805
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
-130 дней
Архив постов
ይቅርታ
ይቅርታ ምንድን ነው?
#ይቅርታ ማለት ለአንድ የተፈጠረ ስህተት የሚደረግ ምህረት ማለት ነው። ይቅርታ ማድረግ ማለት ምህረት ማድረግ ማለት ሲሆን የተፈጠረን ነገር ተነጋግሮና ተማምኖ መፍታትና ከይቅርታ በኋላ ስህተቱን መርሳት ማለት ነው።
ይቅርታ እንዴት ይፈፀማል?
#ይቅርታ አብዛኛውን ጊዜ በሁለት(2) ግለሰቦች ወይም ቡድኖች መካከል የሚፈፀም ነገር ነው።
1ኛው -ይቅርታውን የሚጠይቀው ሲሆን
2ኛው -ይቅርታውን የሚቀበለው ናቸው።
⨳ይቅርባይ መሆን የአሸናፊነት ምልክት ነው። ጥፋትንም አምኖ ይቅርታ መጠየቅም ትልቅነት ነው።
⨳ሁልጊዜ ይቅር መባባል እንዳንዘነጋ እግዚአብሔር በቃሉ ይነግረናል።
ኤፌ 4:31-32
31-መራርነትና ንዴት ቁጣም ጩኸትም መሳደብም ሁሉ ከክፋት ሁሉ ጋር ከእናንተ ዘንድ ይወገድ።
32-እርስ በእርሳችሁም ቸሮችና ርኁሩኆች ሁኑ እግዚአብሔር ደግሞ በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ ይቅር ተባባሉ።
⨳እግዚአብሔር ሀጥያተኞች ሳለን ስለኛ ሀጥያት አንድያ ልጁን ወደ ምድር ልኮ ይቅር ብሎን ልጆቹ አድርጎናል። ያስተማረን ፍቅር ነው።ስለዚህ እኛም እግዚአብሔር እንዳስተማረን እርስ በእርሳችን ያለ አንዳች ቂም በውስጣችን ሳንይዝ(ሳናስቀር) ይቅር መባባል እና በንፁህ ፍቅር መዋደድ አለብን።
⨳ይቅርታና ፍቅር ተያያዥ ናቸው። በውስጣችን ቂም ይዘን ልንዋደድ አንችልም ምክንያቱም ለዛ ሰው ውስጣችን ጥሩ የሆነ ስሜት አይኖረንም። ከልብ የሆነ ፍቅር አይኖረንም።ግን ውስጣችን ያለውን ነገር እግዚአብሔር እንዳስተማረን በይቅርታ ያለ ምንም ቂም ካስወገድን ከልብ የሆነ ፍቅር ለዛ ሰው መስጠት እንችላለን።
#እግዚአብሔር እኛን ይቅር ሲለን ያለ አንዳች ቂም ነው።ከዛም ፍቅሩን በብዙ ሁኔታዎች በህይወታችን ይገልፅልናል። ሁሌም ፍቅሩ ይጨምራል እንጂ አይቀንስም።ስለዚህ ይቅርታ ለንፁህ ፍቅር አስፈላጊ ነው።ሰው ነን ጥፋት ይኖራል ከጎናችን ያሉ ሰዎችን ልናስከፋ እንችላለን ሌሎችም ሊያስከፉን ይችላሉ። ነገር ግን በይቅርታ በማለፍ በፍቅር መኖር አለብን።
ዮሐ 15:9
9-አብ እንደ ወደደኝ እኔ ደግሞ ወደድኋችሁ በፍቅሬ ነሩ።
እግዚአብሔር ይቅርባይ ነው
መልካም ቀን
#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_መነቃቃት
ወደ መንፈሳዊ መነቃቃት የሚያደርሱ መንገዶች
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
መንፈሳዊ መነቃቃት ለብዙ ክርስቲያኖች ከሁሉም የላቀ አስፈላጊ ነገር ነው። ዛሬ እንዴት እናገኘዋለን? በራሳችን ሕይወትም ሆነ በሌሎች ሰዎች እነኚህ የመነቃቂያ መንገዶች ምን ምን ናቸው።
መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስቀምጣቸው ሶስት ደረጃዎች እንመልከት።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
1 የመጀመሪያው ደረጃ መንፈሳዊ ድህነታችንን መቀበል ነው። ብዙ ግዜ መንፈሳዊ ጉድለታቸውን ለማየት እስኪሳናቸው ድረስ እንደታወሩት የሎዶቅያ ክርስቲያኖች እንመስላለን። “ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም የምትል ስለ ሆንህ፥ ጐስቋላና ምስኪንም ድሀም ዕውርም የተራቆትህም መሆንህን ስለማታውቅ፥”— ራእይ 3፥17
ያለንበትን መንፈሳዊ ሕይወት ልንገመግም ያስፈልጋል። ራሳችንን በተለያዩ መንፈሳዊ ልማዶች እየከለልን እግዚአብሔር ካስቀመጠልን የከበረ እና የተሻለ ሕይወት ልንጎድል አይገባንም። አንዳንድ ሰዎች ቤተክርስቲያን ስለሄዱ ብቻ ጥሩ መንፈሳዊ ሕይወት ያላቸው ይመስላቸዋል አንዳዶች ስለዘመሩ መንፈሳዊ እድገት መስሏቸው ይታለላሉ። ማገልገል መልካም ቢሆንም እንደ እግዚአብሔር ሃሳብ አለማገልገል ኪሳራ ነው። ስለዚህ ራሳችንን ቆም ብለን እንይ። እግዚአብሔር በሚፈልገው መንገድ ነው ወይ መንፈሳዊነቴ አገልግሎቴ?
