ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
Открыть в Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
Больше637
Подписчики
-124 часа
-47 дней
-1230 день
Архив постов
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፳፯ (27) ቀን።
❤ እንኳን #በታላቁ_በቈስጠንጢኖስ_ዘመን ለነበረ ለከበረ አባት ለአንጾኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ትምህርቱ በዓለም ለመላ ቁጥሩ #ከሠለስቱ_ምዕት ለሆነ #ለታላቁ_አባት_ለአባ_አንስጣስዮስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከቸሩ_መድኃኔዓለም_ከስቅለቱ መታሰቢያ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤#አባ_አንስጣስዮስ፦ ይህንንም ቅዱስ የከበሩ አባቶቻችም በኒቅያ ከተማ የአንድነት ስብሰባ በአደረጉ ጊዜ በዚህ ጉባኤ ከተሰበሰቡ ሊቃውንት አንዱ እርሱ ነው፡፡ በዚህም ጉባኤ ተስማምተው አርዮስን ከባልንጀሮቹም የቂሣርያ አውሳብዮስ የኒቆምድያ አውሳብዮስና አርናሲስ ናቸው። እሊህም፡ በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ታውቀዋል እሊህም የከበሩ አባቶችም ሥርዓትን ሠርተው ወደ የአገራቸው በተመለሱ ጊዜ እሊህ ከኤጲስቆጶስነት ሹመት የተሻሩት ከሃድያኑ ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄዱ መስለው ወጡ ወደ አንጾኪያም ከተማ በአንዲት አመንዝራ ሴት ዘንድ ተሰበሰቡ፡፡ ብዙ ገንዘብም ሊሰጧት ቃል ገቡላት ወደ ቤተ ክርስቲያን እንድትገባ ይህ አባት ከእርሷ ጋር እንዳመነዘረ የወለደችውም ልጅ የእርሱ እንደሆነ በዚህ ቅዱስ አባት አንስጣስዮስ ላይ ለካህናቱና ለሕዝቡ እንድትናገር አስተማሩዋት። ሕዝቡም እንዲህ አሏት "አንቺ ሐሰተኛ ነሽ በዚህ ቅዱስ አባት ላይም ሐሰት ተናግረሻል፣ በከበረ ወንጌል ካልማልሽ በቀር ቃልሽን አንቀበልም" አሏት፡፡ እርሷም ስለገንዘብ ፍቅር በሐሰት ማለች፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ከሀድያኑ ለንጉሥ ነግረው ከመንበረ ሢመቱ ወደ አጥራክያ ደሴት አሳደዱት በስደትም ሳለ በርሷ የካቲት27፡ ዐረፈ፡፡ ነገር ግን ለእሊህ ከሃድያን ወዮላቸው የእግዚአብሔርን ልጅ ከመለኮቱ ባሕርይ ለይተው "ፍጡር ነው" ብለውታልና ይህንንም ንጹሕ አባት ሰይጣን አባታቸው እንዳስተማራቸው ከአመንዝራ ጋር አንድ ሁነው በተንኰል ከመንበረ ሢመቱ አውጥተውታልና። እግዚአብሔር ግን ቸለል አላለም ይህን አባት ከአሳደዱት በኋላ ያች አመንዝራ ሴት ጭንቅ በሆነ ደዌ ተይዛ ብዙ ተሠቃየች ለሞትም ተቃረበች ያን ጊዜም ይህ ሁሉ መከራ የደረሰባት በከበረ ወንጌል በሐሰት ስለማለች እንደሆነ ተገነዘበች፡፡ በአንጾኪያም ሰዎች ሁሉ ፊት በደሏን አመነች፡፡ እንዲህም አለቻቸው "ይህ ቅዱስ አንስጣስዮስ ከዝሙት ንጹሕ ነው፣ እነዚያ ከሀድያን ብዙ ገንዘብ ሰጥተውኝ በእርሱ ላይ ሐሰት እንድድናገር በከበረ ወንጌልም በሐሰት እንድምል አደረጉኝ እንጂ"፡፡
❤ የአንጾኪያ አገር ሰዎችም ኃጢአቷን ማመኗን በሰሙ ጊዜ እጅግ አዘኑ፡፡ ካህናቱም በጸሎትና በቅዳሴ ጊዜ ስሙን የሚያነሱ ሆኑ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም አመሰገነው በመታሰቢያውም ቀን ስለእርሱ ብዙ ቃላትን ደረሰ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አንስጣስዮስ ጸሎት ይማረን በረከትም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፥ የካቲት 27 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_እብል_አንስጣስዮስሃ_ፍጹመ። ትምህርታቲሁ፡ ዘመልዐ ኲሎ ዓለም። እኩያን ዕደው እለ ተዓጽፋ መርገመ። ነገረ ሐሰት ላዕሌሁ እንዘ ይነቡ ሕሱመ። ኀበ ሰደድዎ አዕረፈ ወኖመ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_27።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን። ወአኃዙኒ ማኅበሮሙ ለእኩያን። ቀነውኒ እደውየ ወእገርየ"። መዝ 21፥16-17። የሚነበበው ወንጌል ማር 15፥22-28።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም። ወገብረ መድኃኒት በማእከለ ምድር። አንተ አጽናዕካ ለባሕር በኃይልከ"። መዝ 73፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 6፥5-12፣ 1ኛ ጴጥ 2፥21-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 10፥36-44። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ19፥16-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ዓምደ ሥላሴ የዕረፍት በዓልና የጾም ወራት። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፳፯ (27) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ታላቁን ገዳም #ማኅበረ_ሥላሴ_ለመሰረቱና እንደ መሶበ ወርቅ ከፍ አድርገው ላስባረኩ፤ #ንጉሥ_ሱሱንዮስ የካቶሊክን እምነት በተቀበለ ጊዜ ምላሱ ተጎልጉሎ የነበርው በመስቀላቸው ባርከው ለፈወሱት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ዓምደ_ሥላሴ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ዓምደ_ሥላሴ (ጎጃም)፦ የትውልድ አገራቸው ጎጃም ሲሆን በአጤ (ዐፄ) ሱስንዮስ ዘመን የነበሩ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደርጉ የነበሩ ገዳማዊ መነኵሴ ናቸው፡፡ ጻድቁ ማኅበረ ሥላሴን ያቀኑ ታላቅ አባት ሲሆኑ በተለይም አንድ የሚታወቁበት ትልቅ ታሪክ አላቸው፡፡ እርሱም አጤ (ዐፄ) ሱስንዮስ ካቶሊካውያን ደግፈው 8ሺህ የአገራችንን ሊቃውንት በአንድ ቀን ባሳረዱ ጊዜ ንጉሡ ወዲያው "ኦርቶዶክስ ይርከስ ካቶሊክ ይንገስ" ብሎ ያወጀበት ምላሱ ተጎልጉሎ ወጣ፡፡ እንደ አርዮስም ሆዱ አብጦ አንጀቱ ተልቶ ሊሞት ባለ ሰዓት አቡነ ዓምደ ሥላሴ አዘዞ ድረስ ሄደው "ፋሲል ይንገሥ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ትመለስ የሱስንዮስም ምላስ ይመለስ" በማለት ተጎልጉሎ የወጣውን ምላሱን በመስቀላቸው ቢባርኩት ምላሱ ተመልሶለታል፡፡
