cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

🇦🇹🇦🇷መንትዮቹ🇦🇹🇦🇷የፋሲልና🇦🇹🇦🇷የባ/ዳር🇦🇹🇦🇷ከነማ🇦🇹🇦🇷ቻናል🇦🇹🇦🇷

ስለ ሁለቱ ክለቦች ፋሲልናባ/ዳር ከነማ መወያያ ቻናል ነው አዳዲስ ዜናዎች ዝውውሮና የቀጥታ ስርጭት የምናስተላልፍበትና አንዳንድ ጠቃሚ ነገሮችንም የምንለቅበት ቻናል ነው። Jion our channel 👉 @bdfaya 👉 @bdfaya 🇦🇹🇦🇷 🇦🇹🇦🇷🇦🇹 👉 @bdfaya 🇦🇹🇦🇷🇦🇹🇦🇷🇦🇹🇦🇷🇦🇹🇦🇷🇦🇹🇦🇷

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
246
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

በ Africa soccer zone የሳምንቱ የአፍሪካ ሊጎች ምርጥ ቡድን ውስጥ ሙጂብ ቃስም እና አቡበከር ናስር መካተት ችለዋል። Via-Bisrat_Sport #ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው 🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹 #join👇 #ተቀላቀሉ👇 #share @bdfaya @bdfaya
Показать все...
🔝#መንትዮቹ_ወንድማማቾች! ሁለቱ ክለቦች በክፉ ጊዜ የተገኙ ናቸው። ድምፅ ማሰማት ባልቻልንበት ጊዜ ወጣቱ ድምፁን እንዲያሰማ መድረክ የሆኑ ናቸው። በየ ክለቦቹ መድረክ የአማራ ጉዳይ ከዳር ዳር ተሰምቶበታል። ባሕርዳር ከነማ ያለ ደጋፊ እንዲጫወት ተቀጥቶ ወደ ጎንደር ስቴዲዬም ተልኮ ነበር። "እኛም የጣናው ሞገድ ደጋፊ ነን" ብለው፣ ኢፍትሐዊነቱን ተቃውመው የፋሲል ደጋፊዎች ግልብጥ ብለው ስቴዲዬም ገብተው ውሳኔ አስቀይረዋል። በቀጣይም በዚሁ ሜዳ ያለ ደጋፊ ይጫወት ተብሎ የነበረው "እንዲህ ከሆነማ ምኑን ደጋፊ አጣ ይቅር" ተብሎ ቀርቷል። ፋሲል ከነማ ባሕርዳር ላይ ሲጫወትም የባሕርዳር ከነማ ደጋፊዎች እንዲሁ እንደ አንድ ሕዝብ ክለብ ሲደግፉትና ሲያበረታቱት ተመልክተናል። አልፎ አልፎ ቅንጦት የገባቸው ደጋፊዎች አያለሁ። የባለፈውን ይረሱታል። አሁን ያለውንም ይረሱታል። ስፖርቱ በራሱ የሕዝብ መድረክ ነበር። ደርቢነት ሳይሆን ጓዳዊነት፣ ወንድማማችነት፣ ከዚህም ከፍ ሲል እንደ ፎቶው አይነት ያላቸውን ወንድማዊነት ነው የምናውቀው። መንትያነት ነው የምናውቀው። ወቅቱ ደግሞ ሕዝብ በየቦታው የሚገደልበት ነው። በዚህ ወቅት ሕዝባችን አንድ ያደረገ ስፖርት መደገፍ ተገቢ ቢሆንም ቅሉ የቅንጦት ያህል እንዳይወሰድ ያስፈልጋል። ሰው እየሞተብን ባለን ሰዓት ሌላውን ረስተን ስፖርት ብቻ ያለ እንዳናስመስለው። ሌላው ደግሞ እንዳያስተዛዝበን። ቀደም ሲል ክለቦች የነበሩ ቢሆንም በዚህ ደረጃ ነጥረው በመውጣት ሁለቱ ክለቦች ናቸው ሊጠቀሱ የሚችሉት። እና ያለ አግባብ በኳስ ስንዘል እንደ አይቶ አያውቅም እንዳያስብለን ቀስ ብለን፣ መንትያነትን ሳንዘነጋ መሆን አለበት! መደገፍ መብትም፣ ያለም ነው። ከዛ ያለፈ እንደ ተለያዩ ክለቦች አድርጎ፣ ወቅቱን ረስቶ መደገፍ ግን ትንሽ ያስተዛዝባል። ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እያገናዘብን ቢሸነፍብህ እርር ያልክም ቻለው፣ ብታሸነፍም ደስታውን እንደዛው! ከዛም ደግሞ /አማረልኝ ብሎ ይላል የሀገሬ ሰው/ አማረልኝ ብሎ ያለ አግባብ ፌስቡክ ላይ መነቋቆር ምናምን ቅብጠት ነው። አደጋም አለው። ሕዝብ እያሰባችሁ፣ ሁለቱ ክለቦች እርስ በእርስ የተደጋገፉትን እያሰባችሁ፣ የጋራ መድረክ የሆኑትን እያሰባችሁ ደግፉ። ከተሸነፈብህ ዋጥ አድርገህ፣ ካሸነፍክ ደግሞ ደስታውን ቻል አድርገህ ይሁን። ይህን የምለው ድሮ በፌስቡክ የሕዝብ ወገን መስለው ሲከፋፍሉ የነበሩት አሁን በሀሰት አካውንት ወደኳሱም መጥተው ስድብ ስላበዙ ነው። አያዋጣም! እንዳትቀብጡብን ለማለት ነው! !👇 https://@bdfaya ጌታቸው ሽፈራው ♨@bdfaya @bdfaya♨
Показать все...
