ru
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Открыть в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 13 369 подписчиков, занимая 1 753 место в категории Транспорт и 2 530 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 13 369 подписчиков.

Согласно последним данным от 20 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 129, а за последние 24 часа — 8, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 38.47%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.24% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 143 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 037 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 11.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 21 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Транспорт.

13 369
Подписчики
+824 часа
+697 дней
+12930 день
Архив постов
የአርብ ገበያ - ሰከላ - ቲሊሊ 62 ኪ.ሜ የአስፋልት መንገድ የግንባታ ፕሮጀክት ስራን ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን አስጀመሩ። በታሪካዊቷ ሰከላ ወረዳ ግሽ አባይ ከተማ ላይ ባዛሬው ዕለት በተካሄደው የመንገዱ ግንባታ ጅማሮ መርሃ-ግብር ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘው ተሻገር ፣ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ብናልፍ አንዱአለም፣ የምክር ቤት አባላት ሚኒስትሮች ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ታድመዋል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የፕሮጀክቱ መጀመር የህዝቡን የቆየ የመሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ከመስጠቱም ባሻገር ሀገራዊ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል። ግሽ አባይ የታላቁ አባይ ወንዝ ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ ስፍራው የበርካታ ታሪካዊ እና ጥንታዊ መስህቦች መገኛ እንደመሆኑ ጸጋዎቹን ለአለም እንድናወጣ ምቹ አጋጣሚን የሚፈጥር ነው ብለዋል። ከዘርፉ በሚገኘው ገቢ ተጠቃሚ እንዳይሆን ደረጃውን የጠበቀ መንገድ አለመኖር በእጅጉ ጎድቶት እንደቆየ አንስተዋል ። በአጠቃላይም የመንገዱ መገንባት አካባቢውን ሁነኛ የቱሪስት መዳረሻ በማድረግ እና በደን ሀብት ፣ በእንስሳት ሀብቱ ታዋቂ የሆነውን ስፍራ ከምርቱ በሚገባው ልክ ተጠቃሚ እንዲሆን ስለሚያስችል መንግስት ይበልጥ ጠንክሮ ይሰራል ብለዋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘው ተሻገር በክልሉ ውስጥ ካሉ እና ለብዙ አመታት በህብረተሰቡ ዘንድ መንገዱ እንዲገነባ ተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብባቸው ከነበሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች ውስጥ ይህ ታሪካዊ መንገድ ምላሽ ማግኘቱ ታላቅ የምስራች ነው ብለዋል። መንግስት በተለይም ባለፋት አመታት አቅም በፈቀደ መጠን ለሚቀርቡ የልማት ጥያቄዎችን ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ እንደሆነ አረጋግጠው። ለፕሮጀክቱ ተግባራዊነም መላው የክልሉ አመራር የአካባቢው ህዝብ ከኢመባ ከተቋራጩ እና ከአማካሪ ድርጅቱ ጋር አጋር በመሆን ያልተቆጠበ ድጋፍ እንዲያደርጉም አሳስበዋል። የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ የመንገዱ መገንባት በመስመሩ የሚገኙ ዞኖች እና ወረዳዎች እንዲሁም ተራርቀው የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች በቅርበት በማስተሳሰር ከማስቻሉም በላይ ከዚህ ቀደም በመንገዱ መበላሸት ሳቢያ ለአላስፈላጊ የተሸከርካሪ መለዋወጫ ወጪ ይዳረጉ የነበሩትን በማስቀረት እና በክረምት ወቅት በተሸከርካሪ እጦት ለእንግልት ሲዳረጉ ለነበሩ የአካባቢው ነዋሪ፣ክረምት ከበጋ ደረጃውን የጠበቀ መንገድ ተጠቃሚ እንደሚያደርጋቸው