MKC_Official
Открыть в Telegram
3 003
Подписчики
+224 часа
-57 дней
+1030 день
Архив постов
3 002
በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ #የቡራዩ ወልመራ ስነመለኮት ኮሌጅ #ለ4ኛ_ዙር ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።
በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ የቡራዩ ወልመራ ስነመለኮት ኮሌጅ 40 በድግሪና 29 በዲፕሎማ ደረጃ ያሰለጠናቸውን 69 ተማሪዎች ለ4ኛ ጊዜ በዛሬው እለት በሆለታ 44 አጥቢያ በድምቀት አስመርቋል።
በዲፕሎማ ደረጃ ከተመረቁት 29 ተማሪዎች ውስጥ 24 ምሩቃን በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሆለታ 44 አጥቢያ በሚገኘው የአጥቢያዋ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት የተማሩ ናቸው።
በምረቃ መርሐግብሩ ላይ የተገኙት የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ ፕሪንሲፓል መጋቢ ጊሹ ጀቤቻ "እግዚአብሔር ጸሎት ይሰማል" በሚል ርዕስ የእግዚአብሔርን ቃል ከኢሳያስ 38፥1-6 ያካፈሉ ሲሆን በፕሮግራሙ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ቀጣና ሰብሳቢ መጋቢ ተፈራ መከታ፣ የቡራዩ ወልመራ ክልል ሰብሳቢ ወንድም አንዷለም ተፈራ እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ የክልልና አጥቢያ መሪዎችና አገልጋዮች ተገኝተዋል።
በዕለቱ የተገኙት የክብር እንግዶች ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ሲያስተላልፉ በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተመራቂ ተማሪዎችን ሸልመዋል።
ከተመሠረተ አራት አመታት ብቻ ያስቆጠረው የቡራዩ ወልመራ ክልል የዛሬውን ጨምሮ እስካሁን 176 አገልጋዮችን አስተምሮ በማስመረቅ ለአገልግሎት ማብቃት ችሏል።
#አገልጋዮችን_ማፍራትና_ማብቃት_የቤተ_ክርስቲያናችን_አላማ_ነው!
Saminariin Waldaa Masarata Kristoos barattoota Kolleejjii Waldaa Masarata Kristoos BuraayuWalmaraatti barachaa turan marsaa 4 ffaaf eebbisiiseera.
Kolleejjiin Waldaa Masarata Kristoos Buraayyuu Walmaraa barattoota 69 kan eebbise yoo ta'u, digriidhaan 40 dippiloomaadhaan 29 har'a Waldaa Masarata Kristoos Hoolataa 44 tti eebbisiiseera.
Barattoota 29 dippiloomaadhaan eebbifaman keessaa; eebbifamtoota 24 Mana Barumsaa Qulqulluu Waldaa Masarata Kristoos Hoolataa 44tti barachaa kan turan fi marsaa 1ffaaf eebbifamaniiru.
Sagantaa eebbaa irratti kan argaman Pricipaal Seeminaarii Masarata Kristoos kan ta’an Tiksee Gishu Jabeecha mata duree "Waaqayyo kadhannaa ni dhaga'a" jedhuu irraatti Isaayaas 38:1-6 irraa ergaa Bilchaataa lallabaniiru. Sagantaa kana irratti Walitti qabaan Qaxanaa Waldaa Masarata Kristoos Giddugaleessa Ityoophiyaa Yeroo kan ta’an; Tiksee Tafarraa Makataa, walitti qabaa Waldaa Masarata Kristoos Naannoo Buraayyuu Walmaraa kan ta’an; Obbo Andu'aaleem Tafarra, Geggeessitootni fi taajaajiltoonni Naannoo fi waldoota iraa affeeraman ebba kana irratti argamaniiru.
Keessummootni kabajaa saganticha irratti argaman barattoota eebbifamaniin baga gammaddan jechuudhaan barattootaa qabxii ol’aanaa galmeessaniif badhaasa kennameera.
