cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ኢትዮጵያን እንቃኛት

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
216
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

Фото недоступноПоказать в Telegram
የዛሬ153 ዓመት ሚያዚያ 6/1860 ዓ/ም ታላቁ ኢትዮጵያዊው ንጉሰ ነገስት ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ ለሐገሩ ክብር በጠላት እጅ አልወድቅም ሐገሬን አሳልፌ አልሰጥም ብሎ በገዛ ጥይቱ ለገዛ ሐገሩ ተሰዋ። መቅደላ አፋፍ ላይ ጩኸት በረከተ፣ የሴቱን አናውቅም ወንድ አንድ ሰው ሞተ። @abiseniyaethiopia
Показать все...
ኦባንግ ሜቶ ትናንት ማታ በምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ገንበል ወረዳ በቦን ቀበሌ እጅግ ቀዝቃዛ በሆነ ሁኔታ ለተጨፈጨፈው ለዚያ የአማራ ብሄር ቤተሰቦች እና ወዳጆች በዚህ ወቅት ብዙዎቻችን የሚሰማንን ድንጋጤ ፣ ሀዘን እና ርህራሄ የሚገልፅ ቃል የለም ፡፡ ትናንት ማታ በምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ገንበል ወረዳ በቦን ቀበሌ በአሰቃቂ እና ዘግናኝ ጥቃት የተገደሉ የኦሮሚያ ክልል ኮሚኒኬሽን ቢሮ “ቁጥራቸው ያልታወቁ” ዜጎች መገኘቱን አስታውቋል ፡፡ ከመቶ ሰማንያ በላይ የተገደሉ ሲሆን ብዙዎቹ ሕፃናት እንደሆኑ የተናገሩ አሉ ፡፡ ከልብ የመነጨ ሀዘኔን መስጠት እና እነዚህን አረመኔያዊ ጭፍጨፋዎች በንጹሃን ዜጎች ላይ ሙሉ በሙሉ ማውገዝ እፈልጋለሁ ፡፡ አንድ ጎሳ ፣ ሃይማኖት ፣ የፖለቲካ አመለካከት ፣ ዕድሜ ፣ ጾታ ወይም ሌላ ማንኛውም ባህሪዎች ቢኖሩም ባይኖሩም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ቤተሰብ በአንድነት ቆሜያለሁ ፤ እኛ በመጀመሪያ እና ከሁሉም በላይ የሰው ልጆች ነን ፣ በተፈጥሮአዊ ዋጋ እና ክብር የተፈጠርን ፡፡ አንዳንዶች ወደዚህ ወደ ሥነ ምግባራዊ ብልሹነት ስለገቡ ብቻ የዚህ አስከፊ የወንጀል ሥቃይ የተጋራንን ሰብአዊነታችንን ፈጽሞ ሊረሳን አይገባም ፡፡ በኦሮምያ ክልል ውስጥ በብሄራቸው ላይ ብቻ የተተኮሩ የብሄር አማራ ዜጎች ላይ የሚደርሰውን የዘር ግድያ እና ስቃይ ለማስቆም የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግስት እና የኦሮሚያ ክልል መንግስት ጠንካራ እርምጃዎችን እንዲወስዱ ጥሪዬን አቀርባለሁ ፡፡ የኦሮሚያ ክልል መንግስት አማራዎችን ሰላማዊ ዜጎች ለመጠበቅ ፈቃደኛ ያልሆነ ወይም ያለ ይመስላል ፡፡ በዜጎቻችን ላይ የሚደርሰውን ግድያ ለመከላከል እና ለማስቆም በተደጋጋሚ አልተሳካም; ከኢትዮጵያውያን ተደጋጋሚ ጥሪ ቢቀርብም ፡፡ በዓለም ዙሪያ ያሉ ኢትዮጵያውያን እያዘኑና እየተበሳጩ ነው ፡፡ በክፋት እና ጥልቅ ኢ-ፍትሃዊነት ላይ ያልታጠቁ ቁጣዎች ፣ ያልታጠቁ ዜጎች ግድያ እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከክልሉ ተፈናቅለዋል ፡፡ ሆኖም ፣ እንደኮነነው ፣ ማለትም ብሄር-ብሄረሰብ መሆን የለብንም sts እና