ru
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Открыть в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 13 307 подписчиков, занимая 1 759 место в категории Транспорт и 2 546 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 13 307 подписчиков.

Согласно последним данным от 15 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 88, а за последние 24 часа — 2, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 40.23%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.41% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 352 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 050 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 17.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 16 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Транспорт.

13 313
Подписчики
+224 часа
+297 дней
+8830 день
Архив постов
የባሕርዳር - ጢስ እሳት መንገድ ግንባታ አፈጻጸም ለማሻሻል እየተሠራ ነው አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2018 (ኢ መ አ):- የጢስ ዓባይ ፏፏቴ መዳረሻ የኾነው የባሕርዳር - ጢስ እሳት መንገድ ግንባታ አፈጻጸም ለማሻሻል እየተሠራ ነው። በመንገድ ፕሮጀክቱ የገጠሙ ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ ችግር፣ የጸጥታ ስጋት እና የሥራ ተቋራጩ የአፈጻጸም ውስንነት በፕሮጀክቱ አፈጻጸም ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ የሚገኝበትን የአፈጻጻም ደረጃ ለማሻሻል የባሕርዳር አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ጥረት እያደረገ ይገኛል። ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮች አሁን ላይ በአብዛኛው የተቀረፉ ሲኾን፣ በሥራ ተቋራጩ በኩል ያሉ ውስንነቶችን ለመፍታት ተደጋጋሚ ውይይቶች እና የእርምት ርምጃዎች ተወስደዋል። በቀጣይም የቅርብ ድጋፍ እና ክትትሉ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። አሁን ላይ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 48 ነጥብ 33 የደረሰ ሲኾን፣ አስፋልት ለማንጠፍ የሚያስችሉ የቤዝኮርስ ጠጠር ማምረት እንዲሁም የውኃ መፋሰሻ ግንባታ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። በአሁኑ ወቅት በተደረጉ ጥረቶች ፕሮጀክቱን ለማፋጠን አስቻይ ሁኔታዎች በመፈጠራቸው በዚህ ዓመት የፕሮጀክቱን አፈጻጸም እስከ 80 በመቶ ለማድረስ ዕቅድ ተቀምጧል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 21 ነጥብ 2 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፣ ሀገር በቀሉ መልኮን ኮንስትራክሽን በማከናወን ላይ ይገኛል። ጎንድዋና ኢንጅነሪንግ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ያከናውናል። ለመንገድ ግንባታው 975 ሚሊዮን ብር በፌደራል መንግስት በጀት ተይዞለታል። የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ ወደ ጢስ ዓባይ ፏፋቴ ለሚመጡ ጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። በአካባቢው የሚመረቱ የተለያዩ የግብርና ምርቶች በቀላሉ ወደ ማእከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል። ወደ ባሕርዳር ከተማ የሚደረገውን የትራንስፖርት ምልልስ ያሳልጣል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የጎሬ - ማሻ - ቴፒ መንገድ ፕሮጀክት ወደ ግንባታ ለመመለስ የሚያስችሉ ጉዳዮች እየታዩ ነው አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2018 (ኢ መ አ) ፡- በተለያዩ ምክንያቶች ለጊዜው ተቋርጦ የቆየውን የጎሬ - ማሻ - ቴፒ መንገድ ፕሮጀክት ወደ ግንባታ ለመመለስ የሚያስችሉ ጉዳዮች እየታዩ ነው፡፡ 141 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የጎሬ - ማሻ - ቴፒ መንገድ ፕሮጀክት በዓለም-አቀፉ የሥራ ተቋራጭ ሃይንዳይ ዴቨሎፕመንት ካምፓኒ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በጀት ተይዞለት ግንባታው ሲከናወን እንደቆየ ይታወቃል፡፡ ኾኖም የግንባታው አጠቃላይ አፈጻጸም 62 በመቶ ከደረሰ በኋላ ከወሰን ማስከበር ጋር የተያያዙ ችግሮች በወቅቱ አለመቀረፋቸውን እንዲሁም የግንባታ ውል ዝርዝር ጉዳዮች ላይ የነበሩ አለመግባባቶችን በምክንያትነት በማንሳት የሥራ ተቋራጩ ግንባታውን ለጊዜው አቋርጧል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱን በፋይናንስ የሚደግፈው የኮሪያው ኤግዚም ባንክ ከፍተኛ አመራሮች በቀጣይ ቀናት አዲስ አበባ የሚገቡ ሲኾን፤ ግንባታው ዳግም በሚመለስበት ሁኔታ ላይ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ጋር የሚመክሩ ይሆናል፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎን የትራንስፖርት እንቅስቃሴው