Walumaa galattii Kolleejjiin Waldaa Waldaa Masarata Kristoos Buraayyuu Walmaraa erga eegalee marsaa 4 ffaa eebbifaman dabalatee barattoota 167 barsiisee eebbisiiseera.
#Tajaajiltoota_Oomishuu_fi_Gahoomsuun_Kaayyoo_Waldaa_Keenyaati!
Odeeffannoo karaa middiyaa hordofuuf፦
Tiiktookiin: https://www.tiktok.com/@mkc1951
Teeleegraaiin: https://t.me/MKC_Official
Yuutubiin: https://youtube.com/@mkcmedia2023
Facebookiin: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
3 002
ከግማሽ ምዕተ አመት በኋላ #ታሪክ ራሱን ሲደግም
በሚቀጥለው ሳምንት 50ኛ አመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓሉን የሚያከብረው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ከዛሬ 50 አመት በፊት በ1968 ዓ.ም የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን ጨምሮ በዘጠኝ ቤተ እምነቶች የተመሰረተው በወቅቱ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ይዞታ በነበረውና አዳማ ከተማ በሚገኘው በናዝሬት የመጽሐፍ ቅዱስ አካዳሚ እንደነበር ታሪክ ይናገራል።
ዛሬ ደግሞ ከግማሽ ምዕተ አመት በኋላ ታሪክ ራሱን ሲደግም ተመልክተናል። ነገሩ እንዲህ ነው፤ ከ50 አመት በፊት አባቶቻችን ወንጌልን በተናጠል መመስከሩ ብቻ በቂ እንዳልሆነ ቢሰማቸው የአብያተክርስቲያናት ህብረትን መሰረቱ፣ ህብረቱም ባለፉት አመታት በብዙ ፍሬ የባረከውን እግዚአብሔርን ሊያመሰግን በሚቀጥለው ሳምንት ቀጠሮ ይዞ ሳለ ዛሬ በዋዜማው እነኝሁ አብያተክርስቲያናት ሌላ ታሪክ ጻፉ። ታሪኩም ልክ እንደ ዛሬ 50 አመቱ ታሪክ በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ ተጻፈ።
ዛሬ ሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም አስር ቤተ እምነቶች ከ50 አመት በፊት የወለዱትን የአብያተክርስቲያናት ህብረት እንዲሁም በቅርቡ ያቋቋሙትን የወንጌል አማኞች ካውንስል በመያዝ በራሳቸው ዘመን ቴክኖሎጂ የሰጣቸውን እድል በመጠቀም በአንድነት ወንጌልን ይሰብኩ ዘንድ በኢትዮጵያ ወንጌላውን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊባል በሚችል ደረጃ በጋራ ባለቤትነት የሚያስተዳድሩትን የሚዲያ ተቋም የኢቫንጄሊካል ሚዲያ ኔትወርክ (EMN) ሲሉ በመሰየም መሰረቱ። ዛሬም በህብረት ዘመኑ በፈቀደላቸው መንገድ ተጠቅመው እንደ አባቶቻቸው ወንጌልን ይመሰክሩ ዘንድ የመግባቢያ ስምምነት ፊርማቸውን አኖሩ። ይህም የፊርማ ስነስርዓት ልክ እንደ ዛሬ 50 አመቱ በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ይዞታ ተከናወነ።
ኢቫንጄሊካል ሚዲያ ኔትወርክም ቅዱሳት መጽሐፍትን መሰረቱ በማድረግ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን ለሕዝቦች ሁሉ ያበስር ዘንድ ጉዞውን ዛሬ አንድ ብሎ ጀመረ።
#ክብር_ሁሉ_ለእግዚአብሔር_ይሁን!
