የአማራ ወጣቶች ማህበር በደጋ ዳሞት <> Amhara Youth Association in Dega Damot
Открыть в Telegram
1 200
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 день
Загрузка данных...
Похожие каналы
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
декабрь '24
декабрь '24
+7
в 0 каналах
ноябрь '24
+25
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '24
+33
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+8
в 0 каналах
Get PRO
август '240
в 0 каналах
Get PRO
июль '240
в 0 каналах
Get PRO
июнь '240
в 0 каналах
Get PRO
май '240
в 0 каналах
Get PRO
апрель '240
в 0 каналах
Get PRO
март '240
в 0 каналах
Get PRO
февраль '240
в 0 каналах
Get PRO
январь '240
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '230
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+1
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '23
+1 245
в 0 каналах
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 09 декабря | 0 | |||
| 08 декабря | +2 | |||
| 07 декабря | 0 | |||
| 06 декабря | +2 | |||
| 05 декабря | 0 | |||
| 04 декабря | +1 | |||
| 03 декабря | +1 | |||
| 02 декабря | 0 | |||
| 01 декабря | +1 |
Посты канала
| 2 | የአማራን ሕዝብ የህልውና ትግል የሚያቀናጅ ኮማንድ ፖስት ተቋቋመ!
ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም. (August 6, 2023)
ከአማራ ሕዝባዊ ግንባር የተሠጠ አስቸኳይ መግለጫ
የአማራ ሕዝብ ላለፉት ረጅም ዓመታት እንደ ሕዝብ ሲደርስበት የነበረውን መስፈሪያ-የለሽ መከራ፣ አገርና ሕዝብን ለማቆየት ሲል ስቃዩን ችሎ ሰላማዊ የለውጥ ሁኔታ ይፈጠራል በሚል ሲታገስ ቆይቷል። ትዕግሥቱን ፍርሃት፣ ዝምታውን የተሸናፊነት፣ መንግሥት ማክበሩን እንደ አላዋቂነት ተወስዶ በመከራ ላይ መከራ ሲደራረብበት ቆይቷል። ይህ ሁሉ የአማራው ታጋሽነት የአገርን ሕልውና ከአደጋ ለመጠበቅ፣ የንጹሃን እልቂትን ለማስቀረትና በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ መፍትሄ ይገኛል ከሚል ፍጹም ስልጡንነት ነበር። ሆኖም የአብይ አህመድ የኦሮሙማ የፓለቲካ አይድዮሎጂን ተከትሎ፣ የአማራውን ሕህዝብ፣ ከክርስትናና ከሙስሊም እምነት ተከታዮች ጋራ አጥፍቶ፣ በምስራቅ አፍሪካ የኩሽ ግዛት ለመፍጠር የጀመረው የፋሺዝም የዘር ማፅዳትና የመስፋፋት ፓሊሲ ከኢትዮጵያም አልፎ በመላው አፍሪካ ቀንድ አገሮች ላይ ታላቅ የፀጥታ ችግር ፈጥሮ፣ ቀጠናውን የኃያላን ጦር አውድማ ሳያደርገው ኢንተርናሽናል ኮሚኒቲው አስፈላጊውን ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።
ይህ የጉግማንጉግ ሰው-በላ የአራዊት አገዛዝ ለሠላም የተዘረጋውን የሕዝባችንን እጅ ለመቁረጥ ምሳሩን መዞ እልቂትን አውጇል። ዐማራው ህልውናውን ለመከላከል ያለው ብቸኛ አማራጭ ኃይል ብቻ በመሆኑ ሳይወድ በግድ በጠላቶቹ ጋባዥነት ወደ ለየለት ጦርነት ውስጥ ገብቷል። የአማራ ሕዝብ በአሁኑ ወቅት የአብይ አህመድ የኦሮሙማ-ኦህዴድ-ኦነግ አገዛዝን ወረራ ለመመከት በበርካታ ግንባሮች እየተፋለመ ይገኛል። ሕዝባችን እየተፈጸመበት ያለውን መረን-የለሽ ጭፍጨፉ፣ አፈናና ግድያ ዝም ብሎ ከመመልከት ወደ ሁለገብ የተከላካይነት ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተጋድሎው ግለትና የጦር ግንባሩ ስፋት አማራው የሚያደርገውን ትግል በበለጠ ውጤታማና አሸናፊ እንዲሆን የተቀናጀ አመራር የሚሰጥ አካል ማዋቀር አስፈልጓል።