የጎሳ አክራሪዎች ይልቁንም በብሄር ላይ በተመሰረተ ግድያ እና በማንኛውም ብጥብጥ ወይም በማንኛውም ንብረት ላይ ውድመት የተሳተፉ አካላት እንዲቆሙ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ እና ይህን ለማድረግ እያሰቡ ያሉት ፣ ላለማድረግ ፡፡ እንዲሁም በመላ አገሪቱ መረጋጋት ፣ ጥበብ ፣ ትዕግሥትና መገደብ ጥሪ ማድረግ እፈልጋለሁ ፡፡ ተጨማሪ የጎሳ ግድያዎች ፣ ሁከቶች እና ጥፋቶች መፍትሄው አይደሉም ፣ ግን ሁላችንም የደም መፋሰስ እና የዘር ማጥፋት ዑደት ሊያበራ ይችላል ፡፡ ንግዶች ፣ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች በቁጣ ወረራ መውደማቸው የተሳሳተ ነው እናም ማገገምን የበለጠ ከባድ ያደርገዋል ፡፡ ለሚጎዳው ርህራሄን ያሳዩ ፣ ሰብአዊነትን ከጎሳ ፣ ከሃይማኖት ወይም ከማንኛውም የሰው ልጅ ልዩነቶቻችን ያስቀድማሉ ፡፡ ይህ የ SMNE መሠረታዊ መርሕ ነው። ይህ እግዚአብሔር ለሰጣቸው የሕይወት እሴቶች ፣ ነፃነት እና ጎረቤትን እንደራስ መውደድ ማንም ሰው ስለ ነፃነት ፣ ስለፍትህ ፣ ስለ ሃይማኖት ነፃነት እና ስለሌሎች ደህንነት ደህንነት ሳይጨነቅ በነፃነት ለመኖር ወይም ለማምለክ ነፃ አይሆንም ፡፡ የ SMNE ዋና መርህ ልዩነታችን ምንም ይሁን ምን የሁሉም ዜጎቻችን ሞት እኛን እንደ አንድ አንድ ሊያደርገን ይገባል ፡፡ የመላው ኢትዮጵያዊያንን እሴት እና ክብር የሚያከብር አንድም የጎሳ የፖለቲካ መሪዎች እና ሁሉን የሚያካትት መንግስት ባይኖረን ኖሮ እና እኛ ሰዎች እንደመሆናችን መጠን ትክክለኛውን ፣ እውነተኛ እና ጥሩን የምንከተል ከሆነ; ዜጎቻችን በብሄራቸው ምክንያት ከመኖሪያ ቤታቸው እንዲፈናቀሉ ምክንያት የሆነው ነገር ሊቀለበስ ይችላል ፡፡ ኢትዮጵያ በእውነት የምንኖርባት እና የምንበለጽግባት ቤት ብትሆን በህዝባችን ላይ እንደዚህ አይነት አሰቃቂ ሞት እና ዘግናኝ የዘር ማፅዳት ተግባራት አንሰማም ነበር ፡፡ እንደዜጎች እራሳችንን ዝቅ እናድርግ ፣ የጎሳ ቡድኖች ርህሩህ ፣ መርሆች እና ይቅር ለማለት እና የራሳችንን እንደምንፈልግ የሌሎችን ነፃነት ፣ ፍትህ እና ደህንነት ለመፈለግ ዝግጁዎች እንሁን ፡፡ በየትኛውም የእምነት ክፍል የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለመታደጋችን ፣ ውድቀቶቻችንን በማዘን እና የራሳችን ፣ የህዝባችን እና የህብረተሰባችን የሞራል ሽግግር ለመፈለግ ወደ እግዚአብሔር ይጮኹ ፡፡ የሃይማኖት መሪዎቻችን የሰዎችን ማታለያ ለመቋቋም ይበረታቱ; እናም ወደ እርሱ ለተጠራቸው ለፈጣሪያቸው ታማኝ በመሆን ደፋር ሁን። ሁላችንም በምንወዳት አገራችን ውስጥ አስታራቂዎች ፣ ተሟጋቾች እና ሰላም ፈጣሪዎች እንሁን - ምንም ጎሳ ፣ የሃይማኖት ቡድን ወይም ሌላ ማንም ሳይጨምር ፣ ሁላችንም ነፃ እስክንሆን ድረስ ማንም ነፃ አይወጣምና! ኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ በዓለም ዙሪያ ባሉ ስፍራዎች ሁሉ አሁንም በአደጋ ወይም በችግር ላይ ያሉትን እግዚአብሔር ይጠብቃቸው ፡፡ ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! @abiseniyaethiopia
Показать все...
