይቷል።
ከዚያ በኋላ የነበሩት በረራዎች የተቋረጡት፤ ከትላንት በስቲያ ረቡዕ አንድ የጦር አውሮፕላን ግጀት በተባለ አካባቢ በአየር ላይ ተመትቷል መባሉን ተከትሎ መሆኑን እኚሁ የአየር መንገዱ ሰራተኛ ያብራራሉ። አውሮፕላኑ በትግራይ አማጽያን በአየር መቃወሚያ መመታቱ ቢገለጽም፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ቃል አቃባይ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ይህንን አስተባብለዋል።
ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/3711/
@ethiocheck
2 485
የነገ ምርጫ/የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን በተመለከተ ያሉት ሂደቶች ፦
- አንድ መራጭ የመራጮች ምዝገባ ካርዱና ለመራጮች ምዝገባ ያካሄደበትን መታወቂያ መያዝ አለበት።
- መራጩ ምርጫ ጣቢያ በደረሰበት ወቅት ሰልፍ ካለ መሰለፍ ይኖርበታል።
- በሰልፉ ላይ ምንም አይነት ቅደም ተከተል (በስም ፣ በፊደል ወይም በምርጫ ካርድ...) የለም።
- የሰልፍ ርቀት የሚያስጠብቁ፣ ሰልፉን ሁኔታ የሚያስተካከሉ አካላት የሚሉትን ማዳመጥ ይኖርበታል።
- መራጩ ተሰልፎ ተራው ሲደርስ ወደውስጥ ገብቶ መዝገቡ ላይ ስሙ መኖሩ ተረጋግጦ የድምፅ መስጫ ወረቀት ይሰጠዋል።
- የድምፅ መስጫ ወረቀት ሲሰጠው እጁ ላይ የቀለም ምልክት ይደረግበታል።
- በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የሚመርጠውን እጩ የሚመርጥበት የተሸፈነ ወይም ደግሞ የተከለለ (የድምፅ አሰጣጥ መከለያ) አለ እዛ ገብቶ ድምፁን ይሰጣል፤ መራጩ ተመልሶ ሲወጣ ባሉት ሳጥኖች ወስጥ ድምፁን ይከታል።
@ethiocheck
2 485
የነገ ምርጫ/የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን በተመለከተ ያሉት ሂደቶች ፦
- አንድ መራጭ የመራጮች ምዝገባ ካርዱና ለመራጮች ምዝገባ ያካሄደበትን መታወቂያ መያዝ አለበት።
- መራጩ ምርጫ ጣቢያ በደረሰበት ወቅት ሰልፍ ካለ መሰለፍ ይኖርበታል።
- በሰልፉ ላይ ምንም አይነት ቅደም ተከተል (በስም ፣ በፊደል ወይም በምርጫ ካርድ...) የለም።
- የሰልፍ ርቀት የሚያስጠብቁ፣ ሰልፉን ሁኔታ የሚያስተካከሉ አካላት የሚሉትን ማዳመጥ ይኖርበታል።
- መራጩ ተሰልፎ ተራው ሲደርስ ወደውስጥ ገብቶ መዝገቡ ላይ ስሙ መኖሩ ተረጋግጦ የድምፅ መስጫ ወረቀት ይሰጠዋል።
- የድምፅ መስጫ ወረቀት ሲሰጠው እጁ ላይ የቀለም ምልክት ይደረግበታል።
- በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የሚመርጠውን እጩ የሚመርጥበት የተሸፈነ ወይም ደግሞ የተከለለ (የድምፅ አሰጣጥ መከለያ) አለ እዛ ገብቶ ድምፁን ይሰጣል፤ መራጩ ተመልሶ ሲወጣ ባሉት ሳጥኖች ወስጥ ድምፁን ይከታል።
@ethiocheck
2 485
ሳዑዲ ዓረቢያ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን በሀገሪቱ መንግሥት የፀጥታ ኃይላት ከፍተኛ ወከባ፣ እስር እና ዝርፊያ እየደረሰባቸው ነው።
የሳዑዲ ዓረቢያ የጸጥታ ኃይላት የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸውንም የሌላቸውን ኢትዮጵያውያን ነዋሪዎች ቤቶች እየዘረፉ ለእስር በመዳረግ ላይ መሆናቸውን የችግሩ ሰለባ ኢትዮጵያውያን ለዶቼ ቨለ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