እንዳይስተጓጎል አስፈላጊ የጥገና ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የመንገድ ግንባታው ዳግም እስኪጀመር ድረስም የጥገና ሥራው የሚቀጥል ይሆናል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ኦሮሚያን እና ጋምቤላን በኢሉ አባቦር በኩል እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን በሸካ ዞን በኩል በቅርበት በማስተሳሰር ከፍተኛ ጠቀሜታ የሚያበረክት ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር ስድስት ወረዳዎች እና ከ15 በላይ ቀበሌዎችን በቅርበት በማገናኘት ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ትስስር የሚያጠናክር ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et\

ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሁለት ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች ተሾሙ !! ኢንጂነር ብርሃኑ ተስፋዬ በግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተርነት እንዲሁም አቶ አለማየሁ ተረፈ በኮርፖሬት
ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሁለት ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች ተሾሙ !! ኢንጂነር ብርሃኑ ተስፋዬ በግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተርነት እንዲሁም አቶ አለማየሁ ተረፈ በኮርፖሬት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተርነት ከጥቅምት 06 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተቋማችንን እንዲያገለግሉ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ተሾመዋል። ሁለቱ አመራሮች ተቋማችን ከመንግስት የተሰጠውን አገራዊ ተልዕኮ በተሻለ ብቃት እና በቁርጠኝነት በመከወን የዘርፉን ራዕይ ይበልጥ እንደሚያሳኩ በመተማመን በከፍተኛ አመራርነት እንኳን ወደ ተቋማችን ተቀላቀላችሁ በማለት መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው እንመኛለን! የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

የቡልቡላ - አላጌ - መንገድ ግንባታ 94 በመቶ ተጠናቀቀ ቡልቡላ፣ ጥቅምት 08፣ 208 (ኢ መ አ):- የቡልቡላ - አላጌ ዋናው መንገድ ግንባታ 94 በመቶው የተጠናቀቀ ሲኾን፣ ቀሪ ውስን የማጠናቀቂያ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። በተመሳሳይ የዚሁ ፕሮጀክት አካል የኾነው ከባራ - ሚቶ ያለው የ9 ነጥብ 2 ኪሎሜትር አገናኝ መንገድ ግንባታ 34 በመቶ የተጠናቀቀ ሲኾን፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የስትራክቸር እንዲሁም የሰብቤዝ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። የመንገድ ግንባታው ወደ ባራ - ሚቶ የሚወስደውን አገናኝ መንገድ ጨምሮ አጠቃላይ 38 ነጥብ 823 ኪሎሜትር ይሸፍናል። የጸጥታ ስጋት፣ በወቅቱ ያልተነሱ በመንገድ ወሰን ክልል የሚገኙ ንብረቶች በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል። ችግሮቹን ለመቅረፍ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የቡታጅራ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ባደረገው የተቀናጀ ጥረት አዎንታዊ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በመኾኑም በፕሮጀክቱ የተመዘገበውን አበረታች ውጤት በማስቀጠል ግንባታውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። የመንገድ ግንባታውን ሀገር-በቀሉ ኪቢሽ ኮንስትራክሽን በማከናወን ላይ ይገኛል። ዩናይትድ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን በመሥራት ላይ ይገኛል። ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ 878 ሚሊዮን ብር በፌደራል መንግስት ተመድቧል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ዕውን መኾን የምሥራቅ ሸዋ፣ የስልጤ እና የሀላባ ዞኖችን ጨምሮ በርካታ ከተሞችን በማገናኘት ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ትስስሩን ያጠናክራል። የጤና፣ የትምሕርት እና መሰል ማኅበራዊ ተቋማት ተደራሽነት በእጅጉ ይጨምራል። የአላጌ የግብርና እና ቴክኒክ ና ሙያ ኮሌጅ መዳረሻውን ምቹ በማደርግ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

Enjoy our content? Advertise on this channel and reach a highly engaged audience! 👉🏻 It's easy with Telega.io. As the leading platform for native ads and integrations on Telegram, it provides user-friendly and efficient tools for quick and automated ad launches. ⚡️ Place your ad here in three simple steps: 1 Sign up 2 Top up the balance in a convenient way 3 Create your advertising post If your ad aligns with our content, we’ll gladly publish it. Start your promotion journey now!