ይህንንም የሚያቀናጅ ኮማንድ ፖስት ተቋቁሟል።
የአማራው የተለያዩ ክፍላተ አገሮች፣ በሥራቸው የፋኖ ብርጌዶች ያሏቸው ኮማንድ ፖስቶች ሲኖሯቸው፣ እነዚህንም በበላይነት የሚያስተባብረው ጀግናው አርበኛ ሉቴናንት ኮረኔል ፉንታሁን ሙሃባ ነው።
የኮማንድ ፖስቱ ዓላማዎች፡-
* ክልሉን ሙሉ በሙሉ ከጠላት ለማፅዳት የተባበረና የተቀነባበረ ትግል እንዲካሄድ ማድረግ፤
* ነፃ የወጡ ከተሞችን ጥበቃ እንዲኖራቸውና ሕዝባዊ አስተዳደር በማዋቀር የአገልግሎት ተቋማት ስራቸውን እንዲቀጥሉ ማድረግ፤
* ትግሉን ለመቀላቀል የሚፈልጉ ኃይሎችን ማሰልጠን፣ ማስታጠቅና ለትግል ማሰማራት፤
* የሎጅስቲክስ አቅርቦትን ለማሳለጥና፣ ጉዳት የደረሰባቸውን በመንከባከብ እርዳታ እንዲያገኙ ማመቻቸት፤
* የጠላት ምርኮኞችንም ዓለም ዓቀፍ ህግ በሚፈቅደው መሠረት መጠብቅ፣ ተጸጽትውና ይቅርታ ጠይቀው ከወገን ጦር እንዲቀላቀሉ መሞከር፣ ወይም ወደፊት ለፍርድ እንዲቀርቡ ማድረግ።
ይህንንም ሕዝባዊ ዓላማ ለማሳካት የተቋቋሙት ኮማንድ ፖስቶችና ብርጌዶች የሚከተሉት ናቸው፡
ኮረኔል ፉንታሁን ሙሃባ አጠቃላይ የኮማንድ ፖስቶቹ የበላይ አስተባባሪ ከመሆኑም በተጨማሪ የወሎን ብርጌዶች ኮማንድ ፖስት ይመራል፡፡ ብርጌዶቹ:-
* አንደኛ ብርጌድ
* ሁለተኛ ብርጌድ
* አሳምነው ብርጌድ-ላሊበላ
እንዲሁም ይህ ኮማንድ ፖስት ከምስራቅ አማራ ፋኖ ዋና አዛዥ አርበኛ ምሬ ወዳጆ ጋር በመመካከር ተናቦ እንዲታገል ተዋቅሯል፤
በጎንደር ያሉ ብርጌዶች ኮማንድ ፖስት በጊዜያዊነት በሻለቃ አንተነህ ይመራል፡፡ ብርጌዶቹ፦
* ምኒልክ ብርጌድ
* ቆስቁስ ብርጌድ
* ደቡብ በጌምድር ብርጌድ
* ቋረኛው ብርጌድ
የሽዋ ኮማንድ ፖስትን የሚመራው በሻለቃ መከታው ሲሆን በእዙ ሥር አራት ብርጌዶች ይኖራሉ፡፡
የጎጃም ኮማንድ ፖስት፦
* ብርጌዶቹ
* የበረኸኛ ብርጌድ
ኮማንድ ፖስቶቹ የዓማራ ሕዝባዊ ኃይሎች ባሉበት ቦታ ሁሉ ተናበውና ተባብረው ይሠራሉ። ሌሎችም ብርጌዶች በሂደት ወደፊት ይካተቱበታል። እንዲሁም በውይይት ላይ ያሉ በተለያየ የፋኖ አደረጃጀት የተዋቀሩ የቁርጥ ቀን ልጆች በሚያደርጉት ትግል፣ ሁሉም ተቀናጅቶ በአንድ ሠፊ ግንባር እንዲዋቀሩ መሬት የረገጠ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
ለጊዜው ከተፈጠረው አጣዳፊ ሁኔታ አኳያ ከላይ የተዘረዘሩት የፋኖ ብርጌዶች በአንድ ዕዝ ሥር ተናበውና ተደጋግፈው ለመታገል የጋራ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ለሕዝብ ስናሳውቅ በታላቅ ኩራት ነው። በዚህ ኮማንድ ፖስት የተካተቱትንም ሆነ በየአካባቢው ከጠላት ጋር የሚፋለሙትን ሁሉ፣ ወገናችን በሚችለውና ባለው አቅሙ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው አደራ እንላለን።
በመጨረሻም በአገር መከላከያ ሥር ተሰልፈህ አገር ለመጠበቅ አደራ የተቀበልክ ሠራዊት፣ ጦርነቱ በሕዝብና በጥቂት አንባገነንና ጨፍጫፊ የብልጽግና ፋሽስታዊና ዘረኛ መሪዎች መካከል መሆኑን አውቀህ ከሕዝባዊ ፋኖዎች ጋራ እንድትቀላቀል፣ ወይም በብልጽግና መሪዎች ላይ አፈሙዝህን እንድታዞር ታሪካዊ ጥሪ ቀርቦልሃል።
በዚህ ጦርነት ግፉና መስዋዕትነቱ የከፋ ቢሆንም፣ የአብይ አህመድ ፋሺስታዊው የኦሮሙማ ሰው-በላ አገዛዝ ፈጽሞ አገር የመምራት እድል ከእንግዲህ ወዲያ አይኖረውም። ከግብረ-አበሮቹም ጋራ ለፍርድ የሚቅርብበት ጊዜ ሩቅ አደለም። ስለሆነም በተለያየ የመንግሥት ሃላፊነት ላይ ያላችሁ ባለስልጣናት፣ በውጭ የዲፕሎማሲ ስራ የተሰማራችሁ፣ አገዛዙን በተለያየ መንገድ የምታገለግሉ፣ ከዚህ ሕዝብ ጨፍጫፊ ሥርዐት እራሳችሁን በጊዜ እንድታገሉ ሞራላዊና ሕሊናዊ ግዴታ አለባችሁ። ለለውጥ የተነሳው ሕዝብ እየደረሰበት ያለውን መከራ ችላ ብላችሁ ከአራጁ አገዛዝ ጋር ከቀጠላችሁ ሕዝባችን በእናንተ ላይ ሊያደርሰው የሚችለውን የበቀል እርምጃ ማስቆም የሚችል ኃይል አይኖርም።
ለሃያ ሰባት ዓመታት የሕወሃት/ኢህአዴግን፣ እንደዚሁም ላለፉት አምስት ዓመታት የኦህዴድ ኦነግ/ብልጽግናን የግፍ ጽዋ የቀመሳችሁ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሆይ! የአማራ ሕዝብ ለህልውናው ብሎም ኢትዮጵያ እንደአገር እንድትቀጥል ለሚከፍለው ከፍተኛ መስዋእትነት የድርሻችሁን እንድትወጡ ወገናዊ ጥሪ ቀርቦላችኋል።
የአማራ ሕዝብ በልጆቹ መስዋዕትነት ያሸንፋል!