ቃላቸውን ከሰጡ ነዋሪዎች መካከል ለ8 ዓመት በጅዳ ነዋሪ የሆኑት አቶ ካልድ ሲራጅ የመኖሪያ ፈቃድ እንዳላቸው እየተናገሩ ከባለቤታቸው እና ሁለት ልጆቻቸው ጋር ለ3 ቀን ታስረው መፈታታቸውን ገልጸዋል።
አቶ ካሊድ፥"ቀጥታ መጡ፤ ልክ ከዝሁር በኋላ ከምሳ ሰአት በኋላ መጡ፤ ሰበሩ። ኢቃማ [ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ] አለን እያልናቸው እንኳን ሊሰሙን አልቻሉም፤...ተንጋግተው መጥተው ነው ቤቱን ሰብረው የገቡት" ብለዋል።
ከትናንትና ወዲያ አንስቶ እስከዛሬ ድረስ የጸጥታ ኃይላቱ "ሀበሻ" የሚሏቸውን ኢትዮጵያውያን ማሰርና ቤቶቻቸውን መስበር መቀጠላቸውን ነዋሪዎች አመልክተዋል።
አቶ አሕመድ ሁሴን የተባሉ ነዋሪ ደግሞ ወከባ፣እስርና ዝርፊያው መቀጠሉን ተናግረዋል።
«ተደበደበ፤ኅብረተሰቡ ንብረቱን ተወረሰ። ምነው ሂዱ ከተባልን ንብረታችንን እንኳን ይዘን ብንሄድ ? እንኳን የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው የመኖሪያ ፈቃድ ያለንም ብንሆን ወደ ሀገራችሁ ግቡ ብንባል በሰላም ብንገባ ምንአለበት እና ኅብረተሰቡ ተዘረፈ እያልን አሁንም አሁንም ኤምባሲ እየደወልን እየተናገርን ነው" ብለዋል።
አክለውም፥ "ሰሞኑን በሐበሻ ላይ የሚሠራው ሥራ ያለአግባብ ነው፤ ይመጣሉ ፤ ቤት ይሰብራሉ፤ሰብረው ሰዉን ይወስዳሉ ፤ ከዚያ ተከትሎ ወጣቱ ተከትሎ እየገባ ኅብረተሰቡ ተዘርፏል" ሲሉ ገልፀዋል።
ያንብቡ : telegra.ph/Saudi-Arabia-06-15
#ዶቼቨለ
@ethiocheck
2 485
ለጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን ማገገሚያ ማዕከል የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።
የጌርጌሴኖን የአዕምሮ መርጃ ማህበር ከተመሰረተ አስራ አምስት አመት የሞላው ሲሆን እስካሁን ከአንድ ሺ (1000) በላይ የአዕምሮ ህሙማንን አስተናግዷል። በመቶዎች የሚሆኑት ከህመማቸው ድነው ሌሎችን እየረዱ ይገኛሉ።
ማህበሩ እስካሁን ሲጠቀምበት የቆየው 1000 ካሜ. የማይሞላ የኪራይ ቤት ሲሆን አሁን ላይ ወደ 450 ህሙማን አገልግሎት እያገኙ ይገኛሉ። በእነዚህ አመታት ሁሉ የቦታ ጥያቄዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል።
ዛሬ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ለማህበሩ የ3000 ካሜ. መሬት ለማህበሩ አስረክቧል። በተጨማሪም ማህበሩ ለሚያስገነባው የማገገሚያ ማዕከል የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል።
6860 Ok ብለው በመላክ ተመዝግበው ማህበሩን መደገፍ ይችላሉ።
@ethiocheck
2 485
#ምርጫ2013
ዛሬ ማምሻውን የአሜሪካ መንግስት ባወጣው መግለጫ ከምርጫ በኋላ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ውይይት እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያን የወደፊት አካሔድ ለመወሰን እና የአገሪቱን ዴሞክራሲ እና ብሔራዊ አንድነት ለማጠናከር ጠ/ ሚ ዐቢይ አህመድ የሚመሩት መንግሥት እና መላ ኢትዮጵያውያን ከምርጫ በኋላ ለሚካሔድ አካታች የፖለቲካ ብሔራዊ ውይይት ቁርጠኛ እንዲሆኑ ነው የባይደን አስተሳደር ጥሪ ያቀረበው።
