cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ነጌሌ አርሲ ደብረ ልዳ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክ ፈለገ-ገነት ሰንበት ትምህርት ቤት(FelegeGenet Sunday School)

የነጌሌ አርሲ ደ/ል/ቅ/ጊ/ቤ/ክ ፈለገ-ገነት ሰ/ት ቤት ሀሳብ አስተያየት ለመስጠት በ@felegegenetbot ሊንክ ያድርሱን @felegegenetbot

Больше
Рекламные посты
254
Подписчики
Нет данных24 часа
-17 дней
-530 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

✞አዝላው ወረደች✞ አዝላው ወረደች ወደ ግብፅ(፪) ስደተኛዋ የአምላክ እናት ይህ ዓለም ለእርሷ መች ተገባት ዓለም በምኗ ታስተናግዳት የፍቅር ምንጯ ተሟጦባት እነ ኮቲባን እየላከች የአምላክን እናት ተሳደበች እነ ሄሮድስን እየላከች ህፃኑን ልትገድል አሳደደች         አዝ= = = = = የክብርን ጌታ ተሸክማ ውርደት ለበሰች እንደ ሸማ የሀብቱን ጌታ በጀርባ አዝላ ሰው ተዘከራት ተቸግራ        አዝ= = = = = በቃሉ ትዕዛዝ ምድርን ሠርቶ ተንከራተተ ማደሪያ እጥቶ ጌታ ሲወለድ የምሥራች በረት ሰጠችው ዓለም ታካች        አዝ= = = = = ግና መላእክት በሰማያት ሃሌ ሉያ አሉ በፍርሃት ወልድን በአብ ቀኝ ከላይ አይተው ደግሞም በምድር ከድንግል ክንድ ከላይም ሳይጎድል ተመልክተው{፪}        አዝ= = = = = ዓለም በምኗ ታስተናግዳት የፍቅር ምንጯ ተሟጦባት እነ ኮቲባን እየላከች የአምላክን እናት ተሳደበች እነ ሄሮድስን እየላከች        አዝ= = = = = ህፃኑን ልትገድል አሳደደች በቃሉ ትዕዛዝ ምድርን ሠርቶ ተንከራተተ ማደሪያ እጥቶ ጌታ ሲወለድ የምሥራች በረት ሰጠችው ዓለም ታካች           መዝሙር        ይልማ ኃይሉ "… በእግዚአብሔር ተዘጋጅቶላት ወደ ነበረው ስፍራ ወደ በረሀ ሸሸች። …"              ራእ፲፪፥፮ ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮    @yamazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯
Показать все...
ሼር  ያድርጉ
የገበያ ግርግር ለሌባ ያመቻል እንዲሉ ብፁዓን አባቶች የቤተክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና አፍርሰው ጳጳስ እንዳይሾሙ ስንናገር "ድሮም አለቃ አያሌው ሲኖዶስን አውግዘውታል" ብለው የሚመልሱ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የሚባሉ አጭበርባሪዎች አሉ። ምእመናን ከዚህ ቀደም በ፲፪ ክፍል ስለኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አጭበርባሪነት እንደተማማርነው ከዚህ አጭበርባሪ ራሳችሁን እንድታድኑ ደግሜ እናገራለሁ። አለቃ አያሌው አቡነ ጳውሎስን ማውገዝ አይችሉም። ምንም እንኳ አቡነ ጳውሎስ አጥፍተው የነበረ ቢሆን እንኳ እርሳቸውን የማውገዝ ስልጣን ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ እንጂ ቄስ አይደለም። በፍትሐ ነገሥት እንደተገለጠው ቄስ ጳጳስን ማውገዝ አይችልም። ጳጳስም ሊቀጳጳሳትን ማውገዝ አይችልም። አንድ ሰው በራሱ የምግባር ክፋት ኖሮበት ሰው ሳያውቅበት ቢቀድስ እግዚአብሔር ራሱን ይመራመረዋል። ምእመናን ግን የሰውየውን ክፋት ባለማወቃቸው ጸጋ እግዚአብሔር አይቀርባቸውም። ። የቀረ ክህነት የለም። አሁንም ማንኛውም ምእመን ቤተክርስቲያን እየሄደ መጠመቅ፣ መቁረብ፣ ንስሓ መግባት፣ ምሥጢራትን መካፈል አለበት። ምእመናንን ከካህናት ለመነጠል ከመንግሥት ቀጥሎ በጣም እየሠራ ያለው ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የሚባለው አጭበርባሪ ነው። ስለዚህ ምእመናን ከድኅነት ራሳችሁን እንዳታርቁ ከዚህ ማፍያ ድርጅት ራሳችሁን ጠብቁ። ጳጳሳት ተስማምተው ክፋት ቢሠሩ በዋናነት ተጠያቂዎቹ ራሳቸው ናቸው። በእነርሱ በደል ምእመናን አይጠየቁም። ዶግማና ቀኖና እንዳይሻር እንደምእመንነታችን ለብፁዓን አባቶቻችን እናሳውቃለን። ቀኖናን