ru
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Открыть в Telegram
6 002
Подписчики
-27824 часа
-2 5467 дней
-1 99730 день
Архив постов
የሲዳማ ማህበረሰብ ቄጠላ ስርዓት በሃዋሳ ስታዲየም በ65ኛው በልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ምስረታ በዓል ላይ 👉🇪🇹🙏 https://youtube.com/shorts/IPPPUZB0fMU?si=xJsJF8AQMxSf70HS

🇪🇹 የሰማዩ አንበሶች ኢትዮጵያ 🇪🇹 https://youtu.be/yxhSy8ApgnY?si=deKyWhEeuufE27Dd

የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት ክብረ በዓል ከጥር 15 -19 በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ይከበራል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 14 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከለውጡ መንግሥት በኋላ
የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት ክብረ በዓል ከጥር 15 -19 በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ይከበራል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 14 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከለውጡ መንግሥት በኋላ ለተቋማት ግንባታ በሰጠው ትኩረት ውስጥ አልፎ ሀገርን በሚመጥን መልኩ ስኬት እያስመዘገበ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡ አየር ኃይሉ "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል መሪ ቃል 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ከጥር 15-19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ዝግጅቶች ያከብራል። የምስረታ በዓሉ ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የታላላቅ ሀገራት አየር ኃይሎች በሚሳተፉበት የጥቁር አንበሳ ትርዒት፣ በአቪዬሽን ኤክስፖ እና በአፍሪካ የአየር ኃይሎች ፎረም እንዲሁም በሌሎች ክንውኖች የሚከበር ይሆናል፡፡ ተጋብዘዋል የኢፌዴሪ አየር ኃይል የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ዳይሬክቶሬት የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@ethiopiancommando?si=0SRgdyWuN3axteCi የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://youtube.com/@ethiopiancommando?si=0SRgdyWuN3axteCi

የዕዙ መገናኛ እና ኢንፎርሜሽን ሲስተም መምሪያ ያሠለጠናቸውን ሙያተኞች አስመረቀ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ታህሳስ 24 ቀን 2018 ዓ.ም የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ መገናኛ እና ኢንፎርሜሽን ሲስተም መ
+2
የዕዙ መገናኛ እና ኢንፎርሜሽን ሲስተም መምሪያ ያሠለጠናቸውን ሙያተኞች አስመረቀ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ታህሳስ 24 ቀን 2018 ዓ.ም የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ መገናኛ እና ኢንፎርሜሽን ሲስተም መምሪያ ከልዩ ዘመቻዎች ዕዝ እና ከባህር ኃይል ቢሾፍቱ በሚገኘው የአየር ወለድ ትምህርት ቤት ለሶስት ወራት ያሠለጠናቸውን የራዲዮ መገናኛ ሙያተኞች አስመርቋል፡፡ በዕለቱ የተገኙት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ መገናኛ እና ኢንፎርሜሽን ሲስተም መምሪያ ሃለፊ ኮሎኔል አብርሃ ዓባይ የግንኙነት ስርዓት ለሠራዊቱ ሀገራዊ ተልዕኮ ስኬት ድል የጀርባ አጥንት በመሆኑ ለዕዙ ግዳጅ ስኬት የግንኙነት ስርዓቱን ማሳለጥ ወሳኝ ነው ብለዋል። የመገናኛ እና ኢንፎርሜሽን ሲስተም ስልጠና ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጅ ተደግፎ መሰጠቱ ተገቢ ነው ያሉት ኃላፊው ሰልጣኝ ተመራቂዎችም ይህንን ተገንዝበው ባገኙት ዕውቀት ሀገራቸውንና ክፍላቸውን በፅናት ማገልገል እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ የዕዙ መገናኛ እና ኢንፎርሜሽን ሲስተም መምሪያ ስልጠና ሃላፊ ሻምበል ግዛው የማነ በበኩላቸው ስልጠናው ከተለያዩ የመከላከያ ተቋማትና ኮሌጅ በመጡ ሙያተኞች መሰጠቱን ተናግረው ስልጠናው የግንኙነት ቴክኖሎጂ አሁን ያለበትና ነገ የሚደደርስበትን ሁኔታ ባገናዘበ መንገድ በተግባርና በንድፈ ሀሳብ መሠጠቱን ገልፀዋል። ዘገባው የአብዱራህማን ሀሰን ነው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ

https://invite-poppo.com/GDYkGr Download the app to meet more interesting friends from all over the world! My ID:48508028

https://invite-poppo.com/GDYkGr Download the app to meet more interesting friends from all over the world!  My ID:48508028 ይህንን አፕሊኬሽን አውርደሽ አክቲቭ አድርጉና በየቀኑ ገንዘብ ስሩበት።

ታላቅ የድል ዜና ከኤፍራታና ግድም ወረዳ………… በ11/03/2018 ዓ.ም 102ኛ ኮማ/ክ/ጦር 5ኛ ሻለቃ 02 ሻምበሎች በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አሞጃ ገብርኤል ጠላት ከንጋቱ 12:00
+9
ታላቅ የድል ዜና ከኤፍራታና ግድም ወረዳ………… በ11/03/2018 ዓ.ም 102ኛ ኮማ/ክ/ጦር 5ኛ ሻለቃ 02 ሻምበሎች በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ አሞጃ ገብርኤል ጠላት ከንጋቱ 12:00 ሠዓት ጀምሮ ከመስቀል በር፣ ከማጥቆሪያና ከከስያት ሀይሉን አሰባስቦ በ03 ዲሽቃ ታግዞ አሞጃ ገብርኤል ላይ ያለውን የወገን ሀይል በመክበብ ተኩስ የከፈተ ሲሆን ሠራዊታችን በፍጥነት አሰላለፉን በማስተካከል በመልሶ ማጥቃት ጠላትን ሙትና ፣ቁስለኛ እና ምርኮኛ አድርጎ የተረፈው ጠላት እግሬ አውጭኝ ብሎ ሬሳውን እና ትጥቁን አንጠባጥቦ ፈርጥጧል። *የጠላት የደረሰ ኪሳራ:-* .የተገደለ ጠላት......15 .የቆሰለ ጠላት......ከ05 በላይ ብሬን መሳሪያ........01 .ጥቁር ክላሽ........03 .ሰደፍ ክላሽ.........05 .ታጣፊ ክላሽ........01 ብሬን አፈሙዝ.......01 .RGD 5 ቦምብ....01 .F 1 ቦምብ..........06 .ብሬን ጥይት.......726 .ክላሽ ጥይት......246 .ወ/ዊ ሳንጃ..........01 .ብሬን ሸንሸን ባለ100...03 .ክላሽ መጋዘን........25 .ስናይፐር መጋዘን.....05 .መገናኛ ሬዲዮ.......01 .የወገብ ትጥቅ......05 .ስ/ፐር ደረት ትጥቅ...04 መረጃው የኤፍራታ ግድም የመንግስት ኮሙኒኬሽን እና የሰሜን ሸዋ ፖሊስ መመሪያ ነው። #ShareThisPost #share #ShareLikeFollowComment #SharePost #ShareThis

የአደዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ስራ ለመጀመር በዝግጅት ላይ መሆኑን አሥታወቀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማህበር፣
የአደዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ስራ ለመጀመር በዝግጅት ላይ መሆኑን አሥታወቀ።  የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማህበር፣ በቀጣይ ስራ ለመጀመር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ የአድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ሁንዴ ገልፀዋል። የአክሲዮን ማህበሩ ለስራ የሚያስፈልጉ ቢሮዎችን፣ ሙያተኞችን፣ የቢሮ እቃዎችን በማሟላት ላይ ይገኛል ሲሉ ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። የአክሲዮን ማህበሩ በዚህ ዓመት የፋይናንስ አቅሙን በማሳደግ፣ ከአስር በላይ ቅርንጫፎችን ለመክፈት ማቀዱንም ጠቁመዋል። አቶ ዲዳ ሁንዴ የአድዋ ድል የማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማህበር፣ ለሠራዊት አባላት የብድር አገልግሎት ለመስጠትም በአሰራር እና በመመሪያ ላይ ተካቷል፣ የሠራዊቱን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ፣ በትኩረት የሚሰራበት ነው ብለዋል። የአክሲዮን ማህበሩ በቀጣይ ለሚጀምረው ስራ ዝግጁነቱን ለመፈተሽ እና ለማረጋገጥ፣ በብሄራዊ ባንክ ኢንስፔክሽን እየተደረገ መሆኑን ስራ አስኪያጁ አቶ ዲዳ ሁንዴ ገልፀዋል። ዘጋቢ ቢያድግልኝ መሪ ፎቶግራፍ አበረ አየነው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

<<የሀሳብ ልዩነትን በጦርነት ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆም አለበት>> ጀነራል ሳሞራ ዩኑስ በትግራይ ክልል ውስጥ የሀሳብ ልዩነት ሲፈጠር በጦርነት ብቻ ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆ
<<የሀሳብ ልዩነትን በጦርነት ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆም አለበት>> ጀነራል ሳሞራ ዩኑስ በትግራይ ክልል ውስጥ የሀሳብ ልዩነት ሲፈጠር በጦርነት ብቻ ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆም አለበት ሲሉ የቀድሞው  የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል ሳሞራ ዩኑስ ገለጹ፡፡ ጀነራል ሳሞራ  እንደተናገሩት፤ ከዚህ ቀደም  የተፈፀመው ከባድ ስህተት የትግራይን ህዝብ ዋጋ አስከፍሏል፡፡  አሁን የትግራይ ህዝብ ጦርነት በቃኝ ብሏል፡፡  በሆነ አጋጣሚ የጦርነት አዝማሚያ ቢፈጠር እንኳ ህዝቡ ይህንን የመደገፍ ሀሳብ እንደሌላውም ገልጸዋል፡፡ እንደ ጀነራል ሳሞራ ገለጻ፣ ከዚህ ቀደም ችግሮችን በውይይት መፍታት ባለመቻሉ የተቀሰቀሰው ጦርነት የትግራይን ህዝብ ከባድ ጉዳት አድርሶበታል፡፡ ህዝቡ እስካሁን ድረስ የጦርነቱን ጦስ በጫንቃው ተሸክሟል፡፡ በመሆኑም እንደዚህ ዓይነት  ከባድ ስህተት  መደገም የለበትም ብለዋል፡፡ «ጦርነት ብታሸንፍም ባታሸንፍም ጣፋጭ ሆኖ አያውቅም» ያሉት ጀነራሉ፤ በክልሉ በርካታ ወጣት ህይወቱን አጥቷል፣ እናቶችም በሀዘን ተጎድተዋል፣ ተቸግረዋልም፤ በመሆኑም ህዝቡ በተደጋጋሚ ውጊያ ውስጥ ሊማገድ አይገባውም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በትግራይ ውስጥ ማንኛውም ችግር ወይም የሀሳብ ልዩነት ሲፈጠር በጦርነት ብቻ ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆም እንዳለበትና፤ ልዩነቶች በሰላም እና በሰላም ብቻ መፈታት አለባቸው በሚል እምነት መፅናት እንደሚያስፈልግም አስገዝበዋል፡፡ በክልሉ የጦርነት ችግር ይመጣል እያሉ ያልተጨበጠ ወሬ የሚለፍፉ የጦር ጀነራሎችን እሰማለሁ ያሉት ጀነራሉ፤ ይህ የግል ሀሳባቸው ሊሆን ይችላል፤ እኔ የምላቸው ግን የእውነት የህዝብ አገልጋይ ከሆኑ በትግራይ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር መፍታት የመጀመሪያው ጉዳያቸው ሊያደርጉት ይገባልም  ብለዋል። via gazetteplus #ዋሱመሐመድ

