🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts
Открыть в Telegram
ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100
Больше2 212
Подписчики
-224 часа
-67 дней
-3430 день
Архив постов
ለዳሩ ተውሂድ የወቅፍ ፕሮጀክት ድጋፍ ማድረጊያ የአካውንት ቁጥሮች ለጠየቃችሁ
Ibnu Mas'oud islamic Center
– ንግድ ባንክ 1000337985328 አጭር ቁጥር 444
– ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል
1365515900001 አጭር ቁጥር 3655159
– ኦሮሚያ ህብረት ስራ 1000087814258 Swift code CBORETAA
– አዋሽ
01410844116300
– አቢሲኒያ
43651528 አጭር ቁጥር i43
– ንብ 7000019119535
– ዳሸን
7943820642111
አላህ ይቀበላችሁ
@abujunaidposts
የነሲሓ ቤተሰቦች ልዮ ኮንፈረንስ 1–5
ነሐሴ 1, 2013 በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል የተካሄደ ፕሮግራም ሲሆን፤
በተለይ ክፍል 4 እና 5 የዳሩተውሂድን ፕሮጀክት ወቅታዊ ሁኔታ ስለሚያብራራ እንድትከታተሉት እጋብዛለው
ባረከላሁ ፊኩም
ክፍል 1/5
https://youtu.be/iEkj0zuxya8
ክፍል 2/5
https://youtu.be/Xv7Csg-_FqA
ክፍል 3/5
https://youtu.be/zZMAdx6xhGY
ክፍል 4/5
https://youtu.be/MUnBXkJVc5k
ክፍል 5/5
https://youtu.be/Druvn0rndOs
@abujunaidposts
🚫 ቁ.2 በኢንተርኔት ከሚሰራጩ ሰሂህ ያልሆኑ ዘገባዎች (አጭር መልዕክት)
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
🔗 Share link
https://t.me/abujunaidposts/241
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
🍂||• በቁርአን እንገሰፅ! •||🍂
🔊 የሱረቱ ዛሪያት ልዩ ቲላዋ 🔉
👉 #ማጅድ_ዛሚል
📖 وَذَكِّرْ فَإِنَّ الذِّكْرَىٰ تَنْفَعُ الْمُؤْمِنِينَ * وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنْسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ * مَا أُرِيدُ مِنْهُمْ مِنْ رِزْقٍ وَمَا أُرِيدُ أَنْ يُطْعِمُونِ * إِنَّ اللَّهَ هُوَ الرَّزَّاقُ ذُو الْقُوَّةِ الْمَتِينُ
[Surat Adh-Dhariyat]
🔚 ከቁርአን ጋር እንኑር!!
http://www.t.me/tenbihat
✍ የምታምንበትን አቋም መተግበርና ማስተላለፍ ቢዳግትህ...
የአፈፃፀም ስልትህን እንጂ አቋምህን አትቀይር!
የዛፎች ቅጠል እንጂ ግንድ እንደማይቀየር ልብ በል!
@abujunaidposts
አሹራ... ታሪክና እርምት 1–4
በአሹራ፣ የቀብር አምልኮና የሁሰይን መገደል ዙርያ በሺዓዎች የሚነሱ ዋና ዋና ብዥታዎችን ለማጥራት ሞክረናል። አላህ በሱና ላይ እስከሞት ከሚፀኑት ያድርገን።
Part 1 https://youtu.be/WmK_NzcVYdg
Part 2
https://youtu.be/xxSgqdIk5tQ
Part 3
https://youtu.be/2hmD6EfzNzQ
Part 4
https://youtu.be/YAmqFXfp8rU
@nesihatv
🔖 የዳዕዋ ኡሱልና አርካን
🎙 አቡጁነይድ እና ጣሀ አህመድ
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/237