ገልጸዋል ፡፡ በፕሮጀክቱ ቆይታ ውቅትም ለአካባቢው ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር ከመሆኑም ባለፈ የሙያ ባለቤትም የሚያደርግ ይሆናል ብለዋል ። በውሉ መሰረት በሶስት ዓመት የግንባታ ጊዜ እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የመስተዳድር አካላት እስከ ፕሮጀክቱ ፍጻሜ ድረስ ድጋፍ ትብብራቸውን እንዲያሳዩ ጥሪ አቅርበዋል። የዲኤም ሲ ተቋራጭ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳንኤል ማሞ ፕሮጀክቱ ከወዲሁ ጥሩ የግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኘ ጠቅሰው በተገቢው ጥራትና ጊዜ ገንብተው እንደሚያስረክቡ ቃል ገብተዋል። አካባቢው ላይ ሰፊ የሙያና የስራ እድል የሚፈጠር በመሆኑ የስራ ባህልን በማሳደግ ተጨማሪ እድልን የሚያስገኘ ነው ብለዋል የአርብ ገበያ - ሰከላ -ቲሊሊ የመንገድ ግንባታውን በብር አንድ ቢሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሶስት ሚሊየን ሶስት መቶ ሺህ አንድ መቶ ሰላሳ ሰባት በር ከሰባ አንድ ሳንቲም ( 1,673,300,137 . 71) ጨረታውን አሸንፎ ግንባታውን የሚያከናውነው ዲ ኤም ሲ (DMC) ኃላፊነቱ የተወሰነ አገር በቀል የሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ፒዩር ኮንሰለቲንግ እና ሳውንድ ኢንጂነሪንግ ሶሉሽን አማካሪ ድርጅቶች ያከናውነዋል። ለመንገዱ ግንባታ የሚያስፈልገውን ወጪ የሚሸፍነው የኢትዮጵያ መንግስት ሲሆን የግንባታ ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ ለተቋራጩ የሶስት ዓመት ጊዜ ተሰጥቶታል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክት አሁናዊ ገጽታው ለረዥም ዓመታት ግልጋሎት ሲሰጥ የነበረ እና ደረጃውን ያልጠበቀ ጠጠር መንገድ ሲሆን በቀጣይ ደረጃውን ከፍ በማድረግ በአስፋልት ኮንክሪት የሚገነባ ይሆናል ፡፡ የጎን ስፋቱም አሁን ካለበት 6 ሜትር እንዲጨምር በማድረግ በወረዳ ከተማ 21.5 ሜትር እንዲሁም በገጠር 10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ይገነባል ፡፡

የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ ኦሮሚያ እና ደቡብ ክልልን የሚያስተሳስረውን የጅማ-ጭዳ 80 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራን ዛሬ በይፋ አስጀመሩ፡፡ በኮንታ ልዩ ወረዳ ጭዳ ከተማ ላይ በተከናወነዉ በዚሁ  የመንገድ ግንባታ ማስጀመር መርሀ-ግብር ላይ ምክትል ጠቅላይ  ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለሥልጣናት በታደሙበት ነው በይፋ ያበሰሩት። ፕሮጅክቱ የህብረተሰቡን የበርካታ አመታት የመሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ከመስጠቱም በላይ ሁለቱን ወንድማማች ህዝቦች ይበልጥ የሚያቀራርብ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልፀዋል። አካባቢው ቡናን ጨምሮ በተለያዩ የተፈጥሮ ፀጋዎች የታደለ በመሆኑ የመንገዱ መገንባት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የላቀ ድርሻ አለው ብለዋል። በተጨማሪም ስፍራው የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻ ገጸ በረከቶችን የታደለ በመሆኑ የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል። ህብርተሠቡም ይህንን ወሣኝ ፕሮጀክት በተቀመጠለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ተገቢውን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርግ አደራ ብለዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ ፕሮጀክቱ የሚገኘበት ሥፍራ የበርካታ የሰብል ምርት መገኛ የቡና እና የቅመማ ቅመም ሀብቶች ማብቀያ የማር የአትክልትና ፍራፍሬም ምርቶች በስፋት የሚመረትበት መሆኑን ጠቅሰው ይህን የላቀ ሃብት ወደ ማዕከላዊ እና አለምአቀፍ ገበያ በማድረስ የሀገሪቱን የወጪ ንግድ በማሳደግ በኩል አስተዋፅኦው የጎላ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ፤ የጊቤ 3 እና የጊቤ 4፤የ ኮይሻ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ ስራ ጋር እንዲሁም ከ በርካታ ፀጋዎች ጋር የሚያስተሳስር ፕሮጀክት በመሆኑ ጠቀሜታው ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡ የጅማ ጭዳ መንገድ በ 2,422,629267,27 ቢሊዮን ብር ጨረታ በማሸነፍ የግንባታ ስራውን የሚያካሂደው ቻይና ቲሲጁ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የተባለ አለምአቀፍ የቻይና የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ የግንባታዉ ወጪ የሚሸፈነዉ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፤ የጃፓን አለምአቀፍ ተራድኦ ድርጅት እና የኢትዮጵያ መንግስት በጥምረት ነው፡፡ ፕሮጀክቱ በአራት አመታት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ። መንገዱ በዞን ከተማ 19 ሜትር ߹ በወረዳ ከተማ 14 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል። የፕሮጀክቱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር በኩል ኪዮንግዶንግ ኢንጅነሪንግ ߹ ኦሪዬንታል ኮንሰልቲንግ ግሎባል እና ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነሪንግ በጋራ ያከናውኑታል፡፡

በገበታ ለሃገር ፕሮግራም የኮይሻ ፕሮጀክት አካል የሆነው የሃላላ ኬላ ክላስተርን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶክተር አብይ አህመድ አስጀመሩ። በጅማሮው ስነ ስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጪ ጉዳይ ሚኒሰትር አቶ ደመቀ መኮንን ፣ የደቡብ ብሔር ፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። በዚሁ እለት በይፋ የተጀመረው የሃላላ ኬላ ክላስተር የዳውሮና የኮንታ ህዝቦችን ታሪክና ባህል ጎልተው የሚወጡበት አንዱ የቱሪስት መዳረሻ ነው። ግንባታው የካቲ ሃላላ ግንብንና የግልገል ጊቤ 3 ሰው ሰራሽ ሐይቅን ማዕከል አድርጎ የሚሰራ ይሆናል። በስነ ስርዓቱ ላይ ክቡር ጠቅላይ ሚነስትር ዶክተር አብይ አህመድ ይህ የኮይሻ ፕሮጀከት በሃገራችን ተጨማሪ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራ እንደሚሆን ገልፀው ፕሮጀክቱ በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ማህበረሰብ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት አሳስበዋል። የደቡብ ብሔር ፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርሰቱ ይርዳው በበኩላቸው የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክረውን ይህንን ፕሮግራም ለማስፈፀም ያለባቸውን ሃላፊነት እንደሚወጡ ገልፀዋል። በ 5 ክላስተሮች ማለትም የጨበራ አማያ ፣ ጉዱሙ ቦካ ፣ ሃላላ ኬላ ፣ ጨበራ ጪርጩራና ኮይሻ በመባል የተከፋፈለው የኮይሻ ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ የሆኑት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ /ር ሃብታሙ ተገኘ መንግስት ልዩ ትኩረት የሰጠው ዛሬ የሚጀመረው የሃላላ ኬላ ክላስተር በታቀደለት ጊዜና በሚፈለገው ደረጃ እንደሚጠናቀቅ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ከየሎ - ሃላላ ኬላ የሚያደርሰው 14 ኪ. ሜ መንገድ ለቱሪስት ምቹ ከማድረግ አኳያ የአስፋልት ደረጃ መንገድ እንደሚጀመርም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በምህድስናው ዘርፍ ብቁ የተማረ የሰው ህይል እውን እንዲሆን ያበረከተው አስተዋጾ የጎላ መሆኑ ተገለጸ። ይህ የተባለው ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ከተለያዩ የሀገራችን የዩንቨርስቲ ተቋማት ከተወጣጡ ምሁራን ጋር በመንገድ ዘርፍ ብቁ የሰው ሀይል ማፍራት ላይ ያተኮረ ውይይት ሲካሄድ ነው ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የኮርፖሬት አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ በቀለ ኢመባ ከ 2003 ዓ.