cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

አሕዛብ ለምን ያጉረመርማሉ መዝ 2፤1

አሕዛብ ለምን ያጉረመርማሉ❓ 🔘መዝ ❷፤1 የሙስልሞችን እየአንዷዷን ጥያቀ እያብጠረጠርን እናያለን #ቻይናል_እንሆ_ብለናል_እንደ_ምትወዱት_ተስፋ_እናደርጋለን። ❶ኛ መጻሕፍቅዱስ እውነት ይጋጫልን❓ ❷ኛ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ አይደለምን❓ ➌ኛ ቁርኣን ከፈጣር የመጣ ቃል ነውን❓ ❹ቁርኣን ስለ ኢየሱስ አይመሰክርምን❓ ❺ማንኛውንም ጥያቀ እንመልሳለን የተዋህዶ ልጆች አለን እናተ አላችው❓ ሸር ያድርጉት

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
178
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

1,ሰው ከመጠመቁ በፊት ሐይማኖቱ ምንድን ነው ? 2,ሰው ሲፈጠር ሐይማኖቱ ምንድን ነው? ሁላችንም ከመጠመቃችን በፊት ሐይማኖታችን ኦርቶዶክስ ነው። ይህን ያልኩት እንዲሁ በደፈናው አይደለም ምክንያት አለኝ። # ኦርቶዶክስ ማለት ቃሉ የግሪክ ሲሆን አማርኛው ትርጉሙ እውነተኛ ፣ ቀጥተኛ መንገድ የሆነች ሃይማኖት ማለት ነው። ማስረጃ አለኝ ኤር 6÷16 " እግዚአብሔር እንዲህ ይላል በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደሆነች እወቁ በእርስዋም ላይ ሒዱ ለነፍሳችሁም መድሐኒት ታገኛላቹ" ይላል መንገድ ማለት ሐይማኖት ማለት ነው ማስረጃ ማቴ 7÷13 " በጠባቢቱ በር ግቡ ወደ ጥፋት የምትወስድ ሰፊ በር ሰፊ መንገድም አለችና ወደ እርስዋ የሚገቡ ብዙዎች ናቸው። ወደ ሕይወት የምትወስደው በር እጅግ ጠባብ መንገድዋም ቀጭን ናትና የሚገቡባትም ጥቂቶች ናቸው" ኤርሚያስ የቀደመችውን መንገድ ጠይቁ አለ በእርስዋ ለይም ተመላለሱ አለ ክርስቶስም መጣ ወደ ጠበበው ደጅ ግቡ አለ በጠበበው መንገድ ላይ ወደ ሕይወት የሚወስደው እርሱ ነው ግቡ አለ የጠበበው መንገድ የቱ ነው ብለህ ስትጠይቅ መልሱ ኦ....ር...ቶ...ዶ...ክ...ስ ነው ጥበቱንም ፆም ፣ ስግደት ፣ ቀኖና ፣ ንስሐ ፣ ስጋ ወደሙን መቀበል ፣ ቆሞ ማስቀደስ ፣ ፀበል መጠጣት ፣ መጠመቅ ........ እነዚህ ሁሉ የኦርቶዶክስን ደጅ ያጠቡታል። ሰፊው መንገድስ ካላችሁኝ እንደመንገዱ ስፋት ማንም የሚገባበትና የሚወጣበት የማይፆምበት፤ የማይሰገድበት የክርስቶስ ወዳጅ የሆኑ ቅዱሳንና ቅዱሳት የማይከበሩበት የክርስቶስ ስጋና ደሙ የማይፈተትበት ለአለባበስ፤ለአነጋገር እና ለአምልኮ ስርአት የሌላቸው ማንም ሰው እንደልብ የሚቦርቅበት የሚጨፍርበት............በአጠቃላይ ሉጋም የሌለበት መንገድ ሁሉ ሰፊው መንገድ ነው እላለው። ኦርቶዶክስ ግን ሉጋም አላት ይህም በፆም፦ ገና ፆም ይገባል ነፍሳችንን እያበረታን ስጋችንን እናደክማለን ከዚያም ይፈታል። ስጋ ሊበረታ ሲል እንደገና የነነዌ ፆም ይገባል ስጋችንን አድክመን ነፍሳችን እናበረታለን ይፈታል ስጋ አረፍኩ ሲል አብይ ፆም ይገባና ስጋችን 0 ይሆናል ነፍሳችን ትበረታለች ስጋ ሲዝል 50 ቀን ይፈልታ 50 ቀን ስጋችን ተደሰትኩ ሲል ሰኔ ፆም ይገልባል ስጋ ይደክማል እንዲ እንዲያ እያልን ስጋን እያደከምን ነፍሳችንን ወደ ገ....ነ....ት ስለዛ ጠባቧና እውነተኛዋ መንገድ ኦ......ር....ቶ....ዶ...ክ..ስ.....