C/E/R/State Guraghe Zone Wolkite Poly-Technic College & Satellite Campus
Открыть в Telegram
Talking all about TVET Training, Technology Transfer & Industry Extention Services
Больше405
Подписчики
-124 часа
+167 дней
+4030 день
Архив постов
+2
#አስደሳች_ማስታወቂያ 😍
#ለአዲስ_የመደበኛ_ስልጠና_ፈላጊዎች_በሙሉ 😍
+9
#ለአሰልጣኝ_መምህራን_ለትኩረት_ዘርፍ_ሴክተርና_ለባለድርሻ_አካላት_ባለሙያዎች_የአቅም_ግንባታ_ስልጠና_መሰጠት_ተጀመረ።
=======================
ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም፡ ኮሌጃችን ከኢትዮጵያ ኢንተርፕሪነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት (EDI) ጋር በመተባበር ለኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል።
የስልጠናው አላማ በስልጠናው እየተሳተፉ የሚገኙት አሰልጣኝ መምህራን በተለያዩ የቢዝነስ ዘርፎች ለሚሰማራት ባለሀብቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች መሰማራት በፈለጉት የቢዝነስ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል የማማከር ስራ ለመስራት እንዲያስችላቸው Training for Advisor (TOA) አቅማቸውን የማጎልበት ስራ ታሳቢ ያደረገ ነው።
ስልጠናውም እየተሰጠ የሚገኘው ከኢንስቲዩቱ በመጡ በዘርፉ የካበተ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች ሲሆን በስልጠናውም ላይ ከኮሌጁ ሁሉም ት/ት ክፍሎች የተውጣጡ አሰልጣኝ መምህራን፣ ከጉራጌ ዞን ቴክኒክና ሙያ መምሪያ እና ከወልቂጤ ከተማ ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ጽ/ቤት የ3ቱ ክ/ከተማዎች የአንድ ማዕከል ባለሙያዎችም በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
+2
የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ(ደ/ር) የመቁረጫ ነጥቡን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጻ ሰጥተዋል፡፡
ዶ/ር ተሻለ በመግለጫቸው የሥራ ገበያውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ነጥብ እንደሚዘጋጅ ገልጸው በዚህ ዓመትም የ12 ክፍል የማጠቃለያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 526,683 የሚሆኑት ከደረጃ 1 እስከ 5 በመደበኛ ስልጠና ለመሰልጠን ተቋማቱን ይቀላቀላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡
ገበያ ተኮር በሆኑ በአጫጭር ስልጠናዎች ደግሞ ከ3 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ዜጎች በተቋማቱ ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡
ሰልጣኞች በተቋማቱ በቂ ክህሎት ታጥቀው እንዲወጡ በክረምቱ የአሰልጣኞች የአቅም ግንበናታ ስልጠና፣ የማሽነሪዎች ጥገና እና አስፈላጊ የማሰልጠኛ ግብዓቶችን የማሟላት ሥራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡
በሀገሪቱ የሚገኙ የመንግስት እና የግል ማሰልጠኛ ተቋማት ይህንን የመቁረጫ ነጥብ መነሻ አድርገው ሰልጣኞችን መቀበል ይጀምራሉ ብለዋል፡፡
ለማህበራዊ ሳይንስ እና ለተፈጥሮ ሳይንስ የተቀመጡ የመቁረጫ ነጥቦች ዝርዝር ከታች ይመልከቱ
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡
ጥቅምት 11፤ 2017
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols
+9
#ሲሰጥ_የነበረው_የአቅም_ግንባታና_የግንዛቤ_ማስጨበጫ_ስልጠና_ተጠናቀቀ።
