cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

TEAM HUDA

"أَفَلَا تَعْقِلُونَ" "አታስተነትኑምን?" አንብቡ! ራሳችሁን፣ በዙሪያችሁ ያሉትን ነገሮች፣ ሌሎች ሰዎችን፣ ፅሁፎችን.... አንብቡ! አስተንትኑ! ጠይቁ! Big thanks for joining! All team huda!

Больше
Рекламные посты
1 707
Подписчики
Нет данных24 часа
-57 дней
-1330 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

መንገዶች በመድረሻቸው ይለካሉ.... መድረሻህ የሚገባው ከሆነ መንገድህ ሩቅ አይደለም፣ ደስ የሚል ተሞክሮ ነው.... አድካሚ አይደለም እውቀት ያጀበው እድገት ነው። መድረሻህ ተራ ከሆነ መንገድህ ቅርብ ቢሆንም ብክነት ነው.... ልፋትህ ቀላል ቢሆንም ባዶ ነው። ለዛም ይመስለኛል ለአኼራ ስንኖር ነገ እንደምንሞት፣ ለ ዱንያ ስንሰራ ገና ጊዜ እንዳለን መኖርን የተመከርነው።  ብቻ...... ጀነት ለመግባት የሚበቃ ስንቅን ለመሸከፍ የዱንያ ቆይታችን በመርዘሙ አድክሞ አያውቅም.... ከደከመን ከመድረሻው ነው። @Re_Ya_zan
Показать все...
7👍 1
ንጋት... ሲነጋ አይኖች ሲከፈቱ፣ አዲስ ቀን ብቅ ያለ ይመስላል። ነገር ግን ንጋት ሁሌ አዲስ ተስፋ አይደለም። የትናንቱን ኮተት ሰብስቦ የሚመለስ፣ ፀሀይ መውጣቷ ብቻ የሚለየው ዳግማው ትናንትም ይሆናል። እድሜያችንም የነዚህ ቀናት ጥርቅም ነው። ዳግማዊ ትናንቶች በየቀኑ ሲደጋገሙ ህይወታችን ወጥ ይሆናል። ዛሬዎችን ማጣት ህይወትን ይበልጥ አሰልችና የሚያስመርሩ ያደቸዋል። በነዚህ ቀናት ስናልፍ አልፎ አልፎ ብቅ የሚሉ አዳዲስ ንጋቶች፣ አዲስ ቅርፅ ያለው ዛሬን ሲሰጡን ትላልቅ የደስታ ቀናት እናልፋለን። የደስታ ቀናችንንም አንድ ብለን ከቆጠርናቸው ብዙ ዳግማዊ ትናንቶች ጋ ደምረን አንድ እርምጃ እንደተንቀሳቀስን ሁሉ.... ዳግም ወደቆጠራ ተመልሰን ሁለት እንላለን። እድሚያችንም ይበልጥ ያጥርብናል። ብዙ የተቃጠለ እድሜም እንዳለ ይሰማናል። ዳግማዊ ትናንቶችን መደምሰስ ባንችልም ግን ከትናንቱ የተወሰነ ልዩነት ለማምጣት ብለን እስካልተነሳን ድረስ አዳዲስ ዛሬዎች ይበልጥ እየራቁን ይመጣሉ። ስለዚህ ቢያንስ ትናንትን ከዳግማዊ ትናንት ለመለየት የቀኑን አጀማመራችንን እንለውጠው ወይንም አጨራረሳችንን። አንድን ቀን ሁለቴ ላለመኖር ያክል ብቻ… @Re_Ya_zan
Показать все...
