805
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
-130 дней
Архив постов
#2013_በንስሐ_ታጥቦ_መሻገር
2014 በአዲስ ልብ እና ማንነት መቀበል
1ኛ ዮሐንስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም።
⁹ በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።
¹⁰ ኃጢአትን አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም።
#ንስሐ ለመንፈሳዊ ለውጣችን ትልቅ ቦታ እንዳለው ልንረዳ ይገባናል መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን በኃይል በሙላት እንዲሰራ የምንፈልግ ከሆነ #የንስሐ ሕይወት ሊኖረን ይገባናል።
ንስሐ ምንድነው በጥቂቱ
1 ድካማችንን በእግዚአብሔር ፊት በመግለጥ ከእግዚአብሔር ኃይል የምንቀበልበት ምስጢር ነው
2 ልባችንን ወደ እግዚአብሔር የመመለስ መንገድ ነው።
“አቤቱ፥ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ #ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ።”
— ሰቆ. 5፥21
3 መጥፎ ተግባራትን በመጥላት ከክፋት መራቅ ነው።
4 እግዚአብሔር በመረጠልን በአዲስ የሕይወት መንገድ ለመኖር ራስን ሙሉ በሙሉ ለእግዚአብሔር ማቅረብ ነው።
5 ንስሐ ለእግዚአብሔር ፍቅር ምላሽ ለመስጠት ቁርጥ ፈቃድ በማድረግ ትእዛዙን በመጠበቅ ለመኖር የወሰነ የሚፀፀት ሰው ልብ ትርታ ነው።
ውጤታማ #ንስሐ ለማድረግ (ራስን ለመመርመር) የሚጠቅሙ ጥቂት መንገዶች
1 በፀሎት መንፈስ በመሆን በቂ ራስን የመመርመሪያ ግዜ መስጠት ቢቻል የግል ሱባኤ ማድረግ
2 በ2013 ምን አይነት ሕይወት ነው ያሳለፍኩት ብሎ ራስን መመርመር
3 በዚህ ዓመት እግዚአብሔር በማይፈልገው በማይከብርበት ቦታ ሳሳልፍ ቆይቻለው
4 ስራዬን ወይም ኃላፊነቴን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ነው ያሳለፍኩት? በንፅህና በታማኝነት?
5 ባለኝ እርካታ በማጣት እግዚአብሔር ባልፈቀደው መንገድ የሚመጣ ገቢ ነበረኝ?
6 ይቅርታ ማድረግ ሲገባኝ ያላደረኩት ወይም ደግሞ ይቅርታ መጠየቅ ሲገባኝ ያልጠየኩት ሰው አለ?
7 ለእግዚአብሔር ቤት ስራ እግዚአብሔር ከሰጠኝ ላይ አስራት በመክፈል እና የሚጠበቅብኝን በማድረግ ጤናማ ዓመት አሳልፌአለው?
እነዚህ በጣም በጥቂቱ ራስን ለመመርመር ሊጠቅሙ መንገድ እንዲሆኑን ነው እንጂ ብዙ ጥያቄ ማውጣት ይቻላል። ነገር ግን በጣም ማሰብ ያለብን ለውጥ የምንፈልግ ከሆነ ራሳችንን ልንፈትሽ ይገባናል።
ሕዝቅኤል 36
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁵ ጥሩ ውኃንም እረጭባችኋለሁ እናንተም ትጠራላችሁ፥ ከርኵሰታችሁም ሁሉ ከጣዖቶቻችሁም ሁሉ አጠራችኋለሁ።
²⁶ አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፤ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ።
²⁷ መንፈሴንም በውስጣችሁ አኖራለሁ በትእዛዜም አስሄዳችኋለሁ፥ ፍርዴንም ትጠብቃላችሁ ታደርጉትማላችሁ።
እግዚአብሔር ሊያጥበን ሊያነፃን እየጋበዘን ነው። ይህን መልካም ግብዣ እንቀበል። አዲሱን ዓመት 2014 በንፁህ ለእግዚአብሔር በሚመች ልብ እንቀበለው።
መልካም የንስሐ እና የኑዛዜ ግዜ ይሁንላችሁ።
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#2013_በንስሐ_ታጥቦ_መሻገር
2014 በአዲስ ልብ እና ማንነት መቀበል
1ኛ ዮሐንስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም።