=========================
ጥቅምት 01/2017 ዓ.ም፡ የ2017 የሥራ ዘመን ግቦችን ማሳካትና ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከርን ታሳቢ አድርጎ በኮሌጃችን ሲሰጥ የነበረው የአቅም ግንባታና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተጠናቀቀ።
በመርሐ-ግብሩ መጀመሪያ ላይ በስልጠናው ከተሰሩት ዶክመንቶች መካከል ለናሙና የተመረጡትን ለተሳታፊዎች እንዲቀር በማድረግ የማስተቸትና የማስገመገም ስራ ተሰርቷል።
በአጠቃላይ ስልጠናው ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተነሱ ገንቢ አስተያየቶች መካከል መሰል የክህሎት ክፍተት ስልጠናዎች በተከታታይ መሰጠት ቢቻሉ፣ የትኩረት ዘርፍ መ/ቤቶች፣ የምርምር ተቋማትና የወልቂጤ ዩኒቨርስቲን በስልጠናው ላይ ማሳተፍ ከፍተኛ እገዛ እንዳለው፣ ኮሌጁ በሚያዘጋጃቸው ስልጠናዎች ላይ የክላስተር ኮሌጆችን እንዲሳተፉ መደረጉ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያነሱ ሲሆን ቢስተካከሉ ያሏቸው ደግሞ የስልጠናው ጊዜ አጭር መሆንና የመምህራን የክህሎት ክፍተቶች ጊዜውን ጠብቆ ቢሞሉ በዋናነት ያነሷቸው ናቸው።
በተነሱት አስተያየቶች ላይ በኃላፊዎች ምላሽ የተሰጠ ሲሆን ከተሰጡት መካከል የመምህራን የክህሎት ክፍተት መነሻነት ተከታታይ ስልጠናዎች እንደሚሰጡ፤ የትኩረት ዘርፍ፣ የምርምር ተቋማትና የወልቂጤ ዩኒቨርስቲን ማሳተፍ ለተግባሮቻችን መሳካት ጠቃሚ በመሆኑና የክላስተር ኮሌጆችን ማሳተፍ ደግሞ የክላስተሩ ሰብሳቢ እንደመሆናችን በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በመጨረሻም የክህሎት ክፍተቶቻችንን በራሳቸው ጥረት መሙላት እንደሚገባ፣ በኮሌጃችን ደረጃ በሁሉም የት/ት ክፍሎች እና በክላስተር ኮሌጆች ደግሞ በስራቸው ለሚገኙ መምህራን የማስፋት ስራ መስራት እንደሚገባና አፈፃፀሙ ክትትል እንደሚደረግ ማሳሰቢያ በመስጠት የመርሐ-ግብሩ ተጠቃሏል።
+8
#ADRA_Ethiopia_ከኢትዮጲያ_ወንጌላዊት_ቤተክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስ_ልማት_ቢሮ_የኮሌጃችን_ማስተባበሪያ_ክፍል_የተግባር_አፈፃፀምና_የስራ_ሂደት_ግምገማ_አካሄደ።
=========================
መስከረም 30/2017 ዓ.ም፡ በሶላር ኢነርጂ ላይ ከኮሌጃችን ጋር በትብብር እየሰራ የሚገኘው #ADRA_Ethiopia #ከኢትዮጲያ_ወንጌላዊት_ቤተክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስ_ልማት_ቢሮ #የኮሌጃችን_ማስተባበሪ_ክፍል የ"Green energy TVET" የፕሮጀክት አጋማሽ የተግባር አፈፃፀም ግምገማና የመስክ ጉብኝት መርሐ-ግብር አካሄደ።
በመርሐ-ግብሩ ላይ ከኢትዬጲያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ልማት ቢሮ የስራ ኃላፊዎች፣ ከክልላችን የፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ዘርፉን የሚመሩ ኃላፊዎችና የቴክኒክና ሙያ ቢሮ ተወካይ፣ ከጉራጌ ዞን የተለያዩ ሴክተር መምሪያዎች የመጡ የፕሮጀክቱ የስትሪንግ ኮሚቴ አባላት እና የኮሌጃችን ዲኖች ተገኝተዋል።
በመድረኩ መጀመሪያ የፕሮጀክቱ አጋማሽ ጊዜ ውስጥ የተሰሩ ስራዎች አፈፃፀም የሚያሳይ ሪፖርት በኮሌጃችን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ በአቶ ኤፍሬም ተሰማ አማካኝነት በዝርዝር ቀርቧል፤ በመቀጠልም በሪፖርቱ መነሻ በተሳታፊዎች አስተያየቶችና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ከተነሱት መካከልም በዋናነት የፕሮጀክቱ የእስካሁን አፈፃፀም አበረታች ደረጃ ላይ የሚገኝ መሆኑንና ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ነገርግን በተለያዩ ምክንያቶች እስከ አሁን ያልተፈፀሙና በሂደት ላይ ሆነው ያልተጠናቀቁ ተግባራትን ደግሞ ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመሆን ማስተካከያ እንዲያደርግ አሳስበዋል።
በመጨረሻም ፕሮጀክቱ በኮሌጃችን ውስጥ የሰራቸውንና እየሰራቸው የሚገኙ ስራዎች በተሳታፊዎቹ የመስክ ጉብኝት እንዲያደርጉ በማድረግ ቀጣይ በትኩረት መፈፀም ያለባቸው ስራዎች ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።
+3
#ኮሌጃችን_የISO_21001_2018_Quality_Management_System_ማረጋገጫ_ለመተግበር_የሚያስችለውን_የግብ_ስምምነት_ተፈራረመ።
=========================
መስከረም 28/2017 ዓ.ም፡ ኮሌጃችን የአለም አቀፍ የጥራት አስተዳደር ስርዓት (ISO" 21001፣ 2018 - Quality Management System) ማረጋገጫን ለመተግበር የሚያስችለውን የግብ-ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የኮሌጃችን የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ም/ዲን አቶ ቦጋለ ተክሌ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በአካል በመገኘት ሲሆን ስምምነቱ የተሳካው የክልላችን የቴ/ሙ/ት/ሥ/ቢሮ በኩል ተከታታይ ጥያቄዎች ሲካሄዱ ቆይተው በመጨረሻም ኢንስቲትዩቱ የኮሌጃችንን ነባራዊ ሁኔታ ከገመገመ በኋላ የአለም አቀፍ የጥራት ማረጋገጫ ("ISO" 21001፣ 2018 Quality managment system') ሰርተፊኬት ማግኘት የሚያስችለንን የቴክኒክና የማማከር ድጋፍ እንዲደረግልን የሚያስችል ነው፡፡
ስምምነቱ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እየተገበርናቸው ከሚገኙ አዳዲስ የለውጥ እሳቤዎች መካከል የተቋማት ደረጃ የማዘመን ዕሳቤን ዕውን በማድረግ ምቹ የስልጠና ቦታ፣ ደረጃውን የጠበቀ የመማሪያ ፋሲሊቲ፣ አለም አቀፍ መስፈር የሚያሟላ የማሽነሪ - ሰልጣኝ ጥመርታ፣ ዲጂታላይዝ የተደረገ ቤተ-መጻህፍት፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን እና በአግባቡ የተዋበና የተደራጀ ምድረ-ግቢ በመፍጠር ኮሌጁን ለሰልጣኞች እና ለተገልጋዮች ሳቢና እርካታን እንዲጨምር ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡
+6
#ሁሉን_አቀፍ_የአቅም_ግንባታና_የግንዛቤ_ማስጨበጫ_ስልጠና_መሰጠት_ተጀመረ።
=========================
መስከረም 27/2017 ዓ.ም፡ ኮሌጃችን የ2017 የሥራ ዘመን የተጣሉ ግቦችን ለማሳካትና ውጤታማ ለማድረግ እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከርን ታሳቢ ያደረገ ሁሉን አቀፍ የአቅም ግንባታና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አስጀመረ።
የአቅም ግንባታና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን ያስጀመሩት የኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤክስ/ም/ዲን አቶ ቦጋለ ተክሌ እንዳሉት የስልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ-ግብሩ በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ የለውጥ እሳቤዎች፣ Project Document Preparation, Action Research, Project Based Learning, Entrepreneurship, Kaizen & Value Chain ርዕሶች ላይ ያተኮረ መሆኑን አላማዎቹም የአሰልጣኝ መምህራንን አቅም መገንባት፣ ከኮሌጁ ጋር በአጋርነት ከሚሰሩ የትኩረት ዘርፍ መሪ መ/ቤቶች፣ የምርምር ተቋማትና ዩኒቨርስቲ ጋር በቀጣይ ጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር ታሳቢ ያደረገ መሆኑን እና በስራ ዘመኑ ለሚሰሩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች መነሻ የሚሆኑ የValue Chain የዶክመንቶችም በጋራ ለማዘጋጀት እንደሆነ አንስተው ስልጠናውን በአግባቡ እንዲከታተሉ አሳስበዋል።