3👍 2
....የሆነ ጥሩ ቀን ላይ ደግሞ... መውደድ... ከፍቅር ቃላት ውጪ የሚገለፅበት ብዙ መንገድ እንዳለው ድንገት ብልጭ ይልልሃል። አለም ስለተስማማበት የተግባር አገላለፅ ሳይሆን... ከቃላት መካከልም በቦታቸው ተብለው፣ በኋላ ላይ ልብ ስትላቸው ከሌላው ልቀው ስለሚገኙት ነው የምልህ። ለምሳሌ... የእናትህን "ጨርሰህ ካልበላህ ወየውልህ!" አይነት... የአባትህን "የት ነው ያመሸኸው?" አይነት... ከተግሳፅ ውጪም ሌሎች ውስጣቸው መውደድን የደበቁ አገላለፆች... አንዳንዴ "ይቅርታ"ን... አንዳንዴ "እወድሃለው"ን ተክተው እንዳሳደጉህ ትዝ ይልህና ፈገግ ትላለህ። ....ከሁሉም ደግሞ... ጉዳዩ የአኽላቅ ተምሳሌት የሆኑት ተወዳጅ ሀቢብ ስለመረጡት አገላለፅ ሲሆን ሚዛኑ ፍፁም ሌላ ታሪክ ይሆናል። እናታችን ዓኢሻ (ረ.0) ጋር ከሚቆዩባቸው ቀናት በአንዱ እንግድነት ከመጡ ሶሃቦቻቸው ጋር ተቀማምጠው ሳለ፣ ከሚስቶቻቸው አንዷ በአንድ አገልጋይ ወደሳቸው ምግብ ወዳስላከችበት ወደዛ ቀን እንሳፈር። ዓኢሻ በድርጊቱ ተበሳጭታ የአገልጋዩዋን እጅ ትመታታለች፣ ምግቡም ከነ ሰሃኑ መሬት ላይ ወድቆ ይሰበራል። ታዲያ እንደማንኛውም አባወራ ያዙኝ ልቀቁኝ በሚያስብለው በዚ አጋጣሚ ላይ ሃቢቡና ቀለል አድርገው "እናታቹ ቀንታ ነው" በሚል ፈገግ በሚያደርግ ማስተባበያ ሸፍነውላት፣ ምግቡንም በምግብ፣ ሰሃኑንንም በሰሃን እንዳስተኩ ይነገራል። "እናታቹ ቀንታ ነው"... ምን አይነት ሰኪና... ምን ያለ ሂክማ ነው! አላልክም?... የማን ጭንቅላት ላይ እንዲ ሁሉን በአንድ የያዘ አገላለፅ ይመጣል? አንድም ንዴቷ እሳቸውን የመውደድ መሆኑን ሲረዱላት የሷን መውደድን.... አንድም እንግዶቹ ስሟን ይዘው እንዳይሄዱ ሲሰትሯት የሳቸውን መውደድን.... "ስለምወድሽ መውደድሽን ተረድቼ አልፌልሻለሁ" አይነት.... ማንስ ቢወዳቸው፣ ቢቀናባቸው መች ይገርማል?.... "በሳቸው ውስጥ መልካም መከተል (ምሳሌ) አለላችሁ" የተባልነውን ልዩ ሰው መከተልን.... ካስተማሩን ብዙ ብዙውን መተግበርን ራህማኑ ይወፍቀን። @Re_Ya_zan
Показать все...
🥰 11👍 3🔥 1
በዘመናችን ግራ ከገባቸው አረዳዶች መሃል የሶሻል ሚድያ "የግል" ትርጉም ይመስለኛል። እንደ አንድ ሙስሊም በጥሩ ማዘዝና ከክፉ መከልከል (ስርዓቱን ከጠበቀ አገላለፅ ጋር) ግዴታችን መሆኑ እንዳለ ሆኖ፣ አንዳንዴ የተቀባዩ አካል ገርበብ ያለ ወላዋይ አቀባበል ያስደነግጣል። ለምሳሌ፤ ሱና እየሆነ ከመጣው ለሰርግ ብቻ ሂጃብ ማውለቅ ባህላችን ጋር.... ከሂጃቡ አለመለበስ፣ ሙሉ ሰርጉ ተቀርፆ ሚድያ ላይ ሲቸበቸብ መታየቱ አስደንጋጭ ሆኖ ሳለ... የሙስሊም ወንድም/እህትነት ምክራቹን ስትለግሱ የሙሽሮች "በግል ህይወታችን አይመለከታቹም" ይበልጥ ጥያቄ ይፈጥራል። ትንሽ የተዘነጋው ነገር... ገመናህን አንዴ ሚድያ ላይ እንዲወጣ በር ከከፈትክ በኋላ "የግል ህይወት" የሚባል ነገር የለም አኺ.... ከጅምሩም ገመናዬ ገመናቹ፣ ሚስቴ ሚስታችሁ ብለህ ስትጋብዘን እንደሚመለከተን አምነህበት አይደል? ባይሆንማ ትናንት ማታ የተገባበዛቹት ራት፣ ሰርፕራይዝ መደራረጋቹ፣ ከእንቅልፋቹ እንዴት እንደተነሳቹ ከኛ ህይወት ጋር ምን አገናኝቶት አጋራኸን? ....የማንንም የሶሻል ሚድያ መብት በመጋፋት አይነት ሳይሆን ሲወደዱ ብቻ የጋራ፣ ሲነቀፉ የግል የሚሆነውን "ህይወታችንን" ስትሻማን ቅር ስለሚል ነው። እንደኔ እንደኔ.... ቢጥምም ቢመርም ካካፈልከኝ አይቀር በገዛ "ሚስታችን ቀሚስ"፣ በገዛ "ልጃችን ባህሪ"፣ በገዛ "መኝታችን ዲዛይን"፣ በገዛ "ውሏችን ፍሰት" የተሰማኝን ከማካፈል ወደኋላ አልልም። ምናልባት ያኔ... ለየትኛው ሰላም፣ መብቃቃት እና ጣፋጭ ኑሮ ሲባል ከአይኖች ደበቅ ማለትን እንደታዘዝን ከመረዳት ጋር፣ "የግል" ምንነት ይገለፅልን ይሆናል። ራህማኑ ወደሱ የሚያቃርቡን ነገሮች ላይ መስራትን ይወፍቀን። @Re_Ya_zan
Показать все...