⁹ በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።
¹⁰ ኃጢአትን አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም።
#ንስሐ ለመንፈሳዊ ለውጣችን ትልቅ ቦታ እንዳለው ልንረዳ ይገባናል መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን በኃይል በሙላት እንዲሰራ የምንፈልግ ከሆነ #የንስሐ ሕይወት ሊኖረን ይገባናል።
ንስሐ ምንድነው በጥቂቱ
1 ድካማችንን በእግዚአብሔር ፊት በመግለጥ ከእግዚአብሔር ኃይል የምንቀበልበት ምስጢር ነው
2 ልባችንን ወደ እግዚአብሔር የመመለስ መንገድ ነው።
“አቤቱ፥ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ #ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ።”
— ሰቆ. 5፥21
3 መጥፎ ተግባራትን በመጥላት ከክፋት መራቅ ነው።
4 እግዚአብሔር በመረጠልን በአዲስ የሕይወት መንገድ ለመኖር ራስን ሙሉ በሙሉ ለእግዚአብሔር ማቅረብ ነው።
5 ንስሐ ለእግዚአብሔር ፍቅር ምላሽ ለመስጠት ቁርጥ ፈቃድ በማድረግ ትእዛዙን በመጠበቅ ለመኖር የወሰነ የሚፀፀት ሰው ልብ ትርታ ነው።
ውጤታማ #ንስሐ ለማድረግ (ራስን ለመመርመር) የሚጠቅሙ ጥቂት መንገዶች
1 በፀሎት መንፈስ በመሆን በቂ ራስን የመመርመሪያ ግዜ መስጠት ቢቻል የግል ሱባኤ ማድረግ
2 በ2013 ምን አይነት ሕይወት ነው ያሳለፍኩት ብሎ ራስን መመርመር
3 በዚህ ዓመት እግዚአብሔር በማይፈልገው በማይከብርበት ቦታ ሳሳልፍ ቆይቻለው
4 ስራዬን ወይም ኃላፊነቴን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ነው ያሳለፍኩት? በንፅህና በታማኝነት?
5 ባለኝ እርካታ በማጣት እግዚአብሔር ባልፈቀደው መንገድ የሚመጣ ገቢ ነበረኝ?
6 ይቅርታ ማድረግ ሲገባኝ ያላደረኩት ወይም ደግሞ ይቅርታ መጠየቅ ሲገባኝ ያልጠየኩት ሰው አለ?
7 ለእግዚአብሔር ቤት ስራ እግዚአብሔር ከሰጠኝ ላይ አስራት በመክፈል እና የሚጠበቅብኝን በማድረግ ጤናማ ዓመት አሳልፌአለው?
እነዚህ በጣም በጥቂቱ ራስን ለመመርመር ሊጠቅሙ መንገድ እንዲሆኑን ነው እንጂ ብዙ ጥያቄ ማውጣት ይቻላል። ነገር ግን በጣም ማሰብ ያለብን ለውጥ የምንፈልግ ከሆነ ራሳችንን ልንፈትሽ ይገባናል።
ሕዝቅኤል 36
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁵ ጥሩ ውኃንም እረጭባችኋለሁ እናንተም ትጠራላችሁ፥ ከርኵሰታችሁም ሁሉ ከጣዖቶቻችሁም ሁሉ አጠራችኋለሁ።
²⁶ አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፤ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ።
²⁷ መንፈሴንም በውስጣችሁ አኖራለሁ በትእዛዜም አስሄዳችኋለሁ፥ ፍርዴንም ትጠብቃላችሁ ታደርጉትማላችሁ።
እግዚአብሔር ሊያጥበን ሊያነፃን እየጋበዘን ነው። ይህን መልካም ግብዣ እንቀበል። አዲሱን ዓመት 2014 በንፁህ ለእግዚአብሔር በሚመች ልብ እንቀበለው።
መልካም የንስሐ እና የኑዛዜ ግዜ ይሁንላችሁ።
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#የዕለት_ስንቅ
በረከታችን ክርስቶስ ነው
“በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።”
— ኤፌሶን 1፥3
እግዚአብሔር ባርኮሃል ማለት ብልጽግና ጤንነት ወይም የተለያዩ የህይወት ስኬቶችን አግኝተሀል ማለት ብቻ አይደለም ። በእርግጥ በረከት ውስጥ እነዚህና ሌሎችም በተለምዶ በረከት ብለን የምንጠራቸው ነገሮች ቢካተቱም እነዚህ ተጨማሪ ነገሮች ናቸው ዋናው በረከታችን የህጉ እርግማን ከህይወታችን ተወግዶ የእግዚአብሔር ህይወት በመካፈል መለኮታዊ በረከት ውስጥ በመግባት የክርስቶስ ህይወት መካፈላችን ነው።
