ru
Feedback
የኢ/ኦ/ተዋህዶ የቅዱሳን ስእል አድኖ

የኢ/ኦ/ተዋህዶ የቅዱሳን ስእል አድኖ

Открыть в Telegram
696
Подписчики
+124 часа
+77 дней
+3830 день
Архив постов
አሐቲ ድንግል #ማርያም ማለት ምን ማለት ነው? ማርያም ማለት፦ እግዝእት:- እመቤት ማለት ነው የዓለሙን ንጉስ በመውለዷ ከፈጣሪ በታች የፍጥረት ንግስት ሆናለችና፤ ጸጋ ዘተውኅበት ለኩሉ ዓለም፦ ለዓለሙ ሁሉ የተሰጠች ጸጋ ማለት ነው። ለአበው በተስፋ የሰጣቸው ሲሆን ለእኛ ደግሞ ከመስቀሉ ሥር እናት ትሁናችሁ ብሎ ሰጥቶናልና። (ዮሐ ፲፱፤፳፮) ለዚህም ነው ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ ንግሲቲቱ በቀኝህ ትቆማለች የሚለውን የዳዊት መዝሙር ሲተረጉም In becoming the mother of creator she become the Mistress of all creation (የፈጣሪ እናት በሆነች ጊዜ የፍጥረታት ሁሉ ንግስት እመቤት ሆናለችና በማለት ተርጉሞታል። (መዝ 44፤9) ተስፋ ማለት ነው፦ ለአዳም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ ካለው ጀምሮ መድኃኒቴን የምትወልጅልኝ ልጄ እያለ ተስፋ አድርጓት በልቦናው መዝገብነት ይዟት የኖረ ስንቁ ናት። አበውም ድንግል ማርያምን መቼ ፀሐይ ክርስቶስን ወልዳልን ከቁረ መርገም ድነን አይተነው እያሉ ተስፋ አድርገዋት ነበር። ተስፋቸው ክርስቶስም ከእርስዋ ተወልዶ ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን ገብተዋል። ለዚህ ምስክር የሚሆነን አረጋዊ ስምዖን "ጌታ ሆይ አገልጋይህን ዛሬ ታሰናብተዋለህ፥ አቤቱ በሰላም እንዳዘዝክ አይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና በህዝብ ፊት ሁሉ ያዘጋጀኸውን ለአህዛብ ብርሃንን ትገልጽ ዘንድ፥ ለእስራኤልም ክብርን" በማለት ተስፋውን አይቶ አርፏል። (ሉቃ 2፥29) የባሕር ከርቤ (Myrrh of the sea) ማለት ነው። ይህ ከርቤ እጅግ ውድ ዋጋ ያለው ከዘይት ጋር ተጨምሮ በጠበብተ ኦሪት ተቀምሞ ለንዋያተ ቅድሳት ማክበሪያ የታዘዘ ሽቱ ነው። ሙሴ ደብተራ ኦሪቱን በኦሪት መቅደሱ ያሉትን ሁሉ በዚህ ሽቱ እንዲቀባ ታዟል። ሽቱ ያረፈባቸውን የነካ ሁሉ እንደሚቀደስ እግዚአብሔር ለሙሴ ነግሮታል። ባህር የተባለ ይህ ዓለም ሲሆን እመቤታችንም ከእርስዋ ስጋን ነስቶ ክርስቶስ ተብሎ ስሙ እንደ ዘይት ተዋህዶን ክርስቲያን ተብለን እንድንጣፍጥ የድኅነት መሳሪያ የመዓዛ መንፈሳዊ ምንጭ ናትና የባህር ሽቱ ትባላለች። ሽቱ ያረፈበትን የነካ ሁሉ እንደሚቀደስ በልጇ ስም አምነው ተጠምቀው በእምነት የሚቀርብ ሁሉ ይጣፍጣልና ይላሉ አበው! የባሕር ኮከብ (Star of the seas) ማለት ነው። ባህር የተባለ ይህ ዓለም ነው፥ በባህር የሚበላም የማይበላም ደግሞ ክፉም ፍጥረት እንዳለ በዚህ ዓለምም አማኒም ከሓዲም መናፍቅም ጻድቅም ኃጥእም ይኖራልና፥ ዳግመኛም ባህር ከሁከት አይርቅም ይች ዓለምም ከሁከት አትርቅምና፥ በባህር ላይ ሲጓዙ በመርከብ ላይ ሆነው የንጋት ኮከብን አብነት አድርገው ከተጓዙ ካሰቡት ይደረሳል። ሰብአ ሰገልን ኮከብ እየመራ ቤተልሔም እንዳደረሳቸው ማለት ነው። እንዲሁም ሁሉ እመቤታችን በዚህ ዓለም የክህደት የኃጢአት ምገድ እንዳያጠፋን የተረፍንባት መርከባችን ናት። ብርህት (Illuminated) ማለት ነው። ብርሃኗ ከፀሐይ ይበልጣል፤ መለወጥ የሌለባት የድኅነት በር ናት ውበቷም በፍፁም ክብርና ሞገስ የተሸለመ ነው፤ እውነት በእውነት የመና መሶብ ነች። ጽድልት መባሏ ነውርና ነቀፋ የሌለበት የእግዚአብሔር እናት በመሆኗ ነው። አሐቲ ፍቅርት፦ ብቻዋን የምትወደድ (Beloved One) ማለት ነው። ንጉስ ውበትሽን ወዷልና ተብሎ የተዘመረላት እግዚአብሔር መዓዛ ድንግልናዋን ወዶ ከእርሷ ሰው እስኪሆን ድረስ፥ ፍጥረትን ሁሉ በዝናብ አብቅሎ በፀሐይ አብቅሎ የሚመግብ ጌታ ጡቶቿን ጠብቶ እስከማደግ ድረስ ደርሶ ብቻዋን በእግዚአብሔር የተወደደች ናትና። የባሕር ምንጭ (Drop of the sea) ማለት ነው። እመቤታችን በዚህ ዓለም በሦስት ዋና ዋና የድኅነት ምንጭ ሆናለችና። የጥምቀት፥ የቁርባን፥ የቅዳሴ ናቸው። ይህም ማለት ከጎኑ የፈሰሰው ውሃ፥ ከጎኑ የፈሰሰው ደም ከእርሷ ባህሪ የተገኘ ነውና ጌታ የተጠመቀውም ከእርሷ በነሳው ስጋ ነው የምንበላው ቅዱስ ስጋው የምንጠጣው ክቡር ደሙ ከእርሷ የነሳው ነውና የቁርባን ምንጭ ትባላለች። ዳግመኛም ማርያም ማለት ልዕልት ማለት ነው።.... (ቀጣዩን መጽሐፉን ገዝተው አንብቡ) አሐቲ ድንግል በአባ ገብረኪዳን ግርማ ገጽ 257 የተወሰደ http://t.me/abagebrekidan http://t.me/abagebrekidan

​​​​ፆመ ፅጌ / የፅጌ ፆም የእመቤታችን ስደት በጾም በጸሎት የምታስቡ ወይም የምታሳልፉ የእመቤታችን የድንግል ማርያም የቃልኪዳን ልጆች ከወዲሁ እንኳን አደረሳችሁ። ለጽጌ ጾም ካላቸው ፍቅር የተነሳ አንዳንድ ምዕመናን ጽጌ ጾም መቼ ነው የሚገባው እያሉ የሚጠይቁ ስላሉ ከወዲሁ ለማስታወስ ጾመ ጽጌ ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 5 ያለው አንድ ወር ከዐሥር ቀን ወይም 40 ቀን ወርኃ ጽጌ፣ ዘመነ ጸጌ፣ ተብሎ ይጠራል፡፡ በነዚህም ቀናት በየቤተክርስቲያኑ የሚነበቡ ምንባቦች፣ የሚዘመሩት መዝሙሮች፣ የሚሰበከው ስብከት፣ የሚቆመው ማኅሌት በጠቅላላው የሚነገረው ስብሐት እግዚአብሔር ሁሉ ሰማይ በከዋክብት ምድር በጽጌያት አሸብርቀው የሚታዩ መሆናቸውን የሚገልጽ ነው፡፡ ወርኃ ጽጌ ለሚከናወነው መንፈሰዊ አገልግሎት መነሻው "መልአኩ ሕፃኑንና እናቱን ወደ ግብፅ ይዘሃቸው ሽሽ፣ የሕፃኑን ነፍስ ሊገድሉት ይፈልጋሉና" ሲል ለዮሴፍ በሕልሙ በነገረው መሠረተ ዮሴፍም ሕፃኑንና እናቱን ድንግል ማርያምን ይዞ ወደ ግብፅ መሰደዱና እመቤታችንና ሕፃኑ ሦስት ዓመት ከመንፈቅ በስደት ከኖሩ በኋላ /ራእይ.12፣6/ ወደ አገራቸው ወደ ናዝሬት የመመለሳቸው መታሰቢያ ነው፡፡ /ማቴ 2፣13-23፣ ት.ኢሳ.19፣1፣ እንባቆም 3፣6-7፣ መዝ.83፣3/፡፡ ይህንንም በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሡ አባ ጽጌ ብርሃን ፍሬ ከአበባ አበባም ከፍሬ እንደሚገኝ ሁሉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንና ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስን በአበባና በፍሬ እየመለሰ በሚያስረዳው ድርሰታቸው እንዲህ በማለት ገልጸውለታል፡፡ "አፈወ ሮማን ማርያም ጽጌ ቀናንሞ ወአበሜ፣ እስከ ተጸምሐየየ በጾም ዘመልክዕኪ ጊዜ ድክታሜ፣ እምተመነይኩ ተሳትፎ ከመ አኅትኪ ሰሎሜ፣ ወፍሥሓኪ ዘአልቦ ፍጻሜ"፡፡ ሲተረጎምም የሮማን ሽቱ የቀናንሞ አበባ የምትሆኚ ማርያም ሆይ፣ በርሃብ በጾም አበባ የመሰለ የመልክሽ ደም ግባት እስኪጠወልግ ድረስ በስደትና በልቅሶ የደረሰብሽን ችግርና ድካም መከራሽንም ሁሉ እንደ እኅትሽ እንደ ሰሎሜ አብሬሽ ብቀበል ምኞቴ ነበር፤ በዚህ ፍጻሜ የሌለውን ደስታሽን እሳተፍ ነበር፡፡ እንዲሁም አባ አርክ ሥሉስ በስደቷ የደረሰባትን ኀዘን ፣ ልቅሶና ሰቆቃ አስመልክተው በደረሱት "ሰቆቃወ ድንግል" በሚለው ድርሰታቸው እንዲህ አሉ፣ ፀሐይን የምትለብሽ የብርሃን ልጅ ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ከሄሮድስ ዘንድ ልጅሽን ባሸሸሽ ጊዜ የደረሰብሽን ችግሮች ጨረቃን የሚጫሙ እግሮችሽ በመንገድ ብዛትና በአሸዋ ግለት እንደ ጎበጎቡ ሲሰማ ሰው ይቅርና ድንጋዩም ባለቀሰ ነበር” የእመቤታችን የስደቷ መታሰቢያ ወር በቤተ ክርስቲያናችን የሚከበረው በማኅሌት፣ በቅዳሴና በዝክር ነው፡፡ በወርኃ ጽጌ ባሉት ሳምንታት ከቅዳሜ ማታ እስከ እሑድ ጠዋት አበው ካህናት የሚያቀርቡት ዝማሬ ከቅዱስ ያሬድ ድጓ፣ ከማኅሌት ጽጌና ከሰቆቃው ድንግል የተውጣጣና ሦስት ወገን ያለው ነው፡፡ ዝክሩም፣ በአሁኑ ወቅት በከተሞች አካባቢ እየተረሳ ቢመጣም፣ ዘወትር እሑድ የአንድ አካባቢ ሰዎች ማዕከላዊ በሆነ ቦታ ተሰባስበው በእመቤታችን ስም የሚዘክሩት ነው፡፡ ዐቅመ ደካሞች፣ ድሆችና መንገደኞች ተጠርተው በእመቤታችን ስም እንዲበሉና እንዲጠጡ ይደረጋል፡፡ ይህም ትውፊት እመቤታችን ወደ ኢትዮጵያ በመጣች ጊዜ ኢትዮጵያውያን አባቶችና እናቶች ያደረጉላትን መስተንግዶ ለማሰብ ነው፡፡ ከእመቤታችን በረከት ያሳትፈን አሜን! 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ አመ ፳ወ፮ ለመስከረም ዘቀዳማይ ጽጌ በዓለ ቶማስ ወሀብተማርያም ማህሌት 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 ለማንኛውም ወርኃዊ እና አመታዊ ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ ..................................................... ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል። @Beteyaredtube16 @Beteyaredtube16 መልክአ ሥላሴ ሰላም ለአፉክሙ ዘማዕፆሁ ሰላም፤ጽጌያቲሁ ሥላሴ ለተዋሕዶ ገዳም፤መንገለ አሐዱ አምላክ ንዋየ መጻኢ ዓለም፤ወልጡ አምልኮትየ በጸጋክሙ ፍጹም፤እምአምልኮ ጣዖት ግሉፍ አሐዱ ድርህም። @Beteyaredtube16 ዚቅ፦ ለሥሉስ ቅዱስ ጥዑም ቃሎም፤ናርዶስ ጸገየ ዉስተ አፍሆሙ፤ @Beteyaredtube16 መግቢያ ዘማኅሌተ ጽጌ @Beteyaredtube16 ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት፤ተሠርገወት ምድር   (🌹#በህብረት_ሁሉም🌹) በስነ ጽጌያት፤ለመርዓዊሃ ትብሎ መርዓት፤ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት። @Beteyaredtube16 ማኅሌተ ጽጌ፦ ጽጌ አስተርአየ ሠሪጾ  እምዓጽሙ፤ለዘአምኃኪ ጽጌ ለገብርኤል ምስለ ሰላሙ፤ወበእንተዝ ማርያም ሶበ  ሐወዘኒ ጣዕሙ፤ለተአምርኪ አኀሊ እሙ፤ማኅሌተ ጽጌ ዘይሰመይ ስሙ፡፡ @Beteyaredtube16 @Beteyaredtube16 ወረብ መዓዛ ጣዕሙ ለተአምርኪ ሶበ ሶበ ሐወዘኒ/፪/ ወበእንተዝ ማርያም አኅሊ ለተዓምርኪ/፪/ @Beteyaredtube16 ዚቅ፦ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ናሁ አስተርአየ ጽጌ መርዓቱኒ ትቤ ወልድ እኁየ ይምዕዝ ከርቤ፤ ዕንባቆም ነቢይ ግብረ ምግባሩ ለወልድ አንከርኩ ይቤ፤ ንጉሠ ሰላም ክርስቶስ ዓቢይ ልዕልናከ ወመንክር ስብሐቲከ፤ለዕረፍት ሰንበት ሠራዕከ፤ @Beteyaredtube16 @Beteyaredtube16 ማኅሌተ ጽጌ እንዘ  ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ ፣አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣ንዒ  ርግብየ  ትናዝዝኒ  እምላህ፣ወንዒ  ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ @Beteyaredtube16 @Beteyaredtube16 ወረብ እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ /፪/ አመ  ቤተ  መቅደስ ሠናይትየ ሠናይትየ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ/፪/ @Beteyaredtube16 ዚቅ፦ ንዒ ርግብየ ወንዒ ሠናይትየ፤እንተ ሐዋርያት ይሴብሑኪ፤መላእክት ይትለአኩኪ፣ፃዒ እምሊባኖስ ስነ ሕይወት @Beteyaredtube16 ማህሌተ ጽጌ ጽጌኪ ማርያም ኮነኒ ሲሳየ ወአራዘ፤ወጸግወኒ እምትካዝ ተአምረኪ መናዝዘ፤ቶማስ ሎቱ አመ ገቦሁ አኃዘ፤እንዘ ይብል ከርቤ እምእዴየ ውኅዘ፣ረከበ በውስተ ቁስሉ አፈወ ምዑዘ @Beteyaredtube16 ወረብ- አመ ገቦሁ ቶማስ ሎቱ አኃዘ/፪/ እንዘ ይብል ከርቤ እምእዴየ ውኅዘ ረከበ  አፈወ ምዑዘ/፪/ @Beteyaredtube16 ዚቅ- ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ወልድ እኁየ ፈነወ ዕዴሁ እንተ ስቊረት፤ለከፎ ሶቤሃ ርስነ መለኮት @Beteyaredtube16 ማኅሌተ ጽጌ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ  ዘየኃቱ፤ዘተጽሕፈ ብኪ  ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤አክሊለ ጽጌ ማርያም  ለጊዮርጊስ ቀጸላ  መንግሥቱ፤አንቲ  ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡ @Beteyaredtube16 @Beteyaredtube16 ወረብ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ/፪/ አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ  መንግሥቱ/፪/ @Beteyaredtube16 @Beteyaredtube16 ዚቅ ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት፤ ወስብሕት በሐዋርያት፤አክሊለ በረከቱ ለጊዮርጊስ፤ ወትምክህተ ቤቱ ለ፳ኤል። @Beteyaredtube16 ሰቆቃወ ድንግል በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ ሕፀተ ግጻዌ ዘአልቦ፤ሰቆቃወ ድንግል እጽሕፍ በቀለመ አንብዕ ወአንጠብጥቦ፤ወይሌ ወላህ ለይበል ዘአንቦ፤ከማሀ ኀዘን ወተሰዶ ሶበ ለኩለሄ ረከቦ፤ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ @Beteyaredtube16 @Beteyaredtube16 ወረብ፦ ከማሀ ኀዘን ከማሀ ኀዘን ወተሰዶ ኀዘን/፪/ ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ ዓይነ ልብ ዘቦ/፪/ @Beteyaredtube16 ዚቅ፦ እወ አማን እምውሉደ ሰብእ አልቦ፤ምንዳቤ ወግፍዕ ዘከማኪ በዉስተ ኩሉ ዘረከቦ፤ @Beteyaredtube16 መዝሙር @Beteyaredtube16 ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ትዌድሶ መርዓት፤እንዘ ትብል ነዓ ወልድ እኁየ፤ ንፃዕ ሐቅለ፤ትዌድሶ መርዓት ንርዓይ ለእመ ጸገየ ወይን፤ወለእመ ፈረየ ሮማን፤ትዌድሶ መርዓት አሠርገወ ሰማየ በከዋክብት፤ወምድረኒ በስነ ጽጌያት፤ትዌድሶ መርዓት እስመ ውእቱ ወልድ ዋሕድ፤እግዚአ ለሰንበት፤ማ፦ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ፤ ወልድ እኁየ ቃለከ አዳም። @Beteyaredtube16 አመላለስ፦ ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ/፪/ ወልድ እኁየ ቃለከ አዳም/፬/ @Beteyaredtube16 🇪🇹👇👇👇👇👇👇 🇪🇹 👉 @Beteyaredtube16 👈                  👉 @Beteyaredtube16 👈 👉 @Beteyaredtube16 👈 🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹      @Beteyaredtube16     # Join & share #

Yemimechewna yemihed🤔
Yemimechewna yemihed🤔

"እኔ በስምሽ አምናለሁ፥ አንቺም ስለእኔ ትማልጃለሽ፥ ልጅሽም ስለአንቺ የልመናዬን ዋጋ ይሰጠኛል።" — ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ 🌺🕊🌺🕊🌺🕊🌺 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥      ⬇️ ለመቀላቀል⬇️        ⬇️⬇️⬇️⬇️             #ሼር     🙏 🙏 🙏 @or22todox

#ማርያም_ደስ_ይበልሽ ማርያም ማርያም ማርያም ደስ ይበልሽ በገብርኤል ሰላምታ በአንቺ ስላደረ የዓለም ሁሉ ጌታ (፪) የአምላክ ቸርነቱ ፈቃዱ ሲሆን ጨለማው ተገፎ ሲወጣ ብርሃን መድኃኒት ሲመጣ ሰይጣን እንደ አፈረ የዜናው አብሳሪ ገብርኤል ነበረ       ድንግል ተቀምጣ በቤተ መቅደስ ሐርና ወርቁን አስማምታ ስትፈትል ንግሥት ገብርኤል ገብርኤል ዜናዌ ሐዲስ የአምላክን መወለድ ስጋ በመልበስ        ገብርኤል ሲያበስራት ድንግል ስትሰማ አምላክ በርሷ አደረ የመለኮት ግርማ እውነተኛ መልአክ መሆኑን ስላየች ይሁንልኝ ብላ ቃሉን ተቀበለች 🌺🕊🌺🕊🌺🕊🌺 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥      ⬇️ ለመቀላቀል⬇️        ⬇️⬇️⬇️⬇️             #ሼር     🙏 🙏 🙏 @https://t.me/or22todox

#ስድቤን_አርቀሽ ስድቤን አርቀሽ ነውሬን የሸፈንሽው እመአምላክ በአንቺ መቼም አላፍርም ስምሽን ጠርቼ እጽናናለሁ ሐዘኔን በአንቺ እረሳለሁ ነውር አለብኝ ብዙ ስድብ አንጀት የሚልጥ ልብ የሚያቆስል ስሜን ለውጠው ቢያንቋሽሹኝ በሐዘን በለቅሶ ድንግል መጣሁኝ እንደ ሃና ሆኜ በቤተ መቅደስ በመረረ ሐዘን ነው የማለቅስ ፍቀጅልኝና ልመለስ ከቤቴ ሐዘኔን በደስታ ለውጪው ከቤቴ በግራም በቀኝም ጠላት ቢከበኝ አብዝቼ እጮሃለው እናቴ ስሚኝ አዝ= = = = = መከራው በዝቶ ግራ ገብቶኛል ድምፅሽን ልስማ ያረጋጋኛል የሰው ህይወቱ ብርቱ ሰልፍ ነው ደስታና ሐዘን የማይለየው በእጃችን ወድቋል ሲሉ ጠላቶቼ አመለጥኳቸው ስምሽን ጠርቼ ሰው የዘራውን ያንኑ ያጭዳል በቆፈረው ጉድጓድ ራሱ ይገባል እናቴ እመቤቴ ብዬ ስጠራሽ ከመከራ ሁሉ ታወጪኛለሽ አዝ = = = = = በምርኮ ሳለሁ በሰው አገር ግፍ ውለውብኝ ስኖር በእስር ምልጃሽ ደርሶልኝ ተፈትቻለሁ በተአምራትሽ እኔ ድኛለሁ ቃልሽን ሰምቶ ጽንሱ ሰገደ ብላለች ኤልሳቤጥ ነው የተወገደ የጌታዬ እናት እኔን አሰበችኝ ታሪኬን ቀይራ ይኸው ባረከችኝ የእመቤቴ ከሆንኩ ማን ይቃወመኛል ወጀቡም ማእበሉም ይታዘዝልኛል አዝ= = = = = ወይንኮ አልቋል የዶኪማስ ቤት ድንግል አማልጅው ነይ የእኛ እመቤት ስምሽ ሲጠራ በየቦታው ይመላልና የጎደለው ግራ የገባው የቸገረው ድንግልን ይጥራት እንድትረዳው ሳዝን ስተክዝ የምታጽናና እናት አለችኝ ርኅርኂተ ልቦና እናቴ እመቤቴ ብዬ ስጠራሽ ከመከራ ሁሉ ታወጪኛለሽ
በዘማሪ እንግዳወርቅ
🌺🕊🌺🕊🌺🕊🌺 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥      ⬇️ ለመቀላቀል⬇️        ⬇️⬇️⬇️⬇️             #ሼር     🙏 🙏 🙏 @ney_ney_emye_maryam

አማላጂቱ ሆይ፦ በጭንቅ፣ በኃጢአትና በበደል ውስጥ ያለን እኛ ምልጃሽን እንፈልጋለንና ይቅር ባዩ ተወዳጅ ልጅሽ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰላሙን፣ ይቅርታውንና ምህረቱን ይልክልን ዘንድ ለምኝልን🙏 ቅድስት ሆይ ለምኝልን

#ለነፍሴ_ነፍሷ_ነሽ ለነፍሴ ነፍሷነሽ ለመንገዴ ፋና አንዳልጠፋ አምናለሁ የአንቺ ልጅ ነኝና(2×) የጻድቃን እናቶች እጅግ ብዙ ናቸው ከብሉይ ከሐዲስ ብንዘረዝራቸው አንቺ ግን አንቺ ነሽ የለሽም ጭማሪ ትኖሪያለሽ እንጂ ትውልድን ስታስምሪ  #አዝ.... ያንችን ስም ተማጽኖ ያንቺን ስም ቀድሶ አንቺን አመስግኖ አንቺን አወድሶ የተጠቀመ እንጂ በረከት አግኝቶ አልታየም እስካሁን የተጎዳ ከቶ  #አዝ.... ጎርጎሬዎስና ሊቁ ዮሐንስ አትናቴዎስና ሊቁ ባስሊዮስ አባ ኤፍሬምና አባ ጊዮርