ru
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Открыть в Telegram
5 344
Подписчики
-22624 часа
-2 2007 дней
-2 65830 день
Архив постов
ይህን ያውቁ ኖሯል.....? በአድዋ ተራራዎች ላይ የአንባገነኑ መሪ የቤኒቶ ሙሶሊኒ የፊት ቅርፅ ሐውልት ቆሞ እንደነበር...... በ 2ተኛ የኢጣሊያን ወረራ ዘመን በአድዋ በሱሎዳ ተራራ ፊት ለፊት ላ
+6
ይህን ያውቁ ኖሯል.....? በአድዋ ተራራዎች ላይ የአንባገነኑ መሪ የቤኒቶ ሙሶሊኒ የፊት ቅርፅ ሐውልት ቆሞ እንደነበር...... በ 2ተኛ የኢጣሊያን ወረራ ዘመን በአድዋ በሱሎዳ ተራራ ፊት ለፊት ላይ በፋሺስት ወታደሮች የተገነባው ይህ ሃውልት ቁመቱ 4.80 ሜትር ከፍታ የነበረው ሲሆን ፤ የጣሊያን ወታደሮች በወቅቱ የዚህ ሐውልት በቦታው የመገንባታቸው ዋንኛው ዓላማ እና ለማስተላለፍ የፈለጉት መልዕክት:- ➻ በ 1888 ዓ.ም ላይ የደረሰባቸውን ሽንፈት በውስጣቸው ለነበረው ቁጭት እና እፍረት ማካካሻ ይሆናል ብለው በማሰብ እንዲሁም በሃጉረ አፍሪካ ለነበሩት ለሌሎቹ የቀኝ ገዢዎች የአውሮፓውያን ሃገራት የጠንካራነት ማሳያ የሞራል ማበረታቻ ምልክት ይሆናል በማለት ነበር ከ 40 ዓመት በፊት ሽንፈታቸው ከተጎነጩባት ቦታ ላይ በወርሃ የካቲት 1928 ዓ.ም ላይ ገንብተው ያቆሙት። ሆኖም ግን አሁን ሐውልቱ በቦታው የለም ሀገራችን ከፋሺስት ጣሊያን ነፃ ከሆነች በኋላ በቦታው ምንም አይነት የሐውልቱ አሻራ እና ፍርስራሽ እንዳይኖር ተደርጎ ሊፈረስ ችሏል። ክብርና ሞገስ ከወራሪ ነፃ ሀገር ላስረከቡን ጀግኖች አርበኞቻችን 🙏 #ታሪክን_ወደኋላ

ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች 🇬🇧በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ 10:00 | ዌስትሃም ከ ኤቨርተን 11:00 | አስቶን ቪላ ከ ሉተን 11:00 | ብራይተን ከ ፉልሃም 11:00 | ሊቨርፑል ከ ኖቲንግሃም 12
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች 🇬🇧በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ 10:00 | ዌስትሃም ከ ኤቨርተን 11:00 | አስቶን ቪላ ከ ሉተን 11:00 | ብራይተን ከ ፉልሃም 11:00 | ሊቨርፑል ከ ኖቲንግሃም 12:30 | ማንችስተር ዩናይትድ ከ ማንችስተር ሲቲ 🇪🇸በስፔን ላሊጋ 10:00 | ሪያል ቤቲስ ከ ኦሳሱና 12:15 | ራዮ ቫልካኖ ከ ሪያል ሶሴዳድ 02:30 | አትሌቲክ ቢልባዎ ከ ቫልንስያ 05:00 | አትሌቲኮ ማድሪድ ከ አላቬስ 🇫🇷በፈረንሳይ ሊግ 1 09:00 | ብረስት ከ ፒኤስጂ 11:00 | ሊል ከ ሞናኮ 11:00 | ሜትዝ ከ ሌ ሃቭሬ 11:00 | ሞንፔሌ ከ ቶሉስ 01:05 | ሬንስ ከ ስታርበርግ 04:45 | ማርሴ ከ ሊዮን 🇩🇪በጀርመን ቡንደስሊጋ 11:30 | ፍራንክፈርት ከ ዶርትሙንድ 01:30 | ባየር ሌቨርኩሰን ከ ፍራይበርግ 🇮🇹በጣልያን ሴሪ ኤ 08:30 | ካግላሪ ከ ፍሮሲኖን 11:00 | ሞንዛ ከ ዩድንዜ 02:00 | ኢንተር ሚላን ከ ሮማ 04:45 | ናፖሊ ከ ኤሲ ሚላን 

ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች 🇬🇧በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ 👉 08:30 | ቼልሲ ከ ብሬንትፎርድ 👉 11:00 | አርሰናል ከ ሼፊልድ 11:00 | በርንማውዝ ከ በርንሌይ 👉 01:30 | ወልቭስ ከ