የኢትዮጵያ የባህር ሀይል የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችል ሁለንተናዊ ቁመና ላይ ይገኛል። ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓ.ም 118ኛው የኢትዮጵ
+4
የኢትዮጵያ የባህር ሀይል የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችል ሁለንተናዊ ቁመና ላይ ይገኛል።       ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓ.ም 118ኛው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቀን በዓል ላይ በመገኘት ንግግር  ያደረጉት የኢትዮጵያ የባህር ሀይል አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ ባስተላለፉት መልዕክት ፣ የለውጡ መንግስት የባህር በር አስፈላጊነት ላይ ባለው የፀና አቋም እና የመከላከያ ሰራዊቱ  ስትራቴጂ አመራሮች ባደረጉት ድጋፍና ክትትል የአንጋፋውን የኢትዮጵያ ባህር ሀይል ወደ ቀድሞ ገናና ስሙ ለመመለስ የተሰሩት ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ገልፀዋል። ኢትዮጵያ በየዘመናቱ የገጠሟትን ፈተናዎች በድል እየተወጣች የመጣች ታሪካዊና ቀደምት ሀገረ መንግስት መሆኗን አውስተው የባህር በር ጥያቄው  የኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ባህር ሀይሉ ራሱን ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ፣ የተቋማት ግንባታ ከማሳደጉም ባለፈ የመነሻ የዉጊያ ትጥቆች ማሟላቱንም ተናግረዋል። የባህር በርና ባህር ሀይል የማይነጣጠሉ መሆናቸውን የገለፁት ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ ሀገራችን ባላት ታሪክና መብት የባህር በር የማግኘት ጉዳይ የህልውና ጉዳይ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ሀገራችን የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ፍትሃዊ ጥያቄ ለጋራ ተጠቃሚነት በሰጥቶ መቀበል መርህ መስራት እንደሚገባም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ ፎቶግራፍ ተሠማ ኡርጌሳ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ

"ኤርትራ በአፍሪካ የበርካታ ኢንዱስትሪ ባለቤት ነበረች፣አሁን ላይ ግን የታሸገ ውሃና ሳሙና እንኳን ከውጭ ለማስገባት የተገደደች ሀገር ሆናለች።አሁን ላይ የውስጥ ችግሯ እንዳለ ሆኖ ከኢትዮጵያ ጋር በ
"ኤርትራ በአፍሪካ የበርካታ ኢንዱስትሪ ባለቤት ነበረች፣አሁን ላይ ግን የታሸገ ውሃና ሳሙና እንኳን ከውጭ ለማስገባት የተገደደች ሀገር ሆናለች።አሁን ላይ የውስጥ ችግሯ እንዳለ ሆኖ ከኢትዮጵያ ጋር በአሰብ ወደብ ምክንያት ውጥረት ውስጥ ገብታለች።በዚህም የኤርትራ ሉዓላዊነት አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል"ዘ ኢኮኖሚስት ‎#ዋሱመሐመድ አሁናዊ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገልግሎቶች ለምን ይቋረጣሉ ? የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ እሁድ በርካታ አገልግሎቶቹ እንደሚቋረጡ ገልጾልናል። ባንኩ " ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገልግሎቶች ለምን ይቋረጣሉ ? የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ እሁድ በርካታ አገልግሎቶቹ እንደሚቋረጡ ገልጾልናል። ባንኩ " ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ እሁድ መስከረም 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት እስከ ለሊቱ 9፡30 ሰዓት ድረስ ከሲቢኢ ብር አገልግሎቶች በስተቀር ሁሉም የባንካችን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች በጊዜያዊነት ይቋረጣሉ " ብሏል። የሚቋረጡት አገልግሎቶች ፦ - የሞባይል ባንኪንግ፣ - ኢንተርኔት ባንኪንግ፣ - ኤቲኤም ማሽኖች - የፖስ ማሽኖች እና በኮር ባንኪንግ የሚሰጡ አገልግሎቶች (Core Banking Services) እንደሆኑ አሳውዋል። ባንኩ ደንበኞቹ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ጠይቋል። #CBE ©tikvahethiopia