ስልጠናውንና የግንዛቤ ማስጨበጫውን እየሰጡ የሚገኙት ከኮሌጁና ከጉ/ዞ/ቴ/ሙያ መምሪያ የተውጣጡ መምህራንና ባለሙያዎች ሲሆን በመርሐ-ግብሩ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት ከኮሌጁ ሁሉም ት/ት ክፍሎችና ከክላስተሩ ከሚገኙ ሁሉም ኮሌጆች የተውጣጡ አሰልጣኝ መምህራን፣ የትኩረት ዘርፍ መሪ መ/ቤቶችና በአካባቢ ከሚገኙ የክልልና የፌደራል ተጠሪ የምርምር ተቋማትና ከወልቂጤ ዩኒቨርስቲ የተጋበዙ ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛል። ስልጠናውም ለቀጣይ ተከታታይ 5 ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
#የሀዘን_መግለጫ 😪😭😥
===================
መስከረም 26/2017 ዓ.ም፡ በወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ ሳተላይት ካምፓስ በዲግሪ መርሃ-ግብር የElectrical Technology ት/ት ክፍል የ4ኛ ዓመት ተማሪ የነበሩት አቶ ዳዊት ደቦጭ በደረሰባቸው ድንገተኛ አደጋ ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው አጠቃላይ የኮሌጃችን ማህበረሰብ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፁ ለመላው ቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በሙሉ መፅናናት ተመኝተዋል!! 😥😭😪
+8
#የEthio_Coders_ሥልጠና_መሰጠት_ተጀመረ!!
=======================
መስከረም 25/2017 ዓ.ም፡ ኮሌጃችን ከወልቂጤ ከተማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት ከከተማ አስተዳደሩ ስር ለተውጣጡ አመራሮችና አስ/ሰራተኞች የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።
የኢትዮ-ኮደርስ ሥልጠና በቴክኖሎጂ የታገዘ መረጃን የመሰብሰብ፣ የመተንተንና የመተንበይ አቅምን የሚያሳድግ ሲሆን ስልጠና በቴክኖሎጅው ዘርፍ ያለብንን ከፍተኛ ክፍተት በመሙላትና የድጅታል አቅምን በማሳደግ በየተቋሙ የሚሰጡ አገልግሎቶች ለማሻሻል ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ ስልጠናውም ያለምንም ክፍያ በነፃ ሁሉም በያለበት በኦንላይን የሚሰጥ ሲሆን ማንኛውም ስልጠና ፈላጊ ዜጋ ተመዝግቦ የእድሉ ተጠቃሚ መሆን የሚችሉ ይሆናል።
በሥልጠናው ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የወልቂጤ ከተማ ም/ከንቲባና የንግድና ገበያ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙባሪክ ዘይኑ እና የከተማው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀምዱ ካሚል ተገኝተው ስለስልጠናው አስፈላጊነትና ጠቀሜታ ጨምሮ የተለያዩ መልዕክቶች አስተላልፈው ስልጠናውን ተከታትለው መጨረስና አላማው እንዲሳካ የበኩላቸውን እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
በተጨማሪ የኮሌጃችን የICT ት/ት ክፍል ኃላፊ አቶ አምሀ አለማየሁ በበኩላቸው እንደገለፁት የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ሀገራዊ ተልዕኮ እንደመሆኑ ኮሌጁ ተቀብሎ ለማሰልጠን ሙሉ ዝግጅት ማድረጉንና ከመሠል ሴክተር መ/ቤቶች ጋር ተቀናጅተን የምንሰራቸው ስራዎችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።
+9
#ኮሌጁ_በቋሚነት_ድጋፍ_እያደረገ_ለሚያስተምራቸው_ህፃናት_የትምህርት_ቁሳቁስ_ድጋፍ_ተደረገ።
=========================
መስከረም 22/2017 ዓ.ም፡ ኮሌጁ ከአጠቃላይ አሰልጣኝ መምህራንና አስ/ሰራተኞች ደሞዝ በቋሚነት በሚዋጣ ገንዘብ ለሚያስተምራቸው የአቅመ-ደካማ ቤተሰብ ልጆች ለአዲሱ የት/ት ዘመን አገልግሎት የሚውል የት/ት መማሪያ ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደርጓል።