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች 🇬🇧በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ 👉 08:30 | ቼልሲ ከ ብሬንትፎርድ 👉 11:00 | አርሰናል ከ ሼፊልድ 11:00 | በርንማውዝ ከ በርንሌይ 👉 01:30 | ወልቭስ ከ ኒውካስትል 🇪🇹በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 09:00 | ፋሲል ከነማ ከ ኢትዮጵያ ቡና 12:00 | ወላይታ ድቻ ከ መቻል 🇪🇸በስፔን ላሊጋ 09:00 | አልሜሪያ ከ ላስ ፓልማስ 11:15 | ባርሴሎና ከ ሪያል ማድሪድ 01:30 | ማሎርካ ከ ሄታፈ 04:00 | ካዲዝ ከ ሴቪያ 🇫🇷በፈረንሳይ ሊግ 1 12:00 | ሬምስ ከ ሎሬንት 04:00 | ሌንስ ከ ናንትስ 🇩🇪በጀርመን ቡንደስሊጋ 10:30 | ኦግስበርግ ከ ዎልቭስበርግ 10:30 | ሞንቼግላድባህ ከ ሃይድንየም 10:30 | ባየር ሙኒክ ከ ዳርምስታድት 10:30 | ስቱትጋርት ከ ሆፈናየም 10:30 | ወርደር ብሬመን ከ ዩኒየን በርሊን 01:30 | RB ሌብዝግ ከ ኮለን 🇮🇹በጣልያን ሴሪ ኤ 10:00 | ሳሱሎ ከ ቦሎኛ 01:00 | ሊቼ ከ ቶሪኖ 03:45 | ጁቬንቱስ ከ ቬሮና 🇸🇦በሳውድ አረቢያ ሊግ 12:00 | አል ፋይሀ ከ አል ናስር

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አርብ ጥቅምት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና ደቡብ አፍሪካ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነታቸውን በማጠናከር በወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት ተስማሙ። በ116ኛው
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አርብ ጥቅምት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና ደቡብ አፍሪካ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነታቸውን በማጠናከር በወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት ተስማሙ። በ116ኛው የሠራዊት ቀን በዓል ላይ የታደሙት የደቡብ አፍሪካ መከላከያ ሰራዊት ትምህርትና ልማት ዳይሬክተር ከኢፌዴሪ መከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ሀላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮነን ጋር  በወታደራዊ ትምህርት እና ሥልጠና ዙሪያ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል። ኢትዮጵያ እና ደቡብ አፍሪካ ሰራዊታቸውን ለማዘመን በሚያደርጉት ጥረት ሀገራቱ ልምድና ተሞክሯቸውን እንዲለዋወጡ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ስምምነት መደረጉን ሌተናል ጀኔራል ይመር መኮንን ገልፀዋል። የደቡብ አፍሪካ ትምህርትና ልማት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጀኔራል ዞዲ ሰዋ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካ ነፃነት ያበረከተችው አሰተዋፅኦ የጎላ እንደነበረ አስታውሰዋል ። ለዘመናዊ ሰራዊት ግንባታ በጋራ ለመስራት የደረሱበት ስምምነት ለሁለቱም ሀገራት ሰራዊት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ እንደሚሆንም ተናግረዋል። በተለይም ደቡብ አፍሪካ ከኢትዮጵያ የሰላም ማስከበር ተልእኮ ስኬቶቿ እና ከአየር ሀይሏ ዘመናዊነት ልምድና ተሞክሮ መውሰድ እንደምትፈልግ ብርጋዲየር ጀኔራል ዞዲ ሰዋ ገልፀዋል ። በዚህ የስምምነት መድረክ ለጀኔራል መኮንኗ ስለ ኢትዮጵያ ዋር ኮሌጅ እና የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን ብርጋዲየር ጀኔራል ዞዲ ሰዋ ደቡብ አፍሪካ በዚህ ረገድ የቀደመ ልምድ ያላት ሀገር በመሆኑ ለኮሌጆቹ በቁሳቁስና በካሪኩለም ቀረፃ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