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
የሺዓና የአህሉሱና የዓሹራ ውሎ
✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
ሙሀረም 12/ 1436 ዓ.ሒ ተፃፈ
የዓሹራ ቀን፤ የፊዓአውንን ትእቢትና አምባገነነንነት ያከተመበትና ለሌሎችም መቀጣጫ የሆነበት፣ ነብዩላህ ሙሳም የተደሰቱበት ለአህሉሱና ታላቅ ትርጉም ያለው የድል ብስራት ቀን ነው። አህሉሱና ይህንን ቀን በአል አያደርጉትም። የተለየ ድግስም ሆነ አለባበስ የላቸውም። ሆኖም መልእክተኛው ﷺ በደነገጉት መሰረት ይፆሙታል፣ መልካም ተግባራትን ይፈፅሙበታል፣ ከአላህ ልዩ ምንዳን በመከጀልም በዒባዳ ያሳልፉታል።
ሺዓዎች ግን ስለ ዓሹራ ቀን ሲያስቡ ሚታወሳቸው የታላቁ ሰሀቢይ የአሊይ ኢብኑ አቢ ጣሊብ ልጅ ሁሰይን የተገደሉበት ቀን መሆኑ ብቻ ነው። ሺዓዎች በዚህ ቀን ሀዘናቸውን ለመግለፅ እራሳቸውን የሚጎዱ ብዙ ነገሮችን በስፋት ይፈፅማሉ። ጭንቅላትንና ሌሎች አካሎቻቸውን በስለት መብጣትና ማድማት (ተጥቢር)፣ ፊታቸውን መደብደብ (ለጥም፣) እራስን በሰንሰለት መግረፍና ማንገላታት፣ በእንብርክክ መሄድ፣ ብዙዎችም ዘንድ ጥቁር መልበስና የለቅሶ ሙሾ ማውረድ ብሎም በራስ ላይ ኩነኔን መጥራት የተለመዱ የአሹራ ትእይንቶቻቸው ናቸው።
በእጅጉ ይገርማል፤
ለኛ ለአህሉሱና ደስታን ሲያላብሰን፣ ተስፋን አሰንቆ ድልን ሲያበስረን፤ ለወንጀላችን ማርታን ለማግኘት ሩጫ ውስጥ ሲከተን፤
ለሺአዎች ግና፤
የሀዘን የዋይታ፣ የውድቀት የሽንፈት ማስታወሻ፣ የተስፋ ማጨለሚያ ነው!!
ሁሰይን የነብዩ ﷺ የልጅ ልጅ በኢስላማዊ እውቀት ከመጠቁ ታላላቅ ሰሀቦች አንዱ ናቸው። በኢባዳ ብርቱ የተወዳጇ የመልእክተኛው ﷺ ልጅ የፋጢማ ረዲየላሁ አንሀ ልጅ ናቸው። ሆኖም...
ቀሪውን በዚህ ሊንክ ያንብቡ
http://clearfaith.blogspot.com/2015/10/blog-post.html?m=1
------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
🚫 በኢንተርኔት ከሚሰራጩ ሰሂህ ያልሆኑ ዘገባዎች (አጭር መልዕክት) #1
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
🔗 Share link https://t.me/abujunaidposts/233
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
🗞 በእየሱስ ዘመን የኢየሩሳሌም ህዝብ የሚያውቀው አምላክነቱን ሳይሆን ነብይነቱን ብቻ ነበር!
ዘመንን የኃሊት በመቁጠር ከ2000 አመታት ተመልሰን እየሱስን ለካዱት የአይሁድ ፈሪሳውያን ለመሆኑ የእየሱስን አምላክነት ነው የምትክዱት ወይንስ ነብይነቱን? በማለት ጥያቄ ብናቀርብ፤
በእርግጠኝነት በጥያቄው በመገረም አይናቸውን ያቁለጨልጫሉ። ለምን ብትሉኝ፤ እየሱስን አምላክ ነኝ ሲል ሰምተውት አያውቁም!! "እየሱስ አምላክ ነው" የሚል ጥሪም ከማንም ሰው ሰምተው አያውቁም።
የዘመኑ ሰዎች አጀንዳ "ኢየሱስ እውነተኛ ነብይ ነው ወይስ አይደለም?" የሚለው ብቻ ነበር። ይህንን ለመረዳት ዛሬ በክርስቲያኖች እጅ ከሚገኘው አዲስ ኪዳን ሶስት ታሪካዊ ክስተቶችን ማቅረብ በቂ ይሆናል።
1ኛ) በማቲዮስ ወንጌል ምዕራፍ 21 አንቀፅ 10 እና 11 ላይ በወቅቱ በእየሩሳሌም ከተማ የሚኖረው መላው ህዝብ የሚያውቀው የእየሱስን አምላክነት ሳይሆን ነብይነቱን እንደነበረ በግልፅ ያሳያል። «ወደ ኢየሩሳሌምም በገባ ጊዜ መላው ከተማ ይህ ማን ነው? ብሎ ተናወጠ። ሕዝቡም፤ ይህ ከገሊላ ናዝሬት የመጣ ነቢዩ ኢየሱስ ነው አሉ» ማቲዮስ 21:10&11
የእየሱስን አምላክነት የሚሰብከው ጥሪ፤ በእየሱስ ዘመን የእየሩሳሌም ከተማ ሰዎች ዘንድ ፍፁም የማይታወቅ መሆኑ በእጅጉ ግልፅ ነው!
