የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Открыть в Telegram
4 889
Подписчики
-25624 часа
-1 8217 дней
-3 02830 день
Архив постов
የኢፌዴሪ መከላከያ የካቲት 09 ቀን 2015 ዓ.ም
የዓድዋን ድል በአል የድሉን ታላቅነት በሚመጥን መልኩ ለማክበር ዝግጅት መጀመሩን የተቋቋመው ኮሚቴ አሥታወቀ።
ኮሚቴው የተቋቋመው ከመከላከያ ሚኒስቴር ከባህል እና ስፖርት ሚንስቴር እንዲሁም ለበአሉ በድምቀት መከበር አስተዋፅኦ ያበረክታሉ ተብለው እምነት ከተጣለባቸው አካላት ነው።
በመሆኑም በአሉን በተደራጀ እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅቱን ለማሠናዳት ታሳቢ ተደርጎ የተቋቋመው ኮሚቴ በዛሬው እለት በመከላከያ ዋና መሥሪያ ቤት መግለጫ ሰጥቷል።
የባህል እና ስፖርት ሚንስትሩ አቶ ቀጀላ መርዳሳ የአድዋ ድል በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ በጣሊያን ቅኝ ገዥዎች እና ለነፃነት በታገሉት የኢትዮጵያ ህዝቦች መካከል በአድዋ ተራራ እና አካባቢው በተደረገ ጦርነት ከየአቅጣጫው የመጡ የኢትዮጵያ ህዝቦች ጠላትን ድባቅ በመምታት አንፀባራቂ ድል የተጎናፀፋበት እና የአፍሪካዊያንን የትግል ታሪክ የቀየረ ታላቅ በዓል ነው ብለዋል።
የአድዋ ድል በቀላሉ የተገኘ ሳይሆን በርካታ የኢትዮጵያ ጀግኖች የህይወት መስዋዕትነት ከፍለው ለእኛ ለልጆቻቸው የሰጡን ዘመን ተሻጋሪ ታሪካችን ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ይሁን እንጅ ይኸው ታላቅ በዓል እስካሁን ድረስ ትኩረት ተሰጥቶት በተከፈለው ዋጋ ልክ እየተከበረ ነው ብለን አናምንም ዘማች አሰልፈው በጀግንነት መርተው በጦርነቱ ላይ የወደቁ ጀግኖች አልተዘመረላቸውም አልተነገረላቸውም ነው ያሉት።
የመከላከያ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት አዳነ በበኩላቸው የአድዋ ድል እንደማንኛውም የአውደ ውጊያ ድሎች በውጊያ የተገኘ ብቻ ሳይሆን ዘመንም ወንዝም ተሻጋሪ ሚስጢረ ብዙ ድል ነው ፤መገፋትን የሚጠሉ እና ነፃነትን አብዝተው የሚሹ አባቶቻችን የአካል እና የህይወት መስዋዕትነት ከፍለው ለእኛ ለልጆቻቸው በክብር ያስረኩብን ታላቅ ታሪክ ነው ብለዋል።
በአሉ በተመዘገበው ድል ልክ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከበረ ባለመሆኑ የድሉን ታላቅነት እና ሀያልነት አጉልቶ በሚያሳይ መልኩ ለማክበር ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራ መጀመሩንም አስታውቀዋል።
በበአሉ ዕለት 21 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ፣ ጀግና አርበኞቻችንን ለማስተወስ ከጥንታዊት ኢትዮጵያ አርበኞች ማህበር ጋር በጋራ በመሆን በዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ አደባባይ የአበባ ጉንጉን እንደሚቀመጥ፣ በዘመን መካከል እየተፈተነች ፈተናውን አልፋ በፅናት የቆመችውን ኢትዮጵያ በክብር የተረከበው የኢፊዴሪ መከላከያ ሰራዊት እግረኛ ጦር ወደ አድዋ ሲሄዱ ጀግና አባቶቻችን የተሻገሩትን የአድዋ ድልድይ ወትሮ ዝግጁነቱን በአሟላ ሞራል ሲሻገር የሚያሳይ በመጨረሻም የበአሉ ፍፃሜ በመስቀል አደባባይ እንደሚሆን ኮሎኔል ጌትነት ተናግረዋል።