⚽ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | ፋሲል ከነማ ከ ባህርዳር ከተማ የኢትዮጵያን ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ 18ተኛ ሳምንት ሶስተኛ ቀን ጨዋታ ክለባችን ፋሲል ከነማ ነገ 10:00 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም ከባህርዳር ከተማ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል። . የቤትኪንግ ኢትዮጵያን ፕሪሚየር ሊግ በአዲስ አበባ ፣ በጅማ እና በባህርዳር ከተሞች ላይ በጥሩ ሁኔታ ታካሂዶ ወደ 4ተኛ ዙር አዘጋጇ ድሬዳዋ ከተማ በመግባት ውድድሩ ቀጥሏል። አፄዎቹ ባሳለፍናቸው ወራቶች 15 ተከታታይ ጨዋታዎችን ያለምንም ሽንፈት በመጓዝ ወሳኝ ነጥቦችን በመሰብሰብ የቻሉ ሲሆን የደረጃ ሰንጠረዡን በ11 ነጥብ ልዮነት በመምራት ላይ ይገኛሉ። ነገም ለማሸነፍ ፣በሰፊ ነጥብ መሪነቱን ለማጠናከርና በጊዜ የዋንጫ ጉዟችን ለመወሰን ጨዋታውን ትኩረት በመስጠት ወደ ሜዳ ይገባሉ። . ፋሲል ከነማ ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች 13 ጨዋታ ማሸነፍ ሲችል ፣ በሁለቱ አቻ ውጤትን በመለያየት ቀሪውን አንድ ጨዋታ ተሸንፏል። በደረጃ ሰንጠረዡ በ41 ነጥብ በ20 ንፁህ ጎል 1ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። . ተጋጣሚያችን ባህርዳር ከተማ ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች መሰብሰብ የቻለው 29 ነጥብን ሲሆን በ10 ንፁህ ጎል በደረጃ ሰንጠረዡ 3ተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። . የእርስ በእርስ ግንኙነት:- ባህርዳር ከተማ ወደ ሊጉ ካደገበት አመት ጀምሮ በ 4 ጨዋታዎች ተገናኝተናል። 2011:- ባህርዳር ከተማ 0-0 ፋሲል ከነማ ፋሲል ከነማ 4-0 ባህርዳር ከተማ 2012:- ፋሲል ከነማ 3-0 ባህርዳር ከተማ በኳቪድ ምክንያት ተቋርጧል። 2013:- ባህርዳር ከተማ 2-2 ፋሲል ከነማ ፋሲል ከነማ 🆚 ባህርዳር ከተማ ነገ ማክሰኞ ሚያዝያ 5 10:00 . በክለባችን በኩሉ ያሉ ዜናዎች፦ ሁሉም የቡድናችን አባላት ከጉዳትና ከቅጣት ነፃ በመሆን ለጨዋታው ዝግጁ ናቸው። 🇦🇹#እናሸንፋለን🇦🇹 #ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው 🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹🇦🇹 #join👇 #ተቀላቀሉ👇 #share @bdfaya @bdfaya
Показать все...
የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ከወላይታ ድቻ ጋር የሚጫወተው ሙሉ ቡድን... ⚽Wolata Dicha 🆚 Fasil Kenema ⚽ የአፄዎቹ መጀመሪያ አሰላለፍ. (Starting) GK ❹➊❹➊ *የፋሲል ከነማ ዋና አሰልጣኝ ስዩም ከበደ *ምክትል አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽ *ምክትል አሰልጣኝ ሙሉቀን አቡሃይ *የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ አዳም ባዘዘው *የቡድን ሀኪም ሽመልስ ደሳለኝ *የፋሲል ከነማ ቡድን መሪ ሀብታሙ ዘዋለ! ጨዋታው በዲስቲቪ 228 Varity 3/4 ላይ ይተላለፋል። 🇦🇹#ድል_ለአፄዎቹ!!🇦🇹 🇦🇹#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው🇦🇹 @bdfaya
Показать все...