መነሻችን የአማራ ሕልውና፣
መዳረሻችን የኢትዮጵያ አንድነት!
የአማራ ሕዝባዊ ግንባር! | 0 |
| 3 | Нет текста... | 0 |
| 4 | Нет текста... | 0 |
| 5 | የአማራ ህዝብ ትግል ከፍ ወዳለ ደረጃ መሸጋገርን አስመልከቶ ከአማራ ህዝባዊ ግንባር የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ‼️
ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
አሻራ ሚዲያ ፣
የአማራ ህዝብ በደምና አጥንቱ ባፀናት አገሩ ላለፉት 50 ዓመታት ስርዓት ወለድ በሆነ ችግር በማንነቱ ሲጨፈጨፍ፣ሲፈናቀል፣ሲሰደድና በሴራ ከአገሪቱ ፖለቲካ እንዲገለል በማደረገ ከምጣኔ ሀብታዊና ማህበራዊ ጥቅሞች ውጭ ሆኖ ቆይቷል።ይባስ ብሎ ላለፉት አመታት በለውጥ ስም የኢትዮጵያን መንበረ ዙፋን የተቆጣጠረውና በጥላቻ ያደገው የዘረኛው ህዎሓት የብኩር ልጅ ኦህዴድ/ኦነግ በስልጠና፣በትጥቅና በስንቅ ባደራጃቸው ገዳይ ኃይሎቹ አማራውን ያለርህራሄ በጥይትና በገጀራ በመጨፍጨፍ የዘር ማጥፋት ፈፅመዋል።ሀብት ንብረቱን ዘርፈውና አውድመው ከሚኖርበት አካባቢ በማፈናቀል የዘር ማፅዳት ፈፅመዋል፤ቅድመ አያቶቹ ባቀኗት ከተማ አዲስ አበባ እንዳይገባ ከልክለዋል፣በኢትዮጵያ ሰማይ ስር ተዘዋውሮ እንዳይሰራ መንገድ ላይ እያገቱ ዘርፈዋል፣ገድለዋል።
አሁን አሁን ደግሞ ከመዝረፉና መግደሉ ባሻገር ህፃናትን ሁሉ ሳይቀር እያገቱ "ማስለቀቂያ" በሚል ዘዴ ከድሃ የአማራ እናቶች መቀነት በሚሊዬንስ ገንዘብ ይቀበላሉ፤የአማራ ባለሃብቶች የባንክ አካውንቶችን አግደዋል።አርሶ አደሩ በጉልበቱ ዘርቶ እንዳይቅም በተጠና መንገድ የአፈር ማዳበሪያ በመከልከል ማሳው ጦም እንዲያድር አድርገዋል።
ይህ ሀሉ አልበቃ ያለው ፈሽስቱ የኦህዴድ/ኦነግ ስርዓት ላለፋት አራት ወራት "ህግ ማስከበር" በሚል ሽፋን በአማራ ክፍለሀገር በመከላከያ ስም የተደራጀ የአንድ ዘር ታጣቂ ሰራዊት በማዝመት የዕምነት ተቋማትን አውድሟል፣ሴቶችን ደፍሯል፣ንፁሃንን ገድሏል፣አሁንም ስፍር ቁጥር የሌለው ሰራዊት ወደ አካባቢው እያስገባ ይገኛል።
የዚህ ሁሉ በደል ባለቤት የሆነው የአማራ ህዝብ የጀመረውን የህልውና ትግል ከፍ ወዳለ ደረጃ በማደረስ ከሐምሌ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ ከተሞችን ከፋሽስቱ ኦህዴድ/ኦነግ ብልፅግና መዋቅር በክንዱ ነፃ እያዎጣ ከተሞችን እየተቆጣጠረ ይገኛል።
በተለይም በጎጃም፣በጎንደር፣በወሎና በሸዋ አብዛኛውን ከተሞች ፋኖ ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት የአሽከሩን ብአዴን ብልፅግና መዋቅር በመበጣጠስ በአስገራሚ ፍጥነት እና ብቃት እየተቆጣጠራቸው ይገኛል።
በመሆኑም የአማራ ህዝባዊ ግንባር የሚከተለውን ጥሪ ያስተላልፋል:-
1ኛ) የአማራ ህዝብ በጀግኖች ልጆቹ የጀመረውን የገዥውን ስርዓት መዋቅር እየበጣጠሰ ከተሞችን የመቆጣጠር ጎዞውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፤