2ኛ) እንደዚሁ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 6 እንደተጠቀሰው ኢየሱስ ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ በተሻገረ ግዜ በጥቂት ምግብ ብዙ ሰዎች መመገብ እንዲችሉ በጌታ ፈቃድ የፈፀመውን ተዓምር ያዩ ሰዎች የመሰከሩት ነብይነቱን እንጂ አምላክነቱን አልነበረም። «ከዚህ የተነሣ ሰዎቹ ኢየሱስ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ፤ "ይህ በእውነት ወደ ዓለም የሚመጣው ነቢይ ነው አሉ"» ዩሀንስ 6:14
ተዓምርን ሁሉ የአምላክነት መገለጫ አድርገው እንደሚያቀርቡ የዚህ ዘመን ሰዎች እንደሚሉት፤ "እየሱስ አምላክ ነው" አላሉም። ነገር ግን እውነተኛ ነብይነቱን ተረድተው መስክረዋል።
3ኛ) በሉቃስ ወንጌል ምእራፍ 7 ላይ እንደሰፈረው እየሱስ በገሊላ ምድር እየተዘዋወረ ይሰብክ በነበረበት ጊዜ በፈሪሳዊው ስምዖን ግብዣ እቤቱ በታደመ ግዜ ኃጢአተኛ የነበረችው ሴት አልቅሳ እግሩ ላይ በተደፋች ግዜ ፈሪሳዊው ስምዖን አይቶ:- «ይህስ ነቢይ ቢሆን፣ ይህች የምትዳስሰው ሴት ማን እንደ ሆነች እንዴትስ እንደ ነበረች ባወቀ ነበር፣ ኃጢአተኛ ናትና ብሎ በልቡ አሰበ» ሉቃስ 7:39
ይህ ፈሪሳዊ ያሰበውና ያሰላሰለው፤ ‘የእየሱስን እውነተኛ ነብይ መሆን ወይም አለመሆን’ እንጂ ስለ አምላክነቱ አልነበረም። ለምን ቢባል፤ እየሱስ አምላክ ነው የሚል እምነት ህይወቱን ሙሉ አልሰማም፤ በልቡም ፍፁም አላደረም።
አንዳንድ የመፅሀፍ ቅዱስ ማብራሪያዎች ላይ ይህ ፈሪሳዊ "ይህስ ነብይ ቢሆን..." ያለበትን ምክንያት ስንቃኝ ‘በዚያን ዘመን ሲነገር የነበረው የእየሱስ ነብይነት ብቻ ስለነበር ነው’ በማለት ያስረዳሉ።
አዎን! በዘመኑ እየሱስን የካዱት ሰዎች እውነተኛ ነብይነቱን አስተባብለዋል!! በዚያ ዘመን ያመኑበትም ሰዎች እውነተኛ ነብይነቱን ተቀብለዋል።
👌 ይህንን እውነታ መረዳት የእየሱስን አምላክነት ለሚያምን ሰው ከባድ ፈተና ነው። እየሱስ ያላስተማረውን እንግዳ እምነት መሰረታዊ አስተምህሮ አድርጎ ማቅረቡ ጥያቄ ውስጥ ይጥለዋል።
እኛ ሙስሊሞች ለእየሱስ ታላቅ ክብር አለን። በአምላክ ፈቃድ ብዙ ተዓምራትን ያደረገ ታላቅ የጌታ መልዕክተኛ ነብይ እንጂ አምላክ አለመሆኑን እናምናለን። ይህም የእየሱስ አስተምህሮ መሆኑ አያጠራጥርም።
የቁርአን አስተምህሮ እየሱስ ለእስራኤል ልጆች ያቀረበው ጥሪ ነብይ ነኝ የሚል እንጂ አምላክ ነኝ የሚል እንዳልነበር ያሳያል። አላህ ለህዝቦቹ ያደረገውን ጥሪ አስመልክቶ እንዲህ ይላል፤ «አላህ ጌታዬና ጌታችሁ ነው፤ ስለዚህ አምልኩት፤ ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» (አላቸው)፡፡ [አል ዒምራን 51]
በሌላ አንቀፅ እየሱስ አምላክ ነው የሚለው አዲስ አስተምህሮ ክህደት መሆኑን ያስተምረናል። [እነዚያ «አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ አልመሲህም አለ፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን አምልኩ» እነሆ! በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም!] አልማዒዳህ 72
በመጨረሻም የእየሱስን ነብይነት ላስተባበሉት አይሁዶችም ይሁን ኃላ አምላክ ነው ላሉ ክርስቲያኖች የተላለፈውን ግልፅ ጥሪ በማስነበብ አቋጫለው። «እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፡፡ በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ፡፡ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ዒሳ የአላህ መልክተኛ ወደ መርየም የጣላት «የኹን» ቃሉ፤ ከእርሱ የኾነ መንፈስም ብቻ ነው፡፡ በአላህና በመልክተኞቹም እመኑ፡፡ «ሦስት ናቸው» አትበሉም፡፡ ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና ተከልከሉ! አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱ ልጅ ያለው ከመኾን የጠራ ነው፡፡ በሰማያትና በምድር ያለ ሁሉ የርሱ ነው፡፡ መመኪያም በአላህ በቃ!» አን’ኒሳእ 117
ስህተትን ለማረም ጊዜው አልረፈደምና ልብ ያለው ልብ ይበል!