የዓለምገና - ቡታጅራ መንገድ ግንባታ እየተካሄደ ነው ቡታጅራ፣ ጥቅምት 06፣ 2018 (ኢ መ አ):- የኦሮሚያ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎችን ጨምሮ በርካታ አካባቢዎችን የሚያስተሳስረው የዓለምገና - ቡታጅራ መንገድ ፕሮጀክት እየተካሄደ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ወደ አዳዲ ማርያም ገዳም የሚወስደውን የ12 ነጥብ 7 ኪሎሜትር መንገድ ጨምሮ በጥቅሉ 132 ነጥብ 7 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል። ከጥቂት ወራት በፊት የተጀመረው የመንገድ ግንባታው አሁን ላይ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ እንዲሁም የፉካ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። የመንገድ ፕሮጀክቱ በከተማ ክልል የብስክሌት እና የእግረኛ መንገድ፣ የአነስተኛ እና ከፍተኛ ከልቨርቶች እንዲሁም የ16 ድልድዮች ግንባታ አካትቷል። የመንገድ ግንባታውን የሚያከናውናው ሀገር - በቀሉ የንኮማድ ኮንስትራክሽን በርካታ ማሽነሪዎችን ወደ ሥፍራው በማንቀሳቀስ ፕሮጀክቱን ለማፋጠን እየሠራ ይገኛል። የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ኤ አይ ሲ ፕሮጀቲስፓ ከስትራይድ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ጋር በጥምረት ያከናውናሉ። ለመንገድ ግንባታው የተመደበው 14 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል። መንገዱ ከዚህ ቀደም ጠባብ እና በአገልግሎት ብዛት በእጅጉ የተገጎዳ ሲኾን፣ አሁን ላይ በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን ከፍተኛ የትራፊክ ፍስሰት ማስተናገድ እንዲያስችል በዞን መቀመጫ የመንገድ አካፋይ፣ የእግረኛ እና የብስክሌት መንገድ ጨምሮ 26 ሜትር ስፋት ይኖረዋል። በወረዳ ከተማ 19 ሜትር፣ በቀበሌ ከተማ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል። የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ በፊት ከዓለምገና ቡታጅራ ለመጓዝ የሚወስደውን ከ3 ሰዓት በላይ የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ተኩል ያሳጥረዋል። በአካባቢው የሚገኙትን የጥያ ትክል ድንጋይ መካነ-ቅርስ እንዲሁም የአዳዲ ማርያም ገዳም የቱሪስት መዳረሻዎችን ለጎብኘዎች ምቹ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል። በመንገዱ የሚገኙትን ዓለምገና፣ ሌመን፣ ተሬ፣ ጥያ፣ ሱተን፣ ኬላ፣ ቡታጅራ እና መሰል ከተሞች ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ትስስር ያጠናክራል። በተጨማሪም የተለያዩ የግብርና ምርት ውጤቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን አከበሩ አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2018 (ኢመአ) : የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ!” በሚል መሪቃል አከበሩ፡፡ ቀኑን አስመልክቶ በተላለፈው መልዕክት ሰንደቅ ዓላማ የኢትዮጵያ የጀግንነት፣ የአሸናፊነት፣ የአንድነትና የድል ምልክት እንደሆነና አባቶቻችን ለሀገር ሉዓላዊነት አጥንታቸውን ከስክሰውና ደማቸውን አፍሰው ያቁዩት የሉዓላዊነት ምልክዕት መሆኑ ተገልጿል፡፡ “አርበኝነትና ጀግንነት በደም ብቻ ሳይሆን በላብ ማህተም የሚጸና ነው” በሚል ተሰምሮበታል፡፡ ቀኑን ስናከብር በብዝሃ አርበኝነትና ጀግንነት ለኢትዮጵያ መንሰራራት በአንድነት መቆም እንደሚገባም መልዕክት ተላልፏል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የያቤሎ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት 98 በመቶ ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣ መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢመአ): ሰባት