2ኛ) የአማራ ህዝብ የጀመረውን በክንዱ ነፃ የመውጣት ጉዞ ለማደናቀፍ በኩሊው ብአዴን በኩል ሐምሌ 27/2015 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ ክልሉ ከቁጥጥራቸው ስር እንደወጣ በይፋ በመግለፅ ተጨማሪ የስርዓቱ ገዳይ ኃይል እንዲገባና ንፁሃንን እንዲጨፈጭፍ ፈቅደዋል።ክልሉም በወታደራዊ አገዛዝ ስር እንዲዎድቅ አዝዘዋል።ስለሆነም:- በአማራ ክልልም ይሁን ከክልሉ ውጭ የሚገኝ ማንኛውም ታጣቂ ፋኖ፣የአማራ ልዮ ኃይል፣የአማራ ፖሊስ፣አድማ ብተና፣ምልስ የሰራዊቱ አባላት፣የሚሊሻ አባላትና ሌሎችም በሙሉ ከዛሬ ጀምሮ በክልሉ ያለው የስርዓቱ መዋቅር መፍረሱን በመረዳት ከአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ጎን እንድትሰለፉና ታሪካዊ ኃላፊነታችሁን ትዎጡ ዘንድ ግንባሩ ጥብቅ ጥሪ ያደርጋል።
3ኛ) የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሙሉ የኦህዴድ/ኦነግ ፋሽስቱ ስርዓት ለግል ጥቅሙና ስልጣኑ ሲል ትናንት በእር በርስ ጦርነት በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ጓዶቻችሁን አስጨፍጭፏል፤የተጨፈጨፉ ጓዶቻቸሁ አስክሬን በወግ ተሰብስቦ ለአፈር ሳይበቃ ከገዳዮቻችሁ ጋር "በሰላም ስምምነት ስም" ክህደት ፍፅሞባችኋል።ዛሬ ደግሞ ይባስ ብሎ በክፉ ቀን ያበላ፣ ያጠጣችሁንና የሸሸጋችሁትን ህዝብ እንድትዎጉ ተገዳችኋል።ትዕዛዙን ባለመቀበል እየከዳችሁ ከአማራ ኃይሎች ጎን እንድትሰለፉ ጥሪ እናቀርባለን።
4ኛ) በአገዛዙ ስቃይና መከራ ውስጥ የምትገኝው ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ከአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ጎን እንድትቆም ጥሪ ቀርቧል።
5ኛ) በስተመጨረሻም የአማራና የኢትዮጵያ ህዝብ ዘብ የሆንከው ጀግናው የአማራ ፋኖ ከህዝብህ ጋር የጀመርከውን የነፃነት ጉዞ አጠናክረህ እንድትቀጥል ጥሪ እያቀረብን የአማራ ህዝባዊ ግንባር በቀጣይ ሁለት ቀናት ውስጥ ላልተወሰነ ጊዜ የማቆይ ኮማንድ ፖስት የሚያቋቁም መሆኑን ይገልፅል።
ኮማንድ ፖስቱ በመላው የአማራ ከተሞች የሚተገበር ሆኖ የአማራን የህልውና የነፃነት ትግሉን ማቀጣጠልና ነፃ የወጡትን የአማራ የቀበሌ፣የወረዳ፣የዞን አውራጃዎችንና ከተሞችን በሚቋቋመው ኮማንድ ፖስት በተመደቡ የአማራ የትግል አካላት እንዲተዳደሩና ህዝቡም አካባቢውን እንዲጠብቅ ደንብ ተዘጋጅቷል።በተጨማሪም ስለንብረትና እስረኛ አጠባበቅን በተመለከተ በኮማንድ ፖስቱ ተካቶ ደንቡ ይፋ ይሆናል።
ድል ለአማራ ህዝብ
ሐምሌ/28/2015 ዓ.ም
የአማራ ህዝባዊ ግንባር | 0 |
| 6 | Нет текста... | 0 |
| 7 | ለታሪክ ፃህፍት የተተወ ታሪካዊ ጀብድ።
የአማራ ህዝባዊ ኃይል (ፋኖ) ደጋ ዳሞት ብርጌድ በሶስቱ አቅጣጫ የገቡትን የአገዛዙን ሃይል አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ ለወሪ ነገሪ የሚሆን አንድም ሃይል እንዳይቀራቸው አድርገው ደምስሰውታል።
ነገሩ እንዲህ ነው የኦሮሙማው ዘንዶ አማራን ለመጨፍጨፍ ከቻለም ለማጥፋት ብዙ ሙከራዎችን አድርጓል። ወደ ወረዳችን ደጋ ዳሞት ስንመጣ ይህን የጥፋት ተልኮ ይዘው ከወራት በፊት ህዝባችንን ለመጨፍጨፍ በወይንውሀ አረፋ ፍልቅልቅ ገብተው በከባድ ውጊያ የተጋዘ ጥቃት ቢያደርሱም በአይበገሬው ክንደ ነበልባሉ ፋኖና በአረዛንው ዳሞት ህዝብ በወሰደው አጣፋዊ እርምጃ በ24 ሰዓታት ውስጥ የአገዛዙ ሰራዊት ከ70-80 የሚደርስ አስክሬን ጭኖ ወደ ኋላ መፈርጦ መሔዱ ይታወቃል።