ታላቅ ንጉስ ካረፉ ዛሬ 118 ዓመታቸዉ ነዉ፡፡ሁሌም በየዓመቱ ጥር 3 ቀን እሳቸዉ በመሰረቱትና አጽማቸዉ በሚገኝበት መልዕልተ አድባር ደብረ ጸሃይ ቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስትያን መታሰቢያ ይደረግላቸዋል፡፡የአባቶቻቸን ልጆች እንሁን መልዕክታችን ነዉ! @abiseniyaethiopia
Показать все...
ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት/ንጉሰ ጎጃም ወከፋ/ ንጉስ ተክለሃይማኖት እና አደዋ ትልቅ ቁርኝት አላቸዉ-------------------- --------------------- ----------------------------------------------ንጉስ ተክለሃይማኖት የጎጃም ጦር ይዘዉ ወደ አደዋ በመዝመት የድሉ አንድ አካል ናቸዉ፡፡---------- --------------------------- የንጉሥ ተክለ ሀይማኖትን ታሪክ ለማወቅ የጎጃም ገዥዎችን ታሪክ ማየት ጠቃሚ ነው፡፡ የጎጃም አገረ ገዥዎች ታሪክ የሚጀምረው ከደጃዝማች ዮሴዴቅ (1744 - 1749) እንደሆነ በርካታ ታሪክ ፀሐፊዎች ዘግበውታል፡፡ ዮሴዴቅ በዳግማዊ ኢያሱ ብርሃን ሰገድ (1664-1699) ዘመን ለማዕከላዊ መንግስት አልገብርም ብሎ ከማስቸገር አልፎ እስከ ጨጨሆ በር ድረስ እየጋለበ ለጎንደር ቤተ መንግስት ስጋት ፈጥሮ እንደነበር አለቃ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራን በመጥቀስ ዶ/ር ሥርግው ገላው ጽፈዋል፡፡ ኢያሱም የዮሴዴቅን ኃያልነት ካየ በኋላ ልብ ሊይዝ የእናቱን ልጅ ዳግማዊት ወለተ እስራኤልን ዳረለት፡፡ (አለቃ ተክለ ኢየሱስ፣2008፡20) ወለተ እስራኤል የእቴጌ ምንትዋብ ልጅ ናቸው፡፡ “ቋረኛዋና ጥሩይቱ እቴጌ ምንትዋብ የአፄ ባካፋ ባለቤት በተዘዋዋሪ ኢትዮጵያን ለሰላሳ ዓመት አስተዳድረዋል፡፡ አፄ ባካፋ በወጣትነታቸው ሰለሞቱ ከሁለቱ የተወለደው ቀጣዩ ንጉሥ ኢያሱ ዓለም ሰገድ ነግሦ እቴጌ ምንትዋብ በሞግዚትነት መንግስቱን ያስተዳድሩ ነበር፡፡ እቴጌ ምንትዋብ ወጣት ሰለነበሩ ከምልምል ኢያሱ ሦስት የሚያማምሩ ልጆችን ወለዱ፡፡”(ጥላሁን ብርሃን፣2008፡33) እነሱም ወለተ እስራኤል፣ አስቴርና አልጣሽ ናቸው፡፡ ምንትዋብ የተጠቀሱትን ሴት ልጆቿን ለታዋቂ ኢትዮጵያውያን መሳፍንት በመዳር ግዛቷንና የኢትዮጵያን አንድነት ለማጠናከር ተጠቅማባቸዋለች፡፡ ከተጠቀሱት ውስጥም ወለተ እስራኤልን ለጎጃሙ ገዥ ደጃዝማች ዮሴዴቅ ተድራ ኃይሉን ወልዳለች፡፡ (አለቃ ተክለ ኢየሱስ፣2008፡22) የንጉሥ ተክለ ሀይማኖት የዘር ሀረግም የሚመዘዘው ከዚህ ትውልድ ነው፡፡ ዮሴዴቅ ታላቅ ኃይሉን ይወልዳል፣ ታላቅ ኃይሉ መርድን እና ድንቅነሽን ይወልዳሉ፣ ድንቅነሽ የዳሞቱን ባላባት ደጃዝማች ዘውዴ ስልን አግብተው ደጃዝማች ጎሹን ወለዱ፣ ደጃዝማች ጎሹ ዘውዴ ደግሞ ደጃዝማች ተሰማን፣ ደጃዝማች ብሩን፣ ደጃዝማች