ነጥብ አራት ኪሎሜትር የሚረዝመው የያቤሎ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት 98 በመቶ ተጠናቅቋል፡፡ የመንገድ ግንባታው በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተሰራ የሚገኝ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱን በማካሄድ ላይ ያለው የስራ ተቋራጭ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ነው፡፡ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃ.የተ.የግ.ማ. በጥምረት እየሰሩ ነው፡፡ መንገዱ በሁለት መቶ ዘጠና ስድስት ሚሊዮን ስምንት መቶ ሃምሳ ሶስት ሺህ አምስት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ብር (296,853,599 ) እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን፣ ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት ተሸፍኗል፡፡ በመንገድ ስራው ከተከናወኑት ስራዎች መካከልም የጠረጋ ስራ፤ አፈር ሙሌት፣ የመንገድ ግራና ቀኝ የዉሃ ማፍሰሻ፣ የድልድይ እና የአስፋልት ስራ ተከናውነዋል፡፡ በመንገዱ ግንባታ በእስካሁኑ ስራም 7 ኪሎ ሜትር ሙሉ በሙሉ የአስፋልት ስራ ተጠናቋል፡፡ መንገዱ 21.5 ሜትር ስፋት ሲኖረው፣ 14 ሜትር አስፋልት፤ የእግረኛ መንገድ እና የመንገድ አካፋይን አካቶ ይዟል ፡፡ የመንገድ ግንባታ ስራው ሲጠናቀቅ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ያቤሎ ከተማ የሚስተዋለውን ከፍተኛ የትራፊክ ጫና ይቀንሳል፡፡ የዞኑ ዋና መቀመጫ ከመሆኑም በተጨማሪ የመንገዱ መገንባት ለነዋሪዎቹ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታዎችን ያስገኛል፡፡ ለአብነትም የቀንድ ከብት ንግድ፣ ለስንዴ ምርት፣ ለጤፍ ፣ ለማዕድን ምርት ብሎም በአከባቢው ለሚገኘው የቦረና ብሄራዊ ፓርክን ጨምሮ የዚህ መንገድ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጾ ያበረክታል፡፡ መንገዱ ቀጠናዊ የንግድ ትስስርን ከማጠናከር አንጻርም ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢ .ፌ. ዴ. ሪ ከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ አዲስ አበባ፣ መስከርም 28 ፣ 2018 (ኢ መ አ):- የስምምነት ሰነዱ በቅርቡ ይፋ የሆነውና እ. ኤ. አ ከ2025-2050 ባሉት 25 ዓመታት ውስጥ እንዲሣካ የሚጠበቀውን የኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢኒሼቲቭ ከፍ ወዳለ የእድገት ደረጃ ለማሸጋገር ከፍተኛ ፋይዳ ያለውን ነው፡፡ ስምምነቱን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴርን በመወከል የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር የትምጌታ አስራት እንዲሁም የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበርን በመወከል ደግሞ የማህበሩ ፕሬዚዳንት የሱፍ መሀመድ ተፈራርመዋል ። ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ እና የፋይናንስ ዕቅድ የጥራት ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲሰሩ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ ከስምምነቱ አላማዎች መካከልም ለኮንስትራክሽን ኢንደስትሪው ትራንስፎርሜሽን ኢኒሼቲቭ መሳካት የባለድርሻ አካላትን ማስተባበር ፣ ከብልሹ አሰራር በፀዳ መልኩ የጋራ እና የተናጥል ኃላፊነት መውሰድ ፣ ለሚፀድቁ መመሪያዎች ተገዥ መሆን ተጠቃሾች ናቸው ። ከዚህም ባሻገር ለኮንስትራክሽን ኢንደስትሪው እድገት የሚበጁ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ፣ የአሰራር ስርአቶችን ፣ እንዲሁም የተለያዩ ስልጠናዎችን ለስራ ተቋራጮች ተደራሽ እንዲሆኑ ቀጣይነት ባለው መልኩ በጋራ መስራትም የሰነዱ ተጨማሪ አላማዎች ናቸው ። በስራ ላይ እንዲውሉ የሚዘጋጁ አዋጆች ፣ ደንቦችና መመሪያዎች አሳታፊ በሆነ መንገድ እንዲዘጋጁና ተግባራዊ እንዲሆኑ ማድረግ ፤ ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው እቅድ መሰረት እንዲመሩ ማስቻል ፣ የተጀመሩ የአቅም ማጎልበቻ ተግባራትን ማጠናከር እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማመቻቸት ተወዳዳሪነትን መፍጠር በሚኒስቴሩ እና በተቋራጮች በኩል ከሚከናወኑ ተግባራት መካከልም በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ በተጨማሪም በሚኒስቴሩ በኩል እየተዘጋጀ ስላለው የኢንዱስትሪ ስነ-ምግባር መመሪያ የማህበሩ አባላት ተገቢውን ግንዛቤ አግኝተው ተገዥነታቸውን በማረጋገጥ ከሚኒስትሩ ጋር በጋራ እንደሚሰሩ ተገልጿል ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን አሠራር ማዘመን ለዲጅታል ኢትዮጵያ ወሳኝ ተደማሪ ምዕራፍ ነው - ሚንስትር ጫልቱ ሳኒ አዲስ አበባ፣ መስከርም 27፣ 2018 (ኢ መ አ):- የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ዲጅታይዝ ማድረግ ዲጅታል ኢትዮጵያን በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ ሚና አለው ሲሉ የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስትር ጫልቱ ሳኒ ተናግረዋል። የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን የአሠራር ሥርዓት ለማዘመን የሚያስችለው የ "ኮንስትራክሽን ሬጉላቶሪ ኢንፎርሜሽን ሲስተም" ዲጂታል የመተግበሪያ ሥርዓት በዛሬው ዕለት በብሔራዊ ሳይንስ ሙዚየም በይፋ ተበስሯል። የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር ጫልቱ ሳኒ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ዛሬ ይፋ የተደረገው ዲጅታል መተግበሪያ በቅርቡ ይፋ የተደረገው የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢንሼቲቭ አንዱ አካል ነው። የዲጅታል መተግበሪያው የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ዘላቂ ተወዳዳሪ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲኾን በማስቻል ረገድ ወሳኝ ምዕራፍ ነው ብለዋል። ይህም በዘርፍ ላይ ይበልጥ ዕምነት እንዲፈጠር ያስችላልም ብለዋል። ፕሮጀክት በማስተዳደር እና በመፈጸም ረገድ አዎንታዊ ለውጦች መታየታቸውን ያነሱት ሚንስትሯ፣ መተግበሪያው ዘርፉን ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግ መኾኑን ገልጸዋል። የዲጅታል መተግበሪያው በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ መልማቱ መንግስት ለዲጅታል ኢትዮጵያ የሰጠው ትኩረት አንዱ ማሳያ እንደኾነም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ከአጠቃላይ ኢኮኖሚው 20 በመቶ ድርሻ እንዳለው አንስተው ኢንዱስትሪውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ወሳኝ ምዕራፍ ነው ብለዋል። የዲጅታል መተግበሪያው የዘርፍን የአሠራር ሥርዓት በማዘመን ብልሹ አሠራርን የሚያስቀር፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን የሚያስችል መኾኑን ተናግረው። ሶፍትዌሩ 9 ንዑሳ ክፍሎች እንዳሉት ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ ደኅንነቱ ሙሉ በሙሉ የተረጋገጠ መረጃ የሚሰጥ ሥርዓት ነው ብለዋል። ከግንባታ ፍቃድ ጋር ተያይዞ የተንዛዙ የአሠራር ሂደቶችን በማስቀረት የተቀላጠፈ የአሠራር ሥርዓት መኾኑንም አንስተዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et