ም ጀምሮ ከበርካታ ዩንቨርስቲዎች ጋራ ውል በማሰር በተለያዩ የምህንድስና የትምህርት ዘርፎች የተማሪዎቹን ሙሉ ወጪ በመሸፈን በማስተርስ ዲግሪ እንዲሰለጥኑ ማደረጉን ተናግረዋል። በዚህም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ዘንድሮው ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ያሉትን ጨምሮ አምስት ሺህ ተማሪዎችን ሙሉ ወጪያቸውን በመሸፈን እንዲሰለጥኑ አድርጓል ነው ያሉት ። ለዚህም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ባለፉት አስር አመታት ከ377ሚሊየን ብር በላይ ለትምህርት ወጪ በማደረግ በመሰኩ ተማሪዎቹ እንዲሰለጠኑ ማድረጉን የቀረበው ይውይይት ሰነድ ይፋ አድርጓል። ይህ በመሆኑም በመሰኩ ያለውን የሙያ ክህሎት እጥረት በመቀረፍ ሀገራዊ ሴከተሩ ላይ አውንታዊ ለውጥ እንዲመጣ ተቋሙ አበርክቶቱ የለቀ መሆኑም ተገምግሟል። በውይይቱ ላይ ከሰባት የሀገር ውስጥ ዩንቨርስቲዎች የተወጣጡ ሙሁራን የታደሙ ሲሆን፣ ሙሁራኑ በምህድስናው ዘርፍ ብቁ ባለሙያ በማስተማር በቀጣይ የመንገድ መሰረት ልማት በቂ እና ብቁ የሰው ሀይል በማፍራት የሀገሪቱን የመንገድ ዘርፈ ይብልጥ ለማሳደግ በአብሮነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። በቀጣይ በይበልጥ ብቁ ባለሙያን በማሰልጠን ለሀገር እድገት ቁልፍ ሚና ያለውን የመንገድ ልማት አሁን ካለበት ከፍ ለማድረግ ባለስጣን መስሪያ ቤቱ ተቋማዊ ማህበራዊ ሀላፊነቱን ይበልጥ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጧል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ በ4ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚገነቡትን የጉደር - ሸነን - ሰዮ እና የአምቦ ከተማ - ጉደር ከተማ መንገዶችን በይፋ አስጀመሩ። በመንገዱቹ ጅማሮ መርሃ-ግብር ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድን ጨምሮ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን ፣ ቀዳማይት እመቤት ዝናሽ ታያቸው፣ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፣ የብልጽግና ፖርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ብናልፍ አንዱአለም ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ፣ ከፍተኛ የፌዴራል እና የክልል ባለስልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል፡፡ በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶቹ ማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እንደተናገሩት መንገድን ማስጀመር ብቻ ሳይሆን የጀመርናቸውን ፕሮጀክቶች በማጠናቀቅ ቀጣይ የብልጽግና ጉዟችንን እናረጋግጣለን ብለዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን በመልዕክታቸው አካባቢዉ ሀገር ወዳድ የሆኑ ጀግኖች መገኛ ብቻ ሳይሆን ለሀገሪቷ ሁለንተናዊ እድገት በተለይም በግብርናው ዘርፍ ጉልህ አስተዋጽዎኦ እያበረከተ የሚገኝ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ጨምረውም አካባቢው የበርካታ ጸጋ ባለቤት ቢሆንም የመንገድ መሰረተ ልማት ባለመኖሩ ምክንያት ምርቱን ወደ ገበያ አውጥቶ ተጠቃሚ መሆን አልቻለም በቀጣይም ወደ ብልጽግና የምናደርገው ጉዞ የተሳካ ይሆናል ብለዋል። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በበኩላቸው በአካባቢው በስፋት የሚገኘውን የሰብል ምርት እንዲሁም የቁም እንስሳት ፣ ፍራፍሬና ውጤቶችን ወደ ተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል በማቅረብ አርሶ አደሩን በእጅጉ ተጠቃሚ ከማድረግ አንጻር ጉልህ ድርሻ ያላቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች እንደሆኑ ገልጸዋል። በመርሀ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዳይሬክተር የሆኑት ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ በዛሬው ቀን ብቻ ከ7.1 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 221.4 ኪሎ ሜትር እርዝማኔ ያላቸው መንገዶች መጀመራቸውን ተናግረዋል። ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ አክለውም የሰዮ -ጉደር -ሸነን ሎት 2 መንገድ ግንባታ 91.8 ኪ.ሜ ርዝማኔ ሲኖረው የአምቦ ከተማ- ጉደር ከተማ ደግሞ 18.5 ኪ.