ru
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Открыть в Telegram
805
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
-130 дней
Архив постов
የሰሚናር ትምህርት 15/05/14 የእኛ ምንም አይነት መልካምነት የእግዚአብሔርን ፍቅር እንደማይጨምር ሁሉ የእኛ ምንም አይነት መጥፎ ባህሪ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አይቀንስም። ፍቅሩን ተረድተን መኖር ይሁንልን @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ “ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።” — 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥17-18 አመስጋኝ ሰው ሁልግዜ ችግሮችን በምስጋና እያስወገደ የሚኖር ደስተኛ ነው። የምናማርር ከሆነ ደግሞ መልካም አጋጣሚዎችን እንኳን ማየት አንችልም። አመስጋኝ ሰው በየዕለቱ ጤናውን እየተንከባከበ ነው። አማራሪ ሰው ጤናው ላይ ችግር እየፈጠረ ነው። ስለዚህ ሁልግዜ የምስጋና ሕይወት ይኑረን የእግዚአብሔር ቃልም የሚለን በሁሉ አመስግኑ ነው። በሁሉ እናመሰግናለን። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ ✅ የማንነታችን የዋጋ ተመን ሰዎች በእኛ ላይ ካላቸው አመለካከት አንፃር ሳይሆን ከእግዚአብሔር በተነገረን የሕይወት ትርጉም አንፃር ራሳችንን ማወቅና ማየት አለብን። ያለበለዚያ የስሜታችን ከፍታና ዝቅታ የሚወሰነው ሰዎች በእኛ ላይ ካላቸው አመለካከት ስለሚሆን እኛ መኖራችን እናቆምና የሰዎች አመለካከት በእኛ ውስጥ መኖር ይጀምራል። ይህ እንዳይሆን የእግዚአብሔር ቃል የነገረንን እንስማ። እኔ 👉በሰማያዊ ስፍራ ተባርኬአለሁ (ኤፌሶን 1:3) 👉በክርስቶስ ሕያው ነኝ (ኤፌሶን 2:6) 👉የክርስቶስ ልብ አለኝ (1ቆሮ 2:6) 👉በክርስቶስ የእግዚአብሔር ፅድቅ ነኝ (2ቆሮ 5:21) 👉የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ (ዮሐ 1:12) 👉በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታሁ ነኝ (ኤፌ 6:10) 👉በክርስቶስ በዋጋ ተገዝቻለው የራሴ አይደለሁም(1ቆሮ6:20) 👉በውስጤ ባለው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ዘወትር በፀጋው የበረታሁ ነኝ (1ቆሮ 3:16) መልካም ዕለተ ሰንበት @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ማወቅ “የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።” — 2ኛ ጴጥሮስ 1፥2-3 @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ማወቅ “የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።” — 2ኛ ጴጥሮስ 1፥2-3