ናት ከአለም ሕዝብ እኛ ብቻ ልንፀድቅ ነው አላችሁ ? አዎና በደንብ ከአለም ሕዝብ እኮ 8 ሰው ብቻ ነው የዳነው በኖህ መርከብ እኛ ከ 8 አንበልጥም እንዴ በእርስዋ ላይ ቁሙ ብዙ ሰው አይፈልጋትም አለ ክርስቶስ ስማችን ኦርቶዶክስ ነው ክርስቲያን ስማችን አልነበረም ያወጣልን ጠላት ነው የሐዋ ሥራ 11÷26 "ደቀመዛሙርቱም መጀመሪያ በአንፆኪያ ክርስቲያን ተብለው ተጠሩ" የክርስቶስ ተከታዮች ናቸውና በክርስቶስ አማካይነት ክርስቲያን ሲሏቸው እነርሱም "ይህ ስም ተስማምቶናል" አሉ ሞትን አሸንፎ የተነሳው እርሱ ስለሆነ በእርሱ ስም መጠራት ፈለጉ በመጠራታቸውም አላፈሩም ህዝቡም ለማስታወስ እንዲመቻቸው በክርስቶስ አያያዙና ክርስቲያን አሏቸው ከዚያም ክርስቲያን መባል መጣ በክርስቶስ ክርስቲያን የተሰኛቹ የሚባለውም ለዚሁ ነው። ሥማችን ኦርቶዶክስ ነበር የቀደመችዋ ቀጥተኛዋ መንገድ ይቺ ቀጥተኛ መንገድ ከማን መጣች ኦርቶዶክስ የማን ሐይማኖት ናት ካልችሁኝ ደግሞ ከአዳም ጀምሮ የመጣው ሐይማኖት ኦርቶዶክስ ነው እላለው እንዴት አትሉኝም? ቆያ ላብራራላችሁ። ይኸውልህ ፦የአዳም ሐይማኖት ተጠምቆ መፈጠር ነው። ማስረጃው ዘፍ 1÷1 "በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ፈጠረ ምድርም ባዶ ነበረች አትታይም ነበር የተዘጋጀችም አልነበረችም ጨለማም በውሃ ላይ ነበር የእግዚአብሔርም መንፈስ በውሃ ላይ ይንሳፈፍ ነበር" ይላል ከውሃ ውስጥ የብሱ ይገለጥ ብሎ ምድርን ፈጠረ ( አፈርን ) ማለት ነው ከአፈር አዳምን ፈጠረ ከአዳም ሔዋንን ፈጠረ ከሔዋንና ከአዳም እኛ ተፈጠርን ሔዋን ከአዳም አዳም ከአፈር አፈር ከውሀ ያ ውሀ የእግዚአብሔር መንፈስ አለበት የአዳም አባት አፈር አያቱ ውሃ ያ ውሃ የእግዚአብሔር መንፈስ አለበት ስለዚያ አዳም በጥንት አያቱ ተጠምቆ የተፈጠረው የእግዚአብሔር መንፈስ ካለበት ውሃ ተዘፍቆ ተፈጠረ ። አይደለም አዳምና ሔዋን የሰው ዘር ቀርቶ ሰማይና ምድር ጭምር በውሃ ተጠምቀው ነው የተፈጠሩት የእግዚአብሔር መንፈስ ካለበት ውሃ። ምነው?ገረማችሁ? ልንገራችሁ 2ኛ ጴጥ 3÷5 ምን ይላል መሰላችሁ " ነገር ግን እነዚያ ሰዎች ሰማያት ከጥንት ጀምሮ በእግዚአብሔር ቃል ተፈጥረው እንደሚኖሩ መሬትም በውሃ መካከልና በውሃ እንደተሰራች ሆን ብለው ይክዳሉ" በዚያን ጊዜ የነበረው አለም በውሃ ሰጥሞ ጠፉ። በኖህ ዘመን የነበሩ ሰዎች ለምን ጠፉ? ቢባል ሰማይና ምድር ከውሃ እንደተፈጠሩ ሆን ብለው ይክዳሉ ስለዚህ ጠፉ በውሃው ጥምቀት ያመኑ ኖህና ቤተሰቦቹ ዳኑ በውሃው ጥምቀት ያላመኑ የኖህ ዘመን ሕዝቦች ጠፉ በውሃው ጥምቀት ያመኑት እስራኤል ዘስጋ ዳኑ በውሃው ጥምቀት ያላመኑት ፈርኦንና ሰራዊቱ ጠፉ 1ኛ ቆሮ 10÷1 መስረጃ "ወንድሞቻችን ሆይ አባቶቻችን ደመና እንደጋረዳቸው ሁሉም በባህር መካከል አልፈው እንደሔዱ ልታውቁ እወዳለሁ ሁሉንም ሙሴ በደመናና በባህር አጠመቃቸው " ስለዚህ አይደለም አዳምና ሔዋን ሰማይና ምድርም የእግዚአብሔር መንፈስ ካለበት ውሃ ተጠምቀው ነው የተፈጠሩት የአዳም ሐይማኖት የእግዚአብሔር መንፈስ ካለበት ውሃ ተጠምቆ መፈጠር ነው ። ያ ውሃ በሰይጣን ተበላሽቶ ተቋረጠ ከዛም ክርስቶስ መጣ ለ ኒቆዲሞስ እንዲህ አለው ዮሐ 3÷5 " እውነት እውነት እልሀለሁ ዳግመኛ ከውሃና ከመንፈስ ቅዱስ ያልተወለደ ሰው ወደ እግዚአብሔር መንግስት ሊገባ አይችልም" አለው። ያ የድሮ ውሃ ተበላሽቶ ክርስቶስ መጣና ያንን ውሃ ቀደሰው ስለዚህ ድጋሚ አዳም ከተወለደበት ውሃ ተወለዱ ከዛ ውሃ ያልተወለደ የእግዚአብሔርን መንግስትን አያይምምምምም ። ስለዚህ አሁን ኦርቶዶክሶች ስንጠመቅ በፊት አዳም ከተወለደበት ውሃ ተወልደናልና የእግዚአብሔርን የልጅነት ፀጋ ተቀብለን ወደ መንግስተ ሰማያት እንገባለንንንንንንን። የተጠመቀ የእግዚአብሔርን መንግስት ይወርሳል ያልተጠመቀ ደግሞ አይወርስም ይህንንንም ጌታ ነው ያለው እኛ የተዋህዶ ልጆች የተጠመቅን ነን መንግስቱ የኛ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተጠመቅን ብቻ ነው አርባ አራት ነጥብ። የተጠመቁ ብቻቻቻቻቻቻ።።።።። ክብር ለእግዚአብሔር ከእናቱ ከድንግል ማርያምና ከፃድቃን ከሰማእታት ከቅዱሳን መላእክት ጋር ይሁንልን አሜን፫ # ኦርቶዶክስ_ሃይማኖት_ለዘለአለም!!! @timhirte_tewahido ለተዋህዶ ልጆች ሸር ያድርጉ
Показать все...
And sew teweldo saytemek befit muslim nw christian
Показать все...