ሊቨርፑል ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል ! በዩሮፓ ሊግ የምድብ ሶስተኛ ጨዋታ ሊቨርፑል ቱሉዝን 5 ለ 1 ፣ ብራይተን አያክስን 2ለ0 እንዲሁም ሮማ ስላቭያ ብራግን 2ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
ሊቨርፑል ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል ! በዩሮፓ ሊግ የምድብ ሶስተኛ ጨዋታ ሊቨርፑል ቱሉዝን 5 ለ 1 ፣ ብራይተን አያክስን 2ለ0 እንዲሁም ሮማ ስላቭያ ብራግን 2ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል። የሊቨርፑልን የማሸነፊያ ግቦች ዋታሩ ኢንዶ ፣ ዲያጎ ጆታ ፣ ግራቨንበርች ፣ ዳርዊን ኑኔዝ እና ሞሀመድ ሳላህ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል። የብራይተንን የማሸነፊያ ግቦች ፔድሮ እና አንሱ ፋቲ እንዲሁም ለሮማ ሮሜሎ ሉካኩ እና ቦቭ ማስቆጠር ችለዋል። የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ያደረጋቸውን ሁሉንም ጨዋታዎች በማሸነፍ በዘጠኝ ነጥቦች ምድቡን በመምራት ላይ ይገኛል። ሞሀመድ ሳላህ በአውሮፓ ውድድሮች ላይ አርባ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ቴሪ ሄንሪን በአንድ ግብ በልጦ ለፕርሚየር ሊግ ክለብ ብዙ ግብ ማስቆጠር የቻለ ተጨዋች መሆን ችሏል የጆዜ ሞሪንሆው ቡድን ሮማ በበኩሉ ሁሉንም ጨዋታዎች ያሸነፈ ሲሆን ዘጠኝ ነጥቦችን በመሰብሰብ ምድቡን በበላይነት ይመራል። ብራይተን በአራት ነጥቦች በምድቡ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። በአሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ የሚመራው ባየር ሌቨርኩሰን በበኩሉ ካራባግን 5ለ1 በሆነ ሰፊ ውጤት ያሸነፈ ሲሆን ምድቡን በዘጠኝ ነጥቦች በመምራት ላይ ይገኛል። @tikvahethsport     @kidusyoftahe

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃሙስ ጥቅምት 15 ቀን  2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሠራዊት ጀግንነት በኬንያዊው ጄኔራል አንደበት  ልጆችሽ በመስዋዕትነታቸው አስከበሩሽ፣ በደምና በአጥንታቸው የማትደፈሪ አደረጉሽ፤ ውድቀትሽን በሚመኙልሽ ፊት ከፍ ከፍ አደረጉሽ፣ መጥፋትሽን በሚያልሙት ፊት አደመቁሽ፣ በታሪክ ብራና ላይ አረቀቁሽ፡፡ በማይናወጥ የክብር ዙፋን ላይ አስቀመጡሽ፡፡ በረሃውን አይፈሩትም፣ በረዶውንም አያስታውሱትም፣ እሾህና አሜካላውንም አይሰቀቁትም፣ ጦርና ጎራዴውንም አይደነግጡለትም፣ ስምሽን አንግበው፣ ሠንደቅሽን አስቀድመው በሞት መካከል ይረማመዳሉ፣ በጠላት ፊት እንደ አንበሳ ያገሳሉ፣ እንደ ነብር ይቆጣሉ፣ ከሁሉም ልቀው ጠላቶቻቸውን ይጥላሉ፣ ኃያላን ነን የሚሉትን ይሰብራሉ፣ ወንድ ከእኛ በላይ የሚሉትን ያንበረክካሉ፣ ሠንደቅሽን በጠላት ሠፈር በኩራትና በድል አድራጊነት ያውለበልባሉ ጀግኖቹ የኢትዮጵያ ወታደሮች፡፡ ጀግኖቹ ታድያ የራሳቸው ቀን የሆነውን የሠራዊት ቀንን “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” በሚል መሪ ቃል  116ኛውን  በዓል በተለያዩ መረሃ-ግብሮች እያከበሩ ውለዋል የኢትዮጵያ ህዝብም በዓሉን አክብሮት ውሏል። በአትሚስ ጥላ ስር የሚገኙት የኢትዮጵያ 7ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ በዓሉን ሲያከብሩት የሴክተር 6 ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሉካስ ኩቶ ስለ ኢትዮጵያ ወታደር እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ወታደር በየትኛውም የአየር ጠባይ ግዳጁን የሚወጣ እና ሁሌም ድል አድራጊ የሆነ ሠራዊት