cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

CHOOSEN GENERATION

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
208
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

🔹 FINAL AND MOST IMPORTANT STEP TO WIN THE FREE APPLICATION🔹 1. Follow our page on Telegram, Instagram or facebook and share our posts 2. Take a screenshot of our page u followed and shared as proof and send it to our telegram account @abe_l or 0913793620 3. Write your name and Gender along with the screenshots 4. We'll give you a number once we checked u've really followed and shared our page 5. The final draw will take place on Sunday March 28, 5:00 in the morning Ethiopian time LIVE on Instagram 🔵Good luck guys!!! 🔵
Показать все...
We have to give our moments for Christ cuz life is a series of moments 🙏 ኢየሱስ የአሁን አምላክ መሆኑን ባመንን በዛ ቅፅበት ሁለንተናችን የሱ ይሆናል @melkam_wetat2 @melkam_wetat2
Показать все...
ውድ choosen generations ...ባለፈው ሳምንት አንድ prog. ለይ ነበርኩ እና በተደጋጋሚ እግዚአብሔር፦ "ብዙዎች ረጅም እድሜ እንደሚኖር ሰው እያቀዱ ነው ነገር ግን ጊዜያቸውን የጨረሱ ሰዎች አሉ በድንገት ወደ ጌታም ይወሰዳሉ"እያለ በተደጋጋሚ ይናገር ነበር..... ይህንን የምለው የሞት ፍርሀት ላጭር አይደለም ግን በእያንዳንዱ ቀን ምን ያህል በክርስቶስ ትምህርት እየተመላለስን፤ፈር እንዳልለቀቅንስ እየመረመርን ይሆን!!?የሚለውን እንድናስብ ላግዛችሁ ነው... ምክንያቱም ከክርስቶስ ት/ት ለሚወጣ በዚያም ለማይኖርም ሰው አምላክ የለውም!! ((አምላክ የለውም፦አማኝ አይደለም ማለት ነው)) 💙...........💙 ጤናማ የህይወት አቋም እንዳለን ማረጋገጫው በህይወታችን የተገለጠ የፀጋ ስጦታ አይደለም ነገር ግን የክርስቶስ ት/ት እርሱም #ቅድስናችን(የህይወታችን ምልልስ) ነው።ማቴ 7፥22 ለይ ከቶ አላወቅኳችሁም እናንተ አመፀኞች ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ። ይላል....#አላውቃችሁም አይደለም ያላቸው ነገር ግን #አላወቅኳችሁም(I never knew) በዝያን ጊዜ እንደሱ ስታደርጉ በእኔ ዘንድ እውቅና አልነበራችሁም ማለት ነው!!እነዚህ በግልጥ የፀጋ ስጦታ አገልጋዮች ናቸው ግን በክርስቶስ ትምህርት ውስጥ ህይወታቸው ስለሌለ ጌታ አላወቃቸውም!! 💙........💙 2 ዮሐንስ 1 (2 John) 9፤ ለሚወጣ ሁሉ በክርስቶስም ትምህርት ለማይኖር ሰው አምላክ የለውም፤ በክርስቶስ ትምህርት ለሚኖር አብና ወልድ አሉት። ☝️☝️ ((meditate on "የክርስቶስ ትምህርት!!?")) ከዛ በኅላ አንድ ነገር መረዳት ጀመርኩ "ጌታ ሆይ ልመስልህ ፈልጋለሁ" የሚለው ፀሎቴ (#መምሰል ተጠግቶ መተዋወቅን የሚከተል መርህ እንዳለው!!) ...... ምክንያቱም የማላቀውን ሰው በፍፁም ልመስለው አልችልም!!ተጠግቼ ሳውቀው ግን ትምህርቱ ምን እንደሆነ (ምን እንደሚወድ፤ ምን እንደሚጠላ ፤እንዴት ባለ የህይወት መርህ ነፍሱ እንደምትደሰት...) ጠንቅቄ ማወቅ እችላለሁ...ይሄ ከሆነ ደግሞ የእርሱ በመሆኔ የምጠቀመውን ብቻ ሳይሆን ህይወቴን በጥቅምነት መልሼ ወደምሰጥበት መረዳት አድጋለሁ ማለት ነው። በእኔ #የማይኖር ቢሆን እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ይጣላል ይደርቅማል እነርሱንም ሰብስበው ወደ እሳት ይጥሏቸዋል ፥ያቃጥሏቸውማል ያለው እርሱ ኢየሱስ ነው!! 💙.......💙 ✍ህይወት ነገ ብለን የምናቅዳት ሳትሆን ዛሬ ብለን የምንኖራት ናትን ምናልባት ከመንገዱ ወጥተን እንዳይሆን ህይወታችንን እንመርምር!! The deeper our knowledge of christ,the deeper our understanding of Him,and z more like Him we become .this process causes us to grow and occurs over an entire lifetime in christ . only when we have entered Heaven for eternity with God does this process reach its culmination!! @melkam_wetat2 @melkam_wetat2
Показать все...