#አንዱ_ስለሁሉም_ሞቴ_። 2ኛቆሮ 5፥14 ጥቅምት 27''መዳኒዓለም''በንጹሕ ደሙ ያዳነን ከወደቅንበት ያነሳን እንኳን አደረሳችሁ #ዓለምን_ከፈጠረበት_ጥበብ_ይልቅ_አምላክ_ሰው_ሆኖ_ያዳነበት_ጥበቡ_ይበልጣል። የፍስካን በዓል እስራኤላውያን የምያከብሩት #ከ430 ዓመት ከግብፅ ባርነት የወጡበትን ቀን በማስመልከት የምያከብሩት በዐል ነው። ⏩ዘጸ ⓬፤42 በእዝያም በአል ሕዝቡ የወደዱትን አንድ እስረኛ ልፈታላችሁ በገዢው ዘንድ ልማድ ነበረ። ⏩ማቴ27፤15➚24 #በመስቀል_ላይ_ተሰቅሎ_የምሞት_የተረገመ_ከሆኔ_ለምን_ጌታችን_አምላካችን_መዳኒአለም_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ተሰቅሎ_ሞቴ❓ 🔜ዘዳ 21፤23 #ክርስቶስ_ሥለ_እኛ_እርግማን_ሁኖ_ከህግ_እርግማን_ዋጀን። ⏪ገላ❸፤⓭ 👉ለኀጢአት ሞትን ለጽድቅ እንድንኖር #እርሱ_ራሱ_በስጋው_ኃጢአታችንን_በእንጨት_ላይ_ተሸከመ_በመገረፍ_ቁስል_ተፈወሳችሁ። 📶❶ኛ ጴጥ❷፤24 #ወሳኝ/ማስተዋል ❶ኛ⏩ቅጣታችንን ተቀብሎ ሞቴ፦ 👉ኢሳ53፤6የሁላችንን በደል በራሱ ላይ አኖረ። ❷ኛ🔜የእኛን ሞት ሞቴ፦ 👉ሮሜ❺፤12፦⓯በአንድ ሰው ምክንያት ሞት ወደ አለም ገባ።በአዳም፣ ❸ኛ⏩ፈውስ እናገኝ ዘንድ፦ 👉ኢሳ53፤❺በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን። ❹⏩ገነትን እንወርስ ዘንድ መርገማችንን ወስዶ ሞቴ 👉ዘጸ21፤23በእንጨት የተሰቀለ የተረገመ ነው ተብሎ እንደ ተጻፈ። ❺⏩ሙታንን ያስነሳ ዘንድ ሞቴ፦ 👉ሮሜ14፤9ሥለዚህ ነገር ሙታንንም ሕያዋንንም ይገዛ ዘንድ ክርስቶስ ሞቶአልና ሕያውም ሁኖአልና። ❻⏩የዲያብሎስን ምክር ያፈርስ ዘንድ ሞቴ፦ 👉❶ኛቆሮ⓯፤56 ሞት ድል በመነሳት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈፀማል። 👆ኢሳ25፤8ሞት ለዘላለም ይዋጣል ጌታ እግዚአብሔር ከፍት ሁሉ እንባን ያብሳል የሕዝቡን ሥድብ ከምድር ሁሉ ያስወግዳል እግዚአብሔር ተናግሮአልና። #ወሳኝ_ትምርትች ❼አንዱ ስለ ሁላችን ምቴ #ምን_አገኘን❓ ✔ህይወትን አገኝተናታል። 🔼ሮሜ5፤12✔ስለዚህ ምክንያት ኀጥአት በአንድ ሰው ወደ አለም ገባ በኃጢአትም ሞት እንደዝው ሁሉ ኃጢአት ሥላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ። 🔽ዘፍ3፤1፦24✔❶እባብም እግዚአብሔር አምላክ ሰፈጠረው ከምድር አውረ ተንኮለኛ ነበረ''ሴትቱንም'' በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን❓አላት። 24አዳምንም አስወጣው ከገነት ህይወት የምወስደውንም መንገድ ለመጠበቅ #ኪሩቤልንና_የምትገለባበጥ_የነበልባል_ሰይፍን_በዔደን_ጌነት_ምስራቅ_አስቀመጠው። በአባታችን በአዳም ምክንያት ገነት በኪሩቤል ሰይፍ እንደ ተዘጋች ኦርት ይናገራል። ⏪ኤፌ2፤3፦5 በእነዝህም ልጅች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ የስጋችንን እና የልቦናችንን ፍቃድ እያደረግን በስጋችን ምኞት በፍት እንኖር ነበርን እንደ ሌሎችም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን። ❹ነገር ግን እግዚአብሔር በምህረቱ ባለ ጠጋ ሥለ ሆኔ። ❺ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነበሣ #በበደላችን_ሙታነ_እንኳን_በሆንን_ክርስቶስ_ጋር_ህይወትን_ሰጠን_በጸጋው_ድናችኋልና። ❽ #ሠላምን_አግኝተናል። 👉ኢሳ 65፤1 ላልጠየቁኝ ተገለጥሁ፦ላልፈለጉኝም ተገኘው፦በስሜም ያልተጠራውን ሕዝብ፦እነሆነኝ፥እነሆነኝ አልኹት። ⏩ኤፌ 2፤13 አሁን ግን እናተ በፍት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል። 14⏩ #እርሱ_ሰላማችን_ነውና፦ሁሉን ያዋሐደ በአዋጅ፦የተናገሩትንም የትዛዛትን ህግ ሽሮ በመካከል ያለውን #የጥል_ግድግዳን_በስጋው_ያፈረሰ_ሰላምን ያደርግ_ዘንድ። 16ጥልንም በመስቀሉ ገደሌ። #ክርስቶስ_ከራሱ_ጋር_አስታረቀን። 2ኛቆሮ5፥18 #በመስቀሉ_ደም_ሠላምን_አደለ ቆላ 1፤19፤20
Показать все...
#በመስቀሉ_ደም_ሠላምን_አደለ ቆላ 1፤19፤20 #❾_አዲስ_ሰው_ሁነናል። 📶2ኛቆሮ5፤17 ስለዝህ ማንም በክርስቶስ ብሆን አዲስ ፍጥረት ነው። 🔜ገላ6፤15 በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት መሆን ይጠቅማል። ⏩ሮሜ6፤4፦5እንዲሁም #እኛም_በአዲስ_ሕይወት_እንድንመላለስ፦ሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን። ❺ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን፤ ትንሣኤውን በሚመስል ትንሳኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን። #የነብዩ_ኢሳይያስን ምዕራፍ 53 ን ያንብቡት ⏩ኢሳይያስ 53፤1፤8 ¹ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል? ² በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል፤ መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም። ³ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም። ⁴ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። ⁵ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። ⁶ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ። ⁷ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። ⁸ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ? ⁹ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ፤ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም ነበር። ¹⁰ እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል። ¹¹ ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሸከማል። ¹² ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።
Показать все...