🇪🇹 ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ዓላማ ለመጠቀም የጀመረችውን እንቅስቃሴ እደግፋለሁ - ዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ 🇦🇹 በኦስትሪያ ቪየና እየተካሄደ ካለው 69ኛው የኤጀንሲ
🇪🇹 ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ዓላማ ለመጠቀም የጀመረችውን እንቅስቃሴ እደግፋለሁ - ዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ 🇦🇹 በኦስትሪያ ቪየና እየተካሄደ ካለው 69ኛው የኤጀንሲው መደበኛ ጉባኤ ጎን ለጎን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እና ዋና ዳይሬክተሩ ራፋኤል ግሮሲ በኢትዮጵያ የኒውክሌር ቲክኖሎጂ ውጥን ዙሪያ ተወያይተዋል። ሚኒስትሩ ኤጀንሲው ብሔራዊ የኒውክሌር ኃይል ግንባታ ላይ የቴክኒክ እና የእውቀት ሽግግር ድጋፍ እንዲያደርግ መጠየቃቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡ ☢️ ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ዓላማ ለመጠቀም የሚያስችል መሠረት በመጣል ወደ ትግበራ ለመግበት ሰፊ ጥረት እያደረገች እንደሆነም አንስተዋል። 👉 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ የኢትዮጵያ የኒውክሌር መሠረተ ልማት በመገንባት ለዘርፈ ብዙ ዔላማ ለማዋል እንዳቀደች በ 'የመደመር መንግሥት' መፅሐፍ ምረቃ ወቅት ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X

የሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መሥከረም 01 ቀን 2018 ዓ.ም ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ መላው የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሲቪል ሠራተኞች በሙ
የሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መሥከረም 01 ቀን 2018 ዓ.ም ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ መላው የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሲቪል ሠራተኞች በሙሉ ከሁሉ አስቀድሜ እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡ አዲሱን አመት ስንቀበል ሀገራችን ኢትዮጵያ የጎደፈ ስሟን ያደሱ በርካታ ድሎችን ባስመዘገበችበት ማግስት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል፡፡ ሀገራችን ከነበረችበት የድህነት ማቅ እንዳትወጣ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ከባንዳዎች ጋር ተጣምረው ያለእረፍት የሰሩ ቢሆንም በህዝቦቿ የተባበረ ክንድ በሠራዊቷ ፅናት ዛሬ የድህነት ተራራ እየተናደ ጠላቶቿ የሀዘን ማቅ እየለበሱ ይገኛሉ፡፡ ዛሬ በብዙ መልካም ማሣያዎች ምሳሌ የሆነችው ሀገራችን ሠላሟ ተረጋግጦ ልማቷ ተፋጥኖ ህዝቦቿ በሠላም ወጥተው የሚገቡበት ጠላቶቿ ወይ ወደ ሠላም የሚመጡበት ካልሆነም እንዲጠፉ ተልዕኳችንን በሚገባ እንወጣለን። እኛ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አመራርና አባላትም በየትኛውም ቦታ የሚሠጠንን ተልዕኮ በድል አድራጊነት ፈፅመን የህዝብን ሠላም በማረጋገጥ ረገድ የህይወት መስዋዕትነት በመክፈል ጭምር በበርካታ አካባቢዎች ከህዝባችን ጋር በመሆን ሠላም ማረጋገጥ ችለናል። ዛሬም ከትላንትናው በላቀ ደረጃ አቅማችንን አጎልብትን እጅግ ልቀን በሀገራችን ላይ በየትኛውም አቅጣጫ የሚቀጣን ጥቃት ለመከላከል ዝግጁ መሆናችንን በዚሁ አጋጣሚ እያረጋገጥኩኝ አዲሱ አመት የሰላም ፣ የብልፅግና የእድገት እንዲሁም የጤና እንዲሆን እመኛለሁ አመሠግናለሁ።