8💯 2👎 1🔥 1
ነገሮችን ያለ ቦታቸው ፈልገህ ታውቃለህ?.... እኔ አውቃለሁ። አባቴን ብዙ ጊዜ ልጅ እያለን አንጠልጥሏቸው በሚገባቸው ፌስታሎች ውስጥ ፈልጌ አጥቼዋለሁ። አባትነት እንደዛ አይነት ነገር ነው.... ሁሉም የዩሱፉ ያዕቁብ አይሆንም፤ ስስቱን ቶሎ አታውቅበትም። አልያም ደግሞ... ፊቱን ያን ያህል የምትመረምርበት ጊዜም አይኖርህም... ምክኒያቱም ብዙ ራቶችህ ላይ ሳትተኛ ባለመድረሱ አትተዋወቁም። ወሳኝ ቀኖችህ ላይ እንኳን በታዳሚያን መሃል ፈልገህ አታገኘውም። ግን ልክ.... የህይወት ናዳ ላይህ ላይ ሊከመር ሲሞክር የሆነ የሚጠብቅህ ዳመና ነገር እንዳለ ልብ ብለህ ቀና ያልክ ቀን... ያኔ የተሳሳተ ቦታ ላይ ስትፈልግ እንደኖርክ ይገባሃል። ሆኖም ማስተዋል እስኪመጣ አንተም ሳታውቀው ሌላ ጎጆ ውስጥ ሌላ ተፈላጊ ሆነሃልና አሁንም የጋራ ጊዜ ማሳለፍ ቀጠሮ ላይ ይቀራል። ግን ተራ ተቀያይራቹ.... ከሱ ይልቅ ባንተ ጊዜ ማጣት መገናኘታቹ ሲቀንስ፣ ደግህን ሲያዩ በኩራት ትከሻህን የደገፉ እኚያ ክንዶች እገዛህን መሻት ሲጀምሩ፣ ጉዳትህን ሲያዩ የሚከስሉ እኚያ ቆዳዎች ከተሸበሸቡ መሰንበታቸውን ስታስተውል... ያኔ ነገሮች ወደ ማረፋፈዱ ከዞሩ ቆይተዋል። .....እኔን ከጠየቅከኝ.... አባትህን በፍቅር ቃላት ጎርፍ መሃል አቅፎ የሚያባብል ክንድ የመጠበቅ አይነት እየፈለግከው ከሆነ ብዙ ትጠብቃለህ። አባትነት ዱዳ ነው... ቋንቋውን እንድታውቅለት ይፈልጋል። ራሱን አሳልፎ ሲሰጥ እውር ነው... እናትነትን በመረዳትህ ብቻ ይረካል። አባትነት... ስለመከበሩ ነው፣ በዙሪያህ ያሉት እንዲያከብሩት ባደረግከው ልክ ያስከብርሃል። እንዲፈሩት ባደረግከው ልክ ያስጠብቅሃል። ብስጩነቱ መብዛቱን አትቁጠርበት እልሃለው.... ከጎንህ አለመገኘቱን አትይበት። ፍላጎቶቹን በድርቅናህ አትፎካከርበት። በእጁ ላይ ከምንም የማትቆጠር ደካማ ነገር ቢያመጣም ውደድለት። የከለለህ ዳመና በህይወትህ ሙሉ ሊከተልህ የታደለ ዘላቂ እንዳልሆነ ስትረዳ.... ያኔ እስከዛሬ ከምንም የቆጠርከው ትንሹም ትልቁም የሚናፈቅ የፍለጋህ መልስ እንደነበር ይገለፅልሃል። መልካም እድል። @Re_Ya_zan
Показать все...