ቁርአኑ ለሴት ልጅ ያለው ቦታ እና መጽሐፍ ቅዱሱ ለሴት ልጅ የሰጠው ቦታ ⛔️ሼር ይፈልጋል⛔️ ክ.1 ሙስሊም ወገናውያን ሴቶችን በተመለከተ መጽሐፍ ቅዱሱ ክብራቸውን ዝቅ አድርገዋል መጽሐፉ ስለ ሴቶች ያለው አመለካከት ልክ አይደለም በማለት ጥቅስ ሲጠቅሱ እንመለከታለን። ያ ደግሞ ስለ መጽሐፉ ምንነት አለማወቅና አለመረዳት በተለይ ደግሞ እደዚህ አይነቶችን ጥቅስ ለሴቶች በማሳየት ሴቶች እህቶቻችንን ለመጽሐፍ ቅዱሱ ለየት ያለ አመለካከት እንዲኖራቸው ያደርጋሉ። በርግጥ ሙስሊሞች በተለይ ደግሞ ይሄን ነገር ለየት የሚያደርገው እንደዚህ አይነት ጥቅሶችን የሚደረድሩት የሙስሊም ሴቶች መሆናቸው ነው። ምክንያቱም የእነርሱ ቀርአን ስለ ሴት ልጅ ምን እንደሚል ስለማያውቁ እና ማወቅም ስለማይፈልጉ ዘለው ወደ መጽሐፍ ቅዱሱ በመግባት እህቶቻችንን ሲያስቱ እንመለከታለን። ጥያቄያቸው፦ እንዴት ከሴት ተወልዶ የሴትን ክብር ዝቅ ያደርጋል የሚል ጥያቄ ያነሳሉ። ይኼ ጥያቄ ለቀባሪው ሰው ማጣት ነው ሚሆነው። ምክኒያቱም የሴትን ክብር ዝቅ የሚያደርግ ቢሆን ኖሮ ከሴት ባልተወለደ ነበር። ነገር ግን በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሴት ልጅ የተጠቀሱት በተለይ ደግሞ በመጽሐፈ ሲራክ ላይ የተገለጡት በሰው ሰውኛ ስናስበው እውነት የሴት ልጅ ክብርን የጣሰ ይመስላል። ነገሮ ግን ጥቅሱን በጥሞና እና በአንክሮ ስንመለከተው ከሐሰት የራቀ እውነት መሆኑን እናገኘዋለን። እስኪ በቁርአኑ ለሴት ልጅ ያለው ቦታ እንመልከትና ሙስሊሞች በመጽሐፋችን ስለ ሴት ልጅ የተሳሳተ መረጃ ብለው የተጠቀሱትን በዝርዝር እንመለከተዋለን። ባሎች በሚስቶቻቸው ላይ ብልጫ አላቸው፡- 2፡228 “… ለነርሱም (ሴቶች) የዚያ በነሱ ላይ ያለባቸው (ግዳጅ) ብጤ በመልካም አኗኗር (በባሎቻቸው ላይ መብት) አላቸው፡፡ ለወንዶችም (ጣጣቸውን ስለሚሸከሙ) በነሱ ላይ ብልጫ አላቸው፡፡ አላህ አሸናፊ ጥበበኛ ነው፡፡” በዚህ ስፍራ ላይ “ጣጣቸውን ስለሚሸከሙ” የሚለው ንግግር በአረቢኛው ቁርኣን ውስጥ የሌለ ሲሆን በተርጓሚዎቹ የተጨመረ ማብራራርያ ነው፡፡ ይህንንም ሀሳብ በመጨመር ይህ ጥቅስ ሊያስከትላቸው የሚችላቸውን ችግሮች ለመቀነስ ሞክረዋል፡፡ ይህ እንዲያውም ችግሩን ያከረዋል እንጂ በፍፁም አያለዝበውም፡፡ “ጣጣ” የተባለው ባሎች ለሚስቶቻቸው የሚያወጡት ወጪ ከሆነ በእጅጉ ያስገርማል፡፡ እውነተኛው አምላክ በእንዲህ ዓይነት እንቶ ፈንቶ ምክንያቶች ላይ ተመስርቶ ደረጃ የሚመድብ አምላክ አይደለም፡፡ በብዙ ማሕበረሰቦች ውስጥ እንዲያውም ከወንዶች ይልቅ ብዙ “ጣጣ” የሚሸከሙት ሴቶች በመሆናቸው በዚህ ደረጃ እንመድብ ከተባለ የበላይነቱ የሚገባው ለሴቶች እንጂ ለወንዶች አይደለም፡። ሴቶች ለባሎቻቸው እርሻ ስለሆኑ በፈለጉበት ሁኔታ “ሊደርሷቸው” ይችላሉ 2፡223 “ሴቶቻችሁ ለናንተ እርሻ ናቸው፡፡ እርሻችሁን በፈለጋችሁት ሁኔታ ድረሱ” ጋብቻ ክቡር መኝታውም ቅዱስ መሆኑ እሙንና ቅቡል ነው፡፡ ታድያ ይህ ሊሆን የሚችለው የሴቷም ፍላጐትና ስሜት ጭምር ከተጠበቀ ብቻ ነው፡፡ ባል ሚስቱን እንደ ግል እርሻው በመቁጠር በፈለገው ሁኔታ ልድረስ ቢል በሴቷ ስነ ልቦና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል፡፡ ሴቶችን ከእርሻ ጋር ማመሳሰልና “በፈለጋችሁት ሁኔታ ድረሱ” የሚለው አባባል ለሰው ህሊና ተቀባይነት ያለው አይደለም፡። ባሎች ሚስቶቻቸውን በመምታት መቅጣት ይችላሉ ፡- 4፡34 “እነዚያም ማመጣቸውን የምትፈሩትን ገስፁዋቸው በመኝታዎችም ተለዩዋቸው (ሳካ ሳታደርሱ) ምቱዋቸውም፡፡ ቢታዘዟችሁም (ለመጨቆን) በነርሱ ላይ መንገድን አትፈልጉ አላህ የበላይ ታላቅ ነውና፡፡” አሁንም እንደተለመደው የቁርኣን ተርጓሚዎች ቃላትን በቅንፍ ውስጥ በመጨማመር የመጽሐፋቸውን ገመና ለመሸፈን ሞክረዋል፡፡ “ሳካ ሳታደርሱ (አካላዊ ጉደት ሳታደርሱ)” የሚለውን ሀሳብ መጨመራቸው “ምቱዋቸው” የሚለው የቁርኣን ትዕዛዝ ከህሊናቸው ጋር ግጭትን እንደፈጠረ ያሳያል፡፡ በትዕግስትና በፍቅር መምከር እየተቻለ መደብደብ ለምን ያስፈልጋል? ምድራዊ መንግሥታት እንኳ ሚስቶችን መምታት ጎልዳፋ ተግባር መሆኑን በመገንዘብ የዜጎቻቸውን መብት የሚያስከብሩ ህግጋትን አውጥተዋል፡፡ ሴትን ልጅ መምታት ኢ-ሞራላዊ የሆነ ኋላ ቀር ተግባር ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ ትዕዛዝ ሊመነጭ የሚችለው ለሴት ልጅ ዝቅተኛ ግምት ካለው አዕምሮ እንጂ ቅዱስ ከሆነው አምላክ ዘንድ ከቶ ሊሆን አይችልም፡፡ ማንም ሰብኣዊነት የሚሰማው ሰው እንዲህ አይነቱን ጎጂ ልማድ መቃወምና መታገል ይኖርበታል፡፡ በገነት ውስጥ ለሙስሊም ወንዶች የስሜት ማርኪያ እንዲሆኑ የተፈጠሩ ሴት ፍጥረታት ይገኛሉ ፡- 78፡30-33 “ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡ አትክልቶችና ወይኖችም፡፡ እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡ የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡” 44፡51-54 “ጥንቁቆቹ በእርግጥ በጸጥተኛ መኖሪያ ውስጥ ናቸው፡፡ በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡ ፊት ለፊት የተቅጣጩ ኾነው ከስስ ሐርና ከወፍራም ሐር ይለብሳሉ፡፡ (ነገሩ) እንደዚሁ ነው፤ ዓይናማዎች የኾኑን ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡” 56፡34-36 “ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡ እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡ ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡ ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡” አንድ ሙስሊም ወንድ በገነት ውስጥ የ100 ወንዶች ጉልበት እንደሚያገኝ ቲርሚዚ መዘገቡን ሚሽካት አል መሳቢህ የተሰኘው የሐዲሳት ስብስብ መጽሐፍ ይጠቅሳል። ይቀጥላል... #ሼር_በማድረግ_ቁርአኑ_ለሙስሊም_እህቶቻችን_እንዴት_ቦታ_እንደሰጣቸው_እናሳያቸው!! @tiyakena_meliss
Показать все...