3 002
አንጋፋ ቤተ እምነቶች ኢቫንጄሊካል ሚዲያ ኔትወርክ (#EMN) በሚል በጋራ ባለቤትነት የሚተዳደር ሚዲያ ለመመስረት የመግባቢያ #ስምምነት ፈረሙ።
ኢቫንጄሊካል ሚዲያ ኔትወርክን ለመመስረትና በጋራ ባለቤትነት ለማስተዳደር የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት የተፈራረሙት የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን ጨምሮ 10 ቀደምት ቤተ እምነቶች፣ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት እንዲሁም የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ናቸው።
በዛሬው እለት በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ በተካሄደው የፊርማ ስነስርዓት የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ፣ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ምክትል ፕሬዚዳንት መጋቢ ሰብረላ ከድርና የቤተ እምነቶቹ ፕሬዚዳንቶችና ተወካዮች ሲገኙ የኢቫንጄሊካል ሚዲያ ኔትዎርክ (#EMN) በሚል የመገናኛ ብዙኃንን በመጠቀም የክርስቶስን ወንጌል ለሕዝቦች ሁሉ የሚያደርስ ተቋም ለመመስረት የስምምነት ፊርማቸውን አኑረዋል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ምክትል ፕሬዚዳንት መጋቢ ሰብረላ ከድር በፊርማ ስነስርዓቱ ወቅት ባደረጉት ንግግር ስምምነቱ ታሪካዊ እንደሆነ ገልጸው እግዚአብሔር በሰጠን የሚዲያ እድል እውቀትና ጸጋን በጋራ ተጠቅመን ወንጌልን ለመስበክና ተተኪዎችን ለማፍራት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውና ይህ ጅማሮ በሌሎች መስኮችም መቀጠል እንደሚገባው ተናግረዋል።
በመግባቢያ ስነዱ መሠረት የኢቫንጄሊካል ሚዲያ ኔትወርክ (EMN) የቅዱሳት መጻሕፍት አስተምህሮን መሰረት አድርጎ አገልግሎቶችን በጋራ በመስጠትና በመምራት፣ የሚዲያ አቅምን በማቀናጀት የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በስፋት የሚያደርስና የወንጌላውያንን ድምጽ በሁለንተናዊ መልኩ እንዲሰማ የሚያደርግ ትልቅ ተቋም እንደሚሆን ይጠበቃል።
#አጀንዳችን_ወንጌል_ነው!
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@mkc1951
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/@mkcmedia2023
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
3 002
+6
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን #የዶዮገና ክልል ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የዶዮገና ክልል ከ29 አጥቢያዎችና አንድ የወንጌል ስርጭት ጣቢያ የተወከሉ መሪዎች፣ አገልጋዮች እና ተጋባዥ እንግዶች የተገኙበት ጉባኤ ሐምሌ 1/2018 ዓ.ም በተሳካ ሁኔታ አካሂዷል።
ጉባኤው በአምልኮ፣ በጸሎት እና በእግዚአብሔር ቃል ትምህርት የተጀመረ ሲሆን፣ በመርሃ ግብሩ ዋናው ቢሮን በመወከል የተገኙት መጋቢ ንጉሴ በቀለ 1ኛ ነገሥት ምዕራፍ 19'ን መነሻ በማድረግ "የተሃድሶ ጥሪ" በሚል ርዕስ የእግዚአብሔርን ቃል አካፍለዋል። በዚህም የእግዚአብሔር መገኘትና የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በጉባኤው መታየቱ ተገልጿል።
በጠቅላላ ጉባኤው የክልሉና በክልሉ ስር የሚገኘው የስነመለኮት ኮሌጅ ዓመታዊ ሪፖርት እና የ2019 በጀት አመት እቅድ ቀርቦ ጸድቋል። ክልሉ አንዲትን የወንጌል ሥርጭት ጣቢያን ወደ አጥቢያነት ያሳደገ ሲሆን በተለያዩ የአገልግሎት፣ የአስተዳደርና የክልሉ እድገት አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይት አስደርጓል።
በመጨረሻም ጉባኤው ወርሃዊ መዋጮቸውን በታማኝነት ለከፈሉ አጥቢያዎች የእውቅና ሰርተፊኬት በማበርከትና ስለቤተክርስቲያን፣ ስለ ቀጠናና የክልሉ አገልግሎት ጠንካራ የምልጃ ጸሎት በማድረግ ተጠናቋል።
#አጀንዳችን_ወንጌል_ነው!
