cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

Allbahirdar

News, Business Directory & Entertainment Portal. Email: [email protected]

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
201
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሠላም አደረሳችሁ!! መልካም የገና በዓል።
Показать все...
የግእዝ ቋንቋ እንደሁተኛ ቋንቋ በትምህርት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው::
Показать все...
መጋቢ ሐዲስ ሮዳስ ዛሬ ባህር ዳር ላይ ቁጭ ብሎ የከተባት ናት 🌙 አመሻሹ ላይ በጣና ዳርቻ ሆነን ከላይ ደማቋ ጨረቃን፤ ከጨረቃ በላይ ቀይዋ ፕላኔት ማርስን 💥 እየተመለከትን ነው፤ የውቧ ጨረቃ ብርሃንም በጣና ባሕር ላይ አንጸባርቆ ለባሕሩ ልዩ ውበት ተሰጥቶታል። ደስ የሚል ነፋሻማ አየርን በባሕሩ ዳርቻ ሳብ እያረግን ለአንክሮ (ለአድናቆት) የተፈጠሩትን እነዚህን ሰማያዊ አካላትን በተመስጦ እየተመለከትን በአድናቆት ምሽቱን ተያይዘነዋል። [አሶንያ፣ ዕብላ፣ ብናሴ፣ ኤራዕ፣ ወርኅ፣ ሶልያና፣ ቀመር] ተብላ በብራና ላይ ተጽፋ ያነበብኳት ስመ ብዙዋ ጨረቃ እንዲህ ተውባ በዚህ ምሽት ባያት ዐጭር ግጥም ጻፍኩላት። 🌙🌙አሶንያ🌙🌙 አንቺ አሶንያ የጠፈር እንክብል ድንቋ የአምላክ ሥራ ድመቂ በኃይል። ብናሴና ኤራዕ፤ ቀመርም ስምሽ ጨረቃም ወርኅም ነሽ በአንክሮ ሳይሽ። በጣና ባሕር ላይ ውብ ድምቀትሽ ጎልቶ ሰንፔር መስለሽ ታየሽ ብርሃንሽ መልቶ። የከተማን ሁከት ጫጫታን አስረሽን በጥበብ ክንፎችሽ ወደ ላይ አክንፊን ይዘሽን ብረሪ ወደላይም አውጭን የቃላት ኳኳታ ጋጋታ አታሰሚን። ለአንክሮ ነውና አምላክ የፈጠረሽ አድንቀን ላይሽን ውስጥሽን እንፈትሽ። ለተመኘ ንፍገት ከቶ የለምና ተነጥቀን እንይሽ በሐሳብ ደመና። [መስከረም 23/ ከምሽቱ 3 ሰዓት በጣና ባሕር ዳርቻ] Photo Credited: Dr Getenet 💥 በአስተያየት መስጫው በተፈጥሮ ላይ መራቀቅና በተፈጥሮ ላይ ያላችሁን የራሳችሁን ፍልስፍና መጻፍ ትችላላችሁ።
Показать все...
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ። ባህር ዳር የመስቀል በዓል አከባበር ይህንን ይመስል ነበር። ፎቶ Abu Abu
Показать все...
የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ አገራዊ ምርጫ ማካሄድ ይቻላል ሲሉ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት አመለከቱ።‼️ ምክር ቤቱም በቀረበው ሪፖርት ላይ እየተወያየ ነው፡፡ የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት አጭር ሪፖርት ኮቪድ-19ኝ መከላከልን ከግምት ውስጥ ያስገባ የምርጫ ስነምግባር፣ ደንብና ማስፈፀሚያ መመሪያዎችን በማዘጋጀት ሃገራዊ ምርጫ ማካሄድ ይቻላል ብለዋል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የወረርሽኝ ስርጭት ከተከሰተ በተለየ ሁኔታ መታየት ሊያስፈልገው እንደሚችል ታሳቢ በማድረግ መዘጋጀት እንደሚያስፈልግም ዶ/ር ሊያ ባቀረቡት ሪፖርት አመልክተዋል፡፡
Показать все...