እኔ ለእስልምና ጥላቻ ኖሮኝ አያውቅም!! ሙስሊሞች ሆይ እወዳችዋለው አልጠላችሁም ግን በሀሳብ እሞግታለው እና ክርስቶስ ከኔ በላይ ይወዳችዋል ኑ ወደ ክርስትና ኑ ወደ ክርስቶስ ኑ ሸክማችሁን ያቀልላችዋል እሱ የሰላም አምላክ ነው። እሱ የፍቅር አምላክ ነው...
Показать все...
👉ሰው ሲወለድ ሙስሊም ነበር ወይ? በውስጥ መስመር ተደጋግመው የመጡልኝን ጥያቄዎች ወደ ቻናል አወጣቸዋለው ✍ወደ መልሱ እንሂድ እና ብዙ ግዜ ሙስሊም ወገኖቻችን ለቅጥፈታቸው እንደመረጃ አድርገው ከሚያቀርቡት የሞኝ ፍልስፍና አንዱ ይህ ነው ሰው ሲወለድ ሙስሊም ነው በማለት ብዙ ግዜ ሲናገሩ ይደመጣሉ። ነገር ግን እስልምና የተመሰረተው የዛሬ 1400 በአረብ ሰው ነው እሱ ራሱ በቁርአኑ ላይ እኔ የእስልምና መስራች ነኝ ብሎል ሱረት አል አንዓም 6:14 ሱረት አል አንዓም 6:163 ሱረት አል ዘሙር 39:12 የመጀመርያ ሙስሊም እንድ ሆን ታዘዝኩ ስለዚህ በዚህ የቁርአን ማስረጃዎች የእስልምና መስራችና ጀማሪ መሀመድ የአረብ ሰው የግመል እረኛ ኢቢን አሚና ነው ስለዚ ሙሀመድ እስልምናን ከመቀበሉ በፊት እስልምና የሚባል ታሪክ የለም ይሄ ፍልስፍናቸው ፉርሽ ይሆናል። ✍እኛ ግን መልሳችን ሰው ሲወለድ ሙስሊም አይደለም አንድ ሰው ሙስሊም የሚባለው አላህን አምላክ መሀመድን ነቢይ ብሎ ካመነና ከተቀበለ በኋላ ነው ይህን ያላደረገ ማንኛውም ሰው ሙስሊም አይባልም ሰው ሙስሊም የሚባለው ባለመጠመቁ ከሆነማ እኮ በአለም ላይ ሳይጠመቁ የየራሳቸው የእምነት ድርጅት መስርተው የሚኖሩ ብዙ አሉ ለምሳሌ ያህል በህንድና በቻይና ሀገር ያሉ ሰዎችን መመልከት ብቻ በቂ ነው። ታድያ ? ስላልተጠመቁ ብቻ ሙስሊም የሚያስብላቸው ከሆነ? እነዚህ ህዝቦች ሙስሊሞች ናቸውን?? አይደሉም ለምን ይዋሻል? በብሉይ ኪዳን ዘመን እስራኤላውያን ጥምቀት በ40 ናበ80፡ቀናቸው አልነበራቸውም ግን? እስራኤላውያን ሙስሊሞች ነበሩን? አልነበሩም ታድያ ለምን ሙስሊም ወገኖቻችን ይዋሻሉ? እስራኤል ከአህዛብ የሚለዩበት በዘመነ ብሉይ ግዝረት ነበራቸው የአብርሃም ልጆች ለመሆናቸው በተወለዱ በስምንተኛው ቀን ይገረዙ ነበር ያ ግዝረት ደግሞ በሐዲስ ኪዳን በጥምቀት ተተክቷል ክርስቶስ ተጠምቆ እኛንም እንድንጠመቅ አዝዞናል፡ማር፡16:16 ከአብርሃም በተቀበሉበት ሥርአት መሰረት እስራኤላውያን በመገረዝ እራሳቸውን ከአህዛብነት ለይተው የአብርሃም የጽድቅ ልጆች የተስፋው ወራሾች ተብለው እንደተጠሩት ሁሉ እኛም ዛሬ በክርስቶስ ክርስቲያን ተብለን የተጠራን በሙሉ የክርስቶስ ለመሆናችንና ፍፁም ድህነት አግንተን የመንግስቱ ወራሾች ለመሆን እንጠመቃለን እንጂ ገና ክርስትናን በጥምቀት ለመጀመር አይደለም የክርስቲያን ልጅ ክርስቲያን ነው የሙስሊም ልጅም ሙስሊም ነው። አንድ ሙስሊም ከርስቲያን ለመሆን አብርሃም እራሱን ለእግዚአብሔር ከለየ በኋላ እንደተገረዘ ሁሉ እርሱም ለክርስቶስ ለመሆኑ ማህተሙ ጥምቀት ነው መጠመቅ ያስፈልገዋል ሳይጠመቅ ድህነት ሊያገኝ የመንግሥቱ ወራሽ ሊሆን አይችልም። ስለዚህ ሰው የሚጠመቀው ክርስቲያን ለመሆን ሳይሆን ለመዳን ነው የመዳን መንገድ አንዱ ክርስተቶስ ኢየሱስ የባህርይ አምላክ እንደሆነ አምኖ መጠመቅ ነው። መጠመቅ በራሱ ክርስቶስ አምላክ ወልደ አምላክ መሆኑን መመስከር ነው። ይህን ለመመስከር ደግሞ የግድ መጠመቅ ያስፈልጋል አንድ አምላክ በሆነው በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ማቴ፡28:19 በመጨረሻም ተራ ተረት ተረት ወደሆነው ወደ ሙስሊም ወገኖቻችን ሀሳብ ስንሄድ እንኳን ሰው ሲወለድ ሙስሊም መሆን አይደለም ሰው ሲፈጠር የተፈጠረው ከተጠመቀ ዐፈር ነው እንዲሁም የእግዚአብሔር መንፈስ ሰፎ ከነበረበት ውሃም ጭምር ምክንያቱም መጽሐፍ እንዲህ ይላልና (ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 1) ---------- 1፤ በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ። 2፤ ምድርም ባዶ ነበረች፥ አንዳችም አልነበረባትም፤ ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ በውኃ ላይ ሰፍፎ ነበር። ስለዚህ የሙስሊሞች ተረት ተረት ምንም ከተረትነትና ከሞኝነት ፍልስፍና ያለፈ ነገር ቁምነገር የለውም። ይህን መልስ ለ 30 ወዳጆ ማጋራት አይዘንጉ መልካም ቀን share👇join👇share @tiyakenaMels
Показать все...