የደጋ ዳሞት ህዝብ ከድል መልስ በሗላም የውስጥ ጠላቶቻችን የብዓዴን ተላላኪዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ወስዶ ባለ 13 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቶ ለተግባራዊነታቸውም ሁሉንም በቃላችን መሰረት መፈጸማችን ይታወቃል። ከነዚህም መካከል እያንዳንዱ ወጣት ፋኖ ስልጠና ሰልጥኖ ዝግጁ እንዲሆኑ ማድረግ የነበረ ሲሆን በቃላችን መሰረት አሰልጥነን ከ2000 ያላነሰ ፋኖ አስመርቀናል።
ከዛም በሗላ የአማራ ህዝባዊ ኃይል (ፋኖ) ዳሞት ብርጌድ የአማራ ፋኖ ቀጠናዊ አንድነት መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ "የአማራ ህዝባዊ ኃይል (ፋኖ) በጎጃም የአንድነት ጥምረት መፍጠራችን ይታወቃል።
የከፋው ነገር የመጣው ከዚህ በሗላ ነው። የአገዛዙ ሃይል አለኝ የሚለውን ሰራዊት አሰባስቦ በሦስቱም አቅጣጫ ማለት በደንበጫ ፈረስቤት፣ በሞጣ ወይንውሐ አረፋ እና በባህርዳር አዴት ቋሪት ፈረስቤት አድርጎ አምባገነኑ ስርዓት አለኝ የሚለውን ከባድ መሳርያና ወታደር አስገብቶ ህዝባችንን ለመጨፍጨፍ የመጣው። ነገር ግን የዳሞትን ህዝብና ፋኖ ለማጥፋት በመጣበት ሰዓት ነበረ አብዮቱ ጎጃም ላይ የፈነዳው። ጎጃም የገባው የብርሃኑ ጁላ ወታደር ሰዓታት ባልሞላ ውጊያ ሬሳ በሬሳ እና እጅ ወደላይ እያለ ትጥቁን ለፋኖና ለህዝቡ ማስታጠቅ ጀመረ። ጎጃም ላይ የጀመረው አብዮት በተመሳሳይ ሰዓት ጎንደር ላይ ፈነዳ። ሽዋም እና ቤተ አምሓራ ቀደም ብሎ አብየቱ የተቀጣጠለበት ቦታ ነበር።
ወደ ወረዳችን የተሰራው ጀብድ ስንመጣ በሦስቱ የአውደ ውጊያ ቦታዎች ማለትም በድኩልኳና፣በአረፋ ፍልቅልቅ እና ሃሙስ ገብያ በነበረው ጦርነት ከ800 በላይ የአገዛዙ ወታደሮች ሬሳ በሬሳ የሆኑበት ብዙዎች የተማረኩበት፤ከዙ 23፣ ሞርታር ፣ዲሽቃ፣ብሬን፣ሰናይፐር እስከ ጥቁር ክላሽ ህዝባችን የታጠቀ ሲሆን ብዛት ያላቸው ተሽከርካሪዎች በአማራ ፋኖ እጅ ገቢ ተደርገዋል።
ይህ ድል እንዲመጣ የአንበሶችን ድርሻ የተወጣችሁ መላው የጎጃም አማራ ፋኖና ወጣት እጅግ የላቀ ምስጋና እያቀረብን። የአማራ ወጣቶች፤ የደጋ ዳሞት ህዝብ እና የአማራ ፋኖ ሁልጊዜም ከጎናችሁ መሆኑን እንገልፃለን።
በመጨረሻም ለህዝባችን ህልውና መኖር ያለምንም ደሞዝ በዱር በገደሉ እየተዋደቀ ያለውን የአማራ ፋኖ እንድትደገፋ ጥሪ ቀርቦላችኋል። በሃገር ውስጥና ውጭ የምትገኙ ባለሀብቶች፣ የዲያስፖራ ማህበረሰብ፣ በአማራ ስም የተቋቋማችሁ ማህበራት በምትችሉት መጠን የሎጅስቲክ አቅርቦት ታቀርቡ ዘንድ ከታላቅ ተማጥኖ ጋር እየጠየቅን፤ መደገፍ የምትፈልጉ በውስጥ መስመር ገብታችሁ ማነጋገር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
የአማራ ወጣቶች ማህበር በደጋ ዳሞት።
አማራነት የማይሰበር ማንነት በፈተናዎች የሚጠነክር አለት ነው። | 0 |
| 8 | ኔትዎርክ የተዘጋ ቢሆንም ያለ ኔትዎርክ ልንጠቀመው የምንችል እና ሰኪውር የመገናኛ መንገድ።
ይህ አፕሊኬሽን የሚሰራው እያንዳንዱን የስልክ Bluetooth እንደ ቴሌ አንቴና በመጠቅም ሲሆን በ300 ሜትር ውስጥ በተከታታይ ስልኮች ካሉ ያለምንም ገደብ ብዙ ኪሎሜትሮችን ሊሰራ ይችላል።
#FireChat ፋየርቻትን እንዴት መጠቀም እንደሚቻል?