የአድዋ ድል በአል የግለሰብ ሳይሆን የህዝብ እና የሀገር በመሆኑ የተወሰኑ ቡድኖች እና ግለሰቦች የፖለቲካ ማስፈፀሚያ ሊሆን አይገባም። ከአላማው ውጭ በአላስፈላጊ ፍላጎቶች እንዳይጠለፍ በተደራጀ እና በተማከለ ደረጃ ይመራል፣ የአንድነታችን ፈተናዎች እና ስጋቶች አንዱ ማስወገጃ መንገድ አድርገን እንጠቀምበታለን እንጅ ማባባሻ እንዲሆን በፍፁም አንፈቅድም፣ ድሉን የጋራችን አድርገን ልናስቀጥል ይገባል ብለዋል።
👉 የኮማንዶ፣ የአየር ወለድና ልዩ ኃይል ማሠልጠኛ ማዕከል ብቁ እና ጠንካራ የሀገር ባለውለታ ኮማንዶዎችን እያፈራ ነው‼️-- ኮሎኔል ቦጃ አጋ
የኮማንዶ፣ የአየር ወለድና ልዩ ኃይል ማሰልጠኛ ማዕከል ብቁ እና ጠንካራ የሀገር ባለውለታዎችን አሰልጥኖ የማብቃት ተልዕኮውን በአስተማማኝ ብቃት እያከናወነ እንደሚገኝ የማሠልጠኛ ማዕከሉ አዛዥ ኮሎኔል ቦጃ አጋ ተናገሩ፡፡
በተለይ ባለፉት አራት ዓመታት የአሠልጣኞችን ብቃት እና ብዛት ማሳደግ ላይ በትኩረት መሰራቱ፤ የተፈለገውን ዓይነት የስልጠና ቁሳቁስ ማሟላት ላይ በጥረት መንቀሳቀስ መቻሉ፤ ሥልጠናውን ከብቃት ጋር ሊያሣልጡ የሚችሉ አዋጪ ተግባራት ሆነው መከናወናቸውንም አዛዡ አብራርተዋል፡፡
ለስልጠና ምቹ የሆነ የመሬት አቀማመጥ መምረጥ፣ እንደ አስፈላጊነቱ የማሥተካከል ሥራ ማከናወን፣ ተገቢ እና ወሳኝ የሆኑ የተኩስ ወረዳዎችን መምረጥ፣ ለአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተስማሚ የሆኑ ወረዳዎችን በቁጥር የበዛ ኃይል ሊያሠለጥኑ በሚችሉበት አግባብ የማመቻቸት ሥራ በትኩረት መሠራቱንም ኮሎኔል ቦጃ ገልፀዋል፡፡
የአሰልጣኞችን ቁጥር ከብቃት ጋር ማብዛት፣ የሰልጥኖ አሰልጣኝ ሥልጠና መስጠት፣ ለማሰልጠኛ ማዕከሉ የሚያስፈልጉ ማህበራዊ አገልግሎት መሥጫዎችን የማሥፋፋት እና የሠልጣኙን ፍላጎት በሚያረካ መልኩ ማሥፋፋት ላይ የተመሰረቱ ዘርፈ-ብዙ ተግባራትም ተከናውኗል፡፡
በእነኝህ የዝግጅት እና የማስፋፋት ስራዎች ላይ ቀድሞ በመዘጋጀት፤ ባሳለፍናቸው እልህ አስጨራሽ ተልዕኮዎች ተኩሶ መምታት፣ ሩጦ መያዝና ተዋግቶ ማሸነፍ የሚችል፣ በአካል ብቃቱ እና በወታደራዊ ጥበብ እንዲሁም በሙያው የተካነ በሳል እና አስተዋይ የኮማንዶ ኃይል በተከታታይነት አሰልጥኖ ማብቃት እንደተቻለም ገልፀዋል፡፡
በብላቴ ማሰልጠኛ ማዕከል ሸልጥነው የተመረቁ ባለቀይ መለዮ ለባሾች በፈፀሙት አኩሪ ተጋድሎ እና ጀግንነት፤ የሀገር ባለውለታ መሆናቸውን እስከወዲያኛው ፅፈው ያለፉ ስለመሆናቸው "ማርሽ ቀያሪ" የሚለው ስያሜያቸው አንዱ ማረጋገጫ ነው ሲሉ አዛዡ ተናግረዋል።
የካበተ ወታደራዊ የሙያ አቅም ባላቸው አሰልጣኞች ሌት ተቀን የሚሠጠው ሁለንተናዊ የኮማንዶ አባላት ሥልጠና፤ የዘመኑን ቴክኖሎጂ የዳሰሰና አዳዲስ የሥልጠና አቅጣጫዎችን የተከተለ መሆኑንም ኮ/ል ቦጃ ጠቁመዋል፡፡
ማሠልጠኛ ማዕከሉ በቀንም ሆነ በማታ፣ በብርድም ሆነ በሙቀት፣ በሜዳም ይሁን በተራራ... በማንኛውም መሰናክል በበዛበት የመሬት ገፅና የአየር ፀባይ ተዋግቶ ማሸነፍ የሚችል የኮማንዶ፣ የአየር ወለድ እና የልዩ ኃይል አባላት በብዛትና በጥራት አሰልጥኖ እያስመረቀ እንደሚገኝ አዛዡ አስረድተዋል፡፡
FDRE Defense Force
✍️ እነሆ አፍሪካ አንድ ሆና ከተባበረች ግንቦት ሲመጣ 60 አመት ይሞላታል!!