ጳውሎስ አስከትሎም እንድህ ይለናል " ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት #ይገዛል።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:28) ተወዳጆች የወልድ ለአብ መገዛት ምንድነው? እስኪ ንገሩኝ ? ተወዳጆች ትልቁ መታዘዝ እና መገዛት የባሪያን መልክ መውሰዱ ነው ። እርሱ ልጅ እና መለኮታዊ አካል ነው ስለዚህ ይታዘዛል ። እንደኛ አይነት መታዘዝ ሳይሆን ይልቁንስ በልግልጽ እንደሚሠራና ሁሉንም ሥልጣን እንዳለው ሁሉን ወራሽ እንደሆነ ልጅ አለበለዚያማ እንዴት አብሮ ዙፋን ላይ ይቀመጣል ስለዚህ ተወዳጆች የወልድ ለአብ መገዛት ይሄ ነው ። የጳውሎስ ሃሳብ ምንድነው ስለመለኮቱ ብቻ ከተናገረ በኃላ በሌላ መንገድ ደግሞ የተዋሐደውን ሥጋ ሲያስብ እሱን የሚያወርዱትን ቃላት ሁላ ይጠቀማል ያለፍርሃት ። እንግድህ ንግግሩ በቀላሉ ስለአምላክነቱ መሆኑ ወይም በተዋሕዶ ሥጋው የሚነገረው ሁሉ ለእርሱ እንደሚያረጋግጥ እንመልከት (ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች ምዕ. 2) ---------- 6፤ እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥ 7፤ ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ 8፤ በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ። 9፤ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ ስለመለኮቱ ሲናገር እነዚህ ታላቅ ነገሮችን እንደተናገረ አየ እርሱም በአምላክ መልክ እንዳለ እና ከወለደውም ጋር እኩል መሆኑን እንደገናም ሥጋ የለበሰበትን ጊዜ ሲያስብ ደግሞ እንደገና ንግግሩን አወረደ በተነገሩት መካከል ትልቅ ልዩነት አለና ። ከአምላክ ጋር እኩል ከሆነ ያለልክ እንደት ከፍ ከፍ አደረገው? በእግዚአብሔር መልክ ከሆነስ እንዴት ስም ሰጠው ? የሚሰጥ ለሌለው ይሰጣልና ፣ከፍ ከፍ የሚያደርገውም የተዋረደውን ከፍ ከፍ ያደርልና ። ነገር ግን ሥጋ መልበሱን መጨመር ካለበው እነዚህ ነገሮችን በመናገረዎ አይሳሳቱም ምክንያቱም ሥጋ አምላክነትን አግናቷልና ሥጋ ከቃል ጋር ተዋሕዶ ኢየሱስ የሚለውን ስም አግኝቷል እና እርሱም መድኃኒት ማለት ነው መድኃኒት ያልነበረው ሥጋ መድኃኒት ሁኗልና ተወዳጆች ጌታ ኢየሱስ እራሱ " ሁልጊዜም እንድትሰማኝ አወቅሁ፤ ነገር ግን አንተ እንደ ላክኸኝ ያምኑ ዘንድ በዚህ ዙሪያ ስለ ቆሙት ሕዝብ ተናገርሁ አለ።" (የዮሐንስ ወንጌል 11:42) እንዳለ እንድሁም " ለአብ ያለው ሁሉ የእኔ ነው፤ ስለዚህ። ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋል አልሁ።" (የዮሐንስ ወንጌል 16:15) (የዮሐንስ ወንጌል ምዕ. 5) ---------- 21፤ አብ ሙታንን እንደሚያነሣ ሕይወትም እንደሚሰጣቸው፥ እንዲሁ ወልድ ደግሞ ለሚወዳቸው ሕይወትን ይሰጣቸዋል። 22-23፤ ሰዎች ሁሉ አብን እንደሚያከብሩት ወልድን ያከብሩት ዘንድ፥ ፍርድን ሁሉ ለወልድ ሰጠው እንጂ አብ በአንድ ሰው ስንኳ አይፈርድም። ወልድን የማያከብር የላከውን አብን አያከብርም። እንዳለ ተወዳጆች ሥጋ ከቃል ጋር በተዋሐደ ግዜ ልጅነትን አገኘ ሥጋ በቃል ከአብ ዘንድ አንተ ልጅነህ በባልን ገንዘብ አደረግ ልጅ እንደመሆኑም መጠን ፍርድ ሁሉ ተሰጠው ልጅ እንደመሆኑ መጠን ሁሉን ወራሽ ሆነ አንድያ ልጅ እንደመሆኑ መጠን የአብ የሆነው ሁሉ የእርሱ ሆነ ተወዳጆች ታድያ ይሄን ከያዝን ጳውሎስ በዚያን ግዜ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል ማለት ምን ማለት ነው ስንል በዳግም ምጻት ጊዜ ከአባቱ የተቀበለውን የመፍረድ ሥልጣን በለበሰው ሥጋ መተግበር ነው ተወዳጆች ጳውሎስ ልጁ ራሱ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል ሲል የወልድን አምላክነት አንድያ ልጅ መሆኑን የሚያስረዳ እንጅ እሱን ዝቅ የሚያደርገው አይደለም ሁሉን ላስገዛለት ሲልም ፍርድን ሁሉ የሱ የሆነውን ገንዘብ ሁሉ በመስጠት በሁሉ ላይ ፈራጅ ስላደረገው እንጅ ተወዳጆች አንድ ምሳሌ ልስጣቹ አንድ ንጉሥ አንድ ብቸኛ ልጅ ቢኖረው አባቱም ልጁን በዙፋኑ ላይ አስቀምጦ ቢያነግሠው አባቱ ሁሉን ነገር ለልጁ አላስገዛለትምን? አስገዝቶለታል እንጅ ልጁስ ከአባቱ የተቀበለውን ሥልጣን እሽ ብሎ የአባቱን ሥልጣን በፈጽም ልጅ ለአባቱ አልታዘዘምን አልተገዛምንስ? ተወዳጆች ልጁ ከአባቱ ተቀብሎ የአባቱን ትዛዝ በፈጸሙ ልጅ ለአባቱ ታዟል አባትም ልጁ በዙፋኑ ላይ ማስቀመጡና መሾሙ ልጁን ከፍ ከፍ አደረገው እንጅ ዝቅ አላደረገውም ከእርሱ ጋር እኩል አደረገው እንጅ አላሳነሰውም ተወዳጆች የወልድም ለአብ መገዛት እንድሁ ነው ሥጋ ቃልን ሲዋሐድ የአብን ልጅነት ስላገኘ አንድያም ልጅ ስለሆነ ከአብ ዘንድ ያለውን ሁሉ ገንዘቡ አድርጓል ፍርድን ንግሥናን ሁሉ የራሱ አድርጓል ስለዚህም በዚህ በተቀበለው ሥልጣን በደግም ምጻት ግዜ ከአባቱ የተቀበለውን የመፍረድ ስልጣን ስተገብር ለወልድ ለአብ መገዛት ይሄ ነው በለበሠው ሥጋ መፍረድ ይገዛል ተብሎ ተነገረለት ተወዳጆች ሥጋ ምን ይኃል ከፍ ከፍ እንዳለ አያችሁ ጳውሎስም ያለልክ ከፍ ከፍ አደረገው ያለው ይሄን ነው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር ይቆየን ሼር አድርጉ ተወዳጆች https://telegram.me/tewahido_ortho
Показать все...