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ “ልጆቼ ሆይ፥ ተመለሱ፤ ባል ለማግባት አርጅቻለሁና ሂዱ #ተስፋ አለኝ ብል፥ ዛሬ ሌሊትስ እንኳ ባል ባገባ፥ ወንዶች ልጆችም ብወልድ፥” — ሩት 1፥12 ሩት 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ ኑኃሚንም፦ እነሆ፥ ባልንጀራሽ ወደ ሕዝብዋና ወደ አማልክትዋ ተመልሳለች፤ አንቺም ደግሞ ከባልንጀራሽ ጋር ተመለሽ አለቻት። ¹⁶ ሩትም፦ ወደምትሄጅበት እሄዳለሁና፥ በምታድሪበትም አድራለሁና እንድተውሽ ከአንቺም ዘንድ እንድመለስ አታስቸግሪኝ፤ ሕዝብሽ ሕዝቤ፥ አምላክሽም አምላኬ ይሆናል፤ ¹⁷ በምትሞችበትም ስፍራ እሞታለሁ፥ በዚያም እቀበራለሁ፤ ከሞት በቀር አንቺንና እኔን አንዳች ቢለየን እግዚአብሔር ይህን ያድርግብኝ እንዲሁም ይጨምርብኝ አለች። 👉ተስፋ የምናደርገው ደስ በሚል ሁኔታ ውስጥ ብቻ ሳይሆን ተስፋ በማይደረግበት ሁኔታ ውስጥ ጭምር ነው። እውነተኛ ክርስትናችን የሚፈተነው ተስፍ በማይሰጥ ሁኔታ ውስጥ ስናልፍ የምንሰጠው ምላሽ ነው። ነገሮች ተስፍ በሚያስቆርጡበት ሁኔታ ውስጥም ቢሆን እንኳን ተስፋ ማድረጋችንን ሳንለቅ በዕምነት እና በፅናት ለውጥ ማምጣት እንችላለን። ተስፍ የተሻሉ ነገሮች እንደሚመጡ ማሰብ ነው። የሩት የዕምነት እና የፅናት ጉዞ በክርስቶስ የዘር ሀረግ ውስጥ መግባት እንዳስቻላት ዛሬም እኛ በምንም #ተስፍ በሚያሳጣ ሁኔታ ውስጥ ብንሆን እግዚአብሔርን አምነን እና ፀንተን ብንከተለው የብዙ መልካም ሕይወት በረከቶች፣ የዘላለም ሕይወት ተካፋዮች የማንሆንበት ምንም ምክንያት የለም። ዘመናችሁ ቀናችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን ተስፋ በማድረግ የደስታ የእረፍት ይሁንላችሁ። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ “ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ ለአርነት ተጠርታችኋልና፤ ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ፥ ነገር ግን በፍቅር እርስ በርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ።” — ገላትያ 5፥13 ✅ አምላካችን ምንም እንኳን ሉዓላዊ አምላክ ቢሆንም በምድር ላይ ያሻንን እንድናደርግና የፈቀድነውን መርጠን እንድንከተል ለሰው ልጆች ማንም የማይወስድብንን ነፃ ፈቃድ አጎናፅፎናል። ነገር ግን ለልጆቹ ካለው ታላቅ ፍቅር የተነሳ እንዳንጠፋበት ስለሚፈልግ ዘወትር የሚጠቅመንን መልካሙን ሕይወት መኖር የምንችልበትን መንገድ ያሳየናል ይመክረናል። ዳዊት በራሱ መንገድ ሄዶ የጠፋ ሰው ነበር ነገር ግን ወደ እግዚአብሔር ሀሳብ ተመልሶ መንገዱን ስለቀናለት የእግዚአብሔር ምክር እንዲህ ይላል “የመከረኝን እግዚአብሔርን እባርካለሁ" — መዝሙር 16፥7 ነፃነታችንን ለመልካም ነገር እንጠቀምበት። በዚህ ቀን ራሳችንን እንፈትሽ ባገኘሁት ነፃነት እንዴት አየተጠቀምኩ ነው? ስሜቴ የፈቀደውን ወይስ የእግዚአብሔርን ፈቃድ? “የእግዚአብሔር ምክር ግን ለዘላለም ይኖራል፥ የልቡም አሳብ ለልጅ ልጅ ነው።” — መዝሙር 33፥11 https://t.me/eccrm https://t.me/eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ ኢሳይያስ 48 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ ታዳጊህ፥ የእስራኤል ቅዱስ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ የሚረባህን ነገር የማስተምርህ በምትሄድባትም መንገድ የምመራህ አምላክህ እግዚአብሔር ነኝ። ¹⁸ ትእዛዜን ብትሰማ ኖሮ፥ ሰላምህ እንደ ወንዝ ጽድቅህም እንደ ባሕር ሞገድ በሆነ ነበር፤ ¹⁹ ዘርህም እንደ አሸዋ የሆድህም ትውልድ እንደ ምድር ትቢያ በሆነ ነበር፥ ስሙም ከፊቴ ባልጠፋና ባልፈረሰ ነበር። ✅ አንተ ከእግዚአብሔር ጋር ከሆንክ እግዚአብሔር ሁልግዜ ከአንተ ጋር ነው። የአንተ አምሳያና የአንተም ጭምር ነው። ታዲያ እርሱ የሚያዘውንና የሚወደውን የምታደርግ ከሆንክ መንገድህን ሊዘጋ የሚችል ከቶ ማንም የለም። የእግዚአብሔር መልካም ስጦታ ሁሉ በሕይወትህ ይፈፀማል። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ ሮሜ 14 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ ወንድምህንም በመብል ምክንያት የምታሳዝን ከሆንህ እንግዲህ በፍቅር አልተመላለስህም። ክርስቶስ ስለ እርሱ የሞተለትን እርሱን በመብልህ አታጥፋው። ¹⁶ እንግዲህ ለእናንተ ያለው መልካም ነገር አይሰደብ፤ ¹⁷ የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና። ¹⁸ እንደዚህ አድርጎ ለክርስቶስ የሚገዛ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኛልና፥ በሰውም ዘንድ የተመሰገነ ነው። 💚 ከወንድሞች እና እህቶች ጋር ባለን እያንዳንዱ እንቅስቃሴ ማነፅን አላማ አድርገን መጓዝ ከእያንዳንዳችን ይጠበቃል። ለሌሎች ያለን ፍቅር ከሚታወቅባቸው መንገዶች መካከል እነርሱን ከሚያሰናክል ነገር ተጠብቀን ይልቁን ለመታነፃቸው በተጋንበት ልክ ነው። የዘወትር ተግባራችን ሰዎችን ለመጥቀም በሚበጅ ተግባር ላይ የተጠመደ መሆን አለበት። እግዚአብሔር ለአካሉ መታነፅ በሰጠን የፀጋ ስጦታ አማካኝነት የራሳችንን ስም ሆነ ዝና ለማቆም ከመስራት ይልቅ የክርስቶስ አካል የሆነችውን ቤተክርስቲያን ለማነፅ እንትጋ። 💚 እግዚአብሔር የሰጠን ጤና የሰጠን ስራ የሰጠን ገንዘብ (ሀብት) እግዚአብሔር የሰጠን መልካም ነገር ሁሉ ተመልሶ እርሱ ለሚፈልገው አገልግሎት ካልዋለ በእኛ ልፋትና ጥረት እንዳገኘን እያሰብን ነው ማለት ነው። ይህ ነው እንግዲህ የተደረገልንን አለማወቅ። የምነሰብከውና የምንዘምረው ብቻ ሳይሆን የምንኖረው ክርስትና ይሁንልን። “ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።” — ኤፌሶን 2፥9 ደጋግመን በማንበብ እና በማሰላሰል ራሳችን የቱጋር እንዳለን እንፈትሽ። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ ሮሜ 14 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ ወንድምህንም በመብል ምክንያት የምታሳዝን ከሆንህ እንግዲህ በፍቅር አልተመላለስህም። ክርስቶስ ስለ እርሱ የሞተለትን እርሱን በመብልህ አታጥፋው። ¹⁶ እንግዲህ ለእናንተ ያለው መልካም ነገር አይሰደብ፤ ¹⁷ የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና። ¹⁸ እንደዚህ አድርጎ ለክርስቶስ የሚገዛ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኛልና፥ በሰውም ዘንድ የተመሰገነ ነው። 💚 ከወንድሞች እና እህቶች ጋር ባለን እያንዳንዱ እንቅስቃሴ ማነፅን አላማ አድርገን መጓዝ ከእያንዳንዳችን ይጠበቃል። ለሌሎች ያለን ፍቅር ከሚታወቅባቸው መንገዶች መካከል እነርሱን ከሚያሰናክል ነገር ተጠብቀን ይልቁን ለመታነፃቸው በተጋንበት ልክ ነው። የዘወትር ተግባራችን ሰዎችን ለመጥቀም በሚበጅ ተግባር ላይ የተጠመደ መሆን አለበት። እግዚአብሔር ለአካሉ መታነፅ በሰጠን የፀጋ ስጦታ አማካኝነት የራሳችንን ስም ሆነ ዝና ለማቆም ከመስራት ይልቅ የክርስቶስ አካል የሆነችውን ቤተክርስቲያን ለማነፅ እንትጋ። 