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@mkc1951
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/@mkcmedia2023
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
3 002
+9
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የተለያዩ #ማረሚያ_ቤቶች ለተሰማሩ የወንጌል አገልጋዮች የሚሰጠው ስልጠና መካሄድ ጀመረ።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሕግ ታራሚዎች አገልግሎት መምሪያ ከቲዲኤምኤም ሚኒስትሪ ጋር በመተባበር በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ላሰማራቸው 61 የቢሮና መስክ አገልጋዮች ለአራት ቀናት የሚቆይ ስልጠና በትላንትናው እለት ማካሄድ ጀምሯል።
ከስልጠናው መጀመር አስቀድሞ አገልጋዮቹ ባለፈው አንድ አመት እየተከበረ የዘለቀውን የአገልግሎቱን 30ኛ አመት ክብረ በዓል አስመልክቶ ኬክ በጋራ ቆርሰዋል።
በትላንትናው የስልጠና ውሎም የአገልግሎቱ የ2018 በጀት አመት ሪፖርት፣ የመምሪያው የአምስት አመት ስልታዊ ዕቅድ፣ የ2019 በጀት አመት ዕቅድ እንዲሁም አሠራርን አስመልክቶ በቢሮ አገልጋዮች ገለጻ ተደርጓል።
በአዲስአበባ የቲዲኤምኤም ስልጠና ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ መርሐግብር በማረሚያ ተቋማት ውስጥ የተሰማሩት እነዚህ የወንጌል አገልጋዮች በቀጣይ ቀናት ስለ ወንጌል ስርጭትና ቤተ ክርስቲያን ተከላ እንዲሁም ደቀ መዛሙርትን ማፍራት በተሰኙ ዋና ዋና ርዕሶች ላይ ትምህርት እንደሚያገኙ ይጠበቃል።
#አጀንዳችን_ወንጌል_ነው!
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@mkc1951
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/@mkcmedia2023
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
3 002
+6
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ጌታን ተቀብለው የድነት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ #109_አዳዲስ አማኞች #ተጠመቁ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ጫንጮ አጥቢያ እንዲሁም በቡራዩ ወልመራ ክልል ስር በሚገኙት ቱሉ ዋቶ ዳለቻ እና በራሬ ሱቁ ስርጭት ጣቢያዎች ጌታን በመቀበል የድነት ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 109 አማኞች ሰኔ 27 እና 28/2018 ዓ.ም የውሃ ጥምቀት በመውሰድ ወደ ቤተ ክርስቲያን ተጨምረዋል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ባስቀመጣችው የአጀንዳ 28:19 የወንጌል ተልዕኮና ስልታዊ እቅድ መሰረት ክልሎችና አጥቢያዎች ወንጌልን ቀዳሚ አጀንዳቸው በማድረግ እየተንቀሳቀሱ ይገኛል።
#ወንጌል_ካልሰራን_ምንም_አልሰራንም!