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
2 ለመንፈሳዊ መነቃቃት ሁለተኛው ደረጃ መናዘዝ እና ንስሐ መግባት ነው። ኃጢአት እንደፈፀምን ልናውቅ እንችላለን ነገር ግን ስለዚያ ምንም አናደርግም ይሆናል። ነገር ግን ኃጢአታችንን በእርሱ ፊት መቀበል ብቻ ሳይሆን ከኃጢአታችን በመመለስ እና ለእርሱ ለመታዘዝ በመሻት ኃጢአታችንን በኑዛዜ እና ንስሐ በመግባት ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ማምጣት አለብን። ከመፅሐፍ ቅዱስ ታላላቅ የተስፋ ቃሎች አንዱ 1ኛ ዮሐንስ 1:9 ነው። “በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።”— 1ኛ ዮሐንስ 1፥9 ነብዩ ኢሳያስ የንስሐ አስፈላጊነት ያስረዳናል። “ክፉ ሰው መንገዱን በደለኛም አሳቡን ይተው፤ ወደ እግዚአብሔርም ይመለስ እርሱም ይምረዋል፥ ይቅርታውም ብዙ ነውና ወደ አምላካችን ይመለስ።” — ኢሳይያስ 55፥7
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
3 ሶስተኛው ደረጃ ባንተ በኩል የእግዚአብሔር ፈቃድ ለመሻትና ለመፈፀም ቃልኪዳኑን ማደስ ነው ። ስለ ኃጢአታችን ልንወቀስ ልንፀልይ እና ኃጢአታችንን ልንናዘዝ ንስሐ ልንገባ እንችላለን ዳሩ ግን እውነተኛ መለኪያው ለመታዘዝ ፈቃደኛ መሆናችን ነው። ሁልግዜም እውነተኛ መነቃቃት ለፅድቅ የሚኖረንን አዲስ ረሀብ መፍጠሩ ነው። በመንፈስ ቅዱስ የተዳሰሰ ሕይወት ኃጢአት ሊታገስ አይችልም። ይህ ሕይወት ረሃቡም ጥማቱም መንፈሱ እና ቃሉ ነው። እዚህ ሕይወት ውስጥ እውነተኛ ደስታና ሀሴት አለ።
“እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።”— ዕብራውያን 12፥1-2
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ጎዶሎ ለብ ያለና ለክርስቶስ እና ለሌሎች ፍቅር የሌለው የክርስትና ሕይወት እየመራህ ይሆን? መንፈሰ ቅዱስ ኃጢአትህን በመናዘዝ እና ፊቱን በመሻት ወደ እግዚአብሔር እንድትመጣ ይርዳህ። ራስህን ለእርሱ በመስጠት ይዳስስህ ይፈውስህ። ዛሬ በዓለም እጅግ የሚፈለገው ነገር ሙሉ ለሙሉ በመንፈስ ቅዱስ በመነቃቃት ራሳቸውን የሰጡ ክርስቲያኖች ማግኘት ነው። አንተም ከእነዚህ አንዱ ለመሆን ያብቃህ። ንቃ እድሉ አለህ።
ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ መነቃቃት ሰሚናር እንድትወስድ እንጋብዝሀለን።
#ሰሚናር_እንዲማር_ለሚጋብዙት_አንድ_ሰው_ሼር_ያድርጉት_እርሶም_ይባረኩበታል።
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
እንኳን ደስ ያላችሁ አዲሶቹ ሰሚናር የወሰዱ እግዚአብሔር የመረጣቸው የጌድዮን ሰራዊት። እግዚአብሔር ለወንጌሉ ስራ መርጦአችዋል እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ነው።
#2013_ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_ሴሚናር
2013 ሶስተኛ ዙር ሰሚናር
ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ተከታታይ የመፅሐፍ ቅዱስ ትምህርት ብዙ ሰዎችን በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ላይ ለውጥ ያመጡበት ትምህርት ሲሆን ይህ ትምህርት በቀላሉ ምዕመናን እንዲረዱት ተደርጎ የተዘጋጀ በመሆኑ በምዕመናን ሕይወት ትልቅ ለውጥ ማምጣት መቻሉን አረጋግጠናል ።
🙏 “ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ ሆሴዕ (4:6) በእርግጥም ዕውቀት አንድን ነገር ማድረግ የምንችልበትን አቅም የሚሰጠን ልዩ ስጦታ ነው። ለዚህም ነው እግዚአብሔር እንዳንጠፋ ቃሉን የሰጠን በክርስትና ሕይወት ፋሬያማ እና አስደሳች ሕይወት መኖር የምንፈልግ ከሆነ የግድ የእግዚአብሔር ቃል በግል ያስፈልገናል። ያለበለዚያ ቤተ/ያን ከመመላለስ ውጪ ለውጥ ባለው የእድገት እና የእርካታ ሕይወት መኖር አንችልም።
🙏 “የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።”
— ሮሜ 12፥2
ስለ ሕይወት ተረድተን በተሰጠን ሕይወት በሙሉ አቅማችን መመላለስ የምንችለው ጤናማና ትክክለኛ እይታ በልባችን ሲኖረን ነው። ይህንን ዕይታ የምናገኘው #በአእምሮ መታደስ መለወጥ ስንችል ነው። ስለዚህ አእምሮአችንን በማደስ ልባችንን መለወጥ ወደሚችለው ወደ እግዚአብሔር ቃል ልንቀርብ ይገባናል። ይህን ማድረግ ከቻልን በሕይወታችን ላይ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲከናወን እና ለቃሉ ተገዝተን ትዕዛዙን ጠብቀን መኖር የምንችልበትን አቅም እናገኛለን።
ለዚህ ነው #በአእምሮ መታደስ የሚያስፈልገን።
“አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።”
— ዮሐንስ 14፥26
🙏 በመንፈስ ቅዱስ ያልተመራ ሕይወት ሁልግዜ በስጋ ወይም በዓለም ነገር መመራቱ የማይቀር ጉዳይ ነው። ይህ ደግሞ የአብዛኛው ክርስቲያን ችግር ነው። ክርስቲያን በዳግም ውልደት መንፈስ ቅዱስ ይቀበላል። ነገር ግን በመቀበል ብቻ ሳይሆን በመኖር ነው #ከመንፈስ_ቅዱስ የሚገኘው ጥቅም በሕይወታችን የሚገለጠው። ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ቢኖርም እንዲሰራ ማድረግ እና ማቀጣጠል ወሳኝ እና አስፈላጊ ነገር ነው። መንፈስ ቅዱስ እንዲሰራ የሚያደርገው ዋና ነገር ቃሉ ነው። ስለዚህ ቃሉን በመጠቀም በመንፈስ የሚመራ ሕይወት ለመኖር ራሳችንን ለመንፈስ ቅዱስ ምሪት ለማስገዛት ፈቃደኛ ልንሆን ይገባል። ሻይ ውስጥ የከተታችሁት ስኳር አማስላችሁ ካልጠጣችሁት ስኳሩ ስለገባ ብቻ እንደማያጣፍጠው ሁሉ በውስጣችን የተቀመጠው መንፈስ ቅዱስ እንዲሰራ ካልፈቀድንለት የጣፈጠ አስደሳች የክርስትና ሕይወት ሊኖረን አይችልም።
ሰሚናሩ የሚሰጥበት ቦታ : ጎተራ ደንቦስጎ ቤተ ፀሎት ከጠዋቱ 5:30 እስከ 7:00
የሚጀምርበት ቀን ግንቦት 22 ዘወትር እሁድ
በነዚህ ስልክ ቁጥሮች መመዝገብ ይችላሉ
ሰላም 0910056879
ሳሮን 0934441751
ታምራት 0916101102
ለመማር ሲመጡ መፅሐፍ ቅዱስ እና ማስታወሻ ደብተር መያዝ አለቦት።
ማስታወቂያ
1 የአባላት ፎርም ለመሙላት ወስዳችሁ ያልመለሳችሁ ነገ እሁድ ግንቦት 15 የመጨረሻ ቀን ስለሆነ እንድትመልሱ እናሳስባለን።
2 ወርሃዊ የፍቅር ስጦታችሁን ይዛችሁ እንድትመጡ ከወዲሁ እናሳስባለን።
2ኛ ቆሮ 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ይህንም እላለሁ፦ በጥቂት የሚዘራ በጥቂት ደግሞ ያጭዳል፥ በበረከትም የሚዘራ በበረከት ደግሞ ያጭዳል።