💚 እግዚአብሔር የሰጠን ጤና የሰጠን ስራ የሰጠን ገንዘብ (ሀብት) እግዚአብሔር የሰጠን መልካም ነገር ሁሉ ተመልሶ እርሱ ለሚፈልገው አገልግሎት ካልዋለ በእኛ ልፋትና ጥረት እንዳገኘን እያሰብን ነው ማለት ነው። ይህ ነው እንግዲህ የተደረገልንን አለማወቅ። የምነሰብከውና የምንዘምረው ሳይሆን የምንኖረው ክርስትና ይሁንልን። “ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።” — ኤፌሶን 2፥9 ደጋግመን በማንበብ እና በማሰላሰል ራሳችን የቱጋር እንዳለን እንፈትሽ። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ “አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ፦ አቤቱ፥ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ።” — መዝሙር 27፥8 እግዚአብሔር አፍቃሪ አባታችን እንደሆነና እኛ እርሱን ከምንሻው በላይ እርሱ ከእኛ ጋር ለመሆን እንደሚናፍቅ ከተረዳን ፀሎታችን ሆነ አምልኮአችን በፍቅር የተሞላ ጣፋጭ የማይሰለችና ተናፋቂ ይሆናል። @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ ሮሜ 8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁵ ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፥ ወይስ ጭንቀት፥ ወይስ ስደት፥ ወይስ ራብ፥ ወይስ ራቁትነት፥ ወይስ ፍርሃት፥ ወይስ ሰይፍ ነውን? ³⁶ ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው። ³⁷ በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን። ³⁸ ሞት ቢሆን፥ ሕይወትም ቢሆን፥ መላእክትም ቢሆኑ፥ ግዛትም ቢሆን፥ ያለውም ቢሆን፥ የሚመጣውም ቢሆን፥ ኃይላትም ቢሆኑ፥ ³⁹ ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ። 💚💚💚💚💚💚💚💚💚💚 የእግዚአብሔርን ፍቅር ተረድተን ለእግዚአብሔር ፈቃድ መኖር በቻልንበት አጋጣሚ ሁሉ ከእግዚአብሔር የሚገኘው ደስታ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ያለ ማንም ከልካይ ሀሴት እያደረግን ደስታችንን ማጣጣማችን የማይቀር ጉዳይ ነው። 🎷🎷🎷🎷🎷🎷🎷🎷🎷🎷🎷 ዛሬ ቀናችሁ ላይ ደጋግማችሁ ይህን አዋጅ በመናገር ሐሴት እያደረጋችሁ ዋሉ እኔ በጣም የተወደድኩ ነኝ ምንም ነገር ከክርስቶስ ፍቅር አይለየኝም በውስጤ ያለውን ደስታ ለሁሉ ሰው አካፍላለው በጣም በጣም ተወዳጅ ነኝ💃💃💃💃 @eccrm @eccrm @eccrm @eccrm

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ ኢያሱ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸ የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም። ⁹ በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፥ አይዞህ አትፍራ፥ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን? 👉ሕይወት የተለየ ምርጫ የላትም ክርስቶስ ነው ሕይወት። ይሕ ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት በውስጥህ ተቀምጧል ክርስቶስ በአንተ አማካኝነት ይህን ሕይወት #ፍቅሩን #ሰላሙን #ዕረፍቱን #ደስታውን መግለጥ ይፈልጋል። ይህ ነው የሁልግዜ የእግዚአብሔር ፈቃድ። ስለዚህ ይህን ሀሳብ በማሰላሰል ቀንህን አሳልፍ እጅግ ደስ የሚል ያማረ ቀን ይሆንልሀል። 👏ቀኑን ሙሉ በማሰላሰል ደጋግመህ ተናገራቸው 🎷እኔ በመንፈስ ቅዱስ የተሞላሁ ስለሆነ በውስጤ ደስታ አለ ፍቅር አለ ሰላም አለ ዕረፍት አለ። 👏👏👏👏👏👏 “ልብህ በኃጢአተኞች አይቅና፤ ነገር ግን ቀኑን ሙሉ እግዚአብሔርን በመፍራት ኑር፤” — ምሳሌ 23፥17