ፋየርቻትን መጠቀም በጣም ቀላል ነው።
አፑን መጀመሪያ ስትጭን አፕሊኬሽኑ ራሱ ሁሉንም ባህሪያቶች እንድትጠቀም ያዝዛል።
ግን እነዚህን መመሪያዎች ወደ ቀላል ደረጃዎች እንከፍላቸዋለን ።
በመጀመሪያ ይህን መተግበሪያ ከፕሌይስቶር ወይም https://t.me/degadamotyouthassociation123/195 አውርዶ መጫን እና አፕ የጠየቀውን ፍቃድ መስጠት አለቦት።
አሁን መተግበሪያውን ይክፈቱ እና የኢሜል አድራሻን በመጠቀም መለያዎን ይፍጠሩ።
ወደ አፕሊኬሽኑ ከገቡ በኋላ በቀኝ ታችኛው ክፍል ላይ የመልእክት መጻፊያ ያያሉ ፣ ለሌላ ሰው አድራሻ መልእክት ለመላክ በላዩ ላይ ይንኩ።
መተግበሪያው ለማንም ሰው የግል መልዕክቶችን እንዲልኩ ያስችልዎታል; እና እነዚህ ሁሉ መልዕክቶች በጣም ሚስጥር ናቸው።
በsettings ውስጥ የራስዎን ምስል እና ሁኔታ ለማዘጋጀት አማራጮችን እናገኛለን።
በሁለተኛው ሜኑ ውስጥ የሚከተሉት አማራጮች አሉዎት፡ አዲስ ቡድን ይፍጠሩ (በአሁኑ ጊዜ እስከ 50 ሰዎችን በአንድ ቡድን ማስቀመጥ ይቻላል)።
በ Discover ምርጫ እገዛ፣ የተለየ ቡድን መፈለግ እና ከዚያ የመቀላቀል ጥያቄ መላክ ይችላሉ።
በFireChat ውስጥ ቡድን መፍጠር በጣም ቀላል እና ለማስተናገድ በጣም ቀላል ነው።
Hashtag Menu: FireChat በ Hashtags ላይ የተመሰረቱ የህዝብ ቻት ሩሞችን እንድትፈጥር ይፈቅድልሃል።
በዙሪያዎ ሌላ የFireChat የሌለበት አንዳንድ ሁኔታዎች ሊኖሩ ይችላሉ፣ ስለዚህ መልእክትዎ አይተላለፍም። ግን አይጨነቁ ፣ ሁሉም የተላኩ መልእክቶች ይከማቻሉ እና አንድ ጊዜ ሌላ ስልክ በ 300m ክልል ውስጥ ሲመጣ ግንኙነቱ ይቀጥላል። እና መልዕክቶችዎ ይላካሉ።
FireChat በመላው አለም ሰዎች ኢንተርኔት በሚዘጋበት ጊዜ የሚጠቀሙት አፕ ነው። በቅርቡ በሆንግ ኮንግ እንዲሁም በሌሎችህ ሰላማዊ ትግሎች ተጠቅመውታል ። | 0 |
| 9 | firechat-9-0-14.apk | 0 |
| 10 | #አስቸኳይ_መልዕክት
#በስናን_ዋብር እና #በድጎ_ጽዮን #ዋብር ያሉ ወደ #ደጋ_ዳሞት ያሉ መንገዶች በአስቸኳይ ይዘጉ።
የአገዛዙ ሃይል ደጋ ዳሞት ላይ በሦስቱም አቅጣጫ በአይበገሬው ፋኖና በደጋ ዳሞት ገበሬዎች እየተረሸነ ሲሆን ቁልፍ ቦታዎችም በፋኖ እና በህዝቡ እጅ ገብተዋል። | 0 |
| 11 | #ደጋ_ዳሞት መረጃ
ደጋ ዳሞት ላይ የገባው የአገዛዙ ሃይል በክንደ ነበልባቶች የአማራ ፋኖ እንደነዶ እየተወቃ ሲሆን በርካታ የአገዛዙ ወታደሎች ሙትና ቁስለኛ የሆኑ ሲሆን ብዙ የአማራ ተወላጆች የመከላከያ አባላት ከነትጥቃቸው የአይበገሬው የአማራ ፋኖ እየተቀላቀሉ ነው።
አሁን ላይ የኦሮሙማው ተልኮ አስፈጻሚ የሆነው መከላከያ ሰራዊት ወደ ደጋ ዳሞት ወረዳ ፈረስ ቤት ከተማ ለመግባት #በሶስት አቅጣጫ የመጣ ቢሆን #በአረፋ በኩል የገባው ሃይል በገበሬዎች እና በፋኖች እየተደቆሰ ሲሆን #በደንበጫ በኩል የገቡት ደግሞ ከሌሊቱ 10፡00 ጀምሮ ውጊያ እየተካሄደ ሲሆን ብዙ የአገዛዙ ጨፍጫፊ ሃይል ሙትና ሬሳ የሆነ ሲሆን በወገን በኩል የሚያስደንቅ ጀብድ እየተሰራ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይሔ ጨፍጫፊ ሃይል #በአዴት በኩል አድርጎ በብርአዳማ በኩል እየመጣ የነበረ ቢሆን በጀግኖች #የቋሪት ፋኖ እየተቀጠቀጠ እንደሆነ ለማረጋገጥ ችለናል።
በመላም አለም የምትገኙ አማራዎች እና የአማራ ወዳጆች ከአማራ ፋኖ ጎን እንድትቆሙና በምትችሉት መጠን እርዳታችሁን እንዳታደርጉ ማሳሰብ እንፈልጋለን።
ድል ለአማራ ፋኖ!
አማራ ወደ ክብሩ ወደመንበረ መንግስቱ ይመለሳል! | 0 |
| 12 | #የአማራ_ሕዝባዊ_ኃይል_ፋኖ_በጎጃም ጥምረት ፈጥሯል።
ፋኖ ተሰባሰብ ፋኖ ተሰማራ፣
እንደ ሆቺ ሚኒ እንደ ችጎቬራ፣
በጣጥሰህ ጣለው ይህን የባንዳ ሴራ።
በዛሬው ዕለት(23/11/15) በደጋ ዳሞት መናገሻ ከተማ #ፈረስ_ቤት ፡ #የአማራ_ሕዝባዊ_ኃይል_ፋኖ_በጎጃም ጥምረት ፈጥሯል።
በአካል ተገናኝተው ጥምረቱን የፈጠሩት፦
1. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በደጋ ዳሞት!
2. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በደምበጫ!
3. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በማቻከል
4. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በጅጋ
5. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በፍ/ሠላም
6. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በባ/ዳር ሲሆኑ እያንዳንዳቸው ከ20 ፋኖ በላይ ተወካይ በመላክ ጥምረቱ ተፈጥሯል።
ከዚህ በተጨማሪ ባለፈው የአማራን ፋኖ የተቀላቀሉት የደጋ ዳሞት ፖሊሶች "እንኳን ወደ ፋኖ ተቀላቀላችሁ" የሚል አቀባበል ተደርጓል።
የአማራ ወጣቶች ማህበር በደጋ ዳሞት ይህ ዘመን ተሻጋሪ ታሪክ እየሰሩ ላሉ ለመላው የደጋ ዳሞት ህዝብ፣ ለፋኖ አመራሮችና አባላት እጅግ የላቀ ምስጋና እያቀረበ፤ሁሌም ከጎናችሁ መሆኑን ማሳወቅ እንፈልጋለን። | 0 |
| 13 | በደጋ ዳሞት ወረዳ #ለአረፋ ና #ወይንውሀ አካባቢ ወጣቶች የተላለፈ #ራስን_የማዳን_የስልጠና_ጥሪ!
አርማችን የአማራ ፋኖ በደጋ ዳሞት አረፋና ወይንዉሀን መቀላቀል ለምትፈልጉ የቁርጥ ቀን የአማራ ልጆች በሙሉ አስቼኳይ ጥሪ ተደርጐላችኋል እና ባፋጣኝ ተመዝገቡ።
#መሰልጠን
#መደራጄት
#አንድ ሆነን የጠላትን ግብዓተ መሬት ማፈጠን ለነገ የማይባል ነጻ መውጫ መንገዳችን ነው።
○○○○○○○○○○●●●●●●●○○○○○○○○○○○
የሥልጠና ጥሪ
ለአረፋና ወይንውሀ አካባቢ ወጣቶች በሙሉ
ፋኖነት ከአባቶቻችን የወረስነው በልባችን ያለና የሚኖር ባህርያችን
ነው።
የአማራን ህዝብ ከጥፋት ለማዳን ያለን አማራጭ ሰላማዊ ሰልፍ እያሉ መሰለፍ ሳይሆን ሰይፍ መዝዞ መፈነን ብቻ ነው᎓᎓ ፋኖነት በልባችን ያለ ባህርያችን ስለሆነ ሥልጠና የማያስፈልገው ቢሆንም ለመደራጀትና በአንድ ሰንሰለት ለመመራትና እንዴት መታገል እንዳለብን ለመመካከር ሲባል የትግል ስልጠና አስፈልጓል። በቢቡኝ ወረዳ ባንዳ አመራሮች ጥሪ መሰረት የኦነግ ሰራዊት የመከላከያን ዩኒፎርም ለብሶ በመከላከያ ስም አካባቢያችን የአረፋ ቀጠና በተለይ ወይንውሀ ከተማ ምሽግ ሰርቶ ከተቀመጠ ቆይቷል ። ስለሆነም በወለጋ ሲያፈናቅልህ የነበረውን ይህን ወራሪ ጠላት ሀይል ከአረፋ ቀጠና መንጥሮ ለማስወጣት ሴት ወንድ ሳንል ስልታዊ ስልጠና በተመረጠ ቦታ በቅርብ ቀን ስልጠና ስለሚጀመር ከ ሀሙስ ገበያ እየመጣችሁ እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን።
የኦነግ ፈረስ ሆነው ኦነግ ሸኔ በመከላከያ ስም ገብቶ የአረፋ ወይንውሀን ሕዝብ እንዲጨፈጭፍ ፈርመው ያስገቡትን የቢቡኝ ወረዳ ባንዳ አመራሮችን ሳንፋረድ ብንቀር በወለጋ ምድር የፈሰሰው የወገኖቻችን የአማሮች አጥንት ይወጋናል። ሥልጠናው ቅዳሜና እሁድና በወርሃዊ በአላት ይሰጣል።
ፋኖነት ባህርያችን ነው᎓᎓ ድል ለአማራ | 0 |
| 14 | Нет текста... | 0 |
| 15 | Нет текста... | 0 |
| 16 | "ወጣቱ ለአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ዋጋ መክፈል አለበት ሲል የአማራ ወጣቶች ማህበር አስታወቀ‼"
ሐምሌ 20 ቀን 2015 ዓ.ም
አሻራ ሚዲያ ፣
ይኼን ያለው የጀግናው ምስራቅ አማራ ፋኖ መሪ ጀግናው ፣ብርቱው ፣ገራገሩ እና አስተዋዩ ዋርካው ምሬ ወዳጆ ነው ።
እውነት ነው ።
በተለይ በአሁኑ ወቅት የአማራ ወጣት ፥ወጣቱ ሀይል ለአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ዋጋ ለመክፈል መወሰን አለበት ፥አለብን ።የህልውና አደጋ ውስጥ ለሚገኘው ህዝባችን ዋስ ጠበቃ መሆን የምንችለው እኛው የአማራ ወጣቶች ነን ።በእዬ አካባቢያችን እየተዋደቀ ፣እየተፋለመ ለሚገኘው የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጅ (ፋኖ) አለኝታና ደጀን መሆን ያለብን እኛው ነን ።
የአማራ ህዝብ ነፃነት ፣ነፃነታችን ያለው በክንዳችን ነው ።የገጠመንን የህልውና አደጋ መቀልበስ የምንችለው በክንዳችን ፣በሀይላችን ፣በጉልበታችን ነው ።ትኩስ ሀይልና ጉልበት ያለው ደግሞ ወጣቱ ላይ ነው ።
የኦነግ ብልፅግና ከተሳካለት እንደ ናዚ ዘራችንን ሊፈጅና ሊያጠፋ ፤ ካልተሳካለት ደግሞ እንደ ኩርድ ህዝብ ሀገር አልባ ሊያደርገን ነው ጦር ያዘመተብን ።የወረረን!