✥መ/ር ምህረተአብ አሰፋ ፔጅ✣

ውድ የቻይናላችን ተከታዮች በሙሉ የምለቀቀውን ሸር እያደረጋችሁ ለወዳጅ በማድረስ የድርሻውን ይወጡ #የማንቂያ_ደውል በቴሌግራም እስኪ ጀምር። #እግዚአብሔር_እንድ_ይላል በመንገደ ላይ ቁሙ ተመልከቱም #የቀደመችውንም_መንገድ_ጠይቁ #መልካምቱ_መንገድ_ወዴት_እንደ_ሆነች_እወቁ ለነፍሳችሁ ዕረፍት ታገኛላችሁ #እነርሱ_ግን_አንሄድባትም_አሉ። ✥ት/ኤር 6፤16 ⏩በየ እለቱ ሙሉ ትምህርት ያገኙበታል

📖" ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት #ይገዛል።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:28) 💧ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል ሲል ምን ማለት ነው? ተወዳጆች ይሄ ቃል ገና ወደፊት የሚፈጸም እንጅ ያለፈ ታሪክ አይደለም ጳውሎስ በዚያን ግዜ ልጁ ራሱ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል በማለት ገና ያልተፈጸመ እንደው ይነግረናል ጳውሎስ ደግሞ እየተናገረ ያለው ጌታ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኃላ ነው እና ይሄን ጌታ ለሞት ይገዛል ብለን ከተረጎምንው ኢየሱስ አልሞተም ገና ወደፊት ይሞታል ወደሚል ስህተት ትምህርት እንሄድ አለን በእርግጥ ይሄን ቃል "ገ" ጠብቆ እና ላልቶ ሲነበብ ሁለት አይነት ትርጉም ነው ያለው በአማርኛው ቢሆንም ግን በሌሎች ቋንቋ ስናረጋግጥ "ገ" ጠብቆ መነበብ እንዳለበት እንረዳለን ላልቶ የሚነበብ ቢሆን ወልድ ለሞት ይገዛል ብለን ሳይሆን ሞት ለወልድ ይገዛል ብለን እንተረጉመው ነበር ግን እንደዚያ አይደለም ከአውዱም ጋር ሲንሄድ የማያስኬደን ሁኖ እናገኘው አለን 💦የጳውሎስ ንግግር ስለትንሣኤ ሙታን ነው ለቆሮንቶስ ሰዎች እሱ በሚጽፍላቸው ግዜ ትንሳኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዎች ነበሩ ጳውሎስም ከሚያምኑ ሰዎች ምስክርነት እየጠራ " ክርስቶስ ከሙታን እንደ ተነሣ የሚሰበክ ከሆነ ግን ከእናንተ አንዳንዶቹ። ትንሣኤ ሙታን የለም እንዴት ይላሉ?" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:12) በማለት ይጠይቃቸዋል ትንሣኤ ሙታን እንደሌለ የሚናገሩትን ለማሣመን እነሱ ባመኑት ከክርስቶስ ትንሣኤ በመጀመር " ትንሣኤ ሙታንስ ከሌለ ክርስቶስ አልተነሣማ፤" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:13) በማለት ያስረዳቸዋል ።ጳውሎስ የክርስቶስ ትንሣኤ ለሰዎች ትንሣኤ ውጤት መሆኑን በመግለጽ ሙታን የማይነሱ ከሆነ ክርስቶስ ተነሥቷል ማለታቸው ሐሰተኞች የሐሰት ምስክሮቹ እንደሚያደርጋቸው ይነግራቸዋል ክርስቶስ ተነሥቷል ብለው መመስከራቸውን እየነገረ " ሙታን የማይነሡ ከሆነ ክርስቶስ አልተነሣማ፤" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:16) " ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት፤ እስከ አሁን ድረስ በኃጢአታችሁ አላችሁ።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:17)በማለት ያስረዳቸዋል አስቀጥሎም " አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:20) በማለት በሰው በኩል የመጣ ሞት በሰው በሆነው ክርስቶስ እንደቀረ ይነግራቸዋል (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 15) ---------- 21፤ ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና። 22፤ ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና። በማለት እንድህ እያለ ከሄደ በኃላ የዓለም ፍጻሜ እንደት እንደሚሆን ሲነግራቸው እንድህ ይላል 📖" በኋላም፥ መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ አለቅነትንም ሁሉና ሥልጣንን ሁሉ ኃይልንም በሻረ ጊዜ፥ ፍጻሜ ይሆናል።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:24) ተወዳጆች መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ግዜ ይላል ምን ማለት ነው? መንግሥቱ የተባለችው የአማኞች ቤተክርስቲያን ናት እና የተመረጡት ጉባኤ ያለባት ; እግዚአብሔር አሁን እንደ ነገሠበት አይደለም ፤ እግዚአብሔር አሁን አልገዛም ብሎ ሳይሆን ክርስቶስ " ደግሞም። እንኋት በዚህ ወይም። እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።" (የሉቃስ ወንጌል 17:21) ይላል። 