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የሚመሩት የአሜሪካ አስተዳደር ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ለሠራተኞቹ ጥረቶች እውቅና ቢሰጥም፤ 6ኛው አገራዊ ምርጫ የሚካሔድበት ከባቢ“አሳሳቢ ነው” ብሏል።
የአሜሪካ መንግስትን አቋም የሚያንጸባርቀው መግለጫ ዛሬ ማምሻውን አንቶኒ ብሊንከን በሚመሩት የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በኩል ነው የወጣው።
የባይደን አስተዳደር የኢትዮጵያ ምርጫ አሉበት ያላቸውን ፈተናዎች ፦
- የተቃዋሚ ፖለቲከኞች እስር፣
- የገለልተኛ ሚዲያ መዋከብ፣
- የአካባቢያዊ እና ክልላዊ መንግሥታት ወገንተኝነት እንዲሁም በመላ ኢትዮጵያ በብሔሮች እና በማህበረሰቦች መካከል የተቀሰቀሱ ግጭቶች ለነፃ እና ፍትሐዊ ምርጫ እንቅፋት ናቸው ብሏል።
"በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች በክልሎች እና ብሔሮች መካከል ያለው ልዩነት መካረር የአገሪቱን አንድነት እና የግዛት ሉዓላዊነት ያሰጋል” ያለው የአሜሪካ መንግስት #ከምርጫው_በኋላ መፍትሔ ሊፈለግ እንደሚገባ አሳስቧል።
“ከምርጫው በኋላ ያለው ጊዜ ኢትዮጵያውያን ተባብረው እነዚህን ልዩነቶች ለመጋፈጥ ኹነኛ ወቅት ነው” ብሏል የአሜሪካ መንግስት።
የአሜሪካ መግለጫ : www.state.gov/elections-in-ethiopia/
@ethiocheck
2 485
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ዞን 27 የጸጥታ ኃይሎች በታጣቂዎች ተገደሉ
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ዞን ጃርደጋ ጃርቴ ወረዳ 27 የጸጥታ ኃይሎች ትናንት ሐሙስ በታጣቂዎች መገደላቸውን የወረዳው አስተዳዳሪ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የጃርደጋ ጃርቴ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አብዮት በቀለ እንዳሉት ከተገደሉት የጸጥታ ኃይሎች በተጨማሪ 10 የፌደራል ፖሊስ አባላት ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በጸጥታ ኃይሎቹ ላይ ጥቃቱ የተነሰዘረው ከጠዋቱ 1 ሰዓት ገደማ እንደሆነ የሚገልጹት አቶ አብዮት፤ ድርጊቱ የተፈጸመው በአካባቢው ይንቀሳቀሳሉ የተባሉ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎችን በማሰስ ላይ ባሉበት ወቅት እንደነበር ይናገራሉ። የጸጥታ ኃይሎቹ በሁለት ዙር ወደ አካባቢው መንቀሳቀሳቸውን የሚያስረዱት ዋና አስተዳዳሪው፤ ጥቃቱ የተሰዘረው በመጀመሪያው ዙር በተጓዙ 47 የፌደራል ፖሊስ እና ሁለት የሚሊሺያ አባላት ላይ ነው ብለዋል።
ከስምንት አመታት በላይ ያገለገሉ እና ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ሁለት ሚሊሺያዎች በበኩላቸው ትናንት ሐሙስ ሰኔ 3፤ አካዩ ቀበሌ በተባለ ቦታ በተፈጸመው ጥቃት 24 የጸረ ሽብር ፖሊስ እና ሁለት የሚሊሺያ አባላት፤ በድምሩ 26 የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ተናግረዋል።
ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/3536/
@ethiocheck
2 485
በትግራይ ክልል 131 ጊዜ የእርዳታ ስርጭት መስተጓጎሉን አንድ የተመድ ኃላፊ ይፋ አደረጉ