ባለራዕይ ሰው አያማርርም! ብዙዎች ስለፀሀይና ዝናብ ሲያማርሩ አንድ ባለራዕይ ግን ዣንጥላ ሚባል ነገርን ፈጥሯል! ባለህበት ነገር ውስጥ ከማማረር ይልቅ ምን መሆን እንዳለበት አስብ ተመልከት! እናንተ ባለራዕይ ናችሁ!! መልካም ቀን😊 @melkam_wetat2 @melkam_wetat2
Показать все...
ሀሳብህን ካልተቆጣጠርከው ሀሳብህ ይቆጣጠርሃል አእምሮ/ሀሳብ የሁሉም የፈጠራ ውጤቶች መገኛ ነው ፡፡ ዛሬ በዙሪያችን የምናያቸው ነገሮች ሁሉ በብዙ ሚሊዮን ዶላር የሚቆጠሩ ኩባንያዎች ፣ ኮምፒውተር፣ ስልክ፣ አውሮፕላን፣ አምፖል፣ ወዘተ... በመጀመሪያ የተፈጠሩት በባለቤቱ ወይም በፈጣሪው አእምሮ ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ አሁን በአዕምሮአችን ውስጥ ያለ ማናቸውም ሕልም ወይም ሀሳብን ዝም ብለህ አታስቀምጠው በእሱ ላይ ስራበት አዳብረው የሙሉ ጊዜ ሀሳብህ አርገው ያንን ሀሳብ አቅርቦ ከአማካሪ ጋር መነጋገር ሊሆን ይችላል ብቻ ወደ እውነታው ለማምጣት ማንኛውንም ነገር አድርግ ምናልባት ዓለምን የሚቀይረው ቀጣዩ ‘ትልቅ ነገር’ በአንተ ውስጥ ያለው ህልም ወይም ሀሳብ ሊሆን ይችላል። መልካም ቀን😊 @melkam_wetat2 @melkam_wetat2
Показать все...
🙏🙏ሰላማችሁ ይብዛ ውድ የክርስቶስ ወዳጆች(ቤተሰቦች) እንኳን ለ2013 ለጌታ የልደት መታሰቢያ ቀን በልዑል እግዚአብሔር ጥበቃ አደረሳችሁ። -አናልፍም ያልናቸውን ቀናት አልፈን አናድርም ያልናቸውን ለሊቶች አድረን ዛሬ ያልነውን ትናንት ብለን ዛሬን አለን አሁንም ለልዑል እግዚአብሔር ንግስናው ፀንቶ ለሚኖር ለማይናወጥ ልጆቹን በሰላም አስገብቶ ላወጣ ለእርሡ ይሁን ደግሞም በበጎነት ለሚያሰማራን ይሁንለት። 🌍አለም የሚያድን የእግዚአብሔር ፀጋ ተገልጧል ።ቲቶ 2-11 🎤በዚያው አገር በሌሊት መንጋቸውን ሲጠብቁ በሜዳ የሚያድሩ እረኞች ነበሩ።🌞የጌታም መልአክ ድንገት መጥቶ በአጠገባቸው ቆመ የጌታም ክብር በዙሪያቸው አበራ ታላቅም ፍርሀት ያዛቸው።መልአኩም ግን እንዲህ አላቸው "አትፍሩ ለህዝብ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምስራች አምጥቼላችኋለሁና።ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋልና እርሡም ጌታ ክርስቶስ ነው። \ሉቃስ፩፥፫፩-፫፰ ወናሁ ትፀንሲ ወትወልዲ ወልደ ወትሰምዮ ስም ኢየሱስ -ውእቱ አቢይ ወይሰማይ ወልደ እግዚአብሔር ልዑል ወይሁቦ እግዚአብሔር አምላክ መንበረ ዳዊት አቡሁ። -ወይነግስ ላዕለ ቤተ ያዕቆብ ለአለም ወአልቦ ማኅለቅት ለመንግስቱ -ወትቤሎ ማርያም ለመልአክ እፎኑ ይከውነኒ ዝንቱ እንዘ ኢያአምር ብእስ -ወአውስአ መልአክ ወይቤላ መንፈስ እግዚአብሔር ቅዱስ ይመፅእ ላዕሌኪ ወኅይለ ልዑል ይፄልለኪ ወዘኒ ይትወለድ አመኔኪ ቅዱስ ውእቱ ወይሰመይ ወልደ እግዚአብሔር ልዑል -ወናሁ ኤልሳቤጥኒ እንተ እምአዝማድኪ ይእቲኒ ፀንሠት ወረከበት ወልደ በልህቃቲሃ ወናሁ ሳድስ ዝንቱ ወረኅ ለእንተ ይብልዋ መካን -(እስመ አልቦ ነገረ ዘይሰእኖ ለእግዚአብሔር) -ወትቤሎ ማርያም ነየ አመተ እግዚአብሔር ወይኩነኒ በከመትቤለኒ ወሖረ ወኅለፈ እምኅቤሀ መልአክ።