10🥰 3👍 2
....ለማስታወስ ያህል... . . ....መስታወትሽ ዋሽቶሻል፣ አስቀያሚ አይደለሽም። ገና የሚስማማሽን የመዋብ ምርጫሽን በመፈለግ ላይ ብቻ ነሽ። መስታወትሽ ዋሽቶሻል፣ የአለም ቆንጆ አይደለሽም። አይተሽ ካልጠገብሽው መልክሽ በላይ የተዋበን ሌላ የፈጣሪሽን ስራ ስላልደረስሽበት ብቻ ነው። . ....አልችልም አትበይ.... ከማብሰሉም፣ ከጥልፉም፣ ከማንበቡም፣ ከፅዳቱም የማትታማዋን አንቺን እስክታገኛት አትቦዝኚ። ሁሉንም እችላለሁ አትበይ.... ጌታሽ የሚያስከብርሽን አሳውቆ ፈጥሮሻልና ያለ ቦታሽ ተፎካክረሽ አላዋቂ አትሰኚ። . ....አላረጀሽም.... ነገሽ የማያስችልሽን አእላፍ ሸክም ዛሬ አንፏቀሽው እደሪ። ገና ልጅ አይደለሽም.... ከሚፈስ የእድሜ ጅረት ጋር ትናንቴን ካልደገምኩ በሚል ስትታገይ ራስሽን አታድክሚ። . ....ውበትሽን መሃከለኛነት ላይ ፈልጊው። በመወደድና ባለመወደድ መሃል የሰላም ጎጆ ይኑርሽ። በመሄድና በመቅረት መሃል ልብሽ ሚዛን ይርገጥ። በዝምታና በጨዋታ መሃል አስታራቂ ዳኛ ሁኚ። አንገት ለማቅናትና ለመድፋትም ተራ ስጪ። እህቴ ሆይ.... አለም ለአስተዋይ ሴት ልዩ ዙፋን አላት። @Re_Ya_zan
Показать все...
🥰 12
....እስኪ ደግሞ... ደግመን ከተቀማመጥን አይቀር ስለዛ የጌታህ ተዐምር እናውራ.... ስለዛ ስሜት ነው የማወራው..... "ሰው" ከመባላችን ውጪ ምናችንም ከማይገናኝ ሌላ ፍጡር ጋር ለብቻችን ለመኖር ድፍረት ስለሚሰጠን ስለዛ የብቸኝነት ስሜት..... ከተወለድን ጀምሮ ጥበቃን፣ ደስታን፣ ምክርን... ለመኖር አስፈላጊ ያልነውን ሁሉ ሲሰጠን ከኖረው አካል (ቤተሰብ) ጨክኖ የመውጣትን ድፍረት ስለሚሰጠን ስለዛ የጉድለት ስሜት.... በእውነቱም የራህማኑ አፈጣጠር ድንቅ ነው። .....ማለት.... እሷኮ እንዴት እንደምታስደስታት ቀርቶ እንዴት መልስ ልትሰጣት እንደሚገባ ያልደረስክበት ውስብስብ ፍጥረት ናት። አንዳንዴ ስሜት የሌለህ ሁሉ ይመስላታል.... እንዴት እንደምታሳያትም ግራ ይገባሃል.... እሷ የተሰጣትን ያህል የቃላት ግርታ እንዳልገራልህ ታውቀዋለህ... ታውቀዋለችም እኮ.... ሆኖም አልተረዳኸኝም በሚል ታኮርፋለች። ነገሮችን በማይገባህ መልኩ ታወሳስባቸዋለች.... እስኪ አሁን ዛሬ ከአንደበትህ የወጣው "አንቺን ደስ እንዳለሽ" ሚኒሊክ ልጅ እያሉ ከሞተው የአክስቷ ባል ውሻ ጋር ምን አገናኘው?.... እምባዋ ቅርብ ነው.... ድንዳኔ በሞላው አለምህ ውስጥ ትንሽዬ ብርጭቆ ናት.... እንዴትም ብታነሳው በጠነከሩ ጡንቻዎችህ እንዳይሰበር ትሰጋለህ። ውስጧ የሰፈሩ ልዩ የፈጣሪዋ ኒዕማዎች አንተ ጋር የሉም.... ያማታል.... ያነጫንጫታል.... ልታጠጋጋው የምትሞክረው የትኛውም አይነት ህመም እያስረዳችህ ካለችው ህመም ጋር አይገጥምም.... ትጨነቃለህ። ስስ ናት.... ግን ደግሞ አንዳንዴ ልታስበው ከምትችለው በላይ የህመም መቋቋም አቅሟ ያስደንቅሃል... ሰው እንዴት ዘይትና እሳትን ይደፍራል?... ትንሽ ከመሆኗም ጋር አለቃ ናት... በጉልበቷ ሳይሆን በማሳዘኗ የፈለገችውን ስታስደርግህ ራስህን ታገኘዋለህ። አንዳንዴ አፍቃሪ ናት.... ሲላት ደግሞ የምታሳያት ፍቅር ሁሉ የሚያንገሸግሻት ራስወዳድ። "የሷን ስሜትና ንግግሮች ከመፍታት ለወፍ ማትስ ማስጠናት ይቀላል" ታስብልሃለች። ሳትወስዳት በፊት ይሄን ሁሉ ታውቅም ነበር...... ግን ታስፈልገኛለች ብለህ ያባትህን ቤት ትተህ ለሷ ጎጆ ለመቀለስ ስትወስን.... እዛ ጋር ይሄን ያዘናጋህ የጌታህ አንድ ተዐምር ነበር። .....