ንጉሴን፣ ልጅ ይማምን ይወልዳሉ፡፡ ደጃዝማች ተሰማ ጎሹ ራስ አዳልን (ንጉሥ ተክለ ሀይማኖትን) ወለዱ፡፡ ከላይ እንደተጠቀሰው አዳል (ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት) የተሰማ ጎሹ ልጅ ነው፡፡ ልጅ አዳል የእናቱ አገር በደብረ ኤልያስ ወረዳ ገነት አቦ ይባላል፡፡ ፊት ትቤ አቦ ይባል ነበር፡፡ ይህችም የልጅ አዳል እናት ወይዘሮ ምዕላድ ነገዷ ከአፄ እስክንድር የማርታ፣ የቴዎድሮስ፣ የዓመተ ክርስቶስ፣ የዕርቄ፣ የኢዮልያ፣ የቱፋ፣ በቋ ልጅ ናት፡፡ (አለቃ ተክለኢየሱስ፣2008፡21 9). ልጅ አዳል በሕፃንነቱ አያቱ ጎሹ በካሳ ኃይሉ (አፄ ቴዎድሮስ) ከተገደሉበትና አባቱ ተሰማ ጎሹ ከተጋዘ በኋላ ዘመድ የጭንቅ ዕለት ነውና በአባቱ አደራ ባይነት ወደ አጎቱ ተድላ ጓሉ የቀድሞዋ መንቆረር ያሁኗ ደብረ ማርቆስ ተልኮ ከልጆቹ ከንጉሴና ከደስታ ጋር እየተማሩ አደጉ፡፡ ከዚያ በኋላ ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት የጎጃም ገዥ ለመሆን ብዙ ፈተናዎችን አልፈዋል፡፡ በቀድሞዋ መንቆረር በአሁኗ ደ/ማርቆስ የሚገኘዉ የጎጃም ገዥዎች ቤተመንግስት በ1845 ዓ/ም ደጃዝማች ካሳ(ኋላ ዳግማዊ ቴዎድሮስ) የጎጃምን ግዛት ለማደላደል ዘመቻ አድርገው ክረምት በ1845 መንቆረር(አሁን ደብረ ማርቆስ) ውስጥ ቤተ መንግስቱ በሚገኝበት ቦታ የሳር ሰቀላ ቤቶችን አሰርተው መክረማቸውና በቦታውም ከተማ እንዲቆረቆር ትዕዛዝ ሰለማስተላለፋቸው የቤተመንግስቱ ጅማሬም ለደጃዝማች ካሳ እና ለደጃዝማች ተሰማ ጎሹ/የንጉስ ተክለሃይማኖት አባት/ መካረሚያ ከተሰሩ ጎጆች እንደሆነ ይነገራል፡፡ በሰቀላ ጎጆዎች የተመሰረተ ሲሆን በእነዚህ ሰቀላ የሳሪ ቤቶች ዘመኑ የሚጠይቀውን እድሳት በማከናወን ደጃች ተድላ ጓሉ(1847-1860)፣ ደጃች ንጉሴ ተድላ(1860)፣ ደጃዝማች ደስታ ተድላ(1860-1861) እንደ ሁኔታው ጎጃምን ሲገዙ ቆይተውበታል፡፡ ከደጃዝማች ደስታ ተድላ በኋላ ጎጃምን የገዙት ራስ አዳል ተሰማ(ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት) በዘመናቸው የቤተ-መንግስቱን የውስጥ አደረጃጀት በማስፋፋት የአስተዳደር ስራ በተደራጀ መንገድ እንዲከናወን በመደረጉና በሳር ክዳን ሰፊና ትልቅ አዳራሽ አሰርተው ሰለነበር በአካባቢው ማህበረሰብ የንጉሥ ተክለ ሀይማኖት ቤተ መንግስት በሚል ስያሜ መጠራት እንደጀመረ ይነገራል፡፡ ሥያሜው ከንጉሥ ተክለ ሀይማኖት በኋላም ሳይለወጥ የአሁኑን ዘመን ደርሷል፡፡ ራስ አዳል ተሰማ በአጼ ዮሐንስ ዘመነ መንግስት ጥር 13 ቀን 1873 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ላይ ‹‹ንጉሠ ከፋ ወጎጃም›› ተብለዉ የሸዋው ንጉስ ምኒሊክ በተገኘበት ነገሡ (ተክለጻድቅ፣200፡59)፡፡ አለቃ ተክለ ኢየሱስ ራስ አዳል ተሰማ ከንግሥና በኋላ ያከናወኗቸውን