ሜ ሲሸፍን በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነቡ መንገዶች ናቸውም ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በመስመሩ ተራርቀው ለነበሩ የአካባቢው ህብረተሰቦች በቅርበት የመገናኘት እድልን በመፍጠር በአካባቢው የሚገኙ ዞኖች እና ወረዳዎችን በአስፋልት መንገድ በቅርበት በማስረተሳስርና የትራንስፖርት ጊዜን በማሳጠር የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በይበልጥ ያሳድጋል ተብሎ ይታመናል፡፡ የጉደር -ሸነን-ሰዮ ሎት 2 መንገድ የሚገነባው ከኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ 3.6 ቢሊዮን ብር ሲሆን ፕሮጀክቱን የሚገነባው የስራ ተቋራጭ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን የተባለ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡ የመንገዱ የጎን ስፋት በዞን 21.5 ሜትር፣ በቀበሌ 14 ሜትር በገጠር ደግሞ 10 ሜትር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ይገነባል፡፡ የአምቦ ከተማ- ጉደር ከተማ መንገድ በ 1ነጥብ 03 ቢሊዮን ብር ወጪ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ መንገድ ሲሆን መንገዱን በአንድ አመት ውስጥ ገንብቶ ለማጠናቀቅ ከባለስልጣኑ ጋር የውል ስምምነት የፈጸመው የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ድርጅት ነው፡፡ የመንገዱ የጎን ስፋት በቀጣይ በጉደር እና በአምቦ ከተሞች ከ 25.1-28.6 ሜትር ሲሆን ከከተማ ውጭ በአማካይ 17.4 ሜትር ስፋት እንደኖረው ተደርጎ ይገነባል፡፡ የመንገዶቹ መገንባት በመስመሩ ላሉ ትንንሽ ቀበሌዎች ይበልጥ የኢኮኖሚ መነቃቃትን በመፍጠር ለአካባቢው ሕብረተሰብ ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል፡፡ የተሽከርካሪ የጉዞ ጊዜን ከመቀነሱም በላይ ለአላስፈላጊ የተሸከርካሪ መለዋወጫ ይወጣ የነበረ ወጪንም በመቀነስ የምርት እና የሸቀጥ ልውወጥን ያቀላጥፋል፡፡ በተጨማሪም የጤና ፣ የትራንስፖርት እና የሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችን ተደራሽነት በማስፋት በአካባቢው ማህበረሰብ ኑሮና በኢኮኖሚው እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥ እንደሚያመጣ ይጠበቃል፡፡

የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የባኮ _ ሻንቡ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ በይፋ መረቁ ። በተመሳሳይም የሻንቡ አገምሳን አስፋልት መንገድ የግንባታ ስራውንም አስጀምረዋል ። በኦሮሚያ ክልል ሀረቶ ከተማ ላይ በተካሄደው የመንገዶቹ ምረቃ እና ጅማሮ መርሀ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚንስቴር ዶ/ር አብይ አህመድን ጨምሮ ፣ ቀዳማዊት እመቤት ክብርት ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው፣ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን ፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ብናልፍ አንዱአለም፣ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ እንዲሁም የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ /ር አብይ አህመድ በፕሮጀክቶቹ ምረቃ እና ጅማሮ መርሀግብር ላይ እንዳሉት የምዕራቡ የኢትዮጵያ ክፍል ካሉት በረከቶች አንጻር ጸጋዎቹን በሚፈለገው መጠን አውጥቶ እንዳይጠቀም ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት አለመኖሩ ዋነኛ ምክንያት መሆኑን አስታውሰው መንግስት በመንገድ ልማት መሰል ችግሮች ሲገጥማቸው ለነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ትኩረት በመስጠት እና ከፍተኛ የገንዘብ መውአለ ንዋይ በመመደብ በተጨባጭ ምላሽ እየሰጠ ስለመሆኑ የዛሬዎቹ ፕሮጀክቶች ማሳያ ተደርገው ሊወሰዱ የሚችሉ ናቸው ብለዋል። ዶ/ር አብይ አህመድ ጨምረውም የግንባታ ስራው የተጠናቀቀው የሻምቡ _ ባኮ እና ግንባታው የሚጀምረው የሻምቡ አገምሳ መንገዶችን በአካባቢው የሚገኙትን ከፍተኛ የግብርና ምርቶች፣የቁም እንስሳትና የፍራፍሬ ውጤቶች በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ አርሶ አደሮች ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከማስቻል አንጻር አገራዊ ፋይዳቸው የገዘፈ እንደሆነም በዕለቱ በነበረው መርሃ ግብር ገልጸዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን የሻንቦ _አገምሳ መንገድ መገንባት የአማራ ክልልን ከኦሮሚያ ክልል ጋር በማስተሳሰር በባህል ፣ በታሪክ፣ በንግድ ተሳስረው ለዘመናት የዘለቁትን ህዝቦች ይበልጥ ግንኙነታቸው እንዲዳብር አይነተኛ ሚናውን የሚጫወት