በትግራይ ክልል 131 ጊዜ የእርዳታ ስርጭት መስተጓጎሉን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ እና አስቸኳይ እርዳታ አስተባባሪ ማርክ ሎውኮክ አስታወቁ። የእርዳታ ስርጭቱን በአብዛኛው ያስተጓጎሉት የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ወታደሮች መሆናቸውን ገልጸዋል። የተመድ የእርዳታ አስተባባሪ ይህን የተናገሩት አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በጥምረት ባዘጋጁት በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ሁኔታ ላይ ያተኮረ ውይይት ላይ ነው።
በቪዲዮ ኮንፍረንስ አማካኝነት ትላንት ሐሙስ ሰኔ 3 በተካሄደው በዚህ ውይይት፤ በክልሉ የከፋ ረሐብ እንዳይከሰት መከላከል፣ የሰላማዊ ሰዎችን ደህንነት መጠበቅ እና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ህግጋት መከበራቸውን ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነበር። ውይይቱ በትግራይ ተፈጽመዋል በተባሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እና የሰብዓዊ ቀውስ ሳቢያ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አስተዳደር ላይ የበረታው ጫና በግልጽ ያሳየ ሆኗል።
የእርዳታ ስርጭት ማስተጓጎልን በተመለከተ የተመድ የእርዳታ አስተባባሪ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ ወታደሮች ድርጊቱን 54 ጊዜ ሲፈጽሙ፤ የኤርትራ ወታደሮች ደግሞ 50 ጊዜ እርዳታ እንዳይሰራጭ አድርገዋል። የሁለቱ ሀገራት ወታደሮች በጥምረት አራት ጊዜ ተመሳሳይ ድርጊት መፈጸማቸውንም ገልጸዋል። የአማራ ሚሊሺያ አባላት ለ21 ጊዜ ያህል የእርዳታ ስርጭት እንቅፋት መሆናቸውን ያስረዱት አስተባባሪው፤ በትግራይ ተቃዋሚ ኃይሎች በኩልም አንድ ጊዜ ይህው መፈጸሙን አስረድተዋል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህንን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/3525/
2 485
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ሰንደቅ ዓላማ ተቃጥሏል ?
ዛሬ ከነበረው የውጭ ጣልቃ ገብነትን ከሚያወግዘው ሰልፍ ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጩት "የአሜሪካ ሰንደቅ አላማ" ሲቃጠል የሚይሳዩ ምስሎች ትክክለኛ ያልሆኑ ናቸው።
ከምስሎቹ ጋር አብረው የተሰራጩት መልዕክቶች ሰንደቅ አላማ የማቃጠል ድርጊቱ በኢትዮጵያውያን ስለመፈጸሙ የሚገልፁ ሲሆኑ ነገር ግን ድርጊቱ ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈፀመ አለመሆኑን "ኢትዮጵያ ቼክ" ድረገፅ የሪቨርስ ኤሜጅ ሰርች መገልገያዎች በመጠቀም ባደረገው ማጣራት አረጋግጧል።
የአሜሪካ ሰንደቅ አላማ ሲቃጠል የሚያሳየውን ፎቶ ፌብርዋሪ 15/2019 በአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ (AFP) የተሰራጨ ሲሆን ድርጊቱ የተፈጸመው ከካርቢያን ደሴቶች አንዷ በሆነችው ሀይቲ ውስጥ ነው።
ሰንደቅ አላማውን ያቃጠለው ግለሰብ ብሮንሰን የሚባል ሲሆን በአሜሪካ መንግስት ይደገፋል የሚባለውን የሃይቲ ፕሬዝደንት ጆቬናል ሞይስ ከስልጣን ይለቅ ዘንድ ለመጠየቅ ሰልፍ ከወጡ ወጣቶች አንዱ ነበር።