💧ነገር ግን ኃጢያት፣ክፋት፣ሞት ሥልጣን ነበረው ምክንያቱም ሰይጣን ሰዎችን ያጠቃ ነበርና ። ስለዚህም አለቅነትንም ሁሉና ሥልጣንን ኃይልንም በሻረ ግዜ ፍጻሜ ይሆናል አለ በሌላ አገላለጽ በሌላ አገላለጽ ሥጋ ከቃል ጋር ሲዋሐድ የአብን ልጅነት እንደማግኘቱ መጠን ልጅ ከአባቱ አደራ እንደሚቀበል ቤተ ክርስቲያን ተቀብሏል ጌታ ኢየሱስ እንድህ እንዳለ " ከዚህም በኋላ በዓለም አይደለሁም፥ እነርሱም በዓለም ናቸው፥ እኔም ወደ አንተ እመጣለሁ። ቅዱስ አባት ሆይ፥ እነዚህን የሰጠኸኝን እንደ እኛ አንድ እንዲሆኑ በስምህ ጠብቃቸው።" (የዮሐንስ ወንጌል 17:11) ስለዚህም ጳውሎስ መንግሥቱን ባስረከበ ግዜ ፍጻሜ ይሆናል አለ ልጁ ከአባቱ የተቀበላቸውን በደሙ ቀድሶ ንጹህ አድርጎ ያስረክባልና በአባቱ እና በሱ እና በመንፈስ ቅዱስ በአንድቷ ፍቃድ በገዛ ደሙ ገንዘቡ አድርጓታልና የዲያብሎስን ኃይል አገዛዝ ሲያጠፋ ከእንግድህ የእግዚአብሔር መንግሥት የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን ማጥቃት አይችሉም የዚያኔ መንግስቱ የተባለች ቤተ ክርስቲያን ለአባቱ ያስረክባል የዝያኔ ፍጻሜ ይሆናል ሲለን ነው ይቀጥል እና ጳውሎስ እንድህ ይላል " ጠላቶቹን ሁሉ ከእግሩ በታች እስኪያደርግ ድረስ ሊነግሥ ይገባዋልና።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:25) ምን ማለት ነው ተወዳጆች ከዚያ በኃላ አይነግሥም ማለት ነው? አይደለም ይልቁንስ አጋንንትን እና ክፉዎችን ሁሉ ከእሱ በታች እስኪያደርግ ድረስ ቤተ ክርስቲያንን መምራት እንዳለበት በቤተ ክርስቲያን ላይ ሊነግሥ እንደሚገባው ሲነግረን ነው ማለትም በእያንዳንዱ ሰው ልብ ውስጥ መንግሥ የሚገባው ጠላቶቹን ድል እስከሚያደርግ እና ከእግሩ በታች እስኪያደርግ መሆን እንዳለበት እንጅ ድል ካደረገ በኃላም ሁሌ እንደሚነግሥ ጥርጥር እንደሌለው ሲነግረን ነው እንድህ ካለ በኃላ " የኋለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው፤" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:26)በማለት ይነግረናል። እንድህ እያለ ከሄደ በኃላ ጳውሎስ እንድህ ይለናል " ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቶአልና። ነገር ግን። ሁሉ ተገዝቶአል ሲል፥ ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:27) ተወዳጆች ጳውሎስ ሊነግረን የፈለገው ምንድነው " ይላል፤ ስለ ልጁ ግን። አምላክ ሆይ፥ ዙፋንህ እስከ ዘላለም ድረስ ይኖራል፤ የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው።" (ወደ ዕብራውያን 1:8) " ይላል። ደግሞ። ጌታ ሆይ፥ አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ፥ ሰማዮችም የእጆችህ ሥራ ናቸው፤" (ወደ ዕብራውያን 1:10) " እንደ መጎናጸፊያም ትጠቀልላቸዋለህ ይለወጡማል፤ አንተ ግን አንተ ነህ፥ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም" (ወደ ዕብራውያን 1:12) ብሎናል " እርሱም ሁሉን እንኳ ለራሱ ሊያስገዛ እንደሚችልበት አሠራር፥ ክቡር ሥጋውን እንዲመስል የተዋረደውን ሥጋችንን ይለውጣል። " (ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 3:21) በማለት የነገረን ጳውሎስ ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጽ ነው ይለናል ጳውሎስ ሁሉን ለራሱ ሊያስገዛ እንደሚችል ነግሮን ሲያበቃ ሁሉን ካስገዛለት በቀር ሲል ምን ማለቱ ነው? ሁሉን እንደመጎናጽፊያ እንደሚጠቀልላቸው የነገረን ጳውሎስ ዓመቶቹም ከቶ እንደማያልቁ የነገረን ጳውሎስ ምን ማለት ፈልጎ ነው ተወዳጆች ጳውሎስ ሊነግረን የፈለገው እነዚህን ጥቅሶች ሲጠቅስልን ወልድ ከአብ ይበልጣል ብለን እንዳናስብ በሥልጣን አንድ መሆናቸውን ሊነግረን ሲፈልግ የተዋሐደውን ሥጋ መሠረት አድርጎ ይነግረናል አብ ይበልጣል እንዳንል ደግሞ ወልድ በሁሉ ላይ ሥልጣን እንዳለው ይንግረናል ስለዚህ የጳውሎስ ዓላማ በአባቱና እና በልጁ በአንድት ሥልጣን ሥጋን እንዳከበሩት መናገር ነው። 🙏ወስብሐት ለእግዚአብሔር #ሸር ያድርጉት የአሕዛብ ጥያቀ ነበረ እንሆ መልሱ #ይቀጥላል https://telegram.me/tewahido_ortho
Показать все...
✥መ/ር ምህረተአብ አሰፋ ፔጅ✣

ውድ የቻይናላችን ተከታዮች በሙሉ የምለቀቀውን ሸር እያደረጋችሁ ለወዳጅ በማድረስ የድርሻውን ይወጡ #የማንቂያ_ደውል በቴሌግራም እስኪ ጀምር። #እግዚአብሔር_እንድ_ይላል በመንገደ ላይ ቁሙ ተመልከቱም #የቀደመችውንም_መንገድ_ጠይቁ #መልካምቱ_መንገድ_ወዴት_እንደ_ሆነች_እወቁ ለነፍሳችሁ ዕረፍት ታገኛላችሁ #እነርሱ_ግን_አንሄድባትም_አሉ። ✥ት/ኤር 6፤16 ⏩በየ እለቱ ሙሉ ትምህርት ያገኙበታል

Показать все...
ቤተ-ክርስቲያን ሆይ ደጆችሽ አይዘጉ ༒

👉ጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በደሙ የዋጃት ቤዛም የሆናት ቅድስት ቤተ ክርስትያንን ከአጽራረ ቤተ ክርስትያን ለመጠበቅ የራሱን ድርሻ ለመወጣት የሚተጋ ቻናል ነው። ✥✥✥✥✥join @Geb19 ✥✥✥✥✥ 👇ለአስተያየትዎ 📧 contact me @efr21 or @GEB19bot ልብ እንበል እናታች እንኳን የማትቀይረን ሞት ከፊታችን አለ🛌

Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.