እስኪ አስቢው.... እሱኮ ምንም ነገር ብታስረጂው አንቺ በፈለግሽው መጠን የማይረዳሽ የሆነ አራት ማእዘን ኸልቅ እኮ ነው። ሰው እንዴት ዳቦ ግዛ ሲሉት ዳቦ ብቻ ገዝቶ ይመጣል?.... እንዴት ያ የተለመደው አቀማመጥሽ ሲቀየር እንደከፋሽ፣ የሆነ ትኩረት፣ የሆነ ፍቅር እንዳስፈለገሽ ወዲያው አይገባውም?.... ለአንድ ሰአት ተኩል አንዲትን ኳስ ሲያሳድድ ያልደከመው.... ለግማሽ ሰዐት የምታስረጂውን ትኩረት ሰጥቶ ማዳመጥ እዳ ይሆንበታል። ያንቺ አርቆ አሳቢነትና ፈትፍቶ ማስረዳት ለሱ ጭቅጭቅ ነው። አንዳንዴ.... ትንሽ ነገር ያስደስተዋል። የሆነ... ባለ በሌለ አቅምሽ ከቀያየርሽውን የሳሎን ቅርፅ ይልቅ ሩዋንዳ ውስጥ ያለ፣ ማንም ግድ የማይሰጠው ፖሊሲ መቀየር አጀንዳ ሆኖ ያስቦርቀዋል። አንዳንዴ ደግሞ ከሱፍራ ሙሉ ምግብ የአንዱ ጨው ማነስ ያስደነፋዋል። ለሱ ህይወት ጥቁርና ነጭ ቀላል ናት.... የምለብሰው የለኝም ስትዪው አደምና ሃዋ ዱንያ ላይ ሳይገናኙ በፊት የገዛልሽን ቀሚስ ይጠራል። ሳይነግርሽ ለሱ አሁንም ቆንጆ እና የሚወድሽ እንደሆንሽ እንድትረጂው ይጠብቃል.... ትናንት ነግሮሽ፣ ጠዋት ቢደግመው... ሲመሽ ቢሰልሰው ያልቅበታል እንዴ?... "በቃ ያን በሚያክል የጡንቻ ስብስብ ውስጥ ሁለት የአእምሮ ሴል ነው ያለው ማለት ነው?" ያስብልሻል። ሳትሄጂ በፊት ታውቂም ነበር...ግን ያስፈልገኛል ብለሽ ከናትሽ ቤት ወተሽ ወደጎጆው ልትከትሚ ስትወስኚ.... እዛ ጋር ይሄን ያዘናጋሽ የጌታሽ አንድ ተዐምር ነበር። وَمِنْ ءَايَٰتِهِۦٓ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَٰجًۭا لِّتَسْكُنُوٓا۟ إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةًۭ وَرَحْمَةً ۚ إِنَّ فِى ذَٰلِكَ لَءَايَٰتٍۢ لِّقَوْمٍۢ يَتَفَكَّرُونَ ለእናንተም ከነፍሶቻችሁ (ከጎሶቻችሁ) ሚስቶችን ወደእነርሱ ትረኩ ዘንድ መፍጠሩ፣ በመካከላችሁም ፍቅርንና እዝነትን ማድረጉ ከአስደናቂ ምልክቶቹ ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ለሚያስተውሉ ሕዝቦች ተዓምራቶች አልሉ፡፡ (30 : 21) ....