ፌስቡክ በመላው ዓለም ሰላም አፍራሽ የጥላቻ ንግግሮችን በጊዜ ባለማስወገዱ ከፍተኛ ጥፋት እያደረሰ ይገኛል፡፡ ይህንን በመቃወም ከፍተኛ ተቃውሞ እየተካሄደ ነው፡፡ ይህንን ተቃውሞ እውቅ የዓለማችን ሰዎች እየተቀላቀሉት ነው፡፡ በአሜሪካ ‹‹የካርዳሺያን እውናዊ ትእይንት (ሪያሊቲ ሾው) " ላይ ገናና የሆነችው ኪም በፌስቡክ ሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ላይ የተጀመረውን ተቃውሞ መቀላቀሏን ይፋ አድርጋለች፡፡ የሙዚቃ አቀንቃኙ የካኒዮ ዌስት ባለቤት ኪም ይህን ተቃውሞ ስትቀላቀል የመጀመርያዋ ሥመ ጥር አይደለችም፡፡ በርካታ የሆሊውድ ዝነኞችም ተቃውሞው ላይ በይፋ ገብተውበታል፡፡ ፕሮፓጋንዳ፣ የሐሰተኛ መረጃ ሥርጭትና የጥላቻ ንግግር ይቁም የሚለው ተቃውሞ እየተደረገ ያለው በተለያየ መንገድ ሲሆን አንዱ ዘዴ የፌስቡክና የኢኒስታግራም አድራሻን ለአጭር ጊዜ በመዝጋት ነው፡፡ የተቃውሞው መፈክር #በጥላቻ ንግግር ማትረፍ ይቁም! የሚል ነው፡፡ በዚህ ተቃውሞ እንቅስቃሴ የሚሳተፉ የዓለም ዜጎች ዛሬ ረቡዕ ለ24 ሰዓታት የፌስቡክ ገጻቸውን ይዘጋሉ፡፡ ከነዚህም አንዷ ኪም ካርዳሺያን ዌስት ናት፡፡ ኪም እንደተናገረችው ‹‹ፌስቡክ በጥላቻ ንግግር ሲነግድ ቁጭ ብዬ ልመለከት አልችልም›› ብላለች፡፡ ከኪም ሌላ ዝነኛው ተዋናይ ሊዮናርዶ ዲካፕሪዮ፣ ኦርላንዶ ብሉም፣ ቦራት በሚል የተሳልቆ ሥራው ዋና ገጸባሕሪ ስም በይበልጥ የሚታወቀው ሳሻ ባረን ኮን እና ጄኔፈር ሎውረን ይገኙበታል፡፡ አቀንቃኟ ኬቲ ፔሪም ይህንኑ ተቃውሞ መቀላቀሏን አስታውቃለች፡፡ ፔሪ በኢኒስታግራም አልበሟ ሰሌዳ ላይ እንደጻፈችው ‹‹ፌስቡክ በጥላቻ ሲነዛ እንዳላየ ሆኜ ማለፍ አልችልም›› ብላለች፡፡ Via:- #BBCAmahric @allaboutbahirdar    @allbahirdar 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Показать все...
ትውልደ ኢትዮጵያዊት አሜሪካዊቷ ደራሲ መዓዛ መንግሥቴ ለቡከር ሽልማት የመጨረሻ ዙር ከታጩ ስድስት ጸሐፍት አንዷ ሆና ተመረጠች! መዓዛ ለሽልማቱ የታጨችው “ዘ ሻዶው ኪንግ” የሚል ርዕስ በተሰጠው እና መቀመጫውን በስኮትላንድ ኤደንብራ ባደረገው ካነንጌት ቡክስ አሳታሚ ለንባብ በበቃው መጽሀፍ ነው። በስነ ጹሁፍ ሰዎች ዘንድ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው “ዘ ቡከር ፕራይዝ”፤ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ተፅፈው በዩናይትድ ኪንግደም እና አየርላንድ ለሕትመት የበቁ የልቦለድ ስራዎችን የሚሸልም ነው። መዓዛ  ለሽልማቱ ከታጩ ስድስት የመጨረሻ እጩዎች አንዷ ሆና መመረጧን “የማይታመን ነው” ብላለች። Via #EthiopiaInsider @allaboutbahirdar    @allbahirdar 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ውድ ተከታታዮቻችን የኦል ባህር ዳር ትኩስና ወቅታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራምና የፌስቡክ ገፃችንን ይቀላቀሉ!!!          || https://facebook.com/allbahirdar ||
Показать все...