~~
በስላባት ማናዬ
ያኔ የአፍሪካ አንድነት የተመሰረተ ሰሞን ብዙዎቹ የአፍሪካ ሀገራት ነጻ እየወጡ ነበር፡፡ ፍጹም ነጻነት ያላገኙ ሀገራትም ነበሩበት፡፡ ከብዙ ጥረት በኋላ ሀሳቡ ተቀባይነት አገኘና የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት ነጻዎቹ የአፍሪካ መንግስታት ተስማሙ፡፡ ነገር ግን ማን አስተባብሮ ድርጅቱን ይመስርት? ቻርተሩንስ ማን ያሰናዳው? የድርጅቱስ መቀመጫ የት ይሁን? የሚሉት መልስ የሚፈልጉ ዋና ጥያቄዎች ነበሩ፡፡
በዚህ ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያ ‹‹እኔ ሀላፊነቱን እወጣለሁ›› ስትል በቀዳማዊ ሀይለስላሴ መሪነት ሀገራቱን አንድ ለማድረግ ተነሳች፡፡ አንድ ማድረግ ሲባልም የመጀመሪያውን የምስረታ ስብሰባ ለማዘጋጀት መነሳሳት ማለት ነው፡፡
ኢትዮጵያ ‹‹አንድ እንሁን›› የሚለውን ጥያቄ እንዳነሳች ከየአካባቢው ተቃውሞው ተነሳ፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ የመሰብሰቢያ አዳራሽ መንገድና ሆቴል የላትም፡፡ ንጽህና የላትም፡፡ ስብሰባውን ለማድረግ ሌጎስ ፣ ናይሮቢና ካይሮ ይሻላሉ›› የሚል ሀሳብ ቀርቦ ነበር፡፡ነገር ግን ቀዳማዊ ሀይለስላሴ በነበራቸው ፖለቲካዊ ብስለት አዲስ አበባ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ጉባኤን እንድታዘጋጅ ከውሳኔ ላይ ተደረሰ፡፡ ከወሰኑም በኋላ የካቢኔ ሚኒስትሮቻቸውን ሰብስበው ጉዳዩን ዘርዘር አድርገው አስረዱ፡፡‹‹…….ጊዜው እየሄደ ነው፡፡ያሉን 12 ወራቶች ብቻ ናቸው፡፡ መሪዎች ሲመጡ የሚያርፉበት ሆቴል የለም፡፡ ጎበዝ እንዴት ይህን ሃላፊነት እንወጣ?›› በማለት ጃንሆይ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ በጊዜው ለዝግጅት የተሰጠው ጊዜ በጣም አጭር ነበር፡፡ ልኡል ራስ መንገሻ ስዩም እንዳሉት ‹‹……. ይህን ስብሰባ የማዘጋጀቱ እድል ሊያመልጠን አይገባም፡፡ ገንዘቡ ከተፈቀደልኝ በተባለው ጊዜ ውስጥ እንዲያውም ከዛ ቀደም ብዬ በ10ወር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ ስራውን አስረክባለሁ፡፡ ›› በማለት ቃል ገቡ፡፡ ቁርጠኛ አመራር ማለት እንዲህ ነው፡፡
ንጉሱም ልኡል ራስ መንገሻ የተግባር ሰው መሆናቸውን ስለሚያውቁ መንገሻ አደርገዋለሁ ካለ ያደርገዋል በማለት በሀሳባቸው ተስማሙ፡፡ ወዲያውም የቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ፣ የአፍሪካ አዳራሽና የግዬን ሆቴል ተሰርተው ስላለቁ በጊዜው ጉድ ተባለ፡፡ በንጉሱ ዙሪያ የነበሩት በሳል ዲፕሎማቶችም ጥልቅ እውቀት የነበራቸው ነበሩ፡፡ ካቢኔው በዛን ወቅት ይመራ የነበረው በአክሊሉ ሀብተወልድ ነበር፡፡ በዛን ወቅት ክቡር አቶ ከተማ ይፍሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፣ ክቡር ዶክተር ተስፋዬ ገብረእግዚ የማስታወቂያ ሚኒስትር ፣ክቡር ዶክተር ምናሴ ሀይሌ እና ክቡር አቶ ሰይፉ ማህተመ ስላሴ የተባሉ ሚኒስትሮች ወደተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት እየሄዱ ፣ ሲያስተባብሩና ሲያግባቡ ነበር፡፡በዛን ወቅት ከፍተኛ ተደማጭነት የነበራቸው የግብጹ መሪ ገማል አብድል ናስር ነበሩ፡፡እርሳቸውን ለማግባባት ትልቅ የዲፕሎማሲ ስራ ተሰርቷል፡፡ ይህ የማግባባት ስራ በወጉ ተከናውኖ ስብሰባው በአዲስ አበባ እንዲካሄድ ሲወሰን ለእንግዶቹ አዳራሽና ሆቴል አልነበረም፡፡በወቅቱ አዲስ አበባ አስፈላጊ የሚባሉትን ጉዳዮች ካላሟላች የመቀመጫነቱ እድል ለሌላ ይተላለፍ ይሆን? የሚል ስጋትም ነበር፡፡
መቼም ከቀዳማዊ ሀይለስላሴ ሀውልት እንዲቆምላቸው መደረጉ በጎ ነገር ሁኖ ከእርሳቸው ስር የነበሩ ሰዎችን ፈጽሞ መዘንጋት የለብንም፡፡ ለዋቢነት አቶ ከተማ ይፍሩን ብንጠቅስ የበርካታ የአፍሪካ መሪዎችን እንዲሁም የነጻነት ታጋዮችን በማሳመን ለስብሰባ አዲስ አበባ እንዲመጡ አድርገዋል፡፡ መሪዎቹ ከመጡ በኋላም በቂ የሚባለውን የዲፕሎማሲ ስራ ያከናወኑ ናቸው አቶ ከተማ፡፡