❤ አጤ (ዐፄ) ሱስንዮስ ግን ለካደበት ክህደት ቅጣቱ ነውና በመቅሰፍቱ ሳይድን በዚያው ታሞ ማቆ ማቆ ክፉ አሟሟት ሞቷል፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ዓምደ ሥላሴ የአጤ (ዐፄ) ፋሲልን ሹመትና ሃይማኖትን በአዋጅ፡አጽንተው ተመልሰው ወደ ገዳማቸው ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ገብተዋል፡፡ አጤ (ዐፄ) ፋሲልንም የማኅበረ ሥላሴን ገዳም ግዛቱን ከሱዳን እስከ ጣቁሳ ድረስ እንዲሆን በአዋጅ ወስነው ሰጥተውት ነበር ነገር ግን ላይጠቀምበትና ላይጸና ነገር የደርግ መንግሥት የገዳሙን ሥርዓት ከማፍረሱም በላይ ርስት ጉልቱን ነጥቆ ወሰደበት፡፡
❤ በደርቡሾች ወረራ ጊዜ እንግሊዞች አጋጣሚውን ተጠቅመው የአቡነ ዓምደ ሥላሴን ቅዱስ ገድል ዘርፈው ወስደውታል፡፡ ዛሬ፡ በእንግሊዝ አገር ገድለ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ይገኛል፡፡ ጻድቁ የካቲት27 ቀን ያረፉ ሲሆን ዐፅማቸው በዚያው በመሠረቱት በማኅበረ ሥላሴ ገዳም በክብር ተቀምጧል፡፡ ከአቡነ ዓምደ ሥላሴ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፳፮ (26) ቀን።
❤ እንኳን #ከዐሥራ_ሁለቱ_ደቂቀ_ነቢያት ለአንዱ ዖዝያ ይባል ለነበረው ለዕውነተኛ #ለቅዱስ_ሆሴዕ ለዕረፍቱ በዓልና ለከበሩ #ለቅዱሳን_ሳዶቅና ከእርሱ ጋር ሰማዕትነት ለተቀበሉ #ሁለት_ሺህ_ስምንት ሰዎች ለዕረፍታቸው በዓል መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ ነቢዩ ቅዱስ ሆሴዕ፦ ዳግመኛም ይህ ነቢይ በአራቱ የይሁዳ ነገሥታት ዘመን ትንቢት ተናገረ። እሊህም ዖዝያን፣ ኢዮአታም፣ አካዝና ሕዝቅያስ ናቸው። በትንቢቱም ድንቆች ሥራዎችን ተናገረ የእስራኤል ልጆች ገሠጻቸው "የአመንዝራ ልጆች" ብሎም ጠራቸው እግዚአብሔርም ቊጣውን ከእርሳቸው እንደማይመለስ አሰረዳቸው። እንዲህም አለ "የእስራኤል ልጆች ቊጥራቸው እንደማይሠፈርና እንደማይቆጠር የባሕር አሸዋ ቢሆን ከጥቂት በቀር አይተርፍም" አለ።
❤ ስለ አሕዛብም በእግዚአብሔር ማመን ተናገረ እንዲህም አለ "እኔ ወገኖቼ ያልሆኑትን እጠራቸዋለሁ እነርሱም ይሰሙኛል። ዳግመኛም ስለ መድኃኒታችን መከራ መቀበልና በደሙ ስለ መዳናችን ስለ ትንሣኤውም እንዲህ ብሎ ተናገረ "እሱ በመከራ ገርፎ ያድነናል እርሱም በመከራ አቊስሎ ይቅር ይለናል ሲያድነንም በሁለተኛው ቀን ነው በሦስተኛውም ቀን ድነን በእሱ ፊት እንነሣለን" እግዚአብሔርንም አውቀን እንከተለው ዘንድ ስለ ሞት ሥልጣን መሻር ስለ መቃብርም መሸነፍ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ "ሞት ይዘህ ማስቀረትህ መቃብርስ ድል መንሳትህ ወዴት ነ" ትንቢትን እየተናገረ ሰባ ዓመት ያህል ኑሮ በበጎ ሽምግልና የካቲት26 ቀን ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሆሴዕ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ ቅዱስ ሳዶቅ፦ ይህንንም የከበረ ሳዶቅን ለፀሓይ ይሰግድ ዘንድ የፋርስ ንጉሥ ብርህም ፈለገው ቅዱሱም "ለፈጣሪዋ እንጂ ለዚች ለምትታይ ፀሓይ ልሰግድ ከእናቴ ማኅፀን አልወጣሁም" ብሎ መለሰለት። ብርህም ንጉሥም መልሶ "ለዚች ፀሓይ አምላክ አላትን" አለው ቅዱስ ሳዶቅም "ዓለሙን ሁሉ የፈጠረ ክርስቶስ አምላክ ነው" አለው። ንጉሡም የቅዱስ ሳዶቅን ራስ በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የከበረ ሳዶቅም ቁሞ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ራሱን ዘንበል አድርጎ ቆረጡት። ያን ጊዜ ከሰማይ ብርሃን በላዩ ወረደ ከዚያ ያሉትም ሁሉ አይተው "እኛ ሁላችንም በቅዱስ ሳዶቅ አምላክ የምናምን ክርስቲያን ነን" ብለው ጮኹ ንጉሡም ሁሉንም ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ ቊጥራቸውም ሁሉት ሺህ ስምንት ነፍስ ናቸው። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት26 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለሆሴዕ_ምጽአተ_ክርስቶስ እንዘ ይስብክ። በቃለ ትንቢት ቡሩክ። የኀሥሥዋ ይቤ #ለእግዚአብሔር_አምላክ። እንበለ ንጉሥ ወኢ #መልአክ። እምድኅረ ነበሩ እስራኤል በበክ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_26።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ። በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባእ ቅድሜከ ገዓሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ 78፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 9፥24-30፣ 2ኛ ጴጥ 1፥19-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥17-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥36-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ወራት። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በዋሻው ደጃፍ የውኃ ምንጭ ነበረ ምሳርንም ወረወረበት ምሳሩም ነቢይ ኤልሳዕ እንዳደረው በውኃ ላይ ተንሳፈፈ። የከበረች አርባ ቀንን ጾም ከሦስት ቀኖች፡በቀር ሳይበላ ፈጸመ። ሲባልም ሲያንቀላፋም ግድግዳ ተጠግቶ ነው እግሮቹም እንደ ዝሆን እግር እስከሚሆን እንዲህ ተጋደለ።