ጀባሩ ታላላቅ ተዐምራቶቹን ከጠቀሰበት ቅደም ተከተል መሃል ከራሳችን ለራሳችን ጥንዶች የተፈጠሩን መሆኑን ስለመጥቀሱ ነው የማወራው። በእርግጥም የሱ ተዐምር ሆኖ ጎዶሎነት፣ መሞላላት የሚያስፈልገን መሆናችንን የሚያስገነዝበን ያ ስሜት ባይኖር ይሄን ውሳኔ ባልደፈርን ነበር። ችግሩ ይሄ አደፋፍሮ ያስገባን ስሜት በተሟጠጠ ጊዜ፤ ራህማኑ እንዳዘዘን አንዳችን የአንዳችን ሰኪና መሆናችን በቀረ ጊዜ፤ ፍቅር እና እዝነት ሚዛናቸውን ጠብቀው መተካካት ባቆሙ ጊዜ.... ከእንቅልፉ እንደባነነ ሰው ሁሉም በአንዴ እንዳዲስ ዱብዳ ይሆናል። ለያዥ ለመካሪ አስቸግረን የገባንበትን ትዳር ወር ተስተካክሎ ሳያልፍ ካልወጣሁ ብሎ መጋደሉ ከመብዛቱ ጋር... እስኪ መነሻችንን አንዴ ደግመን እንፈትሸው። በእውነት ጠቃሚ ኡማ የሚያፈራ ትዳር የመመስረት ትክክለኛ ወንድነት ላይ ደርሰህና ተዘጋጅተህ፤ ወይስ ትዳር ሲባል ያቺ ተቃራኒ ፍጡር እስከዛሬ ጠብቃ ያቆየችው አካል የግልህ ሊሆን እንደሆነ በማሰብ ለሚከንፈው ሃሳብህ በመሸነፍ የወሰድከው እብደት ነበር?.... ብልሃትሽን፣ ትእግስትሽን፣ ውበትሽን አላህ ለወደደው ቤት ተጠቅመሽ የሞቀ የኢማን አለም ልትፈጥሪ ዝግጁ ሆነሽ፤ ወይስ እስከዛሬ ከመነካት ቀርቶ ከመታየት በተጠበቅሽው ልክ ከፍጥረትሽ ተቃራኒ የሆኑ ጠንካራ ክንዶች መሃል ለመታቀፍ የምትፍጨረጨረው ልብሽ አሳስታሽ?.... ከምን አንፃር ዝግጁነት እንደሚለካ ለመጪው የቤት ስራ ይሁነንና... ብቻ ራሳችንን አለም በፈሰሰበት የትዳር ቦይ ተከትለን ተንቧቡተን በሌላኛው ጎን የፍቺ ውድቀታቸው ላይ ሲፈሱ የምንከተል ሆነን እንዳናገኘው ሰከን እንበል። ወላሁል ሙስተዐን። @Re_Ya_zan
Показать все...
👏 2🔥 1
እለተ ጁምዓ አዲሱ ጀምበር፣ ህይወታችንን ያስጀመርንበት ነብዩሏህ አደም ነፍሳቸው ህይወት የተዘራበት የኛ የሰው ልጆች ታሪክ አንድ ብሎ የጀመረበት አዲስ ምዕራፍ ሆነ። ይህ ሁሉ ለመከሰት ግን አንድ ጀምበር በቂው ነበር። ለረጅም ጊዜ ወደ ተግባር ለማምጣት በማሰብም ሆነ ባለማሰብ ሲጠነሰስ የኖረ ነገርን ወደ ክስተት ለመለወጥ እንደ ሂደቱ አዳጋች አይደለም። እንዲሆን ከተወሰነ ቡሃላ ሁኖ ለማየት ምናልባት ሰከንዶች በቂ ይሆናሉ። የህይወት ዙረትም ልክ እለተ ጁምዓ ከብዙ ሂደት ቡሃላ ብዙ ክስተቶችን እንዳስተናገደች ሁሉ፣ ህይወታችንም በአንድ ጀምበር ብዙ ክስተትን ያስተናግል። ይከሰት ይሆን ብለን የሰጋነው፣ አይከሰትም ብለን በጭፍን ያመንነው ሁሉ ወደሆነ ምስቅልቅል ይለወጣል። አንዳንዴ ሁሉም አዲስ ጀምበር የሚናፈቅ አይሆንም። ትናንት እንዳይከሰት ስንፈራው የነበረው በስጋት ቀጠናችን ውስጥ ሲመላለስ የኖረውን ሀሳብ ዛሬ እውን ሆኖ እንደ ተለምዷዊ የአኗኗር ዘይቢያችን እየኖርነው ይሆናል። እዚህ አዲስ ጀምበር ላይ አንድ ቀን ስንቆም ከክስተቱ አስደንጋጭነት በላይ የሚከብደው ጭንቅላታችን ሲሰራ የኖረው እንዳይከሰት በመፍራትና በመጠንቀቅ እንጂ ቢከሰት ምን ማድረግ እንዳለበት በመስራት ላይ አለመሆኑ ነው። ያኔ መላ ቢስ ሁነን እንቀራለን። አዲስ ምዕራፍን ከህይወት ገፅ ላይ ከፍቶ የሚፅፉበትን ነገር አለማወቅ እጅግ በጣም ፈታኝ ክስተት ነው። ነገሩን ይበልጥ የሚያከብደው ደግሞ የሚፃፈውን ካለማወቅ በላይ ገፁን ለመሙላት ዝግጁ የሆኑ ችግሮች መብዛታቸው ነው። የሚናፈቅ ጀምበር እንዳለ ሁሉ የሚያስፈራና የሚጨንቅ ጀምበር በየህይወታችን ውስጥ እየተፈራረቀ ይገኛል። ህይወት የሁለቱ ጀምበር ጥምረት ነውና። @Re_Ya_zan
Показать все...