ተግባራት እንዲህ ዘግበውታል፡፡“ንጉሥ ተክለ ሀይማት በጎጃምና በከፋ ነግሦ ከመጣ በኋላ በጎጃምና በዳሞት ሹም ሽር አደረገ፡፡ የበኩር ልጁን በዳሞት ራስ በዛብህ አሰኘ፤ ቀጥሎ ደግሞ በአፄ ዩሐንስ ፈቃድ ጎጃምን ወረዳ በመንቆረር በዘና ታቦተ ማርቆስን ተክሎ ደበረ፡፡ ብዙ ቅፈፍ አግብቶ 318 ደብተራ ሰራለት፡፡ መልዕልተ አድባር (ከአድባራት በላይ) ይሁን አለ፡፡ ደብረ ማርቆስ ይባል እንጅ መንቆረር አይባል ብሎ አዋጅ ነገረ፡፡ አለቃ መልአከ ፀሐይ መሸሻን፣ ሊቀ ጠበብት ጽሐፌ ትዕዛዝ እሸቴን ሾመ፡፡ ለጥንት ባላአፈሮችም ለመንቆረርና ለዝና ልጆች የዣባጢን የጮቢ የሚባል ሀገር ምንጣፍ ተክቶ ሲሶ ግብዝና ለርሱ፣ ሁለት እጅ ለጥንት ባላአፈሮች ሰጠ፡፡” (የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ገጽ 263) ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት ራስ እያሉ ጀምሮ ከጎጃም የስልጣን ተቀናቃኞቻቸው ጋር እና ከኢትዮጵያ ነገሥታት ጋር በርካታ ጦርነቶችን አካሂደዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የሀገርን ዳር ድንበር ለማስጠበቅ ሁለት ታላላቅ ዘመቻዎችን አድርገዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ የመጀመሪያው የሱዳን ደርቡሾች ድንበር ተሻግረው ጎንደር ድረስ በመግባት ጥር 10 ቀን 1880 ዓ/ም ቤተክርስቲያን አቃጥለው ቀሳውስቱንና ሲያርዷቸውና እንዲህ ተብሎ ሲገጠም፡- ተከተልኸኝ ብየ ዞሬ ዞሬ ሳይ፣ ወይ ጥጋብ ወይ ኩራት ጎንደር ቀረህ ወይ? ወገራ አሳላፊ ደንቢያ እንጀራ ጣይ፣ ተበላህ ጎንደሬ አተትነሳም ወይ? በወቅቱ አጼ ዮሐንስ አስመራ ስለነበሩ ይህንን በቀል ንጉስ ተክለ ሀይማኖት እንዲበቀል መልክት በመላካቸው ንጉስ ተክለ ሀይማኖት 100,000 (አንድ መቶ ሺህ) የሚሆን ሰራዊታቸውን ይዘው በመሄድ ድል አድርገዋል ምንም እንኳን በሁለተኛው ዘመቻ ወቅት ቢሸነፉም (ተክለጻድቅ፣2000፡6)፡፡ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት በር በከፈተው ታላቁ የአድዋ ጦርነት ወቅትም የጎጃምን ጦር በመምራት 3000 (ሦስት ሺህ) ሰራዊት ይዘው በመዝመት ታላቅ ድል አስመዝግበዋል (ተክለጻድቅ፣2000፡109፤ መሪራስ አማን፡2009፡355)፡፡ የግዛት ዘመናቸውም ራስ አዳል ተሰማ ተብለው ከ1861-1872 ዓ/ም ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት ተብለው ከ1873-1893 ዓ/ም በድምሩ ለ32 ዓመት ጎጃምን ገዝተዋል፡፡ በአጠቃላይ በዘመናቸው የተሻለ ነው ብለው ያሰቡትን ነገር ለራሳቸውና ለሀገራቸው ጎጃም ሲፈፅሙ ኑረው ጥር 3 ቀን 1893 ዓ/ም በእለተ አርብ ደብረ ወርቅ ላይ አረፉ፡፡እነሆ የጎጃም መገለጫ የሆኑት ሀገር ወዳዱ እኒህ
Показать все...