የአማራ ወጣቶች ማህበርም ዋርካው ምሬ ወዳጆ ያለውን ተቀብለን የእኛ ዘመን የአማራ ወጣት የአማራ ህዝብ የህልውና አደጋ ይቀለበስ ዘንድ ዋጋ መክፈል አለብን ።የአማራ ወጣቶች ትግል ፍትሃዊ ፣ሞራላዊ እና ግዴታ ነው ።እንደ ህዝብ ተዋርዶና ፣አገር አልባ ፣ተሳዳጅ እና ተቅበዝባዥ ሆነን ላለመኖር ተነስ/ተነሽ ወቅቱ የሚጠይቀው ትግል ለማበርከት እንቁርጥ ፣እንወስን በማለት የአማራ ወጣቶች ማህበር የተለመደ የአክብሮት ጥሪውን ያስተላልፋል ።
አማራ በቆራጥ ልጆቹ ተጋድሎ ታሪኩን ያድሳል ።
ድል ለአማራ ፋኖ‼️
ድል ለአማራ ህዝብ‼️
"ውድ የአሻራ ሚዲያ ቤተሰቦች የአሻራ ሚዲያ ቻናልን ላይክና ሰብስክራይብ በማድረግ ድጋፋችሁን ታሳዩን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።"
ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች አሻራ ሚዲያ የአይበገሬዎቹ ልሳን:-
//
Youtube:- Ashara Tv - https://www.youtube.com/channel/UC2LZu_N0iOJipVUw3RyR4Ng
//
https://www.facebook.com/asharamedia24
//
ቴሌግራም:- https://t.me/asharamedia24 | 0 |
| 17 | #የደጋ ዳሞት ወረዳ 18 የፖሊስ ሠራዊት ከስራ ገበታቸው መጥፋታቸው ተገለጸ‼
ሐምሌ 20 ቀን 2015 ዓ.ም
አሻራ ሚዲያ ፣
የሠራዊቱ አባላት ሙሉ ትጥቃቸው እንደያዙ የፈረስ ቤት ከተማን ለቀው የጠፋ ሲሆን ሰባቱ የአማራ ህዝባዊ ግንባርን መቀላቀላቸው ታውቋል።
ከደጋ ዳሞት የፋኖ መሪዎች በደረሰው መረጃ መሰረት ሰባቱ አባላት ፋኖን ተቀላቅለው የአማራ ጠላት የሆነው የብልጽግና መንግስት ለማስወገድ ተሰልፈዋል።
"ውድ የአሻራ ሚዲያ ቤተሰቦች የአሻራ ሚዲያ ቻናልን ላይክና ሰብስክራይብ በማድረግ ድጋፋችሁን ታሳዩን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።"
ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች አሻራ ሚዲያ የአይበገሬዎቹ ልሳን:-
//
Youtube:- Ashara Tv - https://www.youtube.com/channel/UC2LZu_N0iOJipVUw3RyR4Ng
//
https://www.facebook.com/asharamedia24
//
ቴሌግራም:- https://t.me/asharamedia24 | 0 |
| 18 | #የደጋ_ዳሞት ትግል እና ውጤቱ!
ዳሞት ከጀመረ መጨረስ ያውቅበታል።
#መዳረሻችን የአማራ ነጻነት ነው።
#share
https://fb.watch/ltM5ixRXcT/ | 0 |
| 19 | ከፋኖ ግርማ ቢተው ጋር በተያያዘ ያሉ ክፍተቶች እንዲፈቱ በማሰብ የተደረገ ቃለምልልስ ደርሶናል። ትንሽ ደቂቃዎችን ወስዳችሁ አድምጡት። ፌስቡክ ላይ ከማያያዝ ወደ መፍትሄ መሄድ መልካም ነው። ይህን አስባችሁ ቃለምልልሱን ያደረጋችሁ ተባረኩ።
ትግላችን ተጀመረ እንጂ አላለቀም አሁንም ቢሆን ያሉ ቅርኔዎችን ፈቶ ወደ ፊት የአማራን ነፃነት እስከምናረጋግጥ ድረስ ይቀጥላል።
አላስፈላጊ መስዋትነት እንዳይኖር መግባባቶች ላይ መስራት ይኖርብናል ብለን እናምናለን።
https://fb.watch/lrZysMLnUb/?mibextid=Nif5oz | 0 |
| 20 | የአማራ ህዝባዊ ሀይል(ፋኖ) ዳሞት ብርጌድ
ከድል መልስ ከወረዳው መናገሻ ፈረስቤት ሲደርስ የተደረገለት አቀባበል የሚገርምምምምምምምምም ነው። | 0 |