ሀቅን በተከተለ ሁሉ ላይ የአላህ ሰላም ይስፈን!
---------------
✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
ግንቦት 16/ 2007 ዓ.ል
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
የነሲሓ ቤተሰቦች ልዩ ኮንፈረንስ
በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ★★★★★
ነሐሴ 1/ 2013 ከቀኑ 6:30 ጀምሮ
✔ የነሲሓ ታሪካዊ ሒደቶች
✔ ቤተሰባዊ ምክክሮች
✔ የእውቅና ፕሮግራሞች
✔ ልዩ የምሳ ብፌ ዝግጅት
✔ የዳሩተውሒድ ሪፖርትና ብስራት
✔ ቃለ መጠይቆች እና አዝናኝ ፕሮግራሞች
የመግቢያ ዋጋ
– ለአንድ ሰው 3000 ብር
– ለባልና ሚስት 5,000 ብር
ገቢው ሙሉ በሙሉ ለነሲሓ ቲቪ ይውላል
ትኬቱን ለማግኘት
በተከታዩ ሊንክ ቀድመው ይመዝገቡ
http://nesiha.tv/confe
ወይም ይደውሉ
+251972757575
@nesihatv
ውድ የኢስላም ወንድም እህቶቼ፤ እንኳን ለኢድ አልአድሓ በአል በሰላም አደረሳችሁ
መጪው ዘመን ለሁላችንም የኢማን የእድገትና የስኬት እንዲሆንልን አላህን እንለምነዋለሁ።
አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال وأعاده الله علينا ونحن في عز وكرامة وسعادة
أخوكم في الله
أبو جنيد صالح أحمد
T.me/abujunaidposts
በ7122 የ SMS አገልግሎት በነፃ ቢመዘገቡ፤ የስኬት ጉዞዎን ጀምረዋል!
🖌 ማንነትዎን በማሳደግ ለመለወጥ
🖌 ስኬታማ ቤተሰብ ለመገንባት
🖌 ልጆችዎን በብቃት ለማነፅ
🖌 ማህበራዊ ግንኙነትዎን ለማሻሻል
እጅግ ጠቃሚ ጥቆማዎችን ያገኛሉ።
✊ ለመመዝገብ ይህንን ይጫኑ!
www.nesiha.tv/7122
በ 1 ብር ብቻ የ SMS ወጪ ለስኬታማ ህይወት አስፈላጊ በሆኑ ዕለታዊ መልእክቶቻች ተጠቃሚ ይሁኑ።
✊ ለመመዝገብ ይህንን ይጫኑ
www.nesiha.tv/7122
ስለ ዓረፋ ቀን ዱዓእ ሁለት ነጥቦች
[1] በኢድ ዋዜማው የዓረፋ እለት ዱዓእ ተቀባይነት እንዳለው የሚዘክሩ ሀዲሶች ሀጅ ላይ የሌሉ ሰዎችንም ይመለከታሉን??