ዓፄ # ልብነ # ድንግል (የዙፋን ስም "#አንበሳ # ሰገድ " ወይም # ዳግማዊ ዳዊት) ከነሐሴ ፲ ቀን ፲፬፻፺፱ እስከ ነሐሴ ፴ ቀን ፲፭፻፴፪ ዓ.ም የነገሱ ሲሆን የተወለዱትም # በ1501 እ.ኤ.አ. ነበር። የኢትዮጵያና # አዳል ጦርነትም የተጀመረው በኒህ ንጉስ ዘመን በ1528 እ.ኤ.አ. ነበር። ሚስታቸውም # ሰብለ ወንጌል ትባል ነበር። ዓፄ ልብነ ድንግል የዓፄ ናዖድ ልጅ የዓፄ በአደ ማርያም የልጅ ልጅ ናቸው። ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብም ቅድመ አያታቸው ናቸው። ዓፄ ናዖድ ፲፫ ዓመት ገዝተው ሲሞቱ በ፲፭፻ ዓ.ም. ዓፄ ልብነ ድንግል ገና የ፲፪ ዓመት ወጣት እያሉ ነገሡ። ስመ መንግሥታቸውም ወናግ ሰገድ ተባለ። # ወናግ ማለት # በኦጋዴን (ሱማሌ) ቋንቋ # አንበሳ ማለት ነው። የግዕዙን ወይም የአማርኛውን ቋንቋ «አንበሳ ሰገድ»ን ትተው በኦጋዴን ቋንቋ ወናግ ሰገድ የተባሉበት ምክንያት ምናልባት ያን ጊዜ በይፋትና በፈጠጋር ያለውን ግዛት የሚያውኩ ያዳልና የሱማሌ ተወላጆች ስለሆኑ እነሱ በሚያውቁት ቋንቋ ተሰይሞ ለማስፈራራት ይሁን ወይም የነሱ ገዥ ጭምር መሆናቸውን ለማስታወቅ ይሁን ወይም ከአባታቸው ከዓፄ ናዖድ ስመ መንግሥት (አንበሳ ሰገድ) በትርጉም ቢቀር በአጠራር እንዲለያይ ይሁን በትክክል አይታወቅም። ዓፄ ልብነ ድንግል ራሳቸው ለፖርቱጋል ንጉሥና ለሮማ ሊቀ ጳጳስ በጻፉዋቸው ደብዳቤዎች ላይ «ስሜ ልብነ (ዕጣን) ድንግል ትርጓሜው ድንግል ያበራችለት ይሄም ስም የተሰጠኝ ቅድስት ጥምቀትን በተቀበልኩበት ቀን ነው፤ በነገሥኩ ጊዜ ደግሞ ዳዊት ተባልኩኝ» ስለሚል በዳዊት ላይ ተጨማሪ ወናግ ሰገድ ሆኖ በሁለት ስመ መንግሥት ይጠሩ ነበር ማለት ነው። ዓፄ ልብነ ድንግል በነገሡ ጊዜ ወጣት ስለነበሩ በመንግሥቱ ሥራ እናታቸው እቴጌ ናዖድ ሞገሳ የአያታቸው የዓፄ በአደ ማርያም ባለቤት እቴጌ እሌኒ በሞግዚትነት ያግዟቸው ነበር። እነራስ ወሰን ሰገድና እነራስ ደገልሃን የመሳሰሉትም ታላላቅና ታናናሽ መኳንንት የመንግሥቱ የሥልጣንና የሥራ ተካፋይ ነበሩ። በመጀመሪያ፣ የዓፄ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግሥት የሰላምና የደስታ ቢሆንም የመጨረሻ ጊዜያቸው በግራኝ መነሳት ምክኒያት የጦርነት፤ የሁከት፤ የመከራና የስደት ጊዜ ሆኖባቸዋል። ከፖርቱጋል መንግሥት በቀጥታም ሆነ በእቴጌ እሌኒ በኩል ቢወዳጁ የጀመሩት ወዳጅነት ለጊዜው ጠቡን አጣደፈው እንጂ ከወረራ ሊያድናቸው አልቻለም። # ዋቢ መጽሐፍ # ተክለ ጻድቅ መኵሪያ፤ ፲፱፻፶፫ ዓ.ም.፤ የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ከዐፄ ልብነ ድንግል እስከ ዐፄ ቴዎድሮስ @abiseniyaethiopia
Показать все...