አሜን በአማርኛው ሉቃስ 1፥31-38 ቢነበብ የግዕዙን ሙሉ ትርጉም ይሰጠናል። ስለ ክርስቶስ ልደት እውነቶች አንዳንድ እውነቶች *ሰው ሊቆጠር የሚገባው በወጣው ህግ መሰረት ወደየ ትውልድ ቦታው መሄድ ነበረበት።በወቅቱ የነበረው ነባራዊ ሁኔታ እንደሚያስረዳው ተቆጣሪው ህዝብ ስፍር ቁጥር አልነበረውም።ታዲያ የጌታ እናት ማርያም እና አጮኛዋ ዮሴፍ ለኑሮ ናዝሬት ነበሩ ለቆጠራው ግን ወደ ዳዊት ከተማ ቤተልሔም መጓዝ ነበረባቸው። *ታዲያ በቤተልሔም ሳሉ የማርያም የመውለጃዋ ቀን ደረሰ።በዚያም ስፍራ ሊቆጠር የመጣ ህዝብ ብዙ ስለነበር ቦታ ለማግኘት እጅግ አዳጋች ነበረ። -እንኳን የማረፊያ ቦታ ቀርቶ የማደርያ ቦታ ስላልተገኘ በከብቶች ማደሪያ በበረት ውስጥ የአለም ጌታ መድሐኒ አለም ተወለደ።በጨርቅም ተጠቅልሎ እዛው በበረት ተኛ። *በዘመኑ የነበሩ እረኞች በሌሊት ከብቶቻቸውን ይጠብቁ ነበር።በዚህ አጋጣማ ከእግዚአብሔር አብ ከመንፈስ ቅዱስ ከቅዱሳን መልአክት ከጌታ እናት ማርያምና ከእጮኛዋ ዮሴፍ ቀጥለው የጌታን መወለድ ቀድመው የሰሙት እነኚህ እረኞች ነበሩ ለምን ቀድመው ሰሙ ይህ የእግዚአብሔር አሰራር ነው። *በሉቃስ 2፥13 አስደናቂ ቃል አለ።ድንገትም ብዙ የሰማይ ሰራዊት ከመልአኩ ጋር ታዩ እግዚአብሔርንም አመሰገኑ እንዲህ አሉ"ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ሰላምም እርሱ ለሚወዳቸው ሰዎች በምድር ይሁን" ለሰዎች መዳን በመልአክቶች ዘንድ የፈነጠቀባቸውን ደስታ ታላቅ እንደነበርም መመልከት ተገቢ ና የማያሻማ ጉዳይ ነው። -በእረኞችም ዘንድ በሰማይ ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን በምድርም ለሰው ልጆች በጎ ፈቃድና ሰላም ይሁን ብለው ምስጋናን አቀረቡ። ዋና ነጥቦች ስለክርስቶስ ልደት 1:አምላክ ሰው የሆነበት ታላቅ ቀን ነው። 2:ከሐጢያት ማቅ የሚያወጣ መድህን ነው። 3:በትምህርቱና በህይወቱ አብነት ወይንም ምሳሌ ሊሆነንና 4:በሞቱ የክብሩ ተካፋዮቹ ሊያደርገን ጌታ የተወለደበት ቀን ነው። በመጨረሻ የእልልታና የምስጋና ምንጭ ለሆነው ነቢያት ለመኙት መልአክት ላወደሱት እረኞች ላወሩት ሰብአሰገል ለሰገዱለት ሀጥያተኞች ለዳኑበት ግዞተኞች ለተፈተኑበት ሃዋርያት ላከበሩት ክርስቲያኖች ለወረሱት ለሰዎችና ለመልአክት ታላቅ ደስታ ለሆነው ለዚህ ቀን እንኳን አደረሳችሁ። መልካም የልደት መታሰቢያ ቀን ይሁንላችሁ። @SolMnD @SolMnD
Показать все...
"እዩልኝ" ሊሊ ጥላሁን NEW GOSPEL SONG 🌲Merry Christmas🎄 @melkam_wetat2 @melkam_wetat2
Показать все...
. እዩልኝ ቃልኪዳን ጥላሁን @melkam_wetat2 ❤️ @melkam_wetat2❤️
Показать все...
🌲❤️♡
Показать все...
🎄🎄🎄 @allLaurensongs
Показать все...