ወደ ሀገር ሊገባ የነበረ 200,000 ብር ተያዘ! በጅጅጋ ጉምሩክ ዛሬ በ05/01/13 ዓ/ም ወደ ሀገር ሊገባ የነበረ 200,000 ብር ተይዟል። በትላንትናው ዕለት በመንግሥት ይፋ በተደረገው የብር ኖት ቅያሪ ምክንያት ከሱማሌላንድ በቶጎ ውጫሌ በኩል  በተለያየ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ውጭ የሸሸ የኢትዮጵያ ብር በአንድ ግለሰብ አማካኝነት ወደ ሀገር ሊገባ የነበረ 200,000 ብር በጉምሩክ ፈታሽ  አማካኝነት ከነተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር መዋሉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል። @allaboutbahirdar    @allbahirdar 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ውድ ተከታታዮቻችን የኦል ባህር ዳር ትኩስና ወቅታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራምና የፌስቡክ ገፃችንን ይቀላቀሉ!!!          || https://facebook.com/allbahirdar ||
Показать все...
21 አምባሳደሮች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል ? በማህበራዊ ሚዲያ ላይ "በቢሾፍቱ ከተማ ስልጠና ላይ ከነበሩ አምባሳደሮች መካከል ሃያ አንዱ (21) በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ታውቋል ፣ እንዲሁም የUN አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ወደ ኒው ዮርክ አይመለሱም" የሚል መረጃ በስፋት እየተሰራጨ ተመልክተናል። በዚህ ጉዳዩ ላይ ስማቸውን የማንገልፅላችሁ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራሮች/እንዲሁም በስልጠናው ላይ ተሳታፊ ከነበሩት መካከል አንድ ሰው ተከታዩን ብለውናል ፦ "አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ወደ New York ትላንትና እንደሚበሩ ነግረውኛል። አዲስ ነገር አልሰማሁም። 21 አምባሳደሮች በCOVID-19 አልተያዙም። ነገር ግን ከስብሰባችን በኋላ አንዴ ከመውጣታችን በፊት ከዛም አርብ እለት ምርመራ አድርገናል ነገር ግን የጤና መረጃ የግል confidential ስለሆነ በትክክል ቁጥሩን መናገር አልችልም። ከአምባሳደሮቻችን መካከል ወደ አስራ አምስት (15) የሚሆኑ ወደየሚሰሩበት ሀገር ተመልሰዋል። አሁን ደግሞ እዚህ MINT ያዘጋጀው program ላይ አብዛኞቻችን አለን። ቁጥሩን ባላውቀውም 21 ግን እንዳልሆኑ እርግጠኛ ነኝ ከላይ በጠቀስኩት ምክንያት።" @allaboutbahirdar    @allbahirdar 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ውድ ተከታታዮቻችን የኦል ባህር ዳር ትኩስና ወቅታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራምና የፌስቡክ ገፃችንን ይቀላቀሉ!!!          || https://facebook.com/allbahirdar ||
Показать все...
ኢትዮጵያ ነባሮቹን ባለ10፣ 50 እና 100 የብር ኖቶች የሚተኩ አዲስ የገንዘብ ዓይነቶች እና አዲስ ባለ200 ብር ገንዘብ ይፋ አደረገች፡፡ ኢትዮጵያ ነባሮቹን ባለ10፣ 50 እና 100 የብር ኖቶች ዓይነቶችን ሙሉ ለሙሉ በመተካት ለግብይት የሚሆን አዲስ የገንዘብ ኖት መጠቀም እንደምትጀምር ይፋ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶክተር) አስታወቁ። ነባሮቹን የብር ኖቶች ከሚተከት በተጨማሪም የ200 ብር ኖት ዛሬ ይፋ እንደሆነ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለፁት። እነዚህ አዲስ የገንዘብ ዓይነቶች ለሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎች የሚደረግን ድጋፍ፣ ሙስናን እና የኮንትሮባንድ ሥራዎችን ለመቀልበስ እንደሚረዱ ተጠቁሟል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲሶቹ የገንዘብ ዓይነቶች ላይ የተካተቱ መለያዎች አመሳስሎ ገንዘብ ለማተም የሚደረጉ ሕገ ወጥ ጥረቶችንም ለማስቀረት እንደሚግዙ አመልክተዋል። Via:- (አብመድ) @allaboutbahirdar    @allbahirdar 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ውድ ተከታታዮቻችን የኦል ባህር ዳር ትኩስና ወቅታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራምና የፌስቡክ ገፃችንን ይቀላቀሉ!!!          || https://facebook.com/allbahirdar ||
Показать все...