የድጋፍ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወ/ሮ ሊድያ ሳኒ በድጋፉ ላይ እንደገለፁ ኮሌጁ ለህፃናቱ በየጊዜው አስፈላጊውን የምግብ፣ የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁሶችን በቋሚነት ገዝቶ በመስጠት በሚደረግላቸው ድጋፍ ትምህርታቸውን ያለችግር እንዲከታተሉ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
በተጨማሪ በድጋፉ ላይ ተገኝተው ድጋፉን ለህፃናቱ ያስረከቡት የኮሌጁ ዲን አቶ ኸይሩ አህመዲን በበኩላቸው ህፃናቱ በትምህርታቸው ጠንክረው በመማር ጎበዝ መሆን እንዳለባቸው አሳስበው ይህንን ካደረጉ ደግሞ ሽልማቶችና ሌሎችም ተጨማሪ ድጋፎች ተጠናክሮ እንደሚደረግላቸው ቃል ገብተዋል።
በሌላ በኩል ድጋፉ የተደረገላቸው ህፃናትና ቤተሰቦቻቸው በበኩላቸው እንዳሉት ኮሌጁ እያደረገላቸው ለሚገኙ በርካታ ድጋፎች ትምህርታቸውን ያለ ችግር እንዲማሩ በመደረጋቸው ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይ ትምህርታቸው ጠንክረው በመማርና የተሻለ ውጤት በማምጣት ኮሌጁን ለማስጠራት እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል።
#የእንም_አበሩሰንዳ_የ2017_የሙራ_መስቀር_ቦኼም_አሰናናሁም_አሰናንደም! 💐🌻🌼💐🌻
#እንኳን_ለ2017_የመስቀል_በአል_አደረሳችሁ_አደረሰን 💐🌼🌻💐🌼🌻💐🌼🌻💐🌼🌻
==================================
መስከረም 14/2017 ዓ.ም፡ #የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን በሙሉ እንኳን ለተወዳጁና ተናፋቂው በተለይ ደግሞ በዞናችን በጉራጌ ማህበረሰብ ዘንድ በደማቁ ለሚከበረው #የመስቀል_በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ እያለ 🌻🌼💐 በዓሉ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ የተነፋፈቁ ዘመድ አዝማዶች የሚገናኙበት፣ አቅመ-ደካማ ወገኖቻችን ጠግበው የሚያሳልፉበት በአጠቃላይ ሁላችንም ተደስተንና ጠግበን የምናሳልፈው እንዲሆን ከልብ ይመኛል 🙏💐🙏🌼🙏🌻
***
#ድጋሚ_መልካም_በዓል 🌻🌼💐
#የምዝገባ_ማስታወቂያ !!
#ለነባር_ሰልጣኞች_በሙሉ !!
+1
#የሀዘን_መግለጫ 😥😭😪
==================
መስከረም 10/2017 ዓ.ም፡ በወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክና ሳተላይት ካምፓስ ለበርካታ አመታት በአሰልጣኝ መምህር ሲያገለግሉ የነበሩት ወንድማችን #አቶ_ተሾመ_በቀለ (#አብደላ) በገጠማቸው ከፍተኛ ህመም ምክንያት ለበርካታ አመታት በተለያዩ የህክምና ተቋማት ህክምናቸውን ሲያደርጉ ቢቆዩም በዛሬው ዕለት መስከረም 10/2017 ዓ.ም ተሸንፎ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቶናል 😭😥😭
#አቶ_ተሾመ_በቀለ (#አብደላ) በባህሪያቸው እጅጉን ትሁት፣ ለሰው አዛኝና ከሁሉም ጋር ተግባብተው የሚኖሩ እና በስራቸውም ምስጉን፣ ታታሪና ያላቸውን ነገር በሙሉ ለስራው በመስጠት የሚታወቁ ወንድማችን ነበሩ። 😥😭😥
የኮሌጃችንም ማኔጅመንት እና አጠቃላይ ማህበረሰብ በወንድማችን ሕልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን እየገለጹ 😭😥😭 የሟች ወንድማችንን ነፍስ በገነት እንዲያኖርልንና ለአጠቃላይ ቤተሰቦቹ፣ የስራ ባልደረቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለኮሌጁ ማህበረሰብ ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጥልን ይመኛል። 😪😭😥
+3
#እንኳን_ደስ_አላችሁ_ደስ_አለን 💐💐💐
#ሁሌም_ደስታችሁ_ደስታችን_ነው 😍😍😍
========================