መሆኑን ገልጸው ለፕሮጀክቱ ስኬት ከምንም በላይ ህዝቡ ሰላሙን ማስጠበቅ ይኖርበታል ብለዋል። የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ከዚህ በፊት በአካባቢው የነበረውን ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ችግር በመቅረፍ ህብረተሰቡ ተሽከርካሪዎችን ተጠቅሞ በተጣጣኝ ዋጋ ወደፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል። በተጨማሪም የኦሮሚያ ክልልን ከአጎራባች የአማራ ክልል ጋር በቅርበት በመንገድ የሚያስተሳስሩ በመሆናቸው በክልሎቹ መካከል ያለውን የንግድም ሆነ የህዝቦቹን የእርስ በእርስ ግንኙነት በማጎልበቱ ረገድ አይነተኛ ሚና ይኖራቸዋል ያሉ ሲሆን ግንባታው የተጀመረው የሻንቡ _አገምሳ መንገድ ስራው ተጠናቆ የሚጠበቅበትን ግልጋሎት መስጠት እንዲችል የክልሉ መንግስት ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ የግንባታ ስራው የተጠናቀቀው የባኮ ሻንቡ 60.2 ኪ .ሜ መንገድ የሚጠበቅበትን ግልጋሎት መስጠት እንዲችል እና በተመሳሳይም የግንባታ ስራው የሚጀመረው የሻንቡ አገምሳ 95 ኪሜ መንገድ በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የአካባቢው ህብረተሰብ ፣ የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት እና ባለድርሻዎች መንገዶቹን በመንከባከብ እና የሚገነባውንም መንገድ ከወሰን ማስከበር ጋር ተይስይዞ መስተጓጎል እንዳይገጥሙት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። የባኮ ሻንቡ 60.2 ኪ ሜ መንገድን በብር 993 ሚሊዮን ብር ወጪ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የገነባው የስራ ተቋራጭ ሲ ጂ ሲ ኦሲ ሃላፊነቱ የተወሰነ አለም አቀፍ የቻይና የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው። የፕሮጀክቱን የማማከር የቁጥጥር ስራ ያካሄዱት ሀቲብ ኤንድ አላሚ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ከኮር ኮንሰልት ጋር በጥምረት በመሆን ነው። ሌላኛው የግንባታ ስራው የሚጀመረው የሻንቡ _ አገምሳ አስፋልት መንገድ 95 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው ሲሆን ለግንባታ ስራው 2,080,273 817.86 ብር ወጪ የሚጠይቅ ነው። መንገዱን በሶስት አመት ከስድስት ወር ገንብቶ ለማጠናቀቅ ከባለስልጣን መ/ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው የቻይናው ተቋራጭ ሻንዶንግ ሊኪኖ ግሩፕ ነው። ለተጠናቀቀውም ሆነ የግንባታ ስራው ለሚጀምረው ፕሮጀክት ወጪ የሚሸፈነው የአረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት (BADEA) እና በኦፔክ (OPEC) እንዲሁም በኢትዮጵያ መንግስት ነው። የመንገዶቹ ግንባታ በዞን ከተሞች 19 ሜትር፣ በቀበሌ 12 እንዲሁም በገጠራማው ክፍል 10 ሜትር ስፋት አለው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የደምቢዶሎ - ሙጊ - ዶላ  50 ነጥብ 9 ኪ.ሜ  የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት  ስራን ዛሬ በይፋ አስጀመሩ ፡፡ በደቢዶሎ ከተማ በተከናወነው በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት እንዲሁም  ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ነው የመንገዱ  ግንባታ ጅማሮ በይፋ  ያበሰሩት ፡፡ ፕሮጀክቱ የህዝቡን የዘመናት የመሰረተ ልማት ጥያቄን ምላሽ ከመስጠቱም ባሻገር ለሀገራዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መጎልበት አስተዋጾ የላቀ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። መላው ህዝብ የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ የሚያስፈልገን የልማት ስራ ላይ በማተኮር የሀገራችንን ብልጽግና ለማረጋገጥ መረባረብ አለብን ብለዋል። አካባቢው የምሁራን የታሪክ የተፈጥሮና በርካታ ጸጋዎች ያሉት በመሆኑ የመንገዱ መገንባትም እነዚህን ሃብቶች በማውጣት የሀገራችንን የእድገት ጉዞ ለማፍጠን ሁሉም እንዲተጋ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በርካታ የተፈጥሮ ሃብት መገኛ የሆነውን ደቢዶሎ እና አካባቢውን በመንገድ ልማት በማስተሳሳር ሀገራችን ያላትን ጸጋዎች ይበልጥ ለመጠቀም ልተጋ ይገባል ብለዋል። መላው ህዝብ ለሰላምና ልማቱ ዘብ እንዲቆምም አስገንዝበዋል። የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተለይም ባለፉት ሁለት አመታት የክልሉን ልማት የሚያፋጥኑ በርካታ የመንገድ ፕሮጀክቶች መተግበራቸውን አንስተዋል። ይህም እንደ ሀገር የሚኖረው ሚና የላቀ በመሆኑ ሰላም ላይ በማተኮር በተለይም የክልሉ ህዝብ ይበልጥ እንዲተጋ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ ፕሮጀክቱ የምዕራቡን የሀገራችን ክፋል በማቆራኘት ፍይዳው የገዘፈ ነው ብለዋል። በተለይም የኦሮሚያ ክልልን  ከጋምቤላ  ክልል ጋር የሚያስተሳስር የመንገድ ግንባታ አካል ሲሆን  በቀጣይ በክልሎቹ መካከል ያለውን የንግድም ሆነ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያሳድገው ተናግረዋል ፡፡ በተጨማሪ የአገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ገቢ የሚያስገኝልን ቡናን ጨምሮ የፍራፍሬ እና የግብርና ምርቶችን  በፍጥነት ወደ አጎራባች ክልሎችም ሆነ ከጎረቤት ደቡብ ሱዳን ጋር ለሚኖረው የንግድ ሆነ  የህዝብ ለህዝብ ትስስር ከማሳደግ አንጻር ፋይዳው ከፍ ያለ ነው። በቀጣይ ዕውን የሚሆኑ ፕሮጀክቶች ተዳምረው  ከአዲስ አበባ- ጅማ - መቱ  አድርጎ ጋምቤላ  ይገባ የነበረውን  878 ኪሜ መንገድ አሁን በሚገነባው በደንቢዶሎ በኩል ከአንድ መቶ  ኪ .ሜ በላይ በማሳጠር  ሌላ አማራጭ ከመሆኑም ባለፈ ኪሎ ሜትርን በማሳጠር  እና  የጉዞ ጊዜን  በመቀነስ  ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ላቅ ያለ ነው ብለዋል፡፡ የደምቢዶሎ - ሙጊ - ዶላ መንገድ የሚገነባው  በ 1 ነጥብ 6  ቢሊዮን ብር ሲሆን ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል ፡፡ መንገዱ የሚገነባው የስራ ተቋራጭ ቻይና ሬልዌይ ሰቨንዝ  ግሩፕ የተባለ የቻይና አለም አቀፍ ስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ ዲዛይን እና ግንባታን አካቶ የሚገነባውን መንገድ ስራ  አጠናቆ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት ለማድረግ  ለተቋራጩ የሶስት አመት ከስድስት ወራት ጊዜ  ተሰጥቶታል፡፡ በጠጠር ደረጃ   የነበረና ከ25 አመታት በላይ በማስቆጠሩ  ሳቢያ በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዳው የደምቢዶሎ - ሙጊ - ዶላ  መንገድ በአካባቢው ህብረተሰብና በአሽከርካሪዎች ላይ የትራንስፖርት እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል፡፡ በመሆኑም በቀጣይ ለአካባቢው ከሚያበረክተው ከፍተኛ የሆነ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አንፃር ወደ አስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲያድግ ተደርጎ የሚገነባ ይሆናል፡፡ መንገዱ የሚኖረው የጎን ስፋትም የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በዞንና በወረዳ 20 ሜትር በቀበሌ ደግሞ 15.6 ሜትር ነው፡፡

የሲዳማ ክልልን ከአጎራባች የኦሮሚያ ክልል ጋር በማገናኘት ከማዕከላዊ የደቡብ ኢትዮጵያ ጋር የሚያስተሳስረው የሀዌላ ቱላ - ወተራሬሳ - የዩ - ወራንቻ 84.7 ኪ . ሜ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ስራ ዛሬ በይፋ ተጀመረ፡፡ በመንገዱ ጅማሮ መርሀ -ግብር ላይ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የሲዳማ ክልል፣ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣የትራንስፖርት ሚንስትር ዴኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል ፡፡ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ዛሬ ግንባታው የተጀመረው የሀዌላ ቱላ - ወተራሬሳ - የዩ - ወራንቻ መንገድን ጨምሮ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ገቢ የሚያስገኙልን ምርቶች መገኛ በመሆናቸው ሀገራዊ ፋይዳቸው የጎላ ነው ብለዋል። ይህም የደቡቡን የኢትዮጵያን ክፍል ከኢንደስትሪ ዞኖች ፣ ከጎረቤት አገራት ፣ ከመዲናችን አዲስ አበባ እና ከተለያዩ የሀገራችን አቅጣጫዎች ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችሉ የመንገድ መሰረተ ልማት አውታሮችን እውን እንዲሆኑ በርካታ ተጨባጭ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል። ከሀዌላ ተነስቶ ወራንቻ ድረስ የሚዘልቀው የአስፋልት መንገድ ዲዛይንና ግንባታ ፕሮጀክት ስራው በስኬት እንዲጠናቀቅ የሥራ ተቋራጩም ሆነ የአማካሪ ድርጅቱ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጡም አሳስበዋል። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ፕሮጀክቱ የሲዳማ እና የኦሮሚያ ክልል በንግድም ሆነ የህዝብ ለህዝብ ትስስር ከማጠናከር አንጻር ፋይዳው ከፍ ያለ ፕሮጀክት በመሆኑ የክልሉ መንግስት የመንገዱ ፕሮጀክቱ ተጠናቆ የሚጠበቅበትን ግልጋሎት መስጠት እንዲችል አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። በተለይም ለውጡን ተከትሎ መንግስት እየሰጠ ላለው አፋጣኘ ህዝባዊ ምላሽም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ የጅማሮ መርሀግብር የተካሄደለት የመንገድ ፕሮጀክቱ ለአገራችን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ገቢ የሚያስገኝልን ቡና አብቃይ እና የፍራፍሬ ምርት መገኛ ስፍራ በመሆኑ ምርቶቹን በፍጥነት ወደ ማእከላዊ እና ወደ አለም አቀፉ ገበያ ለማድረስ ፕሮጀክቱ ጉልህ ድርሻውን ይኖረዋል ብለዋል። ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ ጨምረውም የመንገዱ ግንባታ በሚካሄድባቸው መስመሮች ላይ የሚገኙ የመስተዳድር አካላት ፣ የአካባቢው ሕብረተሰብ እንዲሁም የመንገዱ ተጠቃሚዎች ሁሉ የመንገዱ ግንባታ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ለፕሮጀክቶች መዘግየት ምክንያት እየሆነ የመጣውን ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮችን እንዳይከሰቱ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ አሳስበዋል። የዮቴክ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዮሃንስ ተክላይ የመንገድ ፕሮጀክቱን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ እና የጥራት ደረጃ አጠናቆ ለህብረተሰቡ ለማስረከብ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሀዌላ ቱላ - ወተራሬሳ - የዩ - ወራንቻ መንገድ በብር 1,879,883,516.96 ቢሊዮን ብር ጨረታ በማሸነፍ የግንባታ ስራውን የሚያካሂደው የሥራ ተቋራጭ አገር በቀሉ ዮቴክ ኮንስትራክሽን ድርጅት ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ለመንገዱ ግንባታ ስራ የሚውለውን መዋእለ ነዋይ ወጪ የሚሸፍን ይሆናል ፡፡ ከአዲስ አበባ 285 ኪሎሜትር እርቀት ቱላ ከተማ የሚጀመረው ፕሮጀክቱ በሶስት ዓመት ከስድስት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡ አሁናዊ ገጽታው በጠጠር ደረጃ እና ከተገነባ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረው የሀዌላ ቱላ -ወተራሬሳ - የዩ - ወራንቻ መንገድ በአገልግሎት መደራረብ ሳቢያ በመጎዳቱ በህብረተሰቡና መንገዱን በሚጠቀሙ አሽከርካሪዎች ላይ ተፅዕኖ ሲያሳድር የቆየ ነው፡፡ በቀጣይ መንገዱ ሊያበረክት ከሚችለው መህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተቀሜታ አንጻር ደረጃ ከፍ በማድርግ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ ይሆናል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር የሚሳተፈው ድርጅት ኢሲኢ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ እና ዩኒኮን ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ በጋራ ነው፡፡ የመንገዱ የጎን ስፋት በዞን 21.5 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ የሚገነባ ይሆናል፡፡ የመንገዱ መስፋት እና ደረጃ ማደግ በመስመሩ የሚገኙ ዞኖች እና ወረዳዎችን በአስፋልት መንገድ በቅርበት በማስረተሳሰርና የትራንስፖርት ጊዜን ከ3፡30 ወደ 1፡30 ባልሞላ ጊዜ በማሳጠር የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በይበልጥ ያሳድጋል ተብሎ ይታመናል፡፡ ከዛም ባለፈ መንገዱ የሚገነባበት ስፍራ ላሉ ትንንሽ ቀበሌዎች ይበልጥ በኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥርላቸዋል፡፡ ለአካባቢው ሕብረተሰብ ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የሙያ ባለቤትም ጭምር እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