⁷ እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም።
#ለመንፈስ_ቅዱስ_ሙላት
እምነት
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
አሁን መንፈስ ቅዱስ ለመሞላት ሌላኛው ዋና ነገር ላይ እናተኩራለን። በመጀመሪያ ደረጃ ስለ መንፈስ ቅዱስ መረዳት ራሳችንን ለአሰራሩ በማስገዛት ራሳችንን አሳልፈን ሙሉ በሙሉ መስጠት ቀጥሎ ቃሉ ያለውን ሁሉ አምነን #የእምነት_እርምጃ_መውሰድ_አለብን።
“እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው።”
— ዕብራውያን 11፥1
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ጥርጣሬ ያለንን እጃችን የገባን ነገር እንኳን የሚነጥቀን ክፉ በሽታ ነው። እምነት ደግሞ እጃችን እንኳን ባልገባ ነገር የሚያሳርፈን ታላቅ ኃይል ነው። ስለዚህ ቃሉ እንደሚለው ተቀብያለው ብለን አምነን በመንፈስ ቅዱሰ ኃይል ማድረግ የምንፈልገውን ማንኛውም ነገር በእምነት ማድረግ መጀመር አለብን።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ለእግዚአብሔርና ለፈቃዱ ለመገዛት ራሳችንን መስጠት ስንችል በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተናል ማለት ነው። መንፈስ ቅዱስ ይቆጣጠረናል ይገዛናል ማለት ነው። አሁን በዚህ እውነት ልንሰራና እግዚአብሔር በመንፈሱ እንደሞላንና በእርሱ ቁጥጥር ስር እንዳለን ሙሉ በሙሉ እርግጠኞች ሆነን በእምነት በመመላለስ እርምጃ መውሰድ አለብን።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
በክርስትና የተደረጉልን ነገሮች ሁሉ የተቀበልነው አምነን ብቻ ነው። ቶማስ የክርስቶስን ትንሳኤ ካላየው አላምንም ሲል ኢየሱስ ተገልጦ አይቶ አምኖአል። ግን ጌታ እንዲህ አለ #ሳያዩ_የሚያምኑ_ብፁዓን_ናቸው። ስለዚህ እምነት ማየት ሳይሆን ቃሉን ማመን ነው። ቃሉ ተባርከኻል ካለህ አሜን ማለት ነው። ፀድቀሀል ካለህ አሜን ማለት ነው። ተሞልተሀል ካለህ አሜን ማለት ነው። ስለዚህ በእምነት መንፈስ ቅዱስ መሞላታችንን አውቀን ነገሮቻችን ላይ በሙሉ Action መውሰድ አለብን። እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ አምላክን እንደተሸከመች እንደፀነሰች በእምነት እንደቃልህ ይሁንልኝ ብላ ነው ያረጋገጠችው። በመጨረሻም አምላክን የወለደችው። እኛም እንደቃሉ እንደሚሆን እንመን እና እንቀበል።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
#በመንፈስ_ቅዱስ_መሞላት_የስሜት_ሳይሆን_የእምነት_ጉዳይ_መሆኑን_ማስተዋል_አለብን። በምንሞላበት ግዜ ወደ እግዚአብሔር የበለጠ እንደቀረብን ሊሰማንም ላይሰማንም ይችላል። ስለሆነም በስሜታችን ከመታመን ይልቅ በእግዚአብሔር የተስፍ ቃሎች ላይ መደገፍ እና መታመን ይሻላል። ስለዚህ እንደተደረገልን ቆጥረን ማመስገን የእኛ ድርሻ ነው።
ጌታ ሆይ ሁሉን ስላደረክልን እጅግ አድርገን እናመሰግንሀለን። አሁንም በመንፈስህ ዕለት ዕለት መሞላት ይሁንልን በኢየሱስ ስም!!!!
#የተባረከ_ቀን!!!
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#ለመንፈስ_ቅዱስ_ሙላት
መገዛት
በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት ሂደት ውስጥ ሌላኛው መገዛት ነው። መገዛት ማለት የራሳችንን መንገድ ትተን በሕይወት ጉዞአችን ሁሉ ከሁሉ በላይ ክርስቶስን እንዲመራን እና እንዲገዛን ራሳችንን መስጠት ነው። የክርስቲያን ፈተና ከክርስቶስ ይልቅ ራሳችንን በሕይወት ዙፍን ላይ ማስቀመጣችን ነው። በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት በክርስቶስ ቁጥጥር ስር ለመሆንና በእርሱ ለመገዛት እኔነትን አውርደን ጥለን ክርስቶስን በሕይወታችን ዙፍን ላይ ቀዳሚ አድርጎ ማስቀመጥ ነው። ይህም የሚሆነው ለእርሱ ስንገዛና የሕይወታችን ጌታ እንዲሆን ስንፈቅድለት ነው።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ይህ ራሳችንን ለክርስቶስ የማስገዛቱ እና የማስረከቡ ሂደት በሮሜ 6 ውስጥ በግልፅ ተብራርቷል። በዚህ ምንባብ ውስጥ ጳውሎስ ከዚህ ቀደም ኃጢአት በሕይወታችን ውስጥ ስለገዛበት ሁኔታ ይናገራል። አሁን ግን እኛ የክርስቶስ ነን ከእንግዲህ የምንኖረው ለአሮጌው ገዢያችን ኃጢአት ሳይሆን ለአዲሱ ገዢአችን ለኢየሱስ ሊሆን ይገባል። ስለዚህ ራሳችንን ልናስገዛ ይገባናል።
ሮሜ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ብልቶቻችሁንም የዓመፃ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለኃጢአት አታቅርቡ፥ ነገር ግን ከሙታን ተለይታችሁ በሕይወት እንደምትኖሩ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አቅርቡ፥ ብልቶቻችሁንም የጽድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ።
¹⁴ ኃጢአት አይገዛችሁምና፤ ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች አይደላችሁምና።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
እግዚአብሔር ይመስገን ገዢአችንን ለውጠናል በጥንት ዘመን በመጀመሪያ ምዕተ-ዓመት ባሪያ እንደሚሸጥ እና የገዢው ንብረት እንደሚሆን እኛም በክርስቶስ ደም ተገዝተን አሁን የእግዚአብሔር ንብረት ሆነናል። “ ከኃጢአትም አርነት ወጥታችሁ ለጽድቅ ስለ ተገዛችሁ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።” — ሮሜ 6፥-18
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ራሳችንን ክርስቶስ እንዲገዛን በምንፈቅድበት ግዜ እንዲሁ ቁጭ ብለን እግዚአብሔር የፈቀደው ይሁን የምንል ሳይሆን ይልቁንም ጌታ ሆይ ልትጠቀምብኝ በምትፈልገው በማንኛውም መንገድ እንድትጠቀምብኝ ላንተ የተሰጠው ንብረትህ ነኝ በእጅህ ውስጥ ነኝና የምትፈልገውን ሁሉ አድርግ። ለሕይወቴ ያንተን ፈቃድ እንጂ የራሴን ፈቃድ አቁሜአለው ልንል ይገባል።
ከእኔነት ከራስ ፈቃድ የራስ መሻት ተላቀን ለክርስቶስ ተገዝተን መኖር እንድንችል ጌታ ፀጋውን ያብዛልን። የተባረከ ቀን!!!
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#መንፈስ_ቅዱስ_እንዴት_እንሞላለን
1 መጠማት እና መፈለግ
ዮሐንስ 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁷ ከበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢየሱስ ቆሞ፦ ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ።
³⁸ በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ብሎ ጮኸ።