❤ በአንዲትም ዕለት ለደቀ መዛሙርቱ "እንሆ ዓለም አለፈ" አላቸው በጠየቁትም ጊዜ "ንጉሥ ቴዎዶዮስ ሞተ" አለ። በአንዲትም ዕለት ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር የያዘ እንግዳ በአንድ ቄስ ቤት አደረ በተኛ ጊዜ ስለ ገንዘቡ ቄሱ ገደለውና ወስዶ ከአንድ መነኵሴ ደጅ ጣለው ለቅዱስ አቡፋናም በነገሩት ጊዜ ከሟቹ ላይ እንዲጥሉት ቆቡን ሰጣቸው ሲጥሉትም ሟቹ ተነሣ ስለ ገንዘቡ ቄሱ እንደ ገደለው ነገራቸው እጅግም አደነቁ።
❤ በአንዲትም ዕለት አንድ ሰው ቡራኬ ሊቀበል ወደርሱ ሲመጣ ልጁ በጒዞ ላይ ሞተ ልጁንም ተሸክሞ ወደ ቅዱስ አቡፋና ሔደ በፊቱም ሰግዶ ተባርኮ ተመለሰ ያን ጊዜ የሞተው ብላቴና ተነሥቶ አባቱን ተከተለው። ከቆመ ጀምሮ ዐሥራ ስምንቱ ዓመት በተፈጸመ ጊዜ ዕረፍቱን አውቆ ቅዱስ ቊርባንን ተቀበለ ወደ መኖሪያውም ሒዶ ራሱን ዘንበል አድርጎ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ የካቲት25 ሰጠ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አቡናፋር በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት 25 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለክሙ_ቶና_ዲያቆን። #ወሚናስ_ብፁዕ ሠናየ አሚን። #ወይልማድዮስ ነሣኢ አክሊለ ግዕዛን። ሀቡኒ አጋእዝትየ ለብእሲ ምስኪን። ዕሴተክሙ ዘኢርእየ ዐይን"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_25።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ጸገብነ እግዚኦ እምበረከተ ቤትከ። ቅዱስ ጽርሕከ ወመንክር በጽድቅ። ስምዐነ አምላክነ ወመድኃኒነ"። መዝ 64፥4-5። የሚነበቡት መልዕክታት ፊሊ 1፥1-13፣ 2ኛ ጴጥ 1፥10-15 እና የሐዋ ሥራ 9፥1-10። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 9፥12-17። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ወራት። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፳፭ (25) ቀን።
❤ እንኳን ለከበሩ #በቅዱስ_ጳውሎስ ትምህርት ላመኑ #ለቅዱሳን_አውሳንዮስ_ፊልሞ፣ ለድንግል #ቅድስት_ሉቅያ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለከበረ #ሐዲስ_አባ_እንጦኒ ይህም ረውሕ ለሚባለው ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና ከግብጽ አገር ከእስሙናይን አውራጃ ለሆነ ዐሥራ ስምንቱ ዓመት ቆሞ ሳይቀመጥ ለጸለየ #ለአባ_አቡፋ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሮሜ አገር #ከዲያቆን_ቶና ከአገረ ቊስ #ሚናስ_ከጋዛ_ይልማድዮስ በሰማዕትነት ከዐረፉ፣ #ከደማይልናልና_ከርጊኖስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #የከበሩ_ቅዱሳን_አውሳንዮስ_ፊልሞና_ሉቅያ፦ እሊህ ቅዱሳንም በአፍራቅያ አገር ሳለ በከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ትምህርት ያመኑ ናቸው ከሀድያንም ዝሑራ በሚባል ኮከብ ስም ለሚጠሩት ለአርታዳሚ ጣዖት በዓልን በአደረጉ ጊዜ አይተው በስሕተታቸው ሊዘብቱ እሊህ ቅዱሳን ተስብስበው ወደ ጣዖቱ ቤት ገቡ ሰዎችም ለጣዖቱ ሲሠዉና ከፍ ከፍ ሲያደርጉት በአዩአቸው ጊዜ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር እሳትነት ልባቸው ነደደ ከጣዖቱም ቤት ወጥተው ወደ ክርስቶሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሔደው የክብር ባለቤት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብሩንና ልዕልናውን አብዝተው አመሰገኑ። ከዚያ ካሉት አንድ ሰው በሰማቸው ጊዜ በጣዖታቸው ላይ እንደ ዘበቱ የተናገሩትን ልብ ብሎ በመኰንኑ ዘንድ ወነጀላቸው መኰንኑም በፈረስ ተቀምጦ ሔደ ከወታደሮቹም ጋር ቤተ ክርስቲያኒቱን ከበባት ከምእመናንም ሰዎች የሸሹ አሉ።
❤ እሊህም ሦስቱን ቅዱሳን ያዛቸው የብረት ዘንጎችን በእሳት አግለው ቅዱሳኑ ጐኖች ውስጥ አደረጉት ከዚህም በኋላ የከበረ አውሳንዮስን ወደ ጒድጓድ ወረወሩትና ነፍሱን እስከ ሰጠ ድረስ በድንጊያ ወገሩት። የከበረ ፊልሞናንና የከበረች ሉቅያን ግን ብዙ ጊዜ በጸና ሥቃይ ያሠቃዩአቸው ጀመር ነፍሳቸውንም ይወስድ ዘንድ እግዚአብሔርን ለመኑት እርሱም ልመናቸውን ተቀብሎ ነፍሳቸውን የካቲት25 ወሰደ። በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እንሆ የምስክርነታቸውና የሃይማኖቻቸው መታሰቢያ ተጽፎአል። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሐዲስ_አባ_እንጦኒ (ረውሕ)፦ ይህም ከከበሩ ዐረቦች ወገን የቆሮስ ሰው የሆነ ብዙ ገንዘብ ያለው ነው በሰማዕታት አለቃ በቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም አጠገብ በወንዝ ዳርቻ የሚኖር ነው። ይህም ጐልማሳ አብያተ ክርስቲያናትን የሚቃወም ሁኖ ቅዱስ ቊርባንን በመስረቅ ኅብስቱን ይበላዋል የከበረ ደሙንም ከጽዋው ውስጥ ይጠጣል የመሠዊያውንም ልብስ ገፎ በእሳት ያቃጥለዋል በክርስቲያን ሃይማኖትም ላይ ይዘብታል። መኖሪያው ቤቱ በከፍታ ቦታ ላይ ስለ ሆነ ካህናት ሲያገለግሉ ይታዩት ነበር።
❤ በአንዲትም ዕለት በቅዳሴ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ተከፍቶ አየ በፈረስም ተቀምጦ መጣ የቅዱስ ቴዎድሮስንም ሥዕል ተመልክቶ በፍላፃዎች ወጋው። አንዲቱም ፍላፃ ተመልሳ መሐል እጁን ነደፈችው በጭንቅም ከእጁ ላይ መዘዛት ይህንንም ለማንም አልነገረም። በሌላዪቱም ዕለት በወንበሩ ላይ ተቀምጦ ሳለ መሥዋዕትን ተሸክመው ወደ መቅደስ ሲገቡ ካህናትን አያቸው በጻሕሉም ውስጥ ነጭ በግ ተኝቶ ከበላዩ ነጭ ርግብ ሲጋርደው በቅዳሴውም ፍጻሜ ያ በግ በየመለያያው የተከፋፈለ ሆኖ ካህናቱም ከተከፋፈለው ሥጋውን ሲቀበሉ ደሙንም ከጽዋው ውስጥ ሲቀበሉ አየ እጅግም አደነቀ። በልቡም የክርስቲያን ሃይማኖት እጅግ ድንቅ ነው በእውነትም የከበረ ክቡር ነው አለ። ዳግመኛም ያ በግ ተመልሶ እንደ ቀድሞው ኑሮው ሕያው ሁኖ አየ ከዚያም በኋላ ከመቀመጫው ወርዶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ሔዶ ያየውን ሁሉ ለካህናቱ ነገራቸው እርሱም ሰምተው ስለዚህ ድንቅ ሥራ ደስ አላቸው።
❤ በዚችም ሌሊት ተግቶ ሲጸልይ ሊቅ ቅዱስ ቴዎድሮስ ተገለጠለት እርሱም በፈረሱ ላይ ተቀምጦ ነበር እንዲህም አለው "እንሆ በእኔ ላይ ሥዕሌን እስከ ወጋህ ድርስ ክፉ ሠራህ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ሥጋ ላይም ዘበትክ አሁንም ከክህደትህ ተመልሰህ በክብር ባለቤት በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን" አለው ይህንም ብሎ ከእርሱ ተሠወረ። በማግሥቱም በፈረሱ ላይ ሁኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ ወደ ሊቀ ጳጳሳቱም ገብቶ ከእርሱ የሆነውን ሁሉ ነገረው ሊቀ ጳጳሳቱም ሰምቶ እግዚአብሔርን አመሰገነው እርሱንም "በሕዝብ፡ፊት እዳላጠምቅህ እፈራለሁ ነገር ግን ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ሒድ ጌታችን ክርስቶስ የሚያጠምቅህን ይሰጥሃል" አለው። እርሱም ሰምቶ ወደ ዮርዳኖስ ሔደ ወደ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገባ የሌሊቱም እኩሌታ ሲሆን የብርሃን እናት ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ነጭ ሐር ግምጃ ለብሳ ተገለጠችለት ከእርሷም ጋር በንጹሕ ልብስ የተሸለመች ሴት ነበረች በእጅዋም ይዛ አነሣችውና "አትዘን እኔ ካንተ ጋር እኖራለሁና" አለችው። ሲነጋም ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ በሔደ ጊዜ ሁለት ገዳማውያን መነኰሳትን አገኛቸው እነርሱም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቁት። ስሙንም እንጦንስ ብለው ሰየሙት የምንኵስና ልብስ አስኬማንም አልብሰው በሰላም አሰናበቱት ወደ ደማስቆም ሔደ ወደ ቤቱ ገባ።
❤ ባልንጀሮቹና ወገኖቹም በአዩት ጊዜ "የለበስከው ምንድን ነው አሉት" እርሱም "እኔ ክርስቲያን ነኝ" አላቸው በዚያንም ጊዜ ይዘው በሜዳ ውስጥ እየጐተቱ ወደ መኰንኑ እስኪያደርሱት ይደበድቡት ነበር። መኰንኑም ወደ እስር ቤት እንዲጨምሩት አዘዘ በታላቅ ሥቃይም ዐሥራ ሰባት ሌሊት በዚያ ኖረ እንሆ በላዩ ብርሃን ወረደ እንዲህም የሚል ቃል ሰማ "እንጦንዮስ ሆይ አክሊል ተዘጋጅቶልሃልና አትፍራ" ብርሃንን የለበሱ ሁለት አረጋውያንም መጥተው በራሱ ላይ የብርሃን አክሊል አኖሩ በነጋ ጊዜም ወደ አደባባይ ወስደው ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና በዕንጨት ላይ ሰቀሉት። በሌሊትም በላዩ ብርሃን ወረደ ጠባቆችም አይተው ከዕንጨት ላይ አውረዱት በጤግሮስ አቅራብያ ቀበሩት ከመቃብሩም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዲስ በአባ እንጦንስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_አቡፋና፦ ይህም አባት ከቶ ብርሃን በሌለበት ዋሻ ውስጥ የሚኖር ሁኖ በየሁለት ቀን ይጾማል የሚበላውም የሚጠጣውም በመለኪያ ተለክቶ ነው በሌሊትም በመዓልትም አምስት መቶ ጊዜ ይጸልያል። በአንደዲትም ዕለት ወንድሞች ሊጐበኙት ወደርሱ መጡ እንጀራንም አጣ ሦስት እንጀራንም በአገኘ ጊዜ ለሃያ ሰዎች አቀረበላቸው እነርሱም በልተው ጠገቡ ተአምራትም እያደረገ በሽተኞችንም እየፈወሰ ኖረ።
❤ ከዚያም በኋላ እንዲህ የሚል ቃል ከሰማይ ወደርሱ መጣ "አቡፋና ሆይ ዐሥራ ስምንት ቀረህ" የከበረ አቡፋናም" ዐሥራ ስምንት ዕለታት እንደሆኑ አስቦ እሊህ ዕለቶች እስቲፈጸሙ ቆመ ከዚያም በኋላ ሱባዔዎች ናቸው ብሎ ይህንንም በመቆም ፈጸመ እንደ፡ገና ወሮች ይሆናሉ ቢሆኑስ ብሎ ይህንም በመቆም ሳያጓድል አደረሰ። ዳግመኛም እንዲህ የሚል ቃል ወደርሱ መጣ "አቡፋና ሆይ ዐሥራ ስምንት ዓመት ናትና ጽና በርታ" አለው በዚያንም ጊዜ ፈጽሞ ጸና።
+9
፲፫ኛ በዓለ ሢመት
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት 13ኛ በዓለ ሢመት የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በድምቀት ተከበረ ።
+2
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቤተልሔም ግንባታ የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በ13ኛ ዓመት በዓለ ሢመታቸው በጥንታዊውና ታሪካዊው የመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ደረጃውን የጠበቀ የቤተልሔም ግንባታ ለማከናወን የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፳፬ (24) ቀን።
❤ እንኳን #ለከበረ_አባት ለንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ወታደር አለቃ ለነበረው ብዙ ተአምራትን ላደረገ፤ ብዙ ሰዎችን ያጠፋውን ታላቅ ከይሲ በጸሎቱ ለገደለው #ለኤጲስቆጶስ_ቅዱስ_አጋቢጦስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ በጋዛ ሰማዕት ከሆኑ #ከጢሞቴዎስ፣ ከቆጵሮስ ከአገረ #ከሚናስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ኤጲስቆጶስ_ቅዱስ_አጋቢጦስ፦ ይህም አባት በከሀድያን ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ ዘመን ነበር። ወላጆቹም ደጎች ምእመናን ነበሩ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተምረውት ዲቁና ተሾመ። ከዚያም በኋላ እናትና አባቱን ትቶ ወደ አንድ ገዳም ሔደ የሸመገሉ መነኰሳትን አገለገለ። ከእርሳቸውም በጎ አምልኮትን አገለገለ። ከእርሳቸው በጎ አምልኮትን ተማረ አረጋውያኑንም እያገለገለ በገድል ተጠመደ ያለ ማቋረጥም በጾም በጸሎትና በስግደት ይተጋል ከጥዋትም እስከ ምሽት በመጾም የሽንብራ አሠር የሚመገብ ሆነ። ከእንቅልፍም ጋር ሊታገል በወደደ ጊዜ ከሽምብራ አሠር ጋር አመድ እየተመገበ ሰማንያ ቀን ኖረ ከዚህም ተጋድሎ ውስጥ እያለ ኃይሉ ግን ይጨመርለት ነበር። ለአረጋውያንም አገልግሎቱን አላስታጐለም ሲጠራቸው ጌቶቼ ይላቸዋል የጽድቅንና የትሩፋትን ሥራ ሁሉ ፈጸመ።