ዋንጫው የኛ ነው 🏆 ------------------------------ ዘንድሮ የአሰልጣኝ ስዩም ከበደ ቡድን ፋሲል ከነማ የዋንጫው ባለቤት መሆኑ አይቀሬ ነው ። የኢትዮጵያ ኘሪሚየር ሊግ ዛሬ ሲካሄድ ኢትዮጵያ ቡና በሀዋሳ ከተማ 1ለ0 ሲሸነፍ ፣ቅ/ጊዮርጊስ ያለ ጎል ከሰበታ ከተማ ጋር በአቻ ውጤት ነጥብ ተጋርቷል። አሁን ፋሲል ከነማ የኢትዮጵያው ማንችስተር ሲቲ ሁኗል። ከተጋጣሚዎቹ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት በየሳምንቱ እያሰፋ ፣ከዋንጫ ተፎካካሪዎቹ እየራቀ ፣ተፍካካሪዎቹን ተስፋ እያስቆረጠ ወደ ዋንጫው የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ቀጥሏል። ዛሬም ፋሲል ከነማ ሳይጫዎት ተፎካካሪዎቹ ነጥብ ጥለዋል።ዋንጫው ዘንድሮ ወደ ቤቱ ይገባል።የአሰልጣኝ ስዩም ከበደ ልጆች "አፄዎቹ" የማይረሳ ህያው ታሪክ ለመፃፍ ተቃርበዋል ። @Bdfaya
Показать все...
ለሚዲያ አካላት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ************ የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን ያለፉት ሁለት ጨዋታዎችን እና የአፍሪካ ዋንጫ ጉዞውን በተመለከተ ሰኞ መጋቢት 27/2013 ጋዜጣዊ መግለጫ ከቀኑ 8ሰዓት ወሎ ሰፈር በሚገኘው የፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት የተዘጋጀ ስለሆነ በቦታው ተገኝታችሁ ጥያቄያችሁን ማቅረብ ምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
Показать все...
#የፋሲል ከነማ ከክለብ በላይ 3ኛ ዙር ሩጫ በወልቃይት ጠገዴ ዳንሻ ከተማ በዛሬው እለት የተካሄደ ሲሆን በኢትዮጵያ በተለያዩ ቦታዎች ህይወታቸውን ላጡና በተጎዱ ወገኖቻችን የህሊና ፀሎት በማድረግ የተጀመረ ሲሆን ውድድሩም በሁመራ መውጫ ባለው ማደያ በመነሳት መጨረሻውን በጠገዴ መውጫ በሚገኘው ማደያ ላይ በሰላም ተጠናቋል። #ፋሲል ከነማ ከክለብ በላይ ነው
Показать все...
​​አቡበከር ናስር እውቅና ተሰጥቶታል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ የሆነው አቡበከር ናስር በቀድሞ የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋች ስጦታ ተበርክቶለታል። የዘንድሮ የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን እየመራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቡናው አጥቂ አቡበከር ናስር በሊጉ አልፎም በብሔራዊ ቡድኑ እያሳየ ባለው ብቃት በርካታ አድናቆቶችን እያገኘ ይገኛል። ከወራት በፊትም የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ የነበረው ዮርዳኖስ ዓባይ የተጫዋቹን ብቃት አድንቆ የማበረታች እና የአድናቆት መልዕክት ማስተላለፉ ይታወሳል። ዛሬ ደግሞ በኢትዮጵያ መድህን የእግር ኳስ ህይወቱን ጀምሮ በኢትዮጵያ ቡና፣ መከላከያ፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ወልዋሎ ዓ/ዩ የቀጠለው ሙሉዓለም ጥላሁን ለተጫዋቹ የማበረታቻ ሽልማት አበርክቶለታል። በአሁኑ ሰዓት በጀርመን የሚገኘው ሙሉዓለም ተጫዋቹ በዘንድሮ የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ባሳየው አቋም በትዕዛዝ ለአምስት ሳምንታት የቆየ እና ስሙ ከሚለብሰው ቁጥር ጋር የተፃበፈት የመጫወቻ ጫማ አዲስ አበባ በምትገኘው ተወካዩ ፀጋ ጥላሁን (እህቱ) አማካኝነት አበርክቶለታል። ከታኬታው በተጨማሪም በተለያዩ ቀለሞች የተመረቱ የመጫዎቻ ታይቶች እና የስፖርት ቦርሳዎች ለተጫዋቹ ተሰጥቷል። አመሻሽ አስር ሰዓት በተከናወነው ፕሮግራም አቡበከር ስጦታዎቹን ከተቀበለ በኋላ ደስተኛ መሆኑን ገልፆ ለመጀመሪያ ጊዜ በቀድሞ የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋች ለተበረከተለት ስጦታ ምስጋና አቅርቧል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን በተለያዩ የእድሜ እርከኖች የወከለው እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና 2003 የሊጉን ዋንጫ ሲያነሳ ቁልፍ ተጫዋች የነበረው ሙላለም ጥላሁንም ከዚህም በኋላ በኢትዮጵያ እየወጡ ላሉ ወጣት ተጫዋቾች የማበረቻቻ ሽልማት ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን እና ሌሎች የቀድሞ ተጫዋቾችም ይህንን አይነት ተግባር እንዲፈፅሙ እያስተባበረ መሆኑን ለሶከር ኢትዮጵያ ገልጿል። © ሶከር ኢትዮጵያ
Показать все...