³⁹ ይህን ግን በእርሱ የሚያምኑ ሊቀበሉት ስላላቸው ስለ መንፈስ ተናገረ፤ ኢየሱስ ገና ስላልከበረ መንፈስ ገና አልወረደም ነበርና።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ለመኖር የመጀመሪያው እና ዋናው ጉዳይ መጠማት ነው። ያልጠማው ሰው ለመጠጣት ዝግጁ አይሆንም። የእግዚአብሔር መንግስት ዋናው የመቀበያ መንገድ መዘጋጀት ነው። የልብ መዘጋጀት ከሰው ነው። ምሳሌ 16:1 ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን ሊሰራ ላለው ነገር ዝግጁ ነን ወይ? በርግጥ የመንፈስ ቅዱስን ማንነት ያልተረዳ ሰው ሊጠማም አይችልም ለዚህም ነው ብዙ ሰዎች ምንም የማይመስላቸው። የመንፈስ ቅዱስን ኃይል የቀመሰ ሰው ግን ሁልግዜ ጥማት አለው ሁልግዜ ይፈልጋል ምክንያቱም የቀመሰውን ስለሚያውቅ። አንድ እናቴ ሁልግዜ የሚፀልዩት ፀሎት ትዝ አለኝ ያልቀመሰ ይቅመስህ የሚል አስገራሚ ፀሎት። እውነት ነው ስለ መንፈስ ቅዱስን ከመማር በላይ በመቅመስ የሚታወቅ ታላቅ እና አስደናቂ የእግዚአብሔር ኃይል ነው።
2 የንስሐ ሕይወት
“ጴጥሮስም፦ ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።”
— ሐዋርያት 2፥38
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ሌላው ዋና ነገር መንፈስ ቅዱስ ለመሞላት ንስሐ መግባት ነው። ንስሐ ዋናው የክርስትና ቁልፍ ሆኖ ሳለ ብዙ ክርስቲያን የንስሐ ሕይወት የለውም። ነገር ግን ንስሐ ሕይወታችንን የምንቀይርበት ታላቅ ምስጢር ነው። ንስሐ እግዚአብሔር የማይከብርበትን ሕይወታችን ላይ ያለ ማንኛውም ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የማይስማማ ነገር የምናስወግድበት ሂደት ነው። ንስሐ የሚያደርግ ሰው ሁልግዜ መንፈስ ቅዱስ በሕይወቱ እንዲሰራ በር ይከፍትለታል። ንስሐ ባዶ መሆን ወይም መንፃት ልንለውም እንችላለን ስለዚህ በንስሐ ነፅተን መንፈስ ቅዱስ ቦታ እንዲያገኝ የንስሐ ሕይወት ሊኖረን ይገባል።
3 በእግዚአብሔር ፊት ሞኝ መሆን
“ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን እንዲያሳፍር የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ፤ ብርቱንም ነገር እንዲያሳፍር እግዚአብሔር የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ፤”— 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥27
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ሌላው ለመንፈስ ቅዱስ ሙላት በጣም አስፈላጊ ነገር በእግዚአብሔር ፊት ይዘነው የምንመጣው ሞኝነት እና ደካማ መሆናችንን መረዳት ነው። በጣም ብዙ ሰው ይህን ሀሳብ ባለመረዳቱ ከመንፈሰ ቅዱስ ስጦታ ይጎድላል። አንድ ጥሩ ግለፅ የሚያደርግልን ምሳሌ እንይ። ዋና መዋኘት መልመድ የሚፈልግ ሰው የሚከተለው አካሄድ አለ። ዋና በእውቀት ብቻ አይለመድም ግዴታ ዉሀ ገንዳ ውስጥ ገብተን መለማመድ አለብን። አንዳንድ ሰዎች ስለ መንፈስ ቅዱስ እውቀቱ ቢኖራቸውም እራሳቸውን በሞኝነት ለመንፈስ ቅዱስ አሰራር መስጠት አይፈልጉም ይሄ ማለት ደግሞ ዳር ላይ ቆሞ የዋና ውሀ ውስጥ ያለውን አስደሳች ነገር እያወቁ በሌላው መደሰት መጎምዠት ብቻ ይሆናል።
ሌላኛው የዋና ላይ ምስጢር ውሀ ውስጥ ገብቶ ሰውነትን ለቀቅ አድርጎ ለውሀው ራስን መስጨት ነው። ይሄ ካልሆነ ግን የበለጠ ችግር ነው በመስጠምም መጎዳት ስላለ። በመንፈስ ቅዱስ ለመሞላት እና በስጦታዎቹ ለመጠቀም በሞኝነት ሁሉነገራችንን አሳልፈን መስጠት አለብን። እንዴት እና ለምን አያስፈልገውም። የዓለም ጥበበኞች የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን በመንፈስ ቅዱስ መፀነስ አሁንም ድረስ አይረዱትም። ስለዚህ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ተስማምታችሁ መኖር ከፈለጋችሁ ቃሉ የሚመክራችሁ በፊቱ ሞኝ ሁኑ ብሎ ነው። በክርስቶስ ያገኛችሁትን ስልጣን መጠቀም ከፈለጋችሁ ደግሜ እላለው ሞኝ ሁኑ ቃሉን አጥኑ ቃሉን ማድረግ ተለማመዱ የንስሐ ሕይወት ይኑራችሁ ይህ ከሆነ ሙላቱ በሕይወታችሁ ይገለጣል። ተባረኩ!!!