1
Фото недоступноПоказать в Telegram
.....እነዛ.... በጉጉት ተጠባብቀን ያየናቸውን ፊልሞች እኮ አፈላልጌ ደግሜ አየኋቸው። አህህህህ..... ልጅነታችንን ይሸታሉ! ደብዝዘዋል ብቻ ብልህ እንዳታምነኝ.... አለም ከጥቁርና ነጭ ቀረፃ በተላቀቀ ማግስት ነበር እንዴ የታደምናቸው አስባሉኝ እንጂ። ደግሞ እንዳዲስ ምን ቢገርመኝ ጥሩ ነው?..... ለካ በዘመናችን ወጣት ጎረምሳና ኮረዳ ቆመው መሳሳቃቸው ያስቆጣ ነበር.... የወደደ ፍቅሩን ለመግለፅ ለቀናናናት ይጨነቅ ነበር.... ለካ ቀሚስ ከጉልበት በማለፉ ጭኖች እስኪቀሉ ተገርፈዋል.... በመፅሃፍ ገፆች መሃል የተረሳ አእላፍ ፅጌሬዳም ከትዝታው ጋር እንዳበበ ኖሯል.... . . .....ለካ.....ለካ ደግሞ እድሜ ታስሮ አይቀመጥ ነገር ያፈተልካል.... ዘመንም እንደ ሰው ስጋ ለብሶ ይናፈቃል.... በትናንት ውስጥ ወዳለች አንድ እውነተኛ ቀን መመለሻው እንዴት ይሆን ውዴ?... እንጃ.... ብቻ.... ከነ ሙሉ ክፉ ደጉ ያ የኖርንበት ደብዛዛ ጊዜ ቀና ነበር። @Re_Ya_Zan
Показать все...
ጥቋቁር ገፆች (ከገሃዱ አለም ታሪክ-ለትውስታ) . "ህይወት ትውስታ ናት፤ ከተረሳህ ትሞታለህ" . . << <ብዙ ቀን ተማሪዎቼን በደንብ ያላስተማርኳቸው ሲመስለኝ ህሊናዬ አያርፍም እንደምልሽ አስታወስሽ?.... በዛ ሁሉ ጨለማ ህይወትና አሁን የምኖረው ህይወት መሃል ያለው ብቸኛ ልዩነት.... ብቸኛ የደስታ ጭማሪ ህሊናዬ ማረፉ ስለሆነ ነው። እነሱ የሆነ ነገር ሲማሩ.... እንኳንም ያንን ሁሉ አለፍኩት፤ እንኳንም እዚ ጋር ለመቆም ታገልኩ እላለሁ። የመጀመሪያ ብዙ የምለውን ገንዘብ መቀበል የጀመርኩት እዚ ጊቢ ስገባ ነው.... ግን ከህሊናዬ ሰላም ውጪ የትኛውም ገንዘብ በየቀኑ ለማወጣው ጥረት የሚመጥን ሆኖ አይደለም የምቀጥለው። መምህር መሆን ቀላል አይደለም.... በየምሽቱ ለቀጣዩ ቀን መዘጋጀት ይጠይቃል። እኔን ስትሆኚ ደግሞ.... በየምሽቱ እንዴት ሰው ፊት እንደምትስቂ፣ እንዴት የራስሽን ችግር ለራስሽ ደብቀሽ ደስተኛና ባለ ተስፋ እንደምትመስዪ ማስመሰልንም ጭምር መለማመድ ይጠይቃል ምክኒያቱም ወትሮውን ደስተኛና ተግባቢ መሆን ቀርቶ የመኖር ተስፋ ያለው ሰው አይደለሁም። .... የአእምሮ እጢ በሽተኛ ነኝ። አልጠበቅሽም አይደል? አንዳንዴ ክፉኛ ይነስረኛል.... ሀኪሞች በተኛህበት ደም አፍኖህ ልትሞት ትችላለህ እሰኪሉኝ ድረስ አደገኛ እጢ አለብኝ። ይድናል ወይ? አይድንም። እጢ እንዳለብኝ ያወኩት በ 14 አመቴ ነበር.... እሱም ነስር ሲበዛብኝ ሀኪም ቤት ራሴ ሄጄ በተመረመርኩ ጊዜ። የ 14 አመት ልጅ፣ መድሃኒት እንዴት እንደምገዛ.... ቀጠሮ እንዴት እንደምይዝ ምናምን ገና በወጉ ሳላውቀው ከፊቴ የተቀመጠው ዶክተር "ልትሞት ነው" ይለኛል። ለዚህኛው ግድ የለሽነታቸው ወላጆቼን መቼም ይቅር አልላቸውም። ተገደው ሊሆን ይችላል ለኔ ግድ ያልነበራቸው ግን.... እኔንጃ፤ ከዚ በኋላ ይቅር የሚል ልብ የለኝም። ዶክተሮች.... ወይ ደስተኛ በመሆን እድሜህን ታራዝማለህ፣ ወይ ራስህን በማስጨነቅና በመጠበብ ሞትህን ታፋጥናለህ ብለውኛል... ተፈልጎ የሚታዘን ይመስል። ብቸኛ ደስተኛ ቦታዬ ግን ይሄ ነው። በህይወቴ የፈለኩት አንድ ነገር.... "ጎበዝ!" መባል ነበር፤ ከወላጆቼ ለሰራሁት አንድ ነገር እንኳን ማበረታቻ ማየት.... ግን አልሆነም። እስካሁንም ካለኝ ነገር ላይ መስዋትነት በመክፈል ላይ ብቻ ነኝ። ግን እዚ መጥቼ ተማሪዎቼ "እንወድሃለን.... ገብቶናል" ሲሉኝ ለኔ ከዚ በፊት ተሰምቶኝ የማያውቅ የቤተሰብነት ስሜት ይሰማኛል። ሁሌ "ደስተኛ ናቹ? ወዳቹኛል? ትንሽ ነገርም ቢሆን ገብቷቿል?" እያልኩ ማጨናንቃቸው ለዚ ነው። ተጨማሪ አንድ ቀን ለመኖር። ከንግዲህ ልሄድ ነው... ከ 1 ወር በኋላ.... ይሄን ሁሉ የማስረዳሽም ስለምሄድ ለውጥ አያመጣም በሚል ከጠቀመሽ ነው> >> የንግግራችን ማብቂያ ባይሆንም ጭብጡ ነበር። ከዚ በኋላ እንደማልረሳውና.... ለራሱ ባይሆንም ለሌሎች ከተሞክሮው ትምህርት እንዲሆን መኖር እንዲቀጥል መነጋገራችንን አስታውሳለሁ-ከአመት በፊት። ከ800 በላይ መፅሀፎች አሉት.... "ረሀቤን ለማስታገስ ስል መፅሃፎቼን ሽጫለሁ" ሲል ከቀመሳቸው ክፉ ቀናቶች ሁሉ ይሄኛው እንደመረረው ፊቱ ላይ ይንፀባረቅ ነበር። ለዛም መሰለኝ ለኔ ለማስታወሻነት መፅሀፍ መስጠቱን የመረጠው። ውስጡ የተፃፈበት ትንሽ ማስታወሻ "በዚች ምድር ላይ ማንኛውም ጥቁረት፤ ነጩ ልብሽን እንዳያቆሽሸው ከመመኘት ጋር"... ከሚል ፅሁፍ ስር "ህይወት ትውስታ ናት፤ ከተረሳህ ትሞታለህ" የሚል ጥቅስ የታከለበት ነበር። የሚሞተው በእጢ የተመረዘ አካል ሲቀበር ሳይሆን ከትውስታ የተፋቀ ትዝታ ሲደመሰስ ነው ማለቱ ነው። እኔም ሁሌም በህይወት ይኖር ዘንድ ያካፈለኝን ቁምነገሮች ከወረቀት አሰፈርኩ... . . ተፈፀመ @Re_Ya_Zan
Показать все...
👍 1
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.