805
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
-130 день
Архив постов
Repost from ሰማያዊ ወግ (The tradition of heaven)
ክርስቶስ ንጉስ
፪
“የሰው ልጅ ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም።” ማቴ 20፥28
በካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ንጉስ በአል ቤተ ክርስቲያን ለህዝቦቿ የምታስተምረው ሳይሆን እራሷም ክርስቶስ ንጉስ መሆኑን የምትማርበት ቀን ነው።
እየሱስ ንጉስ ቢሆንም መንግስቱ ከዚህ አለም አይደለም። እርሱ ትሁት ንጉስ ነው፣ ሁሉ የእርሱ ሁኖ ልደቱ በበረት ነበር። እርሱ እንደ ምድራዊ ንጉስ በጉልበት ገዢ ሳይሆን አገልጋይ ንጉስ ነው። በስልጣን ሳይሆን በፍቅር እንድንገዛለት ያደርጋል። በፍርሀት ሳይሆን በእውነት እና በመንፈስ እንድናገለግለው ይወዳል።
የክርስቶስ ንጉስነት ከምድር ነገስታት ፍፁም ተቃራኒ ነው። ሀጥያተኛ ከተባሉት ከቀረጥ ሰብሳቢዎች፣ ከአመንዝሮች ጋር ይውላል። ነገስታት፣ ሀብታሞችንና ታላላቅ የተባሉትን ሲቀበሉ ክርስቶስ ግን የተናቁትንና ታናናሾችን ይቀበላል። ነገስታት፣ የሰዎች ስጦታን ይፈልጋሉ ይቀበላሉም። ክርስቶስ ግን ላመኑት ህይወትን ይሰጣል። ለታመሙ ፈውስን፣ ለታሰሩ መፈታትን፣ ላዘኑ መፅናናትን፣ ለጨለመባቸው ብርሀንን ይሰጣል።
ክርስቶስ ንጉስ ቢሆንም እንደ ምድራዊያን የወርቅ አክሊል አልደፋም ይልቅ ስለኛ ሀጥያት የእሾህ አክሊል ደፍቷል። እየሱስ ክርስቶስ ንጉስ ነው፣ ንጉስ ስለሆነ የእሾህ አክሊል አለው። ንጉስ ስለሆነ ባንዲራው መስቀል ነው። የሚያምኑት እንደ ባንዲራ መስቀሉን ይሸከማሉ። “መስቀሉን ተሸክሞ በኋላዬ የማይመጣ፥ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም።” ሉቃ 14፥27።
ክርስቶስ ንጉስ ስለሆነ ህዝብ አለው፣ ለህዝቡም በጀት አለው፣ ለሁሉ የሚያስፈልገውን ይሰጣል፣ ለዚህ ነው እራሱ ክርስቶስ ንጉስ ባስተማረን ፀሎት "የእለት እንጀራችንን.." እያልን የምንፀልየው።
https://t.me/wogse