በ1955 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የተመሰረተ ሰሞን ግዬን ፣ኢትዮጵያ፣ ራስ ሆቴል፣ ጣይቱ ፤ ገነት እና ሂልተን ሆቴሎች ነበሩ፡፡ መሪዎች ሲመጡ የት ይረፉ? ሲባል በግዮን ሆቴል 32 መሪዎችን የሚያስተናግድ 2 ቅጥያ ፎቅ የተሰራው በዛን ጊዜ ነበር፡፡ ከተማውን የማሳመሩ ዝግጅት በሚገባ ከተጠናቀቀ በኋላ መሪዎቹ የሚመጡበት ቀን ግንቦት 1955 እንዲሆን ተወሰነ፡፡ ይህን መሰናዶ በመምራቱ በኩል ትልቁን ሃላፊነት የወሰዱት አቶ ከተማ ይፍሩ ነበሩ፡፡ በዛን ወቅት መሪዎቹ ሲመጡ ሀይለኛ ዝናብ በአዲስ አበባ ይዘንብ ስለነበር ጃንሆይ መሪዎቹን በጃንጥላ ነበር የተቀበሏቸው፡፡ ቀይ ምንጣፍ ተነጥፎም ፖሊስ ባንድ ማርሽ እያሰማ ለመሪዎቹ ክብር 21 ጊዜ መድፍ ተተኮሰ፡፡
መሪዎቹና የልኡካን ቡድኑ አባላት አዲስ አበባ መግባት የጀመሩት ከግንቦት 13 በኋላ ሲሆን ሁሉም ተጠቃልለው የገቡት ደግሞ ግንቦት 15 ነበር፡፡ ግንቦት 16 ምሽት ጃንሆይ በታላቁ ቤተ-መንግስት ለዲፕሎማቶች፣ለጋዜጠኞች ፣ለሌሎችም ታላቅ የራት ግብዣ አደረጉ፡፡
ተጋባዦቹ ወደ አዳራሾቹ ከመግባታቸው በፊት ቤተ- መንግስት ሜዳ ላይ ርችቶች ተተኩሰዋል፡፡ አዳራሹ በተለያዩ ታሪካዊ ስእሎች አሸበረቀ፡፡ ማሪያ ማኬባም በዚህ እለት የዶክተር ጥላሁንን ዜማ ስታዜም ጭብጨባው ቀለጠ፡፡
ኢትዮዽያ ለብዙ ሺህ ዓመታት ብቻዋን በአፍሪካ አህጉር ካሉ ሀገራት ከአውሮፓውያን የቅኝ ግዛት ቀንበር ውጪ ሆና ቆይታለች፡፡ በቅኝ ግዛት ሥርም የነበሩ ህዝቦች ከታገሉ በኃላ ነጻነት ማግኘት ጀመሩ፡፡
ነጻነቱ ከተገኘ በኃላም አፍሪካ አንድ ሆና የተባበረ ክንዷን የምታሳይበት ቀን ተቃረበ፡፡ የአፍሪካ አንድ መሆን ትልቁ ጥቅም ለራሷ ለአፍሪካ ነበርና አህጉሪቱን አንድ ለማድረግ ንቅናቄው በስፋት ተጠናክሮ ቀጥሎ ግንቦት 18 1955 የአፍሪካ አንድነት ቻርተር ሊፈረም ቻለ፡፡
ቀዳማዊ ሀይለስላሴ ዋና ተሰሚነት የነበራቸው መሪ ነበሩና አፍሪካን አንድ ለማድረግ ንቅናቄው እንዲጀመር ኃላፊነት በመስጠት የጀመሩ ጉዞ ከብዙ ጥረት በኋላ ሊሳካ ችሏል፡፡ ይህን ሃላፊነት የወሰዱት የወቅቱ የሀገራችን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ከተማ ይፍሩ ነበሩ፡፡ ያኔ ገና የ36 ዓመት ወጣት የነበሩት አቶ ከተማ አፍሪካ አንድ ልትሆን ሰሞን ቢቢሲ ቃለ መጠይቅ አድርጎላቸው ድርጅቱን ለመመስረት በዝርዝር የታለፈበትን ሂደት ተናግረዋል፡፡
ቻርተሩ በተፈረመ ዕለት ብዙ ኢትዮዽያውያን በተለይ ለዚህ ድል የተጉ በደስታ መፈንደቅ ያዙ፡፡ አቶ ከተማ ይፍሩን ጨምሮ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት ይሰሩ የነበሩ ወጣት ኢትዮዽያውያን ሳይቀሩ የዚህ ታሪክ ተሳታፊ መሆናቸው ትልቅ ደስታ አመጣላቸው፡፡
ኢራን ሰራሽ ድሮን በሶሪያ መትታ መጣሏን አሜሪካ ገለጸች
በሰሜን ምስራቅ ሶሪያ የወደቀው ድሮን ባለቤት ግን እስካሁን አልታወቀም።
https://am.al-ain.com/article/us-says-shot-down-iranian-drone
#_ሶስት_ነገሮችን_አድርግ
👉Join
👉Share
👉Comment
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
መልካም ቀን🙌ሼር አደራ🙏
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
#_ሶስት_ነገሮችን_አድርግ
👉Join
👉Share
👉Comment
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
መልካም ቀን🙌ሼር አደራ🙏
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
#_ሶስት_ነገሮችን_አድርግ
👉Join
👉Share
👉Comment
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