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#የመንፈስ_ቅዱስ_ሙላት
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ክርስቲያኖች ሁሉ #በመንፈስ እንዲሞሉ የእግዚአብሔር ቃል ይነግረናል። #የመንፈስ ሙላት የጎደለበት ሕይወት ማለት እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ ክርስቲያን ከሰጠው ትልቅ በረከትና የሕይወት ዓላማ ጎድሎ መኖር ማለት ነው።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
መፅሐፍ ቅዱስ ስለ #መንፈስ ሙላት ሲናገር ምን ማለቱ ነው? አሰኪ መጀመሪያ #የመንፈስ ሙላት ፍቺ እንመልከት። በመንፈሰ መሞላት ማለት #በመንፈሰ_ቅዱስ ሕልውናና ኃይል ቁጥጥር ስር መሆን ማለት ነው። ጳውሎስ በኤፌሶን 5:18 ላይ መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና ይላል። በዚህ ክፍል በሁለት ነገሮች መካከል ተቃራኒ ሀሳቦችን ያስቀምጣል። ለምሳሌ በአልኮል የተሞላ ሰው በአልኮል ቁጥጥር ወይም አገዛዝ ስር ይውላል። የአልኮሉ ሕልውና እና ኃይል ተፈጥሮአዊ ኃይሉንና ተግባሩን ይገዛዋል። ስለዚህ እርሱ የፈለገውን ሳይሆን ለአልኮሉ ፈቃድ ይገዛል።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ልክ እንደአልኮሉ ሁሉ በመንፈስም የመሞላት ትርጉም እንደዚሁ ዓይነት ነው። እኛ #በመንፈስ_ቅዱስ ቁጥጥር ስር ለመሆን በመንፈስ ልንሞላ ያስፈልጋል። በመንፈስ ቁጥጥር ስር መሆናችን መገለጫው ደግሞ ነገሮችን በራሳችን ማድረግ አቁመን እርሱ በሚሰጠን ኃይል እና ፈቃድ እናከናውናለን ማለት ነው። የእርሱ ፈቃድ ደግሞ ሁልግዜም መልካም እና እጅግ ሰላም የሚሰጥ በእረፍት የታጀበ የሚያረጋጋና አስደናቂ ነው። ስለዚህ #በመንፈስ_ቅዱስ ህልውና ውስጥ ለመኖር ራሳችንን በፈቃዳችን ለጌታ አሳልፈን በመስጠት በህልውናው ውስጥ ልንኖር ይገባናል።
ይህን ሙላት የተቀበለ ሰው
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
- የፅድቅ ሕይወት ምርጫው ያደርጋል
- የእግዚአብሔርን ቃል መገለጥ ያገኛል
- የፀሎት ሕይወቱ ይበረታል
- ደስታቸው የዓለም ነገር ሳይሆን የሰማይ ክብር ይሆናል
- ወንጌልን በድፍረት ይመሰክራሉ
- ትእዛዙን ለመፈፀም ንቁ ናቸው
- ከሀጢአት ለመራቅ ቁርጥ ፈቃድ ያደርጋሉ።
- የእግዚአብሔርን ቃል ያጠናሉ ያደርጉታልም
- ሰላማቸው ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች ይተርፍል
- መልካም ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ናቸው
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
እነዚህ ሁሉ በረከቶች #ከመንፈስ ሙላት ይገኛሉ ስለዚህ የቱ ጋር እንዳለን ራሳችንን እንጠይቅ እግዚአብሔር መልካም አባት ስለሆነ ሁልግዜ ሊሞላን ዝግጁ ነው እኛ ለሞላት ዝግጁ ነን ?
በመንፈስ ለመሞላት ከኛ ምን ይጠበቃል?
ቀጣይ ክፍል እናየዋለን።
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
የተወደዳችሁ የካርዝማቲክ ቤተሰቦች ነገ እሁድ ግንቦት 8 ሳምንታዊ የከሰአት ፕሮግራማችን እንደማይኖር እናሳውቃለን።
የእግዚአብሔር ሰላም ይብዛላችሁ።
ክፍል 5
ከእናታችን ከማርያም ጽናትን እንማር
ዮሐ 19:25
25-ጭፍሮችም እንዲህ አደረጉ።ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ የእናቱም እህት የቀለዮጵም ሚስት ማርያም መቅደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር።
⨳እናታችን ማርያም በመታገሳ ትንሳኤን አይታለች።
⨳ያን ሁሉ የልጅዋን ስቃይ እያየች በትግስት ለማለፏ ዋናው ነገር ያላት እምነት እና ፅናት ነው።በዚህም ምክንያት እግዚአብሔር በፀጋው ሀይል እረድቷታል።
⨳አንድ እናት ልጇ ሲገረፍ ,ሲደማ ,ቆስሎ መስቀል ተሸክሞ ሲወድቅ ,ሲደክም ማየት ጭራሽ ሊሰቀል ወደ ሞት እንደሚሄድ እያወቀች በትግስት መከተል ከባድ ነው።ነገር ግን በእግዚአብሔር ሲታመን እግዚአብሔር የሚታለፍበትን ሀይል ይሰጣል። ይህንንም በእናታችን ማርያም አይተናል።
⨳እንደ አለማዊ እናት ልጇ እንኳን ያን ያህል አይደለም ትንሽ ነገር ሲደርስበት ማየት አትፈልግም። ነገር ግን እግዚአብሔር ነገሮችን ሁሉ ለበጎ እና ለአላማ እንደሚያደርግ ማመን መቻል ችግሮችን በጽናት ማለፍ እንድንችል ያደርገናል።ይህን ከተረዳን ደግሞ ምንም ያህል ችግር ቢመጣ በችግሩ ከማማረር ይልቅ በትግስት መወጣትን እንለምዳለን።የልጅን ስቃይ ማየት ከዛም ሞትን ማየት እና ሬሳን ከመታቀፍ የበለጠ ህመም የለም።ነገር ግን እናታችን ይህን ሁሉ በእግዚአብሔር ፀጋ በጽናት ተወታ ትንሳኤን አይታለች።
#እኛስ በህይወታችን የሚፈጠሩ የተለያዩ ችግሮችን ምን ያህል በጽናት እናልፋለን?