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
የዕለት ስንቅ
#መስጠትን_እንደ_ግዴታና_እንደ_ስራ_ሳይሆን_እንደ_እድል_ቁጠረው
“እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም።” — 2ኛ ቆሮ 9፥7
መቼም ከሚቀበሉት ከመሆን ከሚሰጡት መሆን የተሻለ እድል ነው። ስለዚህ ካለን ነገር ወስዶ ለሰው ማካፈልን እንደ ግዴታ አንቁጠረው እንደ ታላቅ እድል እንጂ። የምታካፍለው እኮ ስላለህ ነው። ይህ ደግሞ ብዙዎች የሚመኙት እና ያልቻሉት ትልቅ እድል ነው አንተ ያገኘኸው። ከሁሉ በፊት መስጠትን እንደ ግዴታ ሳይሆን እንደ እድል ልንቆጥር የሚገባን ዋነኛ ምክንያት በመስጠታችን ምክንያት የምንለውጠውን የሰው ሕይወት (ፍሬውን ) በማሰብ ነው። የአንድን ሰው ሕይወት መንካት ከዛ ሰው ጋር የተነካኩትን ሰዎች ሁሉ የሚደርስ ጉዳይ ነው። በመስጠታችን ምክንያት አንድን ሰው ለአመታት ታግሎ መውጣት ከማይችልበት ሁኔታ ስናወጣው ከዚያ ሰው ጋር የተቆራኙ ሰዎችን ሁሉ ታሪክ የመንካት እድል አለን። በመቀጠል መስጠት እንደ ዘር ስለሆነ እንደ እድል ልንቆጥረው ይገባል። የዘራኸውን በጊዜው ይበቅልልሀል ማጨድህ አይቀርም። የዘራኸው ነው ነገ በጊዜው የምትሰበስበው። ደግሞም የተፈጠርነው ለመልካም ስራ እንደሆነ አንዘንጋ።
“ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱም የምትዘሩትን ዘር ይሰጣችኋል ያበረክትላችሁማል፥ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያሳድጋል፤” — 2ኛ ቆሮ 9፥10
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
የዕለት ስንቅ
#መስጠትን_እንደ_ግዴታና_እንደ_ስራ_ሳይሆን_እንደ_እድል_ቁጠረው
“እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም።” — 2ኛ ቆሮ 9፥7
መቼም ከሚቀበሉት ከመሆን ከሚሰጡት መሆን የተሻለ እድል ነው። ስለዚህ ካለን ነገር ወስዶ ለሰው ማካፈልን እንደ ግዴታ አንቁጠረው እንደ ታላቅ እድል እንጂ። የምታካፍለው እኮ ስላለህ ነው። ይህ ደግሞ ብዙዎች የሚመኙት እና ያልቻሉት ትልቅ እድል ነው አንተ ያገኘኸው። ከሁሉ በፊት መስጠትን እንደ ግዴታ ሳይሆን እንደ እድል ልንቆጥር የሚገባን ዋነኛ ምክንያት በመስጠታችን ምክንያት የምንለውጠውን የሰው ሕይወት (ፍሬውን ) በማሰብ ነው። የአንድን ሰው ሕይወት መንካት ከዛ ሰው ጋር የተነካኩትን ሰዎች ሁሉ የሚደርስ ጉዳይ ነው። በመስጠታችን ምክንያት አንድን ሰው ለአመታት ታግሎ መውጣት ከማይችልበት ሁኔታ ስናወጣው ከዚያ ሰው ጋር የተቆራኙ ሰዎችን ሁሉ ታሪክ የመንካት እድል አለን። በመቀጠል መስጠት እንደ ዘር ስለሆነ እንደ እድል ልንቆጥረው ይገባል። የዘራኸውን በጊዜው ይበቅልልሀል ማጨድህ አይቀርም። የዘራኸው ነው ነገ በጊዜው የምትሰበስበው። ደግሞም የተፈጠርነው ለመልካም ስራ እንደሆነ አንዘንጋ።
“ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱም የምትዘሩትን ዘር ይሰጣችኋል ያበረክትላችሁማል፥ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያሳድጋል፤” — 2ኛ ቆሮ 9፥10
ስለ ምንድን ነው ማሰብ ያለብን?
ማቴ 6:25-33
25-ስለዚህ እላችኋለሁ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት ወይም ስለሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ አይበልጥምን?