የኢትዮጲያውያን ገና በአል የገና (ልደት) በዓል በኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ቀኖና መሰረት ከዘጠኙ ዐብይ በአላት ውስጥ አንዱ በአል ነው። እለቱ በትንቢተ ነቢያት የተነገረለት የሰውን ልጆች በጥንተ ተፈጥሮ የፈጠረ የእግዚአብሔር ልጅ አሁን ደግሞ በሐዳስ ተፈጥሮ ለመፍጠር ማለት ሰውን ለማዳን ሰው ሆኖ የተወለደበት እለት ነው። የልደት በዐል የሚከበረው በየአመቱ ታህሣሥ ፳፱ (29) ቀን ሲሆን በዘመነ ዮሐንሥ ግን (የዘመነ ጳጉሜን ስድስድት ስለሆነች) በዐሉ ታህሣሥ ፳፰ (28) ቀን ይከበራል። ይህም የተጀመረው በአፄ ዐምደ ጽዮን ዘመነ መንግስት ነው ይባላል። የልደት በዓልከጾም ዘመን ጋር የተያያዘ ስለሆነ ገሃድ የለውም፤ የማይፆሙ ሰዎች ግን ዋዜማውን ብቻ ገሃድ ብለው ይፆሙታል። በገና በዓል በተለያዩ አካባቢዎች ወንዶች የገና ጨዋታ የተሰኘውን ባህላዊ ጨዋታ ሲጫወቱ ይስተዋላሉ። የገና ጨዋታ የተለያዩ መንፈሳዊና ባህላዊ አከባበር ከሚከበርባቸው ስፍራዎች አንዱ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው ጃንሜዳ ተብሎ የሚታወቀው ገናን ነው፡፡ የገናን ባህላዊ ጨዋታን ስንመለከት አስቀድሞ የቡድን አባላት የሚሆኑ ሁለት ሰዎች ይመረጣሉ፡፡ ሁለት ሁለት ተጫዋቾች ወደ አባቶች ይቀርቡና በምርጫው ወደ ቡድን ውስጥ ይገባሉ፡፡ የሚያስፈልገው የተጫዋች ቁጥር ሲሞላ ወገን ወገናቸውን ይዘው በዱላ ቀልጣፋ የሆኑ ተጫዋቾች ጥንጓን( መጫወቻ ኳሱ) ወደፊት እንድትቀጥል ይመቷታል ወይም ይመልሷታል፡፡ ተጫዋቾች ብዙ ጊዜ በጨዋታው ስለሚሰጡ ጥንጓን ከእግር መካከል በገባች ጊዜ ከሰው እግር ጋር ደርበው ስለሚመቱ የእግር መሰበር በዚህም ሳቢያ ወገን ለይተው እስከመፈናከት ይደርሳሉ፡፡ በንጉሳውያን ዘመን የመኳንንቱም አሽከሮች፣ የንጉሡና የንግሥቲቷ አሽከሮች የጌቶቻቸውን ስም በጉብዝና የሚያስጠሩት በባህላዊው የገና ጨዋታ ነው፡፡ ጨዋታው በመንደር ልዩነት ከሆነ የታች አምባ ቡድን ሀምሳ ተጫዋቾች ቢሆኑ የላይ አምባ ቡድን ሰባ ሆነው ቢጫወቱ የሚከለክል ደንብ አልነበረም፡፡ ጨዋታው በመጨረሻ ፀብ ስለሚያነሳ ብዙ ጊዜ ጉዳት ያጋጥማል፡፡ ጥንጓም ኃይለኛ ለጊ በመታት ጊዜ ዐይን እስከ ማጥፋት ትደርሳለች፡፡ ተጫዋቾች “በሚና” ብለው በሚጫወቱበት በቆልማማ ዱላ ቢደባደቡም የሚገላግል ዳኛ አልነበረም፤ ጨዋታውን በሚመለከቱ አባቶችም በድብድብ ከመሳቅ በስተቀር ሽምግልናቸው ለገና