❤ እግዚአብሔርም የሚያስደንቁ ብዙዎች የሆኑ ታላላቅ ተአምራቶችን በእጆቹ ገለጠ። ከእርሳቸውም አንዲቷን ብላቴና አዳናት እርሷም እንደ ዕንጨት የደረቀች እስከምትሆን ብዙ ዘመን ጭንቅ በሆነ ደዌ ታማ የኖረች ናት። ዳግመኛም ብዙ ሰዎችን ያጠፋውን ታላቅ ከይሲ በጸሎቱ ገደለው። ከሰውና ከእንስሳም፡አስጨናቂ የሆኑ በሽታዎችን አስወገደ። የተጋድሎውና፡የኃይሉ ጽናት ወሬው በተሰማ ጊዜ ስሙ ሉክያኖስ፡የሚባል መኰንን ወደርሱ ልኮ አስመጥቶ ያለ ውዴታው በግድ የጭፍራ አለቃ አድርጎ ሾመው እርሱ ግን ተጋድሎውን አልተወም ጾምንም ጸሎትንም የትሩፋትን ሥራ የሚጨምር ሆነ እንጂ የቀደመ ሥራውን አልተወም በጥቂት ቀኖችም ዲዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስን እግዚአብሔር አጠፋቸው አምላክን የሚወድ ጻድቅ ሰው ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ነገሠ ይህም ቅዱስ ከጭፍራ ውስጥ ይወጣ ዘንድ ምክንያት የሚሻ ሆነ። ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እጅግ የሚወደው መልከ መልካም የሆነ ወጣት ብላቴና ነበር ክፉ ጋጌንም ተጫነበት በቀንም በሌሊትም ታላቅ ሥቃይን የሚያሠቃየው ሆነ ቅዱስ አጋቢጦስንም ከሚያውቁት ውስጥ አንድ ሰው በአየው ጊዜ "የወታደር አለቃ አጋቢጦስ ቢመጣ በአዳነህ ነበር" አለው የታመመውም "እርሱ በንጉሥ ጭፍራ ሥርዓት ውስጥ ያለ፡፡ በውኑ ይህን ሥራ መሥራት ይችላልን" አለ ሰውዬውም ገድሉንና ሥራውን ሁሉ አስረዳው። ጋጌን ያደረበትም "በእውነት ሊያድነኝ ዘንድ የወታደር አለቃ አጋቢጦስን ፈጥናችሁ አምጡልኝ" አለ። ንጉሥም ይህን በአወቀ ጊዜ ቅዱስ አጋቢጦስን እንዲአመጡት አዘዘ በመጣ ጊዜም በወጣቱ ላይ ጸለየ በከበረ መስቀልም አማተበው በዚያንም ጊዜ በእግዚአብሔር ኃይል ዳነ ንጉሡም በዚህ ደስ ብሎት ቅዱስ አጋቢጦስን አከበረው "ምን እንዳደርግልህ ትሻለህ?" አለው እርሱም ንጉሡን "ከወታደርነት ውስጥ አሰናብተኝ" አለውና አሰናበተው አስቀድሞ ወደ ነበረባትም ቦታው ተመለሰ ብዙ ዘመናትም እጅግ እየተጋደለ ኖረ።
❤ ከዚህም በኋላ የዚያች አገር ኤጲስቆጶስ ይዞ ቅስና ሾመው ይህም ኤጲስቆጶስ በሞተ ጊዜ ቅዱስ አጋቢጦስን ይሾምላቸው ዘንድ ሕዝቡ ሊቀ ጳጳሳቱን ለመኑት እርሱም ሾመላቸው መልካም ተናጋሪዎች የሆኑትን የክርስቶስን መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው። እግዚአብሔርም የትንቢትን ጸጋ የተሠወረውንም የማወቅ ድንቆች ተአምራቶችንም የማድረግ ሀብትን ሰጠው። በሥውር ኃጢአትን ሆነ የሚሠሩትን ኃጢአተኞች የሚገሥጻቸው ሆነ በንስሐም እስኪመለሱ ከመቅደስ ያርቃቸዋል።
❤ ዳግመኛም በገድሉ መጽሐፍ ተጽፎ የተገኘ የታላቅ ወንዝ ወራጅ ውኃን በመስቀሉ አቁሞ ወደ ሌላ መንገድ መለሰው የዕውር ዐይኖችንም ገለጠ ለምጻሞችንም አነጻ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳነ። ያማረና መልካም የሆነ ተጋድሎውንና አገልግሎቱን ፈጽሞ በዚህች ዕለት የካቲት24 ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አጋቢጦስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት24 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለማትያስ_ቆጵሮስ_ወሬዘ። #ጢሞቴዎስ_ዓዲ ዘብሔረ ጋዛ። ትኩላን ዕፀው ለማየ ሃይማኖት ኀበ ሙሐዛ። ይደዩ ውስተ አንፍየ እምፍሬሆሙ መዓዛ። ለጺዓተ ጊጋይ ሕሱም ዘያለስሕ ሕምዛ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_24።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወበትእዛዝከ ይቀውም ዕለት። እስመ ኵሎ ቀነይከ። ሶበ አኮ ሕገከ ተመሐርየ ውእቱ"። መዝ 118፥51-52። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 13፥1-11፣ 1ኛ ጴጥ 2፥16-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 19፥11-21። የሚነበበው ወንጌል ማር 1፥23-29። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ወራት። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ አውሳብዮስን ወደ ግብጽ አገር ወስደው በዚያ ይገድሉት ዘንድ ህርማኖስ ንጉሡን መከረው "እርሱ በዚች አገር ከኖረ ያገር ሰዎችን በላይህ ያስነሣብሃልና ያሰብከው ምንም ምን መሥራት አትችልም" አለው። ንጉሡም ቅዱስ አውሳብዮስን ጽኑዕ ሥቃይን ያሠቃዩት ዘንድ ወደ ግብጽ አገር ወደ ቅፍጥ ገዥ ሉልያኖስ ዘንድ እንዲወስዱት ጻፈ ወደ መኰንን ሉልያኖስም በደረሰ ጊዜ በመንኰራኵር ሕዋሳቱን በመቈራረጥ በግርፋት አሠቃዩት። ዳግመኛም በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት ጌታችንም መልአኩን ልኮ ከመከራው ሁሉ አዳነው አጽናንቶም አረጋግቶ ያለ ጉዳት አስነሣው። ነፍሱንም ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ወሰዳት የጻድቃንና የሰማዕታትንም መኖሪያ አየ ለርሱና ለአባቱ ለዘመዶቹም ያዘጋጀላቸውን ቦታዎች አይቶ ነፍሱ እጅግ ደስ አላት። ከዚያም በኋላ ወደ እሳት ማንደጃ ውስጥ ይጨምሩት ዘንድ መኰንኑ አዘዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ወርዶ እሳቱን እንደ ጠል አቀዝቅዞ ያለ ጥፍት የከበረ አውሳብዮስን አወጣው። መኳንንቱም እንዲህ ብለው መከሩት "መኰንን ሆይ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ እዘዝ ከእርሱም ትግል ታርፋለህ" እርሱም የአውሳብዮስን የከበረች ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና የካቲት23 ቀን ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አውሳቢዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የካቲት23 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለከ_ወልደ_ፋሲለደስ_ሊቀ_ሖራ። ወቢጸ ብፁዕ መርቆራ። አውሳብዮስ ሰማዕት ትቤዝወኒ እምከራ። አርኢ ሊተ ለአምላክ መሐሪ ለአባልከ ምታራ። አመ ለነፍስየ ይትነበብ እኩይ ምግባራ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_23።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፳፫ (23) ቀን።