#በህይወታችን ችግር ሲፈጠር እናማርራለን ወይስ እናመሰግናለን?
#ከእግዚአብሔር እንርቃለን ወይስ ወደ እርሱ በእምነት እንቀርባለን?
⨳እናታችን ማርያም ያስተማረችን በነገሮች ሁሉ ፈተና ሲገጥመን በትግስት ማለፍን ነው።በዚህ ሰአት እግዚአብሔርን በማመን በምናገኘው የእግዚአብሔር ፀጋ ችግሮቻችንን በማለፍ ድል እናደርጋለን።
⨳ለሀገራችንም በምናየው ነገር ተስፋ ሳንቆርጥ ,አብቅቶላታል ,አይለወጥም ፀለይን ግን ፀሎታችን አልተሰማም ሳንል ሳንሰለች በጽናት እንፀልይ የምንችለውን እናድርግ ሁሉም ነገር በጊዜ ይለወጣል መልካም ይሆናል። ለሀገራችንም ትንሳኤ ይሆናል።ደስታ ,ፍቅር ,ሰላም ,አብሮነት ,መተሳሰብ ...ይመጣል።እናታችን ማርያም በአማላጅነቷ ታማልደናለች።
ክፍል 4
ከእናታችን ከማርያም እምነትን እንማር
ሉቃ 1:38
38-ማርያምም እነሆኝ የጌታ ባርያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ አለች።መልአኩም ከእርስዎ ሄደ።
⨳በዚህ ክፍል የማርያምን እምነት እናያለን።እምነቷን ስናይ "እነሆም ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ ስሙንም ለኢየሱስ ትይዋለሽ።" ብሎ ሲያበስራት ቃሉን ሳትጠራጠር በእምነት ተቀብላለች።በሳይንሳዊ መንገድ ስናየው ለማመን ማይቻል ከዛም በላይ በተፈጥሮአዊ ህግም መሰረት ማይመስል ነገር ነው።ማርያም ግን ቃሉን በማመኗ ለአለም መዳን ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጋለች መድሀኒት የሆነ ልጅ ወልዳለች።
⨳እምነት ማለት እንዲሁ እግዚአብሔርን መጠበቅ(ማመን) ነው እንጂ በመጠራጠር ወይም ከሳይንሳዊ መንገድ ጋር ከአስተያየነው አይሰራም።በሳይንስ የማይፈቱ ቋጠሮች ሁሉ በእምነት ይፈታሉ።
#እኛስ እምነታችን የቱ ጋር ነው?
#ፀሎት ስናረግ ምን ያህል አምነን ነው ወየስ በልምድ?
#ቅዱስ ቁርባን ስንቀበል አምነን ነው ወይስ በልምድ?
#ቃሉን ስናነብ እና ስንሰማ ምን ያህል አምነን ነው?
⨳እግዚአብሔር በእኛ ውስጥ ለመስራት እምነታችንን ይፈልጋል።እኛ እግዚአብሔር እንዲሰራብን ምን ያህል ዝግጁዎች ነን።የእግዚአብሔርን ስራ ለመስራት ከራሳችን አልፎ እንደ ማርያም ለሌሎች የእግዚአብሔር ሀሳብ በእኛ እንዲፈፀም በእምነታችን ጠንካራ መሆን አለብን።በእምነታችን ስንጠነክር እግዚአብሔር እግዚአብሔር በእኛ ይከብራል ታምርም ያደርጋል።