መልካም ቀን🙌ሼር አደራ🙏
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
#_ሶስት_ነገሮችን_አድርግ
👉Join
👉Share
👉Comment
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
መልካም ቀን🙌ሼር አደራ🙏
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
#_ሶስት_ነገሮችን_አድርግ
👉Join
👉Share
👉Comment
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
መልካም ቀን🙌ሼር አደራ🙏
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
👉 "የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ሃይል የሚጠበቅበትን ተልዕኮ እንዲወጣ ለማስቻል ከፋይናንስ፣ ሰው ሃይልና ጊዜ አንፃር አባል ሃገራት አስፈላጊውን ዋጋ ከፍለዋል‼️"
♦️ "ሽብርተኝነት፣ ኢ-ሕገመንግስታዊ የሆነ የመንግስታት ለውጥና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች በአህጉራችን በተደጋጋሚ እየተከሰቱ ይገኛሉ። ይህ ስብሰባም እነዚህንና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ገቢራዊ ሃሳቦችን እንደሚያቀርብ ተስፋ አደርጋለሁ‼️"
-ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል የአባል ሀገራት ኤታማዦር ሹሞችና የፖሊሲ አውጭ አካላት ስብስባ በአዲስ አበባ እያካሄዱ ነው።
የዕለቱ የክብር እንግዳ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር እኔዳሉት፤ በአህጉራችን አፍሪካ በርካታ ችግሮች እያጋጠሙ የሚገኙ መሆኑንና በተለይም የአንድ ሀገር ችግር የጎረቤት አገራትም ችግር በመሆኑ በትብብር መስራቱ ወሳኝነት እንዳለው አውስተዋል።
በኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ ሽብርተኝነት፣ ኢ-ሕገመንግስታዊ የሆነ የመንግስታት ለውጥና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች በአህጉራችን በተደጋጋሚ እየተከሰቱ እንደሚገኙ ጠቁመው፤ ይህ ስብሰባም እነዚህንና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ገቢራዊ ሃሳቦችን እንደሚያቀርብ ተስፋቸውን ገልፀዋል።
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ በዚህ ስብሰባ የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል ረቂቅ የድርጊት እቅድና በጀትን ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ ዶክመንቶች ጋር ትኩረት አድርጎ እንደሚወያዩም ተናግረዋል።
የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ጌታቸው ሽፈራው በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ባለፉት ቀናት የድርጅቱን ሁለንተናዊ ቁመና እና ተቋማዊ ቅርፅ ለማሳደግ የሚያስችሉ ሐሳቦች መቅረባቸውን አስረድተዋል።
ስብሰባው በኤታማዦር ሹሞች ደረጃ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ሲሆን፤ ለድርጅቱ የተልዕኮ አፈፃፀም አስቻይ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ሩሲያ “አውሬው-2” የተሰኘ አህጉር አቋራጭ ሚሳይል ልታስወነጭፍ ነው ተባለ
የፎረይን ፖሊሲ መጽሄት ሩሲያ በዩክሬን ላይ "አዲስ የጥቃት ማዕበል" ልትከፍት ትችላለች ሲል ዘግቧል
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሚሳይሎች ሁሉ ንጉስ እንደሆነ የሚነገርለትን ሃይፐርሶኒክ "አውሬው- 2" ወይም “ሳርማት” ሊያስወነጭፉ ይችላሉ በሚል ምዕራባውያን በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