የአላህ መልእክተኛ «ከዱዓዎች ሁሉ በላጩ (የኢድ ዋዜማ) የአረፋ ቀን ዱዓ ነው...» ማለታቸውን ቲርሚዚይ ከአብዱላህ ኢብኑ ኡመር የዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች ተመሳይ ይዘት ያላቸው ሀዲሶችም ይገኛሉ።
ታዲያ የዓረፋን እለት በዱአዕና በዚክር ያሳለፈ ሰው ታላቅ ክብርና ምንዳን የሚያገኘው ሀጅ ላይ ሲሆን ብቻ ነውን? በእርግጥ በዚህ እለት ክብር ባለው የዓረፋ ምድር የተገኘ ሰው የጊዜንም የቦታንም ክብር ተጎናፅፏልና በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘቱ እንዲሁም ዱአው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ መሆኑ አያጠራጥርም። ይሁንና ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት፤ እነዚህ ከአረፋ እለት ክብር ጋር ተያይዞ የዱአ ተቀባይነትን የተመለከቱ ሀዲሶች በማንኛውም ቦታ የሚገኙ ሙስሊሞችን ይመለከታሉ። በመሆኑም በሀጅ ስራ ላይ የሌሉ ሰዎችም በዱዓ ሊበረቱ ይገባል።
ታላቁ አሊም ሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን በዚህ እለት የሚባሉ በሀዲስ የተላለፉ ዱአዎችን አስመልክቶ ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች መሆኑን ተጠይቀው ተከተዩን መልሰዋል¹ «በምላሻችን እንደገለፅነው፤ ይህ ለሁጃጆችንም ይሁን ሌሎችን የተመለከተ ጥቅል መልእክት ነው። ነገር ግን ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች ይበልጥ የተገባ ነው። ምክኒያቱም ሁጃጆች በዚህ እለት በዓረፋ ምድር በኢህራም ውስጥ ስለሚገኙ ከሌሎች በበለጠ ዱዓቸው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ ነው። ስለዚህም የዓረፋን እለት በሀጅ ተግባር ላይ የሌሉ ሰዎች እንዲፆሙት ተደንግጓል። እለቱ ብልጫ ያለወወ ስለሆነም አላህን በማስታወስ፣ ማርታን በመለመን እና ዱዓ በማድረግ ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ፤ ሁጃጆችንም በኢባዳ ይካፈሏቸዋል ማለት ነው።» ከሸይኹ ድረገፅ የተወሰደ የድምፅ ፈትዋ
[2] በዓረፋ እለት ሁጃጆች በአረፋ ምድር እንደሚሰባሰቡት ለዱዓና ለዚክር መሰባሰብ "ታዕሪፍ"ን በተመለከተ፤
ይህ ተግባር አንዳንድ ሰለፎች እንደፈፀሙት የተረጋገጠ ነው። ከነሱም መካከል ኢብኑ አባስ ይገኙበታል፤ ኢማሙ አህመድም ባይተገብሩትም እንደሚቻል ተናግረዋል።
ነገር ግን ያወገዙትና ከቢድአ የመደቡትም አሉ። የኡለማዎቻችንን ማብራሪያዎች ስንፈትሽ ተከታዮቹ ድምዳሜዎች ላይ ያደርሱናል፤
1) "ታእሪፍ"ን መተግበር በራሱ ችግር የለውም። ተግባሩን እንደሱና ወይም ሙስተሀብ ነገር መውሰድ ግን አይገባም። ጉዳዩ የኢጅቲሀድ መስአላ ነውና ተግባሩ የሚወገዝ ተግባር አይሆንም። የፈፀመውም ሰው ቢድአ ሰራ አይባልም።
2) ታእሪፍ ስንል ከምድረ አረፋ ውጭ ባሉ የየሀገሩና የየከማው መስጂዶች መሰባሰብን የተመለከተ እነጂ ለዚህ ብሎ ጉዞ ማድረግ አይፈቀድም። አላህ የአረፋን ምድር ለዚህ ቀን ኢባዳ መሰባሰቢያ እንደመረጠው በየሀገሩ አንዳንድ ቦታዎችን፣ መስጅዶችንና ቀብሮችን በመምረጥ ወደነሱ ጉዞ አድርጎ መሰባሰብ በፍፁም አይፈቀድም። ይህ የነብዩ መስጂድንም ይሁን በይተልመቅዲስን ያካትታል።
3) ይህ መሰባሰብ ጩኸትና ሱና ያልሆኑ የጋራ አምልኮዎች ከታከሉበት ቢድአ እንደሚሆን አያጠራጥርም። በተመሳሳይ መልኩ ኢባዳ ያልሆኑ ግጥሞችና መንዙማዎችን ለዚህ መለያ ማድረግ ጥፋት ነው።
እነዚህን ነጥቦች በዝርዝር ለመረዳት የሚያስችሉ ማብራሪያዎችን ከኡለማዎች ድርሳናት እንደሚከተለው እናያለን።
ቀሪዉን የፅሁፍ ክፍል ተከታዩን ሊንክ በመከተል ያንብቡት
https://www.facebook.com/682494683/posts/10158937378539684/
t.me/abujunaidposts
@abujunaidposts
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