ሽረው ውሳኔ ቢያስተላልፉ እንደልጅነታችን እንቃወማለን። (የምንቃወመው ግን ውሳኔያቸውን እንጂ ክህነታቸውን አይደለም)። ከቻልን የአምስቱም አኃት አብያተ ክርስቲያናት የጳጳሳት ጉባኤ አድርገው ጉዳዩን እንዲያዩልን መጠየቅ ነው። ቀኖናን እና ዶግማን ያላፈረሱ አባቶቻችንን መከተል ነው። ስለዚህ በጥቂት ሆዳሞችና፣ መለካውያን ጳጳሳት ምክንያት የተሻረ ክህነት የለም። ክህነት እስከ ዕለተ ምጽአት ይቀጥላል። ስለዚህ ቴዎድሮስ ይነግሣል እያሉ በሕልም ሊያኖሯችሁ የሚፈልጉ እነዚህ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ድርጅቶች እንዳያታልሏችሁ ተጠንቀቁ። ። ቅዱሳት መጻሕፍትን እያጣመሙ እንዳያታልሏችሁ የትርጓሜ መምህራንን ጠይቁ።
Показать все...
ከ25ቱ የባለፈው ሕገወጥ ኤጲስ ቆጶስ ሆንን ባዮች አንዱስ እንኳ ለእጩነት መቅረብ አይችልም። ይህ ብቻ ሳይሆን በቅስና እና በቁምስና መዓርግ እንኳ መቀጠል አይችሉም። ስለዚህ እነዚህን ሰዎች ቅዱስ ሲኖዶስ ክህነታቸውን አንስቶ በንስሓ በጨዋነት (ጨዋ ሆነው እንዲኖሩ) እንዲኖሩ ቢያደርግ መልካም ነው። ምክንያቱም የቤተክርስቲያን ቀኖና የሚያዝዘው ይህንን ነው። ካልጰጰስኩ አገባለሁ የሚል ካለም ያግባ። ቅዱስ ሲኖዶስ ባለፈው የሠራውን ስሕተት ሁለተኛ መድገም የለበትም። ባለፈው እነ አባ ሳዊሮስን፣ አባ ዜናማርቆስንና አባ ኤዎስጣቴዎስን የሐዋርያትን ቀኖና ሽሮ ነበር የመለሳቸው (ይህንን በጊዜው የብዙ አጨብጫቢ አድርባዮችን ስድብ ታግሼ ድርሻዬን ለመወጣት ጽፌ ነበር)። ቢቻል ይህንንም እንደገና ዐቢይ እና ሽመልስ ፊት ተስማምተናል በሚል እሳቤ ሳይሆን እግዚአብሔር ምን ይለናል በሚለው ለክታችሁ ወደ ጨዋነታቸው ብትመልሷቸው መልካም ነው። ይኽው አሁን የሲኖዶሱ ፈተና ሆኑ። የእግዚአብሔርን ሕግ ሽራችሁ የምታደርጉት ነገር በሙሉ መጀመሪያ በእናንተው ላይ ነው መከራ የሚያመጣው። ። በመንፈስቅዱስ መመራት ያለበት ቅዱስ ሲኖዶስ በመለካውያን ትእዛዝ እና ዛቻ የሚመራ ከሆነ ግን ምእመናን ለመንፈስቅዱስ አድልተው ይቃወሙታል። ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር ሕግ እና ቀኖና ትመራለች እንጂ በእጅ ብልጫ እና በመንግሥት ጫና አትመራም። ለቤተክርስቲያን አስተምህሮ አድልቶ እምቢ የሚል መኖር አለበት። የእግዚአብሔርን ቀኖና ከማስፈጸም ይልቅ የመንግሥትን ጉዳይ አስፈጽማለሁ የሚል ጳጳስ ካለ ግን ወደ ሀገረ ስብከቱ እንዳይመጣ፣ በእነርሱ ላይም እንዳይሾም ምእመናን እምቢ ማለት ይችላሉ። ቤተክርስቲያን የሁላችን ናት እንጂ ጳጳሱ እንደፈለገ ያለቀኖና እና ዶግማ የሚያዝዝባት አይደለችም። ስለዚህ ቤተክርስቲያን በቀኖናዋ መሠረት ትመራለች። ቀኖናዋን ሳያውቁ ጰጵሰው መለካዊ ሆነው ካስቸገሩ ደግሞ እነዚህን አውግዞ መለየት ይገባል። ውግዘት የተሠራው ለዚህ ነውና። ለቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና መከበር እስከመጨረሻው መታመን ያስፈልጋል። ሥጋዊ መከራን ፈርቶ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና ሲፈርስ ዝም ማለት ትልቅ ነውር ነው። ። ፈሪና ቦቅቧቃ ጳጳስ መኖር የለበትም። ለእውነት እስከመጨረሻው የሚቆም እንደ አቡነ ጴጥሮስ ለእግዚአብሔር የታመነ ጳጳስ መሆን ያስፈልጋል። ብፁዓን አባቶቻችን ዶግማውንና ቀኖናውን መሠረት አድርጋችሁ ከወሰናችሁ እስከሞት ድረስ በፍቅር እንታዘዛችኋለን። እንደባለፈው ስብሰባችሁ መለካዊ ውሳኔ ብትወስኑ ግን ተቃውሟችንን እንገፋበታለን። የተወሰነ ቀን ጩኽን ዝም የምንለው ጉዳይ አይደለም። ይህ ሃይማኖት ነው። በሃይማኖት ቀልድ የለም።
Показать все...
ፍትሐ ነገስት ሙሉ መፅሃፉ በ pdf ስላገኘነው ሙሉ ክፍሉን /ከ-10 ቀጥሎ የሉትን ክፍሎች በደንብ አንብቧቸው ተረዷቸው መልካም ንባብ
Показать все...
ወደዚህ ምድር ያመጣን እንዲሁም የሚያኖረን እግዚአብሔር ነው። ስለዚህ ልንፈራውም ልናፍረውም የሚገባን እርሱን ነው። ለሰው አድርባይና አሽቃባጭ መሆን አይገባም።
Показать все...
በዚህ ዓለም መኳንንት (ነገሥታት) ኃይል ተረድቶ የተሾመ ኤጲስ ቆጶስ ቢኖር ይሻር። ፍት. ነገ. ፭
Показать все...