መሆኑን በሚገባ አውቃለሁ ብለዋል። በቀጠናው የኢትዮጵያ ወታደሮች በመኖራቸው በርካታ ነገሮችን መስራት ተችሏል በተለይ በሶማሊያ አንፃራዊ ሠላም እና መረጋጋት እንዲኖር ከላብ ጠብት እስከ ህይወት መስዋዕትነት እየከፈሉ ያሉ የቁርጥ ቀን ልጆች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። ዓለም አቀፍ አሸባሪ የሆነው አልሸባብ የኢትዮጵያን ወታደሮች ጋር ቆሞ መዋጋት እንደማይችል እና እንደማይፈልግ በተለያዩ ጊዜያት አረጋግጫለሁ አይቻለሁ ይህ ደግሞ የእናንተን ጀግንነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ጄኔራል ሉካስ ኩቶ በመጨረሻም እኔ በምመራው ሴክተር ውስጥ የኢትዮጵያ 1 ሻለቃ በመኖሩ ከምነግራችሁ በላይ እጅግ በጣም ደስተኛ ነኝ ምክንያቱም ጀግኖች፣አሸናፊዎች፣ቆራጦች በመሆናችሁ ጭምር ነው። በሠላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ያላችሁም በኢትዮጵያ ውስጥም ለምትገኙ የጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አመራሮች እና አባላት እንኳን 116ኛው የሠራዊት ቀን አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። "በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት"

ኢትዮጵያ በሃይልና በወረራ ማሳካት የምትፈልገው ነገር የለም - ጠ/ሚ ዐቢይ የሀገሪቱ መከላከያ ሰራዊትም “በሃይል ፍላጎቶቻችን ለማሳካት ቃታ እንደማይስብ አረጋግጥላችኋለሁ” ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ  ኢትዮጵያ በሃይል እና በወረራ ማሳካት የምትፈልገው ነገር የለም አሉ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ 116ኛው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ቀን በአዲስ አበባ ሲከበር ባደረጉት ንግግር፥ የመከላከያ ሠራዊት ዋነኛ ዓላማው ሰላምን ማጽናት መሆኑን አንስተዋል። የመከላከያ ሰራዊት በሃይል የሀገሪቱን ፍላጎት ለማሳካት ቃታ እንደማይስብም ነው የተናገሩት። በውጊያ ከማሸነፍ በሰላም ማሸነፍ እጅጉን ይበልጣል” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ መላው የኢትዮጵያ ሃይል በድርድር በውይይት ኢትዮጵያን የሚያጸና ስራን እንዲያከናውን ጥሪ አቅርበዋል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከኢትዮጵያ ያነሰ ዓላማ የለውም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ “ሰራዊቱ የተደራጀው ለኢትዮጵያውያን፣ የሚመራው በኢትዮጵያውያን እና የሚሰራው ለኢትዮጵያ ነው” ሲሉም ተናግረዋል። የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በበኩላቸው ሉዓላዊነቷ ሳይደፈር የተረከብናትን ሀገር እንደታፈረችና እንደተከበረች ለማስቀጠል ዝግጁ መሆናችንን ለሕዝባችን እናረጋግጣለንም ብለዋል። “የሠራዊታችንን ዝግጁነት በማዳበር የማድረግ ዐቅማችንን በማሣደግ የውጭም ሆነ የውስጥ የጸጥታ ሥጋትን እየመከትን ነው” ሲሉም ገልጸዋል፡፡ የምድር፣ የዓየር፣ የባህር እና የሳይበር ኃይላችን ዘመኑን እና ኢትዮጵያን በሚመጥን ሁኔታ በመገንባት አስተማማኝ ደረጃ ላይ አድርሰናል ነው ያሉት፡፡ በሱዳን የተከሰተው ችግር በኢትዮጵያም እንዳይከሰት በማሰብ የታጠቁ ኃይሎችን እና ኢ- መደበኛ አደረጃጀቶችን ወደ ህጋዊ መስመር ለማስገባት እየተሠራ መሆኑንም ነው የተናገሩት። ኢትዮጵያ በዘመናዊ መልኩ የመከላከያ ሰራዊት ያደራጀችው ጥቅምት 15 ቀን 1900 ዓ.ም እንደነበር ይነገራል። የወቅቱ የኢትዮጵያ መሪ አጼ ምኒሊክም ፊታውራሪ ሃብተጊዮርጊስ ዲነግዴ (አባ መላ)ን የመጀመሪያው የጦር ሚኒስትር አድርገው መሾማቸው የሚታወስ ነው።