እንደ እንግሊዙ "ዘ ኢንዲፔንደንት" ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ፑቲን በዩክሬን ላይ ዘመቻ የጀመሩበትን አንደኛ አመት ምክንያት በማድረግ 208 ቶን የሚመዝነውን "አውሬው- 2" ሚሳይል በቀናት ውስጥ በማስወንጨፍ ምዕራባውያንን ለማስደንገጥ ተዘጋጅተዋል፡፡
15 የኒውክሌር አረሮችን መሸከም የሚችለው ሚሳይል እንደፈረንጆቹ ከየካቲት 15 እስከ 25 ባለው ጊዜ ውስጥ ሊተኮስ እንደሚችልም ወታደራዊ ባለሙያዎች ለጋዜጣው ተናግረዋል።
የሚሳይሉን ሙከራ ለማድረግ በሩሲያ ሩቅ ምስራቅ ካምቻትካ አከባቢ ርቀው የሚገኙ ባለስልጣናት በዝግጅት ላይ መሆናቸውም ነው የተገለጸው፡፡
በተጨማሪም አህጉር አቋራጭ የባላስቲክ ሚሳኤል ሙከራ በሰሜን ካምቻትካ በምስራቅ ሩሲያ ውስጥ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
ሚሳይሉን ከማስወንጨፍ በተጨማሪ ሩሲያ በ10 ቀናት ውስጥ በዩክሬን ላይ አዲስ ጥቃት ለመፈጸም 1800 ታንኮች፣ 700 አውሮፕላኖች ፣ 2700 መድፎች ፣ 810 የሮኬት ማስወንጨፊያዎችን እና 500ሺህ ወታደሯቸዋን ዝግጁ ማድረጓ ሮይተርስ አንድ የዩክሬን ባለስልጣንን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
የአሁን ወታደራዊ ዘመቻ ጦርነቱ ሲጀመር ከነበረበት መልክ የበለጠና የተጠናከረ እንደሚሆንም ነው የተገለጸው፡፡
“ሳርማት” ሚሳይል የሩሲያው ፕሬዝዳንት "ሮኬት ኪንግ" እያሉ የሚያወዱሱት እንዲሁም የሰሜን አትልንቲክ የጦር ቃል ኪዳን /ኔቶ/ “አውሬው -2” ብሎ የሚጠራው አህጉር አቋራጭ ሚሳይል ነው፡፡
ሚሳይሉ 15 የኒውክሌር አረሮች የሚሸከም፣ 116 ጫማ ርዝመት ያለው እንዲሁም ከ1600 ማይል ርቀት በስድስት ደቂቃ ውስጥ ወደ ብሪታንያ መድረስ የሚችል መሆኑም ይነገራል።
የሩስያ ፕሬዝደንት ፑቲን አህጉር አቋራጭ ባሊስቲክ ሚሳይሉ በሰሜን ወይም በደቡብ ዋልታ ላይ መብረር በመቻሉ እና በዓለም ላይ ማንኛውንም ኢላማ የመመታ በመሆኑ በከፍተኛ ኩራት ማወደሳቸው ይታወሳል፡፡
"ምንም አይነት የመከላከያ ስርዓቶች ሊቋቋሙት አይችሉም፤ “ሩሲያን ለመፈታተን የሚፈልጉ ጠላቶቻችን ቆም ብለው ሁለት ጊዜ እንዲያስቡ እናደርጋለን" ሲሉም ነበር የተናገሩት ፑቲን የሚሳይኩን ሙከራ በተደረገበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፡፡
ያሳዝናል!በስተመጨረሻ የTDF አባላት እውነቱን መናገር ጀመሩ። ትርጉም በናትናኤል አስመላሽ
ተፃፈ በዳንኤል ወዲ አቡነ እንድርያስ
"ለካ በህይወት መትረፍ ያሳዝናል"
ሁሌም ፈጣሪዬን ሳመሰግን፣ለኔ ያደረግክልኝ ለማን አደረግክለት እል ነበር፤ ዛሬ ግን ምን ነበር እንደተሰዉት ብሰዋ ኖሮ ለምን በቀላሉ ተመትቼ በህይወት ተረፍኩ ብዬ አምርሬ የቁጭት ለቅሶ አለቀስኩ።መስዋእትነት ተመኘሁ!ግን ማን በሰጠኝ!ወይኔ!እነዛ ከፊቴ የረገፉት ምልምል ወጣቶች ሁሉ ለካ ህዝብን ለማዳን አልነበረም ።
.
.
.
በመሃከላችን የወደቀው ሞርታር ፈንድቶ ለኔ እግሬ ላንተ ደሞ ልብህ ላይ አርፎ ወድያው ክቡር መስዋዕትነት የተቀበልከው የትግል ጓደኛዬ ዛሬ ትዝ አልከኝ፣ካንተ ጋር መስዋእት ሆኜ በነበር ብዬ ተመኘሁ!ግን ማን በሰጠኝ!በምን ዕድሌ!
ክቡር ህይወታችሁን የከፈላቹ ጓደኞቼ እንኳንም አሁን እየሆነ ያለው ነገር አላያችሁ፣ አልሰማችሁ፤ትገረሙ ነበር!ጉድ ነው!
እጃችን፣እግራችን እና የዓይን ብርሃናችን ያጣነው ለዚህ ነበር እንዴ?፣ከ800ሺ ወጣቶች ያጣነው፣እንደ ህዝብ ከሰው በታች የሆንነው ለእናንተ ስልጣን(ወንበር) ነው እንዴ?፣ይሔ ሁሉ ዋጋ ለእናንተ ስልጣን ነው እንዴ?
የትግራይ ህዝብ ሆይ እኔ በግሌ ይቅርታ ልጠይቅህ ፍቀድልኝ፤ታግዬ ነፃነትህ ስላላስጠበቅኩልህ፣ከዚህም አልፎ ማስደፈርያህ እና ማስገደያህ ሆንኩኝ፤ወደ ትግል የወረድኩት እኮ ነፃ ላወጣህ መስሎኝ ነበር፤ግን ለካ እንደዛ አይደለም።ይቅርታ!ይቅርታ አድርግልኝ!