❤ እንኳን #ለሐዋርያውና_ለሰማዕቱ_ለቅዱስ_ፖሊካርፐስ ለዕረፍቱ በዓል፣ ለክቡር #ለቅዱስ_ፋሲለደስ ልጅ ለከበረ #ለቅዱስ_አውሳብዮስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ ከምስራቃዊ #ቅዱስ_ቴዎድሮስ አገልጋይ #ከቅዱስ_አውስግንዮስ ከምስክርነቱ መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሐዋርያውና_ሰማዕቱ_ቅዱስ_ፖሊካርፐስ፦ ይኽም ቅዱስ ሐዋርያና ሰማዕት የሆነው ፖሊካርፐስ ከ70 ዓ.ም እስከ 156 ዓ.ም የነበረ ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእዩ ከመሰከረላቸው ከ7ቱ አብያተ ክርስቲያናት የአንዱ ይኸውም የሰርምኔስ ዻዻስ የነበረ ነው፡፡ ይኽም ቅዱስ ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ቃል በቃል የተማረና ደቀ መዝሙሩ የነበረ ነው፡፡ አቡነ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ የቅዱስ ፖሊካርፐስ ባልንጀራው ነበር፡፡ ቅዱስ ፖሊካርፐስ ከ46 ዓመታት በላይ በፍጹም ትጋት ቤተ ክርስቲያንን አገልግሎ አረማውያን በ86 ዓመቱ በአደባባይ በእሳት አቃጥለው በሰማዕትነት አርፏል፡፡
❤ የቅዱስ ፖሊካርፐስ የሰማዕትነቱ ዜና የተገኘው የራሱ የሆነችው የሰምርኔስ ቤተ ክርስቲያን ሰማዕትነቱን በአካል በተከታተሉ ወንድሞች አማካኝነት ጽፋ ለሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ከበተነችው መልእክት ነው። በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት የሰማዕትነታቸው ሁኔታ፣ ሳይፈሩ ሰውነታቸውን ለሰይፍ ለስለት እንዴት እንደሰጡ፣ ስለ ክርስቶስ ለመመስከር እንዴት ይጨክኑ እንደነበር በሙሉ ዜና ገድላቸው እየተጻፈ በየአብያተ ክርስቲያናቱ ይሰራጭነበር። እንደ አግናጥዮስ ሁሉ በሮም ፖሊካርፐስ ሰማዕት በሆነበት ጊዜም በሰምርኔስ ከተማ የሕዝብ በዓል ተደርጎ ነበር:: እንደልማዳቸው በዓሉ በሚከበርበት በእስታድየማቸው የአራዊት ትርኢት ነበር። አሬኒከስ የተባለ አንድ ክርስቲያንም "የአሕዛብ ጣዖታትን ካላመለክህ ለአራዊት እንሰጥሃለን" ብለውት አሻፈረኝ ብሎ በመፅናቱ በዚያ በአራዊት ተበልቶ ሰማዕት ሆነ። በዚህ ጊዜም ሕዝቡ "ክርስቲያኖች እንዲህ እንዲፀኑ የሚያስተምራቸው ዋነኛው ፖሊካርፐስ ነው እርሱ ተይዞ ይምጣ" እያሉ ጮሁ።
❤ ቅዱስ ፖሊካርፐስ የሞት ፍርድ ሲፈረድበት ፀንቶ በከተማዋ ቢቆይም ምእመናን እንዲሸሽ እያለቀሱ ስለለመኑት ባጠገብ ወዳለች መንደር ሸሸ። በዚያ ሳለ ሰማዕት እንደሚሆን በራእይ ተረድቶ እንደሚሞት ለወንድሞችና እህቶች ነገራቸው። ወዲያው በጥቆማ ተይዞ ወደ ሰምርኔስ ከተማ እያንገላቱ ወስደው ሕዝብ በተሰበሰበበት በበዓሉ አደባባይ አቆሙት። እርሱም ክርስቶስ በሕዝብ አደባባይ ቆሞ የተቀበለውን መከራ እያሰበ የመከራው ተካፋይ ስላደረገው በፍጹም ደስታ መከራውን ይቀበል ነበር። በሕዝቡ ፊት አቁሞ የሚያናዝዘው ሹም ክርስቶስን እንዲክድ ብዙ ማግባቢያዎችንና ማስፈራሪያዎችን ቢያቀርብለትም ያለፍርሃት ፀንቶ ክርስቲያንነቱን ስለመሰከረ በእሳት እንዲቃጠል ተፈረደበት። ወታደሮቹ እሳቱ ውስጥ ከገባ
በኋላ የሚያመልጠን መስሏቸው ለማጠር ሲዘጋጁ አይቶ "ወደ እሳቱ እንድገባ ያበረታኝ ጌታዬ በእሳቱ ውስጥም ፀንቼ እንድቆይ ያስችለኛል" አላቸው።
❤ ወታደሮቹ እጅና እግሩን አስረው ወደ እሳቱ ሲያቀርቡት አይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ እንዲህ በማለት የመጨረሻ ጸሎት አደረገ፦ "አቤቱ ልዑል እግዚአብሔር የተወደደው ልጅህ የኢየሱስ ክርስቶስ አባት ሆይ በልጅህ አንተን እንድናውቅ ሆነናል። የመላእክትና የኀይላት እንዲሁም የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ አንተ ነህ፤ ፍጥረታትም ሁሉ የሚኖሩት ባንተ ነው በመንፈስ። ቅዱስ አጋዥነት ለዘላለማዊ ሕይወት ትንሣኤ ያለፍርሃት ከክርስቶስ መከራ ተካፋይ ከሆኑት ከሰማዕታት ወገን እንድቆጠር ስላደረግኸኝ እና በዚህች ቀንና ሰዓት በሚገባ ስላስተማርኸኝ አመሰግንሃለሁ። እንደ እነርሱ ዛሬ በፊትህ ተቀብያለሁና እንደ መልካምና የተወደደ መሥዋዕት አድርገህ ተቀበልልኝ። አንተ አስቀድመህ እንዳሳየኸኝ እና እንዳዘጋጀኸኝ አንተ እውነተኛና ታማኝ አምላክ ነህና ስለሁሉ ነገር አመሰግንሃለሁ፣ አከብርሃለሁ፣ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ። ከሰማያዊው ዘላለማዊ ሊቀ ካህናት ከተወደደው ልጅህ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሱ ጋር ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክብርና ምስጋና ለአንተ ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን!።"
❤ የጸሎቱ ይዘት ዛሬ ቤተ ክርስቲያናችን ከምታስተምረው ምሥጢረ ሥላሴ ጋር አንድ አይነት ሲሆን ይህንኑም የመሰለ ጸሎት አላት። በዚህም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጥንታዊና ከምንጮቹ ከሐዋርያት የተረከበችው ለመሆኑ ታላቅ ማስረጃ ነው። ቅዱሱ ጸሎቱን ሲጨርስ በእሳቱ ውስጥ ወረወሩት። በቅዱሳኑ ላይ አድሮ ተአምር የሚሠራ እግዚአብሔር ለምእመናን መጽናኛ የሚሆን ድንቅ ተአምርን አደረገ። እሳቱ የቅዱሱን ሰውነት ዙሪያውን እንደግድግዳ ከቦ የማያቃጥለው ሆነ። ሕዝቡም እሳቱ እንዳላቃጠለው ባዩ ጊዜ "በጦር ተወግቶ ይሙት" እያሉ ጮሁ፤ ወታደሮቹም በጦር ወጉትና በዚህ ሰማዕትነቱን ፈጸመ። ክርስቲያኖች እንዳያመልኩት በሚል የከበረ ሥጋውን አቃጠሉ፤ በዚህ ጊዜ ደስ የሚያሰኝ የእጣንና የሽቶ መአዛ ሸተተ። ክርስቲያኖችም ተረፈ አፅሙን በክብር ወሰደው ቀበሩት ቤተ ክርስቲያንም በስሙ ሠሩለት። ከቅዱስ ፖሊካርፐስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከት ያሳትፈን በጸሎቱ ይማረን!።