በጉራጌ ዞንና በኮሌጃችን ክላስተር ስር የሚገኙትና በየጊዜው ከፍተኛ መሻሻልና ውጤት እያስመዘገቡ የአካባቢያቸውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት እያረጋገጡ የሚገኙት #የአረቅጥ እና #የአገና ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጆች ደረጃቸውን በማሳደግ ወደ #ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅ በማደጋቸው ኮሌጃችን የተሰማውን ልባዊ ደስታው ይገልፃል። የኮሌጆቹ ደረጃ በማደጉ ከማህበረሰባቸው በተጨማሪ ለዞናችንም አቅም ከመሆን አንፃር ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ሲሆን በቀጣይም ኮሌጃችን ከኮሌጆቹ ጋር ያለውን የጠበቀ የመደጋገፍና ተባብሮ የመስራት ልምድ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ያረጋግጣል። 🙏❤🙏
======================
#በድጋሚ_እንኳን_ደስ_አላችሁ_ደስ_አለን 💐💐💐
+9
#ሁሉንም_የኮሌጁን_ማህበረሰብ_ያሳተፈ_የግምገማና_የሽልማት_መርሐግብር_ተካሄደ።
=========================
መስከረም 06/2016 ዓ.ም፡ አጠቃላይ የኮሌጁን ማህበረሰብ ያሳተፈ በ2016 የስራ ዘመን የእቅድ አፈፃፀም፣ የ2017 የስራ ዘመን የተግባር እቅድ እንዲሁም ቀጣይ በኮሌጁ ሊተገበሩ ለታቀዱ አዲሱ የዘርፉ የሪፎርም ስራዎች ላይ የግምገማና የምክክር መድረክ ተካሄደ።
በመድረኩ የሁለቱ ዋና የስራ ሂደቶች የ2016 ሪፖርትና የ2017 እቅዶች በየዘርፎቹ አስተባባሪ ም/ዲኖች እንዲሁም የፋይናንስ አፈፃፀም ደግሞ በስራ ሂደቱ አስተባባሪ በመጨረሻም የዘርፉ የሪፎርም ስራዎች በተለይ ደግሞ ኢንተርፕሪነራል ተቋም ምስረታ ሂደት ደግሞ በኮሌጁ ዲን እንዲቀርቡ ተደርገዋል።
በመቀጠልም በመድረኩ ተሳታፊ አሰልጣኞችና አስ/ሰራተኞች በቀረቡት ሪፖርቶችና እቅዶች ላይ የግልፀኝነት ጥያቄዎች ያነሱ ሲሆን ከሪፎርም ስራዎች በተለይም ኢንተርፕሪነራል ኮሌጅ ምስረታ ሂደት በጣም ጥሩና ለስራ ሞራል የሚጨምር መሆኑንና ማሳካት የሚቻል መሆኑን ነገርግን በቀላሉ ሊሳካ የሚችለው የአሰራር ማነቆዎች ተከታትሎ መፍታት ሲቻል እና የሁሉም አካላት ቁርጠኝነት ሲጨመርበት መሆኑን አፅንኦት ሰጥተው አንስተዋል።
በመቀጠልም ከተሳታፊዎች የተነሱ ገንቢ አስተያየቶችና ግልፀኝነት የሚጠይቁ ጥያቄዎች ላይ በኮሌጁ ዲኖችና አስተባባሪዎች ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል።
በመድረኩ ላይ የወልቂጤ ከተማ ሳ/ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ኃላፊ በEthio-Coders ስልጠና ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ተሰርቶ የጋራ የግብ-ስምምነት ተፈራርመናል።
በመጨረሻም ግንባር ቀደም ፈፃሚ አሰልጣኞች፣ አስ/ሰራተኞችና የት/ት ክፍል ተጠሪዎች እንዲሁም በክህሎት፣ በቴክኖሎጂና የጥናትና ምርምር ውድድሮች ላሸነፉ አሰልጣኞች የእውቅና ሽልማት ተሰጥቶ የመድረኩ ማብቂያ ሆኗል።
የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1499ኛው የነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያለ መልካም ምኞቱን እየገለፀ በዓሉን ስናከብር በነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) አስተምህሮቶችና ትሩፋቶች መሰረት የተቸገሩትን በማገዝ፣ የተራቡትን በማብላት፣ የታረዙትን በማልበስና የመሳሰሉትን በጎ ተግባራት ላይ በመሳተፍ እንድናከብር ጥሪውን ያስተላልፋል 🙏😍🙏
#በድጋሚ_መልካም_የመውሊድ_በዓል !! 🙏😍🙏
#እንኳን_ለ2017_አዲስ_አመት_በሰላምና_በጤና_አደረሳችሁ !!🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻
========================