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@mkc1951
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/@mkcmedia2023
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
3 002
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን #ጭሮ ከተማ የተገነባው የወጣቶች #ማዕከል ተመረቀ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የኢቫንጌልየም ሚሽን ኢትዮጵያ በምዕራብ ሐረርጌ ጭሮ ከተማ ያስገነባው ርኆቦት የወጣቶች ማዕከል ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ተመርቋል።
በመሐል ጭሮ መሠረተ ክርስቶስ አጥቢያ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው የወጣቶች ማዕከል ሲመረቅ የኢቫንጌሊየም ሚሽን ኢትዮጵያ መስራች ሚሽነሪ ሽመልስ ረታ፣ የዞኑ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የአብያተክርስቲያናት መሪዎች፣ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ክልሎችና አጥቢያ መሪዎችና አገልጋዮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በስፍራው ተገኝተዋል።
የኢቫንጌልየም ሚሽን ኢትዮጵያ መስራች ሚሽነሪ ሽመልስ ረታ ማዕከሉን መርቀው ሲከፍቱ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ማዕከል በወጣቶች ሕይወት ውስጥ ሁለንተናዊ ለውጥ እንዲያመጣ ፍቅርን፥ እውነትን እና ሰላምን መካከለኛ በማድረግ ተግተን ልንሰራ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የምዕራብ ሐረርጌ ክልል ዋና ጸሐፊ ወንጌላዊ ዘላለም አለማየሁ ግንባታው ኢቫንጌልየም ሚሽን ኢትዮጵያ ባለፉት 30 ዓመታት በክልሉ ሲያካሂድ የቆየው ሁለንተናዊ አገልግሎት አንድ አካል መሆኑን ገልጸው ማዕከሉ በተለይ በከተማዋ በተለያዩ ሱሶች ተጽዕኖ ውስጥ የወደቀውንና እና ለልዩ ልዩ አደጋ ተጋላጭ የሆነውን ትውልድ ለመታደግ ቤተ ክርስቲያን ከእግዚአብሔር የተቀበለችውን አደራ እንድትወጣ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ የምዕራብ ሐረርጌ ዞን የሴቶች፥ ወጣቶች እና ሕጻናት ቢሮ ተወካይ አቶ ጨምር ገመቹ በበኩላቸው ይህ ግንባታ ለከተማዋ በዓይነቱ አዲስ እና ወጣቶችን በልዩ ልዩ ክሕሎቶች የሚያንጽ እንደሆነና ለቀጣዩ ትውልድም መልካም እሴቶችን አስተላላፊ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልጸው በከተማዋ እንዲህ ያለ ማዕከል ለመገንባት ብዙ ዋጋ ለከፈለችው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ያላቸውን ምስጋና በዞኑ ስም አቅርበዋል።
ዲጂታል ቤተ መጻሕፍት፥ የስፖርት ማዘውተሪያ፥ የሙዚቃ መሣሪያ ትምህርት ቤት እና ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ አዳራሾች የሚኖሩት ይህ ማዕከል በመጠናቀቁ የከተማው አብያተክርስቲያናት እና የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን መሪዎችና አገልጋዮች እንዲሁም ወጣቶች ደስታቸውን ገልጸዋል።
#አገልግሎታችን_ሁለንተናዊ_ነው!
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@mkc1951
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/@mkcmedia2023
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
3 002
+8
የመሠረተ ክርስቶስ ኮሌጅ #አዳአበርጋ ካምፓስ ተማሪዎቹን አስመረቀ።
በመሠረተ ክርስቶስ ኮሌጅ ምዕራብ ሸዋ አዳአበርጋ ካምፓሰ ላለፉት አራት አመታት በድግሪ መርሐግብር የነገረ መለኮት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 51 ተማሪዎቹን በዛሬው እለት በድምቀት አስመርቋል።
በምረቃ መርሐግብሩ ላይ የተገኙት የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ በስፍራው በመገኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ ሲገልጹ ለተመራቂዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፕሬዚዳንቱ በመልዕክታቸው እግዚአብሔር በጥበብ፣ በቅድስናና በታማኝነት ቤተ ክርስቲያንና ማኅበረሰቡን የምታገለግሉ ያድርጋችሁ ሲሉ ተመራቂዎችን ባርከዋል።
የአዳአ በርጋ መሠረተ ክርስቶስ ኮሌጁ በምዕራብ ሸዋና አካባቢው በእግዚአብሔር ቃል የበቁ አገልጋዮችን በማፍራት ላይ ይገኛል።
#አገልጋዮችን_ማፍራትና_ማብቃት_የቤተ_ክርስቲያናችን_አላማ_ነው!
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@mkc1951
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/@mkcmedia2023
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
3 002
የክረምት የልጆች ትምህርት
#Summer_Camp ደረሰ
እንኳን ለ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት በሰላም አደረሳችሁ‼️
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የልጆች አገልግሎት ክፍል ከዚህ በፊት እንደሚያደርገው ለ2018 ዓ.ም የክረምቱን ወራት ለልጆች በሚሆን መልኩ “#መንፈስ_ቅዱስ_ለልጆች” በሚል ርዕስ ትምህርት አዘጋጀቷል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አጥቢያዎችም ይህን ስርዓተ ትምህርት በመጠቀም በሐምሌ እና ነሐሴ ወራት ውስጥ ባሉት ከሁለት እስከ አራት ሳምንታት ልጆችን እንድታስተምሩ ልከናል፡፡
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የልጆች አገልግሎት ዴስክ
3 002
+3
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዲላና አካባቢው #የወንጌል ስርጭት ዘመቻ ተካሄደ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ዲላና አከባቢው ክልል ስር የሚገኙ አጥቢያዎች ለአንድ ወር የቆየ የወንጌል ስርጭት ዘመቻ አካሂደዋል።
አጥቢያዎቹ ባካሄዱት የአንድ ለአንድና የጀማ ወንጌል ምስክርነት ከ8,000 በላይ የሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ስለጌታ ኢየሱስ አዳኝነት ሲሰሙ 145 ሰዎች ጌታን ተቀብለዋል።
ወንጌል ባልደረሰባቸው አካባቢዎች የሚካሄዱት ተመሳሳይ ምስክርነቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ይጠበቃል።
#አጀንዳችን_ወንጌል_ነው!
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@mkc1951
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/@mkcmedia2023
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
3 002
+4
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዲላና አካባቢው #የወንጌል ስርጭት ዘመቻ ተካሄደ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ዲላና አከባቢው ክልል ስር የሚገኙ አጥቢያዎች ለአንድ ወር የቆየ የወንጌል ስርጭት ዘመቻ አካሂደዋል።
አጥቢያዎቹ ባካሄዱት የአንድ ለአንድና የጀማ ወንጌል ምስክርነት ከ8,000 በላይ የሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ስለጌታ ኢየሱስ አዳኝነት ሲሰሙ 145 ሰዎች ጌታን ተቀብለዋል።
ወንጌል ባልደረሰባቸው አካባቢዎች የሚካሄዱት ተመሳሳይ ምስክርነቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ይጠበቃል።
#አጀንዳችን_ወንጌል_ነው!
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@mkc1951
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/@mkcmedia2023
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
3 002
+9
በሰሜን ሸዋ ዞን #ደብረብርሃን ከተማ የሰላም ግንባታ ስልጠና ተካሄደ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሕግ ታራሚዎች አገልግሎት መምሪያ በሰሜን ሸዋ ዞን ደብረብርሃን ከተማ ለሐይማኖት አባቶች፣ የአካባቢ ሽማግሌዎች፣ የሰላምና ጸጥታ ባለሙያዎች እንዲሁም የማረሚያ ቤት ሀላፊዎች እና ፖሊሶች "ተሓድሶአዊ ፍትህ" በሚል ርዕስ ከሰኔ 21-24/2018 ዓ.ም የሰላም ግንባታ ስልጠና አካሂዷል።
ከዚህ በተጨማሪ ከተለያዩ ትምህርት ቤት ለተውጣጡ መምህራን፣ ተማሪዎች እና የሕግ ታራሚዎች ግጭትን መከላከል በሚል ርእስ በደብረብርሃን ማረሚያ ቤት በተመሳሳይ ስልጠና ተሰጥቷል።
ቤተ ክርስቲያኒቱ በእነዚህ ቀናት በአካባቢው እያከናወነች የምትገኘውን የሰላም ግንባታ አገልግሎት ለማገዝ የሚረዱ የሰላም መልዕክት ማስተላለፊያ ቁሳቁሶችን በትምህርት ቤቶች ለሚንቀሳቀሱ የሰላም ክበባት አበርክታለች።
በዚህ ስልጠና የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ለረዥም አመታት በሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች እያከናወነች በምትገኘው የሰላም ግንባታ ስራ ተጠቃሚ የሆኑና በእርቅ ከማህበረሰቡ ጋር የተቀላቀሉ የሕግ ታራሚዎችና የተጎጂ ቤተሰቦች ተገኝተው ምስክርነታቸውን አቅርበዋል።
#ሰላምን_መገንባት_የቤተ_ክርስቲያናችን_አላማ_ነው!