✝ ✝ ✝
❤ #የቅዱስ_ፋሲለደስ_ልጅ_ቅዱስ_አውሳብዮስ፦ ይህም የከበረ ፋሲለደስ ለአንጾኪያ መንግሥት የሠራዊት አለቃ ነው። ለመንግሥት ልጅችም አባታቸው ነው እርሱም ከፋርስ ሰዎች ጋር ጦርነት ውስጥ እያለ ዲዮቅልጥያኖስ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክርስቶስን ክዶ ጣዖትን እንዳመለከ ሰማ። እጅግ አዝኖ ወደ ልጁ ወደ አውሳብዮስ ልኮ ይህን ነገረው የከበሩ የቤተ መንግሥት ሰዎች ዘመዶቹን ዳግመኛ ጠራቸው እነርሱም የንጉሥ ልጅ ዮስጦስ፣ አባዲር፣ ገላውዴዎስና ቴዎድሮስ ከእርሳቸውም ጋር ያሉትን ጠርቶ ስለ ከሀዲው ንጉሥ ነገራቸው። ሁሉም እጅግ አዘኑ ዳግመኛም እንዲህ አላቸው "እኔ ደሜን አፈሳለሁ" ሁሉም በዚህ በጎ ምክር ተስማምተው እርስ በርሳቸው ተማማሉ። ጠላቶቻቸውንም ድል አድርገው ወደ አገራቸው በተመለሱ ጊዜ ንጉሡ ከሠራዊቱ ጋር ወጥቶ በደስታ ተቀበሏቸው።
❤ ከዚህም በኋላ የቅዱስ ፊቅጦር አባት ህርማኖስ ለቅዱሳኑ ጣዖትን እንዲአቀርብላቸውና እንዲሰግዱለት ንጉሡን መከረው ንጉሡም ህርማኖስ እንደ መከረው አደረገ። በዚያንም ጊዜ ቅዱሳንን ጠርቶ እንዲህ አላቸው "እኔ እጅግ እንደምወዳችሁ እናንተ ታውቃላችሁ አሁንም ለአጵሎን ሰግዳችሁ ልቤን ደስ ታሰኙ ዘንድ ከእናንተ እሻለሁ"። ቅዱሳንም ሰምተው እጅግ ተቆጡ አውሳብዮስም ንጉሡን ሊገድለው ሰይፋን መዘዘ ንጉሡም ሸሽቶ ተሸሸገ ከንጉሥም ባለሟሎች ብዙዎችን ሥራዊቱንም ጭምር ገደለ የከበረ ፋሲለደስም ባይከለክላቸው ከንጉሥ ቤት ምንም ሰው ባልቀራቸው ነበር።
❤ የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ምኒልክ ከአደዋ ጦርነት ከተመለሱ በኋላ በአዲስ አበባ በምትበል ከተማው መካከል በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ቤተክርስቲያን አሠራ። ስሟንም ገነተ ጽጌ ብለው ሰየሟት። ቅዱስ ጊዮርጊስ በጦርነት ቦታ ሁሉ ይረዳው ነበርና። ልመና ክብሩ በኛ ለዘላለሙ በዕውነት ይደረግል። በረከቱ ከእኛ ጋር ትሁን እኛንም በቅዱስ ጊዮርጊስ አማላጅነት ይማረን ለዘለዓለሙ አሜን!!! ምንጭ፦ ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተአምር ዐሥራ ሰባት።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዐይንቲነ። በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ 78፥10-11። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 26፥46-55።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔር። ነገሥተ ምድር ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር። ወዘምሩ ለአምላክነ"። መዝ 67፥31-32 ወይም መዝ 79፥6። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 4፥7-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 9፥23-32። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 17፥1-7። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም ዓድዋ በዓልና የጾም ወራት። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፳፫ (23) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያ°ገበዝ (ጠባቂ) ለአድዋው አርበኛ፣ ለፍጡነ ረድኤት፣ ለገባሬ ተአምር #ሊቀ_ሰማዕታት_ለቅዱስ_ጊዮርጊስ_በ1888ዓ.ም በአድዋ ጦርነት ንጉሠ ነገሥትን ምኒልክና ሠራዊቱ ለረዳበት፤ ኢትዮጵያ በሮማውያንን (ጣልያንን) ድል ለተቀዳጀችበት ለ130 (ለአንድ መቶ ሠላሳኛው) ለዓድዋ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ ልመናው ጸሎቱ በረከቱ አማላጅነቱ በዕውነት በመላው ሕዝበ ክርስቲያን ይደረግልንና #ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ያደረገው_ተአምር_ይህ_ነው፦ በዚያን ወራት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ከአንድ ሺህ ስምንት መቶ ሃምሳ አራት ዓመት በኋላ የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ አጤ ምኒልክ በነገሡ በሃያ ስድስት ዓመት የምኒልክ የጦር አለቃ ገበየሁ ድል ከአደረጋቸው በኋላ እንደገና ምኒልክም ወግተው ኢትዮጵያን በቅኝ አገዛዝ ሊገዙ የሮም ሰዎች መጡ።
❤ ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ አጤ (ዓፄ) ምኒልክ መስከረም፯ ቀን ፲፰፻፹፰ (1888 ዓ.