ፎቶውን ለAFP ያነሳው ግለሰብ ሄክተር ሬታማል የሚባል የፎቶ ባለሙያ እንደነበር "ኢትዮጵያ ቼክ" ማምሻውን በድረገፁ ላይ ባወጣው ፅሁፍ ገልጿል።
@ethiocheck
2 485
አሜሪካ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ላይ ተጨማሪ ማዕቀቦች ልትጥል እንደምትችል አስጠነቀቀች
አሜሪካ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ላይ ተጨማሪ ማዕቀቦች ልትጥል እንደምትችል የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር አስጠነቀቁ። የሚኒስትሩ ማስጠንቀቂያ ትናንት ሐሙስ በተደመጠበት የአሜሪካ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ስብሰባ፤ ጂም ሪሽ የተባሉ ሴናተር ሀገራቸው በሰብዓዊ መብት ጥሰት የምትከሳቸውን ማዕቀብ በመጣል ለመቅጣት የምትጠቀምብትን “የማግኒትስኪ ድንጋጌ” እንድትጠቀም ጥቆማ ሰጥተዋል።
በአሜሪካ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ባደረገው ውይይት ማብራሪያ የሰጡት የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ሚኒስትር ሮበርት ጎዴክ “ግጭቱን የሚያባብሱ መንገዳቸውን ካልቀየሩ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ተጨማሪ እርምጃ ይጠብቁ” ሲሉ ተደምጠዋል። ለሁለት ሰዓታት ገደማ በዘለቀው ውይይት የኢትዮጵያ ሽግግር፣ ምርጫ እና የህዳሴ ግድብ ድርድርን የተመለከቱ ርዕሰ ጉዳዮች የተነሱበት ይሁን እንጂ ቅድሚያውን የያዘው የትግራይ ውጊያ እና አሜሪካ ይህንኑ ለማስቆም የምታደርገው ጥረት ነበር።
ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/3397/
2 485
እነ ጃዋር መሐመድ ከዛሬ ጀምሮ ፍርድ ቤት መቅረብ አንፈልግም አሉ
በእነ ጃዋር መሐመድ መዝገብ የተከሰሱ 24 ተከሳሾች ከዛሬ ጀምሮ ጉዳያቸውን ለመከታተል ወደ ፍርድ ቤት እንደማይቀርቡ አስታወቁ። ተከሳሾቹ በትግራይ እየተካሄደ ነው ያሉትን “የጅምላ ግድያ እና ኢ-ፍትሃዊ አገዛዝ” ለመቃወም ለሁለት ቀናት የረሃብ አድማ እንደማዲያደርጉም ገልጸዋል።
ተከሳሾቹ ፍርድ ቤት ያለመቅረብ ውሳኔያቸውን ያስታወቁት፤ መደበኛ የክስ ሂደታቸውን እየተመለከተ ላለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ የጸረ-ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 18 በጽሁፍ ባቀረቡት አቤቱታ ነው። በችሎቱ ላይ ንግግር ያደረጉት አቶ ጃዋር መሐመድ፤ የኮሎኔል ገመቹ አያና እና የሌሎች ተከሳሶችን ጉዳይ በመጥቀስ የፍርድ ቤት ውሳኔ በተገቢው መንገድ ተፈጻሚ እየሆነ አይደለም ብለዋል።
“እኛ እዚህ የመጣነው ከተፈረደብን ለመቀጣት፤ ነጻ ከተባልን ለመውጣት ነው” ያሉት አቶ ጃዋር፤ “ከዛሬ ጀምሮ በገዛ ፍቃዳችን ፍርድ ቤት አንቀርብም” ሲሉ ለፍርድ ቤቱ አስታውቀዋል። ይህንን ውሳኔ ደግፈው የተናገሩት አቶ በቀለ ገርባ በበኩላቸው “በግድ ተጎትተን እና ተደብድበን ካልሆነ በቀር ወደዚህ ፍርድ ቤት አንመጣም” ሲሉ ተደምጠዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ዝርዝሩን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/3350/
2 485
እነ እስክንድር ነጋ በእስር ቤት ባሉበት የምርጫ ቅስቀሳ እንዲያደርጉ ፍርድ ቤቱን ጠየቁ
.
የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ለመጪው ሀገራዊ ምርጫ ካሉበት እስር ቤት ሆነው የተለያዩ የምርጫ ቅስቀሳ ሂደቶችን እንዲያደርጉ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትን ጠየቁ። አመራሮቹ ጥያቄውን ያቀረቡት በትላንትናው ዕለት የሰበር ሰሚ ችሎት በመጪው ምርጫ በዕጩነት ተመዝግበው መወዳደር እንደሚችሉ ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ ነው።
ምንጭ፦ ኢትዮጵያን ኢንሳይደር
2 485
እነ አቶ እስክንድር ነጋ ለመጪው ምርጫ በእጩነት ተመዝግበው መወዳደር እንደሚችሉ የሰበር ሰሚ ችሎት ወሰነ
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሁለተኛ ሰበር ሰሚ ችሎት የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ አመራሮች አቶ እስክንድር ነጋ፣ ስንታየሁ ቸኮል፣ ቀለብ ስዩም እና አስካለ ደመሌ ለፓርቲው በእጩነት ተመዝግበው መወዳደር እንደሚችሉ ውሳኔ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው ዛሬ ሰኞ ግንቦት 16 በነበረው የችሎት ውሎው ነው።
ችሎቱ ውሳኔውን የሰጠው የባልደራስ ፓርቲ አመራሮችን በተመለከተ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተላለፈውን እና በስተኋላ ላይም በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጸደቀውን ውሳኔ ውድቅ በማድረግ ነው። የባልደራስ ፓርቲ እነ አቶ እስክንድር ነጋ በመጪው ምርጫ በእጩነት እንዲመዘገቡለት ምርጫ ቦርድን ቢጠይቅም፤ አመራሮቹ በህግ ከለላ ስር ስለሚገኙ ለምርጫ እጩነት መመዝገብ አይችሉም በማለት ቦርዱ ጥያቄውን ሳይቀበለው መቅረቱ ይታወሳል።
አምስት የሰበር ሰሚ ዳኞች የተሰየሙበት የዛሬው ችሎት፤ በምርጫ አዋጁም ሆነ በህገ መንግስቱ ላይ የዜጎች የመምረጥ ወይም የመመረጥ መብት የሚነፈገው በህግ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ ካገኘ በኋላ ነው ብሏል። ስለሆነም በተያዘው ጉዳይ የፓርቲው አመራሮች በህግ የተላለፈባቸው ውሳኔ ባለመኖሩ በእጩነት መመዝገብ ይችላሉ ሲል ፍርድ ቤቱ ወስኗል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/3307/
2 485
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ነገ ይጀምራል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርሰቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ነገ ግንቦት 17 ቀን 2013 ዓ/ም ከቀኑ በ10:00 ሰዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በሚያካሂድ የጸሎት ሥነሥርዓት ይጀምራል።
ነገ በሚያካሂደው ጉባኤ ቋሚ ሲኖዶሱ በምልአተ ጉባኤው መታየት ይገባቸዋል በማለት ያዘጋጃቸው አጀንዳዎች ምልአተ ጉባኤው በሚሰይማቸው ብጹአን አባቶች እንዲታዩ ካደረገ በኋላ መካተት ያለባቸው አጀንዳዎች ለይቶ ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በማቅረብ የሚያጸድቅ ይሆናል።
በጉባኤው የጸደቁት አጀንዳዎች መሰረት በማድረግና በቅደም ተከተል በመወያት ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ ይጠበቃል።
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የጉባኤውን መከፈት በማስመልከት የመክፈቻ መልዕክት ያስተላልፋሉ።
መረጃው የቅዱስ ሲኖዶስ ጽህፈት ቤት/የኢኦተቤ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
@ethiocheck
2 485
#BREAKING
የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ /ባልደራስ/ ከፍተኛ አመራሮች የሆኑት ፕሬዚዳንት አቶ እስክንድር ነጋ ጨምሮ ፣ አስቴር ስዩም ፣ ስንታየሁ ቸኮል እና አስካለ ደምሌ በመጪው ምርጫ በዕጩነት እንዲመዘገቡ ፤የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት 2ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ መስጠቱን ፤የባልደራስ የሕግና የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ሔኖክ አክሊሉ ገልጸዋል ።