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@mkc1951
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/@mkcmedia2023
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
3 002
📢 #ማስታወቂያ
አዲስ መጽሐፍ በቅርብ ቀን - #የምሕረቱ_ፍኖት
ሐምሌ 11፣ 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 በምስራቅ አዲስአበባ መሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ይመረቃል።
#ሁላችሁም_ተጋብዛችኋል!
3 002
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን #የገፈርሳ_ቡራዩ መዘምራን
WALDAA MASARATA KIRISTOOS GAFARSAA BURAAYYUUTTI FAARFATTOOTA GARTUU NAGAA
https://youtu.be/29g59poDE2Q?si=1lozhElSfDCsFCHe
3 002
+9
#አመታዊ የሙሉ ጊዜ አገልጋዮችና የትዳር አጋሮቻቸው #ሴሚናር በአዳማ ተካሄደ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ደቡብ አዳማ ክልል አገልጋዮችና የትዳር አጋሮቻቸው የጋራ ጊዜ እንዲኖራቸው በማለም የሚዘጋጀው አመታዊ ሴሚናር በመሐል አዳማ አጥቢያ ሰኔ 22/2018 ዓ.ም ተካሂዷል።
ሴሚናሩ በደቡብ አዳማ ክልል አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ ሰብሳቢ ደረሰ ታደሰና የክልሉ ዋና ጸሓፊ መጋቢ ሻሾ ቱሉ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ሲጀምር ዶ/ር አብርሃም ተ/ማርያም የእግዚአብሔርን ቃል ሙሉ ቀን አስተምረዋል።
ዶ/ር አብረሃም ከእግዚአብሔርን ቃል በዘጸአት 8፥1 "ያገለግለኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ።" ያለውን እውነት መነሻ በማድረግ በመጀመሪያ እግዚአብሔር ከተያዝንበት ሁኔታዎች ወጥተን እንድናገለግለው ይፈልጋል ሲሉ እንዲሁ በዘጸአት 18 መሠረት እግዚአብሔርን ስናገለግል ቤተሰብን ይዘንና ለሌሎችም ኃላፊነት በማካፈል መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተው አስተምረዋል።
የሴሚናሩ ተሳታፊዎችም የሚያገለግሉትን ሕዝብ ስለ መውደድ እና እግዚአብሔርን በመጠበቅ ውስጥ ሆኖ ማገልገል እንዴት ፍሬያማ እንደሚያደርግ ከቃሉ መማራቸውን በምስክርነታቸው አረጋግጠዋል።
የሙሉ ጊዜ አገልጋዮቹ በዛሬው እለት ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመሆን በተለያዩ ስፍራዎች የጋራ ጊዜ እንደሚያሳልፉ ይጠበቃል።
መረጃዎቻችንን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ 👇
በቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@mkc1951
በቴሌግራም: https://t.me/MKC_Official
በዩቱብ: https://youtube.com/@mkcmedia2023
በፌስቡክ: https://www.facebook.com/mkcpresidentoffice