ም ) ላይ "እግዚአብሔር በቸርነቱ እስከ አሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ፡፡ እኔም እስከ አሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ፡፡ እንግዲህ ብሞትም ሞት የሁሉ ነውና ስለ እኔ ሞት አላዝንም፡፡ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም፡፡እንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም፡፡ አሁንም አገር የሚያጠፋ፤ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት፤ እግዚአብሔር የወሰነልንን የባህር በር አልፎ መጥቷልና እኔም የአገሬን ከብት ማለቅ፤ የሰውን መድከም አይቼ እስከ አሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር፡፡ አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም፡፡ የአገሬ ሰው፤ ከአሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም አንተም እስከ አሁን አላስቀየምኸኝም፡፡ ስለዚህ ስንቅህን በአህያ አመልህን በጉያህ ይዘህ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ፡፡ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ፤ ለሚስትህ፤ ለሃይማኖትህ ስትል በኀዘን እርዳኝ፡፡ ወስልተህ የቀረህ ግን በኋላ ትጣላኛለህ አልተውህም፡፡ ማርያምን! በዚህ አማላጅ የለኝም"፡፡ ዘመቻዬም በጥቅምት ነውና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረይሉ ከተህ ላግኝህ" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ ዳግኛም በፈረሶታቸው መጣብር ላይ በጦራቸው አንደበት ላይ የመስቀል ምልክት እንዲያደርጉ ጭፍሮችን አዘዛቸው መስቀል ጠላትን ድል አድራጊ እንደሆነ አስቀድሞ ያውቅ ነበርና።
❤ አዋጁን ካስነገሩ በኋላ ከዚያም ተነሥቶ ወደ ትግራይ ክፍለ አገር ዘመቱና ከትግራይ አውራጃ አንዷ የምትሆን አድዋ የምትባል አገር ደረሱ፡፡ የሣህለ ማርያም (ዳግማዊ ምኒልክ) ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) በንጉሡ ትዕዛዝ ታቦተ ጊዮርጊስን አስይዘው ከሊቀ ጳጳሱ ከአባ ማቴዎስ እንዲሁም ከቀሳውስቱና ከመነኰሳቱ ጭምር ከንጉሡ ጋር ወደ ጦርነቱ ተጓዘች፡፡ በዚያም ጊዜ የአክሱም ጽዮን መነኰሳትና ካህናት የእመቤታችንን ሥዕል ይዘው ወደ ንጉሡ ወደ ምኒልክ መጥተው ከሊቀ ጳጳሱ ከነአቡነ ማቴዎስ ጋር ተቀላቀሉ ከዚያም ሌሊቱን ሙሉ ጸሎት ምሕላ ሲያደርሱ አደሩ።
❤ ቅዳሜ ማታ ለእሑድ አጥቢያ የካቲት ሃያ ሁለት ቀን ነው ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) የጦር ልብሱን ለብሰው ከሠራዊቱ ጋር ወደ ጦር ግንባር ሄደ፡፡ ከዚያም ከሮማውያን የጠላት ጦር ጋር ተገናኝቶ ከሌሊቱ ዐሥራ አንድ ሰዓት ጦርነቱን ጀመረ፡፡ የንጉሡ የሣህለ ማርያም (የምኒልክ) ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) ሌሊት በታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስና በእመቤታችን ሥዕል ፊት በጸሎትና በስግደት እያደረች ሲነጋ ወደጦርነቱ ቦታ በመሄድ እጅግ ለሚያስደንቅ የአነጋገሯ ኃይል ቃል በጦርነቱ መካከል እየተገኘች ለንጉሡ ወታደሮች የሞራልና የብርታት ድጋፍ ትሰጣቸው ነበር። በእውነትም ለተመለከታት ሁሉ እንደ ኃይለኛ ተጋዳይ አርበኛ ትመስል ነበር እንጂ የሴቶች የተፈጥሮ ባሕርይ በእርሷ ላይ አይታይባትም ነበር። የንጉሡም ወታደሮች የንግሥቲቱን የጀግንነት አነጋገር በሰሙ ጊዜ በእሳት ላይ እንደተጣደ የብረት ምጣድ ልባቸው ጋለ ይልቁንም ላም እንዳየ አንበሳና የፍየል መንጋ እንዳየ ነብር እየተወረወሩ በጦርነቱ መካከል በመግባት የጠላትን ጦር በሰይፍ ይጨፈጭፋት ነበር። መጽሐፍ ሹመትን ሽልማትን ያየ አርበኛ ከጦርነት ከሰልፍ ወደኋላ አያፈገፍግም ብሎ ተናግሯልና። በዚያም ጊዜ ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) በጦርነቱ መካከል ሳለ ሊቀ ጳጳሱ አባ ማቴዎስ እንዲሁም የአክሱም መነኰሳትና ሌሎቹ ካህናት በሙሉ ታቦተ ጊዮርጊስንና ሥዕለ ማርያምን ይዘው ከንጉሡ በስተኋላ በደጀንነት ቆመው ጸሎተ ምህላ ያደርሱ ነበር። ንግሥቲቱ ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) በጸሎት ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም ከእነርሱ አትለይም ነበር። የጽዮን አገልጋዮችም በእግዚአብሔር የሕጉ ታቦት ፊት መለከት ይነፉ ነበር።
❤ በዚህም ዕለት ይኸውም የካቲት ሃያ ሦስት ቀን በሮማውያንና በኢትዮጵያውያን መካከል ከፍተኛ ጦርነት ሆነ በዚህም ጊዜ በሰማይ ታላቅ ተአምር ተደረገ። ማለትም የቀስተ ደመና ምልክት ታየ ከዚያም ከቀስተ ደመናው ውስጥ መልኩ አረንጓዴ የመሰለ ጢስ ይወጣ ነበር፡፡ ከዚህም ጢስ ውስጥ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ያለ ድምጽ ተሰማ፡፡ ከዚህም የነጐድጓድ ድምጽ የተነሳ በሮማውያን ወታደሮች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና ሽብር ሆነ ለመዋጋት አልቻሉም፡፡ ይልቁኑ ኃያሉ ገባሬ ተአምር ማር ቅዱስ ጊዮርጊስ በአምባ ላይ ፈረሱ ተቀምጦ ከነፋስ ሩጫ ይልቅ እየተፋጠነ በአየር ላይ በተገለጸ ጊዜ በግንባራቸው ፍግም እያሉ ወደቁ፡፡ "የኢትዮጵያ ህዝብ አምላካቸው ሊረዳቸው መጣ እንግዲህ ማን ያድኅነናል" አሉ ምድርም ጠበበቻቸው በዚህን ጊዜ የኢትዮጵያ ሠራዊት የሮምን የጦር ሠራዊት ፈጁዋቸው የተረፉትንም ማረኳቸው ፈጽመውም እስኪያጠፏቸው ድረስ በሮማውያን ላይ በእግዚአብሔር ሥልጣን የኢትዮጵያውያን እጅ እየበረታ ሄደ፡፡ ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) በእግዚአብሔር ኃይልና በተአምራት አድራጊው በቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳይነት የሮማውያንን የጦር ሠራዊት ድል አድርገው የድል አክሊል ተቀዳጅተው ተመለሱ፡፡
❤ ስለዚህም በዳዊት የምስጋና ቃል የድል ዘውድ ያቀዳጀኝን እግዚአብሔር "ባለ ዘመኔ ሁሉ አመሰግነዋለሁ ለፈጣሪዬ እዘምራለሁ" አለ ሕዝቡም ሁሉ "በክብር ከፍ ከፍ ያለ እግዚአብሔርን በፍጹም ምስጋና እናመስግነውለን የሮማውያንን ኃይል ቀጥቅጦ አጥፍቷልና ሠረገሎቻቸውንም ሠባብሯልና ሠራዊቱንም ሁሉ በምድር ላይ በትኗልና" እያሉ አመሰገኑ። በፈጣሪው በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል በጦርነቱ መካከል የረዳውን ቅዱስ ጊዮርጊስንም በፍጹም ማድነቅ አደነቁ። የሮማም የጦር ሠራዊት በኢትዮጵያውያን ፊት ተዋረዱ ዳግመኛም በኢትዮጵያ ላይ ራሳቸውን ከፍ ከፍ አላደረጉም። በምኒልክም ዘመነ መንግሥት ኢትዮጽያ ከጦርነት ለዓርባ ዓመት ያህል አረፈች።