ጳጉሜ 05/2016 ዓ.ም፡ #የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ ለመላው የሀገራችን ህዝቦች እንኳን ለ2017 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል 🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻
አዲሱ ዓመት የጤና፣ የብልዕግና፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የአብሮነት እንዲሁም ከማንኛውም በላይ የሰላም እንዲሆንልን ይመኛል 🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼
አዲሱ ዓመት ኮሌጃችን በዘርፉ የተሰጡትን ዋነኛ ተልዕኮዎች ማለትም የሰው ኃይል ልማትና ተቋም አቅም ግንባታ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን እና የዲግሪ የሳተላይት ስልጠናን በተቀመጡት ስታንዳርድ መሠረት ፈፅመን የማህበረሰባችንን ዘርፈ-ብዙ ችግሮች የምንፈታበት፤ ከህዝባችን ጋር ያለንን መቀራረብና መተጋገዝ ከወትሮው በተሻለ አጠናክረን የምናስቀጥልበት፤ በተለይ ደግሞ አዳዲሶቹን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና የለውጥ እሳቤዎች ተግባራዊ በማድረግ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ ግንባር ቀደም ኮሌጅ የምንሆንበት እና በአጠቃላይ ህዝባችን ከኮሌጃችን የሚፈልጋቸውን ዘርፈ-ብዙ አገልግሎቶች በጥራት በማቅረብ እርካታችሁን የምንጨምርበት እንዲሆንልን ከልብ ይመኛል 🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻
=========================
#በድጋሚ_መልካም_አዲስ_አመት 🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻🌼🌻
+5
#ወደ_አረብ_ሀገራት_ለሚሄዱ_ዜጎች_የሚሰጠው_የክህሎት_ስልጠናና_የብቃት_ምዘና_ተጠናክሮ_ቀጥሏል!!
=========================
ነሀሴ 27/2016 ዓ.ም፡ ወደ አረብ ሀገራት ለስራ ስምሪት ለሚሄዱ ዜጎች የሚሰጠው የክህሎት ስልጠናና የብቃት ምዘና ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ስልጠናው ዜጎች ለስራ የሚሰማሩባቸውን ሀገራት ባህልና ልምድ አውቀው ስራቸውን በአግባቡና በጥራት እንዲሰሩ እንዲሁም ተወዳዳሪነታቸውንና ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ነው።
በተጨማሪም ስልጠናውን በአጭር ጊዜ ካጠናቀቁ በኋላ የብቃት ምዘና (COC) እንዲወስዱ በማድረግ ወደ ፈለጓቸው ሀገራት የስራ ስምሪት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው።
በዚሁ አጋጣሚ የስልጠናው፣ የብቃት ምዘናው እና የዚህ ታላቅ የስራ እድል ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉ ዜጎች በኮሌጁ ተገኝታችሁ በመመዝገብ የእድሉ ተጠቃሚ መሆን የምትችሉ መሆኑን በደስታ እንጋብዛለን።
#የበለጠ_መረጃ
0911318770
0923062919
0113301590 አድራሻዎች ማግኘት ይችላሉ።
=======================
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
+3
#3ኛ_ዙርና_የአመቱ_የማጠቃለያ_የአረንጓዴ_አሻራ_መርሐግብር_ተካሄደ።
=========================
ነሐሴ 23/2016 ዓ.ም፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ማህበረሰብ የዓመቱ ማጠቃለያ 3ኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐግብር አካሄደ።
መርሐግብሩ በኮሌጁ የኮንስትራክሽን ካምፓስ ግቢ ውስጥ የተካሄደ ሲሆን የተተከሉትም ምርጥ ዘርና በአጭር ጊዜ ውስጥ መድረስ የሚችሉ የፍራፍሬ ችግኞች ናቸው።
አጠቃላይ በመርሐግብሩ ላይ አጠቃላይ የኮሌጁ የማኔጅመንት አባላት እና የአስተዳደር ሰራተኞች ተገኝተው አሻራቸውን አኑረዋል።
========================
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