ዘልአለማዊ ክብር ለጀግና ሰማእታት ይሁን
✍️ ኢትዮ-ኤርትራ ላይ የቀጠለው ሴራ - የፖታሽ ጂኦፖለቲካ
~~~~
በእስሌማን ዓባይ
ኃያላኑ የመጪውን ዘመን ዓለም አቀፍ የምግብ ሰንሰለት ጠቅልሎ መያዣ ስትራቴጂ ላይ ከተጠመዱ አስርት ከመታት ተቆጥረዋል። ለነዚህ ጉልበተኛ መንግስታት በምግብ ራስን መቻል ማለት የሉዓላዊነት ጉዳይ ጭምር ነው። በዚህ አጀንዳ ላይ የነበራቸው ስጋት ከተጠበቀውም በላይ ተፋጠነና በዩክሬይን ሩሲያ ጦርነት ላይ ጥርሱን አግጥጦ መጣና ነገራቸውን ሁሉ "ከምኔው ከምኔው" አደረገባቸው። በአፍሪካ ስም የተለመነ በርካታ መርከብ የስንዴ ጭነት በድብቅ ወደ አውሮፓ ሲጓጓዝ መጋለጥ መጀመሩም የዚሁ ጣጣ ውጤት ነው። በዚህ መሀል በትግራይ ስንዋጋ የባጀንበት ጦርነት የምግብ አቅርቦቱን ቅዠት ያጦዘበት ወቅት ነበርና በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል የሚገኘውን ሀብት ደግመው ደጋግመው እንዲያስታውሱት ያደረገ ሆነ።
በርግጥ የኢትዮጵያና የኤርትራ የጋራ ትብብር ቀይ ባሕር ላይ ለመፈርጠምም ሆነ የውጭ ጣልቃ ገብነትን የመቋቋም ጉልበታቸውን የማይደፈር ማድረጉ ወዘተ... ጉዳዩች ለምዕራቦቹ "የማናባት ደም ፈሰሰ" የማጣላት አጀንዳቸው ሰበብ ሊሆኑ ይችላሉ። ፍጥጥ ብሎ መታየት የሚችለውን አንድ መነሾ ደግሞ በዚህ ፅሁፍ በተለዬ እንመልከተው። ይኸውም የፖታሽ ጂኦፖለቲካ ነው።
በአለም የፖታሽ አቅርቦት ካናዳ፣ አሜሪካ ራሺያ፣ ጀርመን፣ ስፔን፣ እንግሊዝ፣ ደረጃውን በቅደም ተከተል ይይዛሉ። በሌላ በኩል ከፍተኛ ፖታሽ አምራች ቢሆኑም ይህንን ለማሟላት በገፍ ኢምፖርት የሚያደርጉ ሀገራትም አሉ - እዚጋ ቻይና 70 በመቶ የፖታሽ ምርቷን፣ ብራዚል 90 በመቶ እና ሕንድ 100 ፐርሰንት የፖታሽ ፍላጎታቸውን በኢምፖርት ነው የሚሸፍኑት። ታዲያ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ የሰላም ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ የፖታሽ ሀብታቸው የአለም ጉልበተኞችን ማሻኮት ነው የጀመረው።
አሜሪካ፣ ቻይና፣ ሩሲያ፣ አውስትራሊያ፣ ዋነኞቹ ሲሆኑ እነ ህንድ ቱርክ እና ሌሎችም በፉክክሩ ውስጥ ተጠቃሽ ናቸው። ከመሬት በታች 400 እና 500 ሜትር መቆፈር ይጠይቅ የነበረው የፖታሽ ማዕድን በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ባለው የደናከል ረባዳ ምድር ላይ ግን በመሬት ላይ የመገኘት ያህል በቅርብ ቆፍረው የሚያወጡት በርካሽ ወጪ የሚመረት፤ በዛ ላይ የጥራት ቁንጮ ላይ መገኘቱ ይበልጡን ተፈላጊ አደረገው።
UNDP በ 2011 ዓ/ም ይፋ ባደረገው ጥናት ይህንኑ የሚያስረግጥ ሲሆን፤ [1] በኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር መካከል 365 KM ስኩዌር በሚሆነው ደንከል ገፀ መሬት ላይ በሚባል ደረጃ፣ ቁጥር አንድ የፖታሽ ማዕድን ሀብት መከማቸቱን ይጠቁማል።
እንደ UNDP ጥናት፤ በኤርትራ የሚገኘውና ደንከልን የሚጋራው ኮሉሊ የፖታሽ ማዕድን ብቻ 1.1 ቢልዮን ቶን ፖታሽ ያለው ሲሆን ምርቱም 200 ዓመት የሚዘልቅ፤ 16 ሜትር በማይሞላ ከመሬት በታች ርቀት ላይ ነውም የሚገኘው። ሌላው የደንከል ክፍል ደግሞ እስከ 14 ቢልዮን ቶን እንደሚሆን የተጠና ነው።
በዚህ የማዕድን ልማት ፕሮጀክት ተሳታፊ ከሆኑ ኩባንያዎች መካከል በኤርትራ በኩል የተፈራረመው ደንከል PLC የተባለ የአውስትራሊያ ኩባንያ ነው። በ 2011 ኤርትራ ላይ የተጣለው ማዕቀብ መነሳቱን ተከትሎ፣ የኮሉሊ ፖታሽ ፕሮጀክትን ለማልማት ሲፈራረም የኩባንያው አክሲዮን በከፍተኛ ዋጋ ጨምሮ በዓለም ዐቀፍ የአክሲዮን ገበያዎች መቸብቸባቸውን የምናስታውሰው ዘገባ ነው።
ኩባንያው በኮሉሊ ፕሮጀክት ከኤርትራ ጋር የፈረሙት ስምምነት የፕሮጀክቱ 50 በመቶ ባለቤት የኤርትራ ማዕድን ኮርፖሬሽን ነበር። የዛሬ 3 አመት ገደማ(2011 ላይ) ግንባታ ለመጀመር እንቅስቃሴ ላይ የነበረው ደንከል plc በዓመት 472,000 ቶን ፖታሽ አመርታለሁ” ብሎ ነበር። በሌላ በኩል ኮሉሊ ፖታሽ ፕሮጀከት አቅራቢያ የሚገኘው ቢሻ የወርቅ ማዕድን ለቻይናው ZIJN MINING የተሰጠ ሆኗል።
ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት የተፈራረመው CIRCUM MINERALS Ltd የተባለ የአሜሪካ ኩባንያ ነው። ስምምነቱ በ 2017 የተፈረመ ሲሆን በአመት 1.5 ሚሊዮን ቶን የልዩ ጥራት ፕሪሚዬም ፖታሽ፤ እንዲሁም 2 ሚልዮን ቶን በድምሩ በአመት 3.5 ሚሊዮን ቶን ፖታሽ አመርታለሁ ብሎ ነበር። ይህ አሜሪካዊ ኩባንያ የፖታሽ ልማቱን 100 ፐርሰንት ባለቤትነ የሚሰጠው ስምምነት ነበር የተፈረመለት። ይህ ለምን እንደሆነ አላህ እና ፈራሚዎች ናቸው የሚያውቁት። ይህ አሜሪካዊ ኩባንያ የሃያ አመት ሊዝ የተሰጠው ሲሆን እስከ 30 ዓመታት ሊራዘምለትም ቃል ተገብቶለታል። በ2021 እኤአ ላይ ምርት ሊጀምር ያሰበ፤ የፕሮጀክቱ ዋጋም 2.1 ቢሊዮን ዶላር የተሰላ ነበር።
ታዲያ ይህ የሃያላን ጡንቻ የተጋጠመት ሐብት ለመልማት የኢትዮ ኤርትራ የጋራ ትብብር ዋነኛው ሲሆን የሁለቱ ሀገራት ትብብር ከግቡ መድረስ አለመድረሱ ደግሞ በውጭ ሀገራት መዳፍ ስረ ስለመሆኑ የተለያዩ ተንታኞች ሲገልፁት የነበረ ነው። በዚህ መሀል ቤይጂንግ ወደ አስመራ ዘልቃ መግባት ጀመረች።
የቻይናው ሲቹዋን ሮድ እና ብሪጅ ግሩፕ የኮሎሊ ፖታሽ ፕሮጀክትን 50 በመቶ ድርሻ በኤርትራ ከሚገኘው የአውስትራሊያ ኩባንያ ላይ ገዝቷል።የቻይናውና የአውስትራሊያው ኩባንያ የድርሻ ስምምነት ፈርመዋል። በሁኔታዎች መሰረትም፣ ስምምነቱ እስከ ግንቦት 31፣ 2023 ድረስ ተፈፃሚ ይሆናል። 😎
በተጨማሪም የቻይናው ኩባንያ በአስመራ ወርቅ ፕሮጀክት 60 በመቶ ድርሻ ያገኘ ሲሆን በ 60፡40 ጥምርታ በቻይና SRBM እና በኤርትራ መንግስት ባለቤትነት አራት የወርቅ ማዕድም ቦታዎችን ያቀፈ ነው።
850,000 ቶን ዚንክ፣ 381,000 ሜትሪክ ቶን መዳብ፣ 436,000 ounces ወርቅ እና 11 ሚሊዮን ounces የብር ማዕድን እንዳለው በጥናት የተረጋገጠ ነው። እንግዲህ ይህ ሁሉ አለም አቀፍ ጥልፍልፍ በኢትዮ-ኤርትራ ወዳጅነት ላይ ጥላውን አጥቁሮ ቆይቶ ህወሃት ትጥቅ ከፈታ በኋላ እንኳን አይኑን በምን እንዳጠበ ባይታወቅም ሀፍረቱን ጥሎ የሀሰት ዘመቻ ላይ ተጠምዷል። የሩሲያ ወይም የቻይና ባለስልጣን ለጉብኝት ወደ አፍሪቃ ቀንድ ከመጣ ሁለቱንም ሀገራት አከታትሎ ይዘይራል - ካፒታል በመያዝ። በቀጣይ ቀን ደሞ ወይ የአውሮፓ አሊያም የአሜሪካ ባለስልጣን አለሁኝ ብሎ ወደነዚሁ ሀገራት ይከሰታል - ማስፈራሪያውን አስከትሎ..። ታዲያ ይህ ኢትዮ ኤርትራን ነጣጥሎ ለማዳከምና ለመዝረፍ የሚደረግ ሴራ ይሳካ ይሆን? አዲስ እና አስመራ በሁለትና ሶስት አመታት ከተሻገሩት አለም አቀፍ ሴራ አንፃር በቀጣዩ መሰናክል መፅናትስ ይቸግራቸዋልን? ኢትዮጵያዊያን ለአንድነታችን ከተባበርንና መንግስት የበኩሉን ሚና በሚገባ መወጣት ከቻለ በርግጠኝነት ኢትዮ ኤርትራ አሸናፊ ናቸው።
በጄነራል አበባው ታደሰ የተመራ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ወታዳራዊ ልዑክ በቱርክ ጉብኝት አደረገ
********
በኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሠራዊት ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል አበባው ታደሰ የተመራው ወታደራዊ የልዑካን ቡድን በቱርክ ወታደራዊ ኃይል በተዘጋጀው ወታደራዊ ልምምድ ላይ ተሳትፏል።
የቱርክ ወታደራዊ ኃይል በክረምት ወቅት የተጣለበትን አገራዊ እና ዓለም-አቀፋዊ ግዳጅ ለመወጣት ያለውን አቅምና ዝግጁነት ለማሳየት ከጥር 24-25 ቀን 2015 ዓ.ም በምስራቅ ቱርክ በምትገኘው ካርስ ግዛት ወታደራዊ ልምምድ አካሂዷል።
በቱርክ የሚገኘው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ወታዳራዊ ልዑክ በወታደራዊ ልምምድ ላይ ከመሳተፍ በተጨማሪ በወታደራዊ ዘርፍ የሁለቱን ሀገራት ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ከቱርክ አቻው ጋር እንደሚመከር በአንካራ የኢዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