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ “ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ፥ እስከ እግዚአብሔርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ።” — ኤፌሶን 3፥18-19 ❤ የአንተ ከፍታህና ምርጡ እግዚአብሔር ነው። በመሆኑም የእግዚአብሔርን ፍቅር ብርሀን እውነት ውበት ተረድተህ በኑሮህ ስትገልፀው ዛሬ በዓለም ላይ እውነተኛ ደስታ ካላቸው ሰዎች መካከል አንዱ ትሆናለህ። - የእግዚአብሔርን ፍቅር ዕለት ዕለት ለመረዳት ትጋ - ፍቅሩን ተረድተህ ማረፍ ከቻልክ የምስጋና ሕይወት ይበዛልሀል።

#የማለዳ_የማሰላሰያ_ሀሳብ 🍎 ሕይወት በትርጉም የተሞላና የጣፈጠ የሚሆነው አካሄዳችን ከተፈጠርንበት ዓላማ ጋር በፅኑ የተስማማና የታረቀ እስከሆነ ድረስ ብቻ ነው። “እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።” — ኤፌሶን 2፥10 ራሳችንን እንፈትሽ በእግዚአብሔር መንገድ ነው ወይስ በራሴ መንገድ ነው አየሄድኩ ያለሁት? በእግዚአብሔር ሀሳብ ወይስ በራሴ ሀሳብ ነገሮችን እያደረኩ ነው? የእግዚአብሔርን ፈቃድ ወይስ የራሴን ፈቃድ እያደረኩ ነው። ለመለወጥ ዝግጁ በሆንበት ነገር ሁሉ ሕይወታችንን በጣም የሚጠቅም ለውጥ አለ። 🍇 የእያንዳንዱ ፍጥረት ሕይወት የሚቀናለትም ሆነ የሚሰምርለት ከተፈጠረበት ዓላማ ጋር ተስማምቶ እስከዘለቀ ድረስ ብቻ ነው።

#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_መነቃቃት_ሰሚናር * የለውጥ ሁሉ ለውጥ የአስተሳሰብ ለውጥ ነው። “የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። — ሮሜ 12፥2 #ሰሚናር_ጥር_8_ይጀምራል ሰዓት ከጠዋት 5:30 እስከ 7:00 ቦታ ጎተራ ዶንቦስኮ ቤተፀሎት ለመማር ስትመጡ መፅሐፍ ቅዱስ እና ማስታወሻ መያዧ ደብተር ይዘው ይምጡ። የመጀመሪያ ክፍል ርዕስ እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ፍቅር በተገለጠልን ልክ በፍቅሩ እየተደሰትን እንኖራለን። ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ብናውቅ ኑሮዋችን ሁሉ የአሸናፊነትና የደስታ ሕይወት ይሆናል። ለሕይወት እና ለእውነተኛ መንፈሳዊነት የሚያስፈልገውን ሁሉ የመለኮት ኃይል ሰጥቶናል። ( 2 ጴጥ 1:3)

ዉድ የካራዝማቲክ ቤተሰቦች የጌታ ፍቅር እና ሰላም ይብዛላችሁ እያልን ነገ ሳምንታዊ የእሁድ ፕሮግራም በፊሶን የመዝሙር ኮንሰርት ምክንያት የማይካሄድ መሆኑን እያሳወቅን የእንቅስቃሴው አባላት በሙሉ በዚህ የቤተክርስቲያን ፕሮግራም ላይ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንድትሆኑና ወጣቶችን እንድታበረታቱ እንጋብዛለን::

የተወደዳችሁ የካርዝማቲክ ቤተሰቦች የጌታ ፍቅር እና ሰላም ይብዛላችሁ እያልን የነገዉ ሳምንታዊ ፕሮግራም የማይካሄድ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን።

የተወደዳችሁ የካርዝማቲክ ቤተሰቦች የጌታ ፍቅር እና ሰላም ይብዛላችሁ እያልን የነገዉ ሳምንታዊ ፕሮግራም ከ9:00 ሰአት ጀምሮ በቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ACS አዳራሽ የሚካሄድ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን።