cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ABRHOT

በዚህ ቻናል ሀሳብ ያላችለሁ @ownkin

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
185
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

✍️ ሄዶን እውነት እውነት አለ ምናቤን ያነጠው እውነት ስሜት አለ ነበሬን የሸጠው እኔ ውስጥ እኔ አለ ነገ የማለውጠው @merekkk
Показать все...
በዝምታ መሀል እንዳለው ሹክሹክታ በለቅሶ መሀል ላይ እንደ ጮኸ እልልታ በድቅድቅ ጨለማ እንዳለችው ጨረር በተንጣለለው ሀይቅ እንደገባች ጠጠር በሞት ከተማ ውሰጥ እንዳለችው ህይወት ሀሰትን እንደ እውነት በቆጠረች ምድር ያለች ቅንጣት ውሸት . . . . . .እውነት
Показать все...
✍ህያው ..ህይወትን ለምን ሸሸኍት?.. ፍቅር በህግ ሲደቆስ: ብርሀን በጭለማ ሲለኮስ: ፈገግ ያሉት እየከሰሙ: ጆሮዎች ዋይታ ሲሰሙ: የተስፋ መጥኔ ሲላላ: ጸንተው በቆሙት አናት ላይ የመውደቅ ጥላ ሲያጠላ: የድክመት ብርታት ሲጎላ ሀይለኛ ሀይሉ ሲከዳው: ታዲያ የኔ ጥርስ ምን ተዳው.. ከዓለም እውነት ተጣልቶ በጉያው ነገን አግቶ ዛሬን እያታለለ: አለ ፈገግ እንዳለ.. @merekkk መ ረ ቅ
Показать все...
✍🏼ህያው በቃ አልናፍቅሽም? . . አየሁ.. የ'ናቴን ሙዳይ ከፈትኩት አየሁ.. እንደ ባለጌ ጎረምሳ ያባቴን ኮት ኪስ ደፈርኩት አዘንኩ.. ውስጡ አልነበረም ያሰብኩት። . . በቃ አልናፍቅሽም?.. @merekkk
Показать все...
✍️ሄዶን የለምም አንልም ኖሮም አላየንም አለንም አንልም ባዶም አይደለንም። @merekkk
Показать все...
ሳያዩ የሚያምኑ ብፁሀን ለመባል የሚንደረደሩ፣ አሉ በሀገሩ አሉ በመንደሩ። ፍርድን ይሽታሉ፣ ከለኮሱት እሳት ያመልጡ ይመስሉ፣ ወይ ወረድ ወይ ፍረድ እግዜርን ይላሉ ቢወርድ እና ቢፈርድ ከፈራጁ ጀርባ በፍርድ ሰገነት ፍርዱን ለመታዘብ ይቆሙ ይመስሉ። ጦርነት አውጆ በንፁሀን ደም ላይ የተረማመደ፣ ና ውረድ ይለዋል የሚወርድ መስሎት እርሱ እንደወረደ።
Показать все...
ስርየት የማይሞት ሲያጣጥር ሺ ጉድጓድ ሲያስቆፍር ሲደግስ ሲጣራ ሲያስለቅስ ሲያቅራራ ለደሃ በጀና ሙታን ይነሳሉ ያንዱ ስቃይ ላንዱ ስርየት ነው እያሉ ✍melat eshetu
Показать все...
ቢሆን” እንዳመተ ፍዳ ልክ እንደ በፊቱ ሐጢያት ስናበዛ ቢገለጥ ቅጣቱ በለምጥ ቢመታን ቢቀር ምህረቱ በጥቁሮች መዲና በዚች ኩሩ አገር በጣም ብዙ አበሻ ፈረንጅ ይሆን ነበር ምንጭ: ዮርዳኖስ አስራት
Показать все...
ቂምና ምስጋና ሆድ የለህምና እንደኔ በሆድህ ቂም መያዝ ባታውቅም ለሆዳም ሆዴ ስል በሆዴ ቂም ይዤ በፊትህ ባልፀድቅም በሰው ፊት ፃድቅ ነኝ ተመስገን እያልኩኝ በሰማይ በምድር የእለት እንጀራዬን እየከለከልከኝ አመት ፆሜን ሳድር ተመስገን ! ተመስገን ነው !😄😄 ✍ melat eshetu
Показать все...
( የጨረፍታ ብርድ ) የቆላ ሰዎች ወደ ደጋ፤ የደጋ ሰዎች ወደ ቆላ እየተፈራረቁ ፣ እየተሰደዱ፣ እየተተረማመሱ መኖር ለአያሌ ዘመናት የነበረ ደግሞም የሚቀጥል ነው ። በተለምዶ ቢሆን በዛን ዘመን የአንድ ሰው ፊት አይቶ እገሌ መልኩ ቁጭ ደገኛ አይደል የሚመስለው ይሄኛው ደግሞ ቁርጥ ቆለኛ አይደል የሚመስለው እየተባባሉ መገመት ያረጀ ያፈጀበት ልማዳችን ነው ። ወሎ በሚባለው በያኔ ክፍለ ሀገር ከቆላ አካባቢ ሁለት ሰዎች እልም ያለ ጠብ ውስጥ ይገባሉ ። የአካባቢ መንደርተኞች ሽማግሌዎችን አሰናድተው ሽምግልና ያስቀምጧቸዋል ፤ ጠበኞችም ባንገታችን ካራ ይግባ ሲሉ ለያዥ ለገናዥ ያስቸግራሉ ። ንትርኩ በዚህ የሚቋጭ አይደለም እና ወደ ደሴ ተጉዘው ችግራቸው በፍርድ እዲከድኑት የአካባቢ ሽማግሌዎች ይበይናሉ ። መንደሬው ወደ ደሴ የሚሄዱበት ቀነ ቀጠሮ ቆርጦ እነዛን ጠበኞችን እስከ ገጠሩ መውጫ አፋፍ ድረስ ተሰናበታቸው ። ጠበኞችም እየተፍገመገሙ የቆሪጥ እየተገለማመጡ አንደኛው ለአንድኛው የአይኑን ሽፍሽት ሳያርገበግቡ ስንቃቸውን ለብቻቸው እንደተመገቡ የዕኩለ ቀን ጉዞአቸውን አገባደዱ ። ጀንበር በምታዘቀዝቅበት ሰአት ከደሴ አቅራቢያ ጊንባ እየተባለ በሚነገርለት ስፍራ ደረሱ ። ምሽቱን መጓዝ ስላልቻሉ በከፊል ጫካ ከሆነ ስፍራ አድረው በነጋታው ፍርዳቸውን ለመቀበል ተስማምተው እዛው ጫካው ውስጥ ተኙ ። በጫካው ውስጥ ካለው የአራዊት ድምፅ እና የአዋፋት ጫጫታ ይልቅ የጊንባ ብርድ አጉል ረበሻቸው ። ብርዱ አይጣል ነው ፤, አያስቆም አያስቀምጥም ። ከዛም ጠበኞች የነበሩት ሰዎች ተቃቅፈው ተቀመጡ ። ኋላም እርስ በእርሳቸው እርቅ አውረደው እንዲህ ተባባሉ " የጨረፍታ ብርድ አለውድ ያስተቃቅፋል "። ለፍርድ ደሴ መሄዳቸው ትተው በመጡበት ተመለሱ ። አሁን ድረስ በአካባቢው ይሔ ወሬ ይወራል ። ይቺ አጭር ታሪክ ጠብ በደላላ ለሆነ ከምንም ነገር ይልቅ ጠብ ለሚቀድው የጨረፍታ ብርድ ፍቱን መድሃኒት ናት ። ✍ ፊሊሞን ነጋ @ownkin @djmdx
Показать все...