አግዛቸው ተፈራ
Открыть в Telegram
"አምላኬ ሆይ፥ በፊትህ የምንለምን ስለ ብዙ ምሕረትህ ነው እንጂ ስለ ጽድቃችን አይደለምና ጆሮህን አዘንብለህ ስማ፤ ዐይንህን ገልጠህ ጥፋታችን... ተመልከት።" (ዳን. 9፥18)
Больше984
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
984
ዘወረደ ብለን ሳምንቱን ሰይመን፣
ጌታን ለመዘከር ከሰማይ መውረዱን፣
በቃሉ 'ሚያድነው ባይሁድ መሰቀሉን፣
ዐውጀን ሰብከነው ዘምረን ተቀኝተን፣
እንዳለነው አለን።
በልባችን ስፍራ አላገኘም ቦታ፤
እኛን ለመፈለግ የወረደው ጌታ፤
መውረዱን ስንዘክር ለብዙ ዓመታት፣
ልባችን ተወርሯል በብዙ አማልክት።
ወገኖች ሆይ ንቁ!
ቦታውን የያዙት በቶሎ ይልቀቁ፤
ተከፍቶለት ይግባ የልቡናችን በር
የወረደው ከላይ በውስጣችን ይደር።
(ከዚህ ቀደም የተለጠፈ)
984
ባለፈው የካቲት 2 ቀን 2016 ዓ.ም. ተመርቆ ለንባብ የበቃው የወንድማችን የወንድወሰን ገብረ ትንሣኤን የሕይወት ታሪክ የያዘው “ሠዓሊው ደቀ መዝሙር” መጽሐፍ በሥርጭት ላይ ይገኛል። አንብባችኹ ብዙ የምታተርፉበት ግሩም መጽሐፍ ነው።
መጽሐፉን በሚከተሉት አድራሻዎች ማግኘት ትችላላችኹ፦
መገናኛ መተባበር ሕንጻ ላይ፦ 092 769 7055
እንዲሁም ሣር ቤት ኢገስት 0911 62 76 80 ያገኙታል።
984
ከአንድ መሪጌታ ጋር በወንጌል ዙሪያ እየተነጋገርን ሳለ፣ ንግግራችን አዳኝ ክርስቶስ ነው እና ቅዱሳንም ያድኑናል በሚሉ የወንጌልና የገድላትና የድርሳናት ትምህርት ላይ ማጠንጠን ቀጠለ። በዚህ ጊዜ ከመልክአ ሥላሴ የሚከተለውን ጠቀስኹለት።
"ሰላም ለጕርኤከሙ ስቴ አንብዐ ደም ዘኢኀሠሠ
ብዑላነ ሞገስ ሥላሴ ኢታንድዩኒ ሞገሰ
እመ ትትኄየዩኒሰ ወተኀድጉኒ ጽኑሰ
ሚካኤልኑ ለአምጽኦ ሥጋየ ጌሠ
ወእመ አኮ ገብርኤል ወሀበኒ ነፍሰ።
ትርጉም፦ የደም እንባ መጠጥን ለማይሻ ጕረሮአችኹ ሰላምታ አቀርባለኹ።
በሞገስ ባለጠጋ የኾናችኹ ሥላሴ የሞገስ ድኻ አታድርጉኝ።
እንደ ተቸገርኹ ብትተዉኝና ቸል ብትሉኝ
ሚካኤል ገሥግሦ ሥጋዬን ለማስገኘት ይኾንለታልን?
ገብርኤልስ ነፍስን ይሰጠኛልን?"
በዚህ ላይ ተመሥርቼ አዳኝ እግዚአብሔር ብቻ መኾኑን፣ በፍጡር መልአክም ኾነ ሰው መዳን እንደማይገኝ ሳብራራለት ምን ቢለኝ ጥሩ ነው፦ 'የመልክአ ሥላሴ ደራሲ እኮ መናፍቅ ነው ይባላል።'
እኔም ታዲያ መናፍቅ ከኾነ ድርሰቱን ለምን ትጠቀሙበታላችኹ? ይህ የመልክእ ቀለም ሚካኤልና ገብርኤልን ስለሚጠቅስ የሚካኤልና የገብርኤል በዓል ዕለት በየወሩ ለምን ይባላል? አልኹት። ርሱም ሥርዐቱ የቈየ ስለ ኾነ ይባላል እንጂ ሰውዬውስ መናፍቅ ነው በማለቱ ጸና።
ማስተዋል ቢቻል በየወሩ ለሚካኤልና ለገብርኤል በተመደቡት ኹለት ቀናት "[ሥላሴ] እንደ ተቸገርኹ ብትተዉኝና ቸል ብትሉኝ ሚካኤል ገሥግሦ ሥጋዬን ለማስገኘት ይኾንለታልን?
ገብርኤልስ ነፍስን ይሰጠኛልን?" ይባላል።
ስንቱ ሰው ይህን አስተውሎ በመላእክት ከመማፀንና ከመላእክት አምልኮ በመውጣት ሕይወትን ወደሚሰጥና የሞገስ ባለጠጋ ወደ ኾነው እግዚአብሔር "ሞገሳችን፣ ክብራችን፣ በርሱ የምንጠጋበት የመድኀኒታችን ቀንድ፣ የማእዘን ራስ የሕይወት ደንጊያ" (ሞገስነ ወክብርነ ቀርነ መድኀኒትነ በዘቦቱ ናሰምክ ዕብነ ሕይወት ወርእሰ ማእዘንት ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ- ከመጽሐፈ ሰዓታት እውነተኛ ገጽታ የተወሰደ) በኾነው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የመቅረብን እውነት ይረዳ ይኾን?
(የዛሬ ፭ ዓመት ተለጥፎ የነበረ)
984
በመከራ ውስጥ ያሉትን ማጽናናት በጣም ከባድ ነው። ምናልባት እናጽናናለን ብለን ኼደን በቍሳለቸው ውስጥ ዕንጨት ሰድደን እንመለስ ይኾናል። ታዲያ የእኩይ ... ማነው "የእከይ እና የሥቃይ ጣጣ" ለዚህ ጥሩ መፍትሒ ነው።
ብዙ ሰዎች እከይና ሥቃይ ባመጡባቸው ጣጣ ለብዙ እንግልትና መከራ፣ ለተስፋ መቍረጥም ተዳርገው፥ ራሳቸውን ከቆሙት በታች፣ ከሞቱት በላይ አድርገው እየቈጠሩ፣ ከእግዜርም ተኳርፈው ይገኛሉ። “የእከይ እና የሥቃይ ጣጣ” መልስ ለሌላቸውና መልስ ዐጥተው በመልስ ማጣት ውስጥ ግን ምላሽ ያገኙ ሰዎችን ተመክሮ፣ ርእሰ ጕዳዩን የሚያብራሩ ፍልስፍናዎችን በእግዚአብሔር ቃል ሚዛን ላይ በማስቀመጥ የሚመረምር ምርጥ መጽሐፍ ነው።
ዛሬ በምድራችን የሞላውንና ጤናማው ወንጌል ኰስሶ እንዲታይ ያደረገውን መስቀል አልቦና ተድላንና ደስታን ብቻ በተስፋ እያስኰመመ የሚገኘውን፥ በኋላም ብዙዎችን ለተስፋ መቍረጥ የብልጥግና ወንጌል በእግዚአብሔር ቃል መዶሻ እየቀጠቀጠ ልክ ያገባዋል። የእከይንና የሥቃይን ጣጣ ብቻ ሳይኾን፥ ክብሩ ሲገለጥ ደግሞ ሐሤት እያደረግን ደስ እንዲለን፥ በክርስቶስ መከራ በምንካፈልበት ልክ ደስ እንዲለን (1ጴጥ. 4፥13) ከመስቀሉ ወደልተፋታው የወንጌል መሠረት እንድንመለስ የሚያደርግ ብርቱ መልእክትንም ሸክፏል።
መጽሐፉን ከAlex Zetsa'at ገዝታችኹ እንድታነብቡት፥ በመከራና በሥቃይ መንገድ እያለፉ ላሉም ስጦታ አድርጋችኹ እንድታበረክቱ እጋብዛለኹ። ገዝታችኹ እንድታነብቡት፥ በመከራና በሥቃይ መንገድ እያለፉ ላሉም ስጦታ አድርጋችኹ እንድታበረክቱ እጋብዛለኹ።
984
የወንድዬን ሕይወትና አገልግሎት የሚተርከውን የዚህን መጽሐፍ የመጨረሻውን ጽሑፍ እንዳረታ ዕድል አግኝቼ ማንበብ ስጀምር፥ አርታዒው ወንድም ሽመልስ ይፍሩ፥ “… ከዚህ ቀደም በምንም አጋጣሚ ስለማላውቀው ሰው ውስጥ አንጀቴ ተላወሰ። በርግጥም ሕይወቱና አገልግሎቱ ቀልብ ይስባል፤ ያለፈበት መንገድ ስሜትን ሰቅዞ ይይዛል፤ አኗኗሩም ኾነ አሟሟቱ ያስቀናል። ‘የጻድቁን ሞት እኔም ልሙት’ ያሠኛል። የቤተ ሰቡ ታሪክ ይመስጣል፤ ኹኔታቸው ምስል ይከሥታል፤ ልብን በእግዚአብሔር ደስታ ይሞላል። …” ሲል ያሰፈራቸው ቃላት፥ ታሪኩን በጕጕት እንዳነብበው ያጫሩብኝ አንዳች ስሜት ነበር። ርሱ የተፈጠረው ያ ስሜት በኋላ እኔም ላይ ተጋብቶ አይቼዋለኹ። ለካስ የእውነተኛ ደቀ መዝሙር ሕይወቱ ብቻ ሳይኾን ሞቱም ጌታን ያከብራል! (ፊል. 1፥20)።
ወንድዬ በሥጋ መለየቱ ለውድ ቤተ ሰቦቹ፣ ለቅርብ ጓደኞቹና ወዳጆቹ ብዙ እንዳጐደለ ግልጽ ነው፤ ጌታ ታማኝ አገልጋዩን ወደ ርሱ መጥራቱ፥ በሞቱም፣ ክብሩን ሊገልጥ ወደዶ እንደ ኾነ ግን ይህን መጽሐፍ የሚያነብብ ኹሉ ያረጋግጣል የሚል ጽኑ እምነት አለኝ። ወንድዬ ስለ ርሱ የሞተለትን ጌታ ዐውቆና አምኖ ርሱን መከተል ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ ወዳገለገለው ጌታ እስከ ኼደበት ጊዜ ድረስ፥ በጥቂቶች ዘንድ ብቻ የታወቀው የደቀ መዝሙራዊ ሕይወቱና አገልግሎቱ ታሪክ በብዙዎች እንዲታወቅ፣ በዚህም ብዙዎች ጌታን እንዲያከብሩ፣ ለጌታ በተኖረው ሕይወት እንዲወቀሡ፣ ንስሓ እንዲገቡ፣ ሕይወታቸውንና አገልግሎታቸውን እንዲያስተካክሉ የሚመከሩበትና የሚገሠጹበት አንዳች ነገር አያጡም የሚል እምነት አለኝ።
ወንድዬ በኅብረት ውስጥ አገልግሎቱ፣ በቤተ ሰባዊ ሕይወት፦ አርኣያነት ባለው ባልነቱና አባትነቱ፣ በመንግሥት መሥሪያ ቤት በታማኝ ሠራተኛነቱ፣ በየስፍራው በወንጌል አብሣሪነቱ፣ በእውነተኛ የጸሎት ሰውነቱ፣ በተሰጡት የጸጋ ስጦታዎች ለቤተ ክርስቲያን መታነጽ በነበረው አበርክቶቱ፣ በቤትም በደጅም በኖረው አንድ ዐይነት ሕይወቱ ትልቅ የጌታ ምስክር ነው። የሕይወትና የአገልግሎት ታሪኩን የሚያነብብ ኹሉ ራሱን ይመለከትበታል፤ ስለ አገልጋዩ ጌታን ያከብራል፤ በብዙ ይመከርበታል፤ ይገሠጽበታል፤ የሕይወት፣ የኑሮና የአገልግሎት አቅጣጫውንም ቆም ብሎ የሚያስተካክልበትን ጠቃሚ ትምህርት ይቀሥማል። ዕንኾ! ኹሉ ሊያነብበው የሚገባ ለጌታ የተኖረ የሠዓሊው ደቀ መዝሙር ድንቅ ታሪክ።
984
"በምድርም የሚኖሩ ኹሉ እንደ ምናምን ይቈጠራሉ፤ በሰማይም ሰራዊት በምድርም ላይ በሚኖሩ መካከል እንደ ፈቃዱ ያደርጋል፤ እጁንም የሚከለክላት ወይም፦ ምን ታደርጋለኽ? የሚለው የለም።" (ዳን. 4፥35)
"በከመ ፈቀደ ይገብር ወበከመ ኀለየ ይፌጽም አልቦ ዘይክል ተዋሥኦቶ ወአልቦ ዘይብሎ ምንተ ገበርከ ዘንተ አሕሠምከ ወዘንተ አሠነይከ።"
ትርጕም፦ "እንደ ወደደ ያደርጋል፤ እንደ ዐሰበም ይፈጽማል። ርሱን መከራከር የሚችል የለም፤ ምን አደረግኽ (ያደረግኸው ምንድነው?) ይህን ለምን አከፋኽ፥ ይህንስ ለምን አሳመርኽ የሚለውም የለም?" (መጽሐፈ ሰዓታት)።
984
Repost from Hintset
ዓመታዊ ለሆነው የሕንጸት የመጽሐፍ ዕውቅና ሥነ ሥርዐት፣ በነገረ መለኮት ዘውግ ውስጥ ካሉት ዘርፎች መካከል፣ በዕቅበተ እምነት ዘርፍ የሚከተሉት መጻሕፍት ታጭተዋል። የሕንጸት መጽሐፍ ክበብ አባላት ብቻ ዕጩ መጻሕፍትን በሚከተለው መስፈንጠሪያ በመጠቀም ጽምፅ መስጠት ይችላሉ።
https://hintset.org/forum/book-club/book-award/
984
የቆዩ መጻሕፍትን ሳገላብጥ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሐዋርያዊ ድርጅት በ1960 ዓ.ም. ታትሞ የወጣ "መዝሙር ሐዋዝ" የተሠኘ፥ የመዝሙር ግጥሞችን የያዘ አነስተኛ መጽሐፍ አገኘኹ። ግጥሞቹን የደረሷቸው በአብዛኛው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ናቸው።
"የዘወትር መዝሙር ክፍል ፩" በሚለው ሥር በሚገኘው በዚህ መዝሙር መካከል ላይ፦
"ሕይወትን የሚሰጥ ወደ አብ የሚወስድ
ከኢየሱስ በቀር የለም ሌላ መንገድ" (ገጽ ፶፰-፶፱) የሚሉ ስንኞች አሉ።
ልብ በሉ! የዚህ መዝሙር ደራሲ በጉባኤ ያልዋለ፥ ምስጢር ያላደላደለ አንድ የሰንበት ተማሪ ሳይኾን፥ ከሊቃውንቱ አንዱ የነበሩት አለቃ ነቢየ ልዑል ዮሐንስ ናቸው።
የሚገርመው ያ ዘመን አኹን እኛ እንዳለንበት እንደዚህ ዘመን፥ ወንጌል የሚወገዝበት ኑፋቄ የሚሞገስበት ዘመን ባለመኾኑ፥ ደራሲው አለቃ ነቢየ ልዑልም ኾኑ ኹለቱ ስንኞች አልተወገዙም። ዘንድሮ ቢኾን ግን ከመወገዝ አያመልጡም ነበር። በወንጌል ወደ ፊት መጓዝ ሲገባን ምን ያኽል የኋሊት እንደ ተመለስን እናስተውል!!
ዜማውን የምታውቁ አስቀጽሉንና
ሕይወትን የሚሰጥ ወደ አብ የሚወስድ
ከኢየሱስ በቀር የለም ሌላ መንገድ
ብለን እንዘምር አያ!