26-ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ አይዘሩም አያጭዱምም በጎተራም አይከቱም የሰማዩ አባታችሁም ይመግባቸዋል እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን?
27-ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው?
28-ስለ ልብስስ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ?የሜዳ አበቦች እንዴት እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ።
29-አይደክሙም አይፈትሉምም ነገር ግን እላችኋለሁ ሰለሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም።
30-እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገር ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሳር እንዲ የሚያለብሰው ከሆነ እናንተ እምነት የጎደላችሁ እናንተንማ ይልቁን እንዴት?
31-እንግዲህ።ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ።
32-ይህንስ ሁሉ አህዛብ ይፈልጋሉ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና።
33-ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግስት ጽድቁንም ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።
#ዛሬ እኛ ስለምንድነው የምንጨነቀው?
⨳በመጀመሪያ ጭንቀት ከምን ይመጣል?
ካለማመን
በቀላል ምሳሌ ስናየው ፀሎት ፀልየን ነገራችንን ለእግዚአብሔር ከሰጠን በኋላ ምን ያህሎቻችን ነን ሳንጨነቅ የፀሎታችንን መልስ በትግስት የምንጠብቀው?
⨳ለምሳሌ ወፎችን ያሳየናል የሰማይ አባታቸው ያስብላቸዋል ያበላቸዋል የሚያስፈልጋቸውን ይሰጣቸዋል።ዛሬ እግዚአብሔር ለኛ ለዛውም በአምሳሉ ለፈጠረን እስትንፋሱን እፍ ላለብን ሰዎች ከነሱ አብልጦ ያስብልናል የምንፈልገውን ብቻ ሳይሆን የሚያስፈልገንን ይሰጠናል።
#ለምሳሌ አንድ ልጅ ህፃን እያለን ቤተሰቦቹ ናቸው የሚያስፈልገውን የሚያደርጉለት።አንድ ህፃን ወተት ሲሰጠው ለነገ ምን እጠጣለሁ ብሎ አያስብም የተሰጠውን ይጠጣል ከጠገበ ይተወዋል ካልጠገበ ያስጨምራል እንጂ ለነገዬ አይልም ግን ለነገዬ ብሎ ስላላሰበ አያጣም። ለነገው ደግሞ ቤተሰቦቹ ያዘጋጁለታል።እሱ ሚፈልገውን ብቻ አይሰጡትም( ለምሳሌ ሁሌ ጣፋጭ ነገር አይሰጡትም ) የሚያስፈልገውን እንጂ።
⨳እኛም ከእግዚአብሔር ጋር እንደ ልጅ እና አባት ከሆንን እኛ ተጨንቀን ሳይሆን እንደ ልጁ የምንፈልገውን ብቻ ሳይሆን የሚያስፈልገንን ያውቃል።ማወቅ ብቻ አይደለም ይሰጠናል እናም እምነታችንን በአባታችን ላይ እናርግ።እግዚአብሔር ለቃሉ ታማኝ ነው የተናገረውን ይፈፅማል።
⨳ሌላው ከእኛ ሚጠበቀው ነገር የእግዚአብሔርን መንግስት ለመውረስ እርሱን ደስ የሚያሰኝ በሚያከብር ስራ በመስራት ትዛዙን በመፈፀም መኖር ነው ሌላው የሚያስፈልገን ነገር ሁሉ ይሰጠናል መልካም የሚያስብልንና ፍቅር የሆነ አባት ስላለን።
#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_ሰሚናር
የሶስት ወር ሰሚናር በአንድ ሳምንት
የምስራች የሚናገር፥ ሰላምንም የሚያወራ፥ የመልካምንም ወሬ የምስራች የሚናገር፥ መድኃኒትንም የሚያወራ፥ ጽዮንንም፦ አምላክሽ ነግሦአል የሚል ሰው እግሩ በተራሮች ላይ እጅግ ያማረ ነው።” — ኢሳይያስ 52፥7
ሰላም ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እግዚአብሔር ረድቶን ለወጣች የተዘጋጀው ልዩ የክረምት ስልጠና #1ኛ_ዙር ትላንት ሰኞ ነሐሴ #3 ጀምረናል። በቀጣይ ሳምንት በሚጀመረው #2ኛ_ዙር ከነሐሴ 10 እሰከ ነሐሴ 15 ምዝገባ ጀምረናል። ስለዚህ ሁላችሁም ሰዎችን እያስመዘገባችሁ በረከታችሁን ተቀበሉ።
+251916584487
+251936960959
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