ምንጭ፦ ባልደራስ ፓርቲ
@ethiocheck
2 485
ምርጫው ሰኔ 14 እንደሚከናወን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
የመጪው ምርጫ የድምጽ መስጫ ቀን ሰኞ ሰኔ 14፤ 2013 እንደሚሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ድምጽ የሚሰጥባቸው ቦታዎች የመራጮች ምዝገባ ሂደቱ ያለምንም ችግር በተከናወነባቸው ቦታዎች ብቻ እንደሚሆን የቦርዱ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ሶልያና ሽመልስ ዛሬ ሐሙስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።
በመራጮች ምዘገባ ወቅት አቤቱታ በቀረበባቸው በሶማሌ ክልል በሚገኙ ሰባት የምርጫ ክልሎች የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ በሰኔ 14 እንደማይከናወን የቦርዱ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ገልጸዋል። ቦርዱ በእነዚህ ሰባት የምርጫ ክልሎች ማጣራት እያደረገ መሆኑን የጠቆሙት ሶልያና፤ ማጣራቱን የሚያከናውኑ 10 ቡድኖች ወደ ስፍራዎቹ መላኩን አስረድተዋል።
የመራጮች ምዝገባ እስካሁንም ባልተጀመረባቸው እና በርካታ ተፈናቃዮች ባሉባቸው ቦታዎች በሰኔ 14 ድምጽ እንደማይሰጥም የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊዋ አመልክተዋል። በሁለቱም ምክንያቶች በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ስር ባለው የመተከል ዞን በዕለቱ የድምጽ መስጫ ሂደቱ እንደማይደረግም ጠቁመዋል። በእነዚህ ቦታዎች የሚደረገው የድምጽ አሰጣጥ “አሁን ካለው ሰኔ 14 ውጭ የሚታይ ነው” ሲሉ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊዋ አብራርተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/3266/
2 485
ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባ ፍርድ ቤት ምርጫውን አሳልፎ ከሁለት አመት በኋላ የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጥ ጠየቁ
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ጃዋር መሐመድ መዝገብ የሚያካሂደውን ምርመራ አቋርጦ ምርጫው ካለፈ በኋላ ለ2015 እና 2016 ቀጠሮ እንዲሰጣቸው አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባ ጠየቁ። ሁለቱ ተከሳሾች ጥያቄውን ያቀረቡት ዛሬ ሐሙስ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በነበራቸው መደበኛ የክስ ሂደት የችሎት ውሎ ላይ ነው።
በመጀመሪያ ተቃውሟቸውን ያሰሙት አቶ በቀለ ገርባ ቀጠሮ ምንም ፋይዳ ስለሌለው ፍርድ ቤቱ ግንቦት 18 ቀጠሮ ከሚሰጥ ይልቅ ከሁለት ዓመት በኋላ ለ2015 ወይም 2016 ቢሰጥ ይሻላል ብለዋል። “ሰው በአደባባይ በሚረሸንበት አገር ፍርድ ቤት መቅረብ እድለኝነት ነው” ያሉት አቶ በቀለ ገርባ፤ ይህም ሆኖ ግን ምንም ፍትህ ለማይገኝለት ነገር ፍርድ ቤት መመላለስ እንደሌለባቸው ጠቅሰዋል።
ይሄንኑ ተቃውሞ ደግፈው የተናገሩት አቶ ጃዋር መሐመድ “እናንተ ነፃ ናችሁ ብትሉንም እነሱ ግን አይለቁንም” በማለት ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የሚፈልገው የእኛን መታሰር ስለሆነ የፍርድ ቤቱንም የእኛንም ጊዜ ከምንገድል ከሁለት አመት በኋላ ቀጠሮ ቢሰጥልን ይሻላል ሲሉ ተደምጠዋል።
ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/3246/
2 485
ከህወሓት ጋር ተኩስ በማቆም ተደራደሩ በሚል የሚቀርቡ ግፊቶችን ፈጽሞ እንደማይቀበልም መንግሥት አስታውቋል!
ከህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ተኩስ በማቆም ተደራደሩ በሚል የሚቀርቡ ምንም ዓይነት ግፊቶችን ፈጽሞ እንደማይቀበል መንግስት አስታወቀ፡፡ኢ-ፍትሐዊ እና ያልተገቡ ክሶች እና ዘመቻዎች በኢትዮጵያ ላይ እየተደረጉ ነው ሲል መንግስት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል በተለያዩ አምስት ዝርዝር ጉዳዮች ላይ መግለጫ አውጥቷል፡፡
መንግስት ምንም እንኳን በአጋሮቹ ለሚገለጹ ስጋቶች እና ለሚነሱ ጥያቄዎች ተባባሪ ሆኖ በቅንጅት ለመፍታት ያለውን ዝግጁነት ቢገልጽም በእንዲህ ዓይነት ያልተገቡ ዘመቻዎች ኢትዮጵያን ከልክ ባለፈ ጫና ውስጥ ለማስገባት የሚደረገው ጥረት የሚያስቆጭ ነው ሲል የሚያትተው መግለጫው ዘመቻው ችግሮችን ከመፍታት ይልቅ ይበልጥ የሚያባብስ መሆኑን ይገልጻል፡፡
በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፎችን ለማድረግ ከመቻልም በዘለለ የአቅርቦት በሮች ሁሉ ተመቻችተዋል ያለም ሲሆን ተፈጽመዋል የተባሉ ሰብዓዊ ጥሰቶች በፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ እና ፌዴራል ፖሊስ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጭምር መመርመራቸውን፤ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ መደረሱን ያስቀምጣል፡፡
በተለይም ከፊቱ ምርጫ እንዳለበት ሃገር ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችሉ ውይይቶችን ከተለያዩ አካላት ጋር ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝም ነው መንግስት በመግለጫው የጠቆመው፡፡ውይይቱን በትግራይ ክልል ጭምር ከህጋዊ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ከሲቪል ማህበረሰብ አባላት፣ ከግሉ ዘርፍ ፣ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከምሁራን፣ ከታዋቂ ግለሰቦች እና ከሌሎች አካላትም ጋር ለማድረግ ያለውን ዝግጁነት ማሳየቱንም ነው ያስታወቀው፡፡
Via Al ain
@ethiocheck
2 485
#Attention📣
የዓለም ጤና ድርጅት በህንድ የተከሰተው የኮቪድ-19 ቫይረስ አሳሳሳቢ ዝርያ እንደሆነ እና ዓለም አቀፍ ስጋት እየሆነ እንደመጣ ቫይረሱ እስካሁን ድረስ በ44 ሃገራት እንደተሰራጨ ገልጿል።
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት / EPHI / ፤ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ለኮቪድ-19 አጋላጭ ሁኔታዎችን በማስቀረት የመከላከያ መንገዶቸን በጥንቃቄ እንዲተገብር አሳስቧል።
በዚሁ አጋጣሚ በህንድ የሰው ልጆች እንደቅጠል እየረገፉ ነው። ሆስፒታሎች ሞልተዋል፣ የኦክሲጅን እጥረትም አጋጥሟል።
ባለፉት አምስት ቀናት ብቻ ህንድ ውስጥ 19,952 ሰዎች ሲሞቱ 1,750,209 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።
@ethiocheck