ጨዋታ አልተለመደም፡፡ “እግር ይብሳል፣ ያንከላውሳል፡፡” እያለ ማስፈራራት፣ ራስን መቀወር ወይም እንቆራቆስ ብሎ እጅና እግርን በዱላው መምታት በገና ጨዋታ የተለመደ ነበር፡፡ የገና ጨዋታ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በሌሎች አገሮች የታወቀውና በኦሊምፒክ የስፖርት በዓል ከሚደረጉ ውድድሮች አንዱ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ይህም ጨዋታ ሆኪ በሚል ስም ይጠራል፡፡ ፈረንጆች የፊት አደጋን መከላከያ ዘዴ ይጠቀማሉ፡፡ በኢትዮጵያ ያገር ባህል ገና ጨዋታ በሚደርስ አደጋ ማንም ተጫዋች አይጠይቅም፡፡ በገና ጨዋታ አሸናፊ ለሆኑት ቡድኖች ፊሪዳና ጠጅ ተሰጥቷቸው እየበሉና እየጠጡ፣ እየዘፈኑ ሲሸልሉና ሲያቅራሩ ሜዳውን የጦርነት ድል ያገኙበት ያስመስሉት ነበር፡፡ ከሚዘፍኑትና ግጥሞች ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡ “ማታ ነው ድሌ፣ ይሄ ነው አመሌ፡፡ አሲና በል አሲና ገናዬ፡፡ ኦ! ጉ! አሲና በል አሲና ገናዬ፡፡ ግፋው ግፋው አለኝ እኔ እንደምን ልግፋው፣ የአንድ በሬ ጨጓራ እንደ ቅል የነፋው፡፡ የብብቱ ሽታ፣ የመንፈቅ በሽታ፡፡ የጀርባው መርሬ፣ ያውላል ጥድ በሬ፡፡ ካስር ጋን አተላ፣ አይተርፈው በአንኮላ፡፡ እግርህ የሸረሪት ሆድህ የእንቁራሪት፣ ቀን እንደጠላሁ ና እንዳትመጣ ሌሊት፡፡” ስድብ ለተራው ሕዝብ ብቻ ሳይሆን በመኳንንቱና በነገሥታቱም ላይ ሊሰነዘር ይችላል፡፡ በሚደርስባቸው ስድብ ግን ምንም ዓይነት ቁጣና ቅጣት አያደርጉም፡፡ “በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ በገና ጨዋታ የለም ሎሌ ጌታ፡፡” የሚለው የዘፈን ግጥም ይህን ባህል ይገልፃል፡፡ የገና ጨዋታ ከክርስትና ሃይማኖት በፊት ይዘወተር እንደነበርና በኢትዮጵያ ከታኅሣሥ የመኸር ወቅት ጋር የተያያዘ ባህል ነበረ፡፡ ከበዓሉ ጋር የተያያዘ ብዙ የስነቃል ግጥሞችን ይገኛሉ፡፡ “ታኅሣሥ ገሠገሠ ከተፍ አለ ገና፣ እጠብቅሀለሁ አንተ ልጅ ቶሎ ና፡፡ ይወዘውዘኛል አልጠላኝም ገና፣ ፍቅር ሞገደኛው እየነሳኝ ጤና፡፡ ምግብ አያስበላ አያስለብስ ልብስ፣ ሞገደኛው ፍቅሩ ይዞኝ በታኅሣሥ፡፡ በማለዳ ጀንበር በገና ጨረቃ፣ እኔን እኔን ብላ መጣች ተደብቃ @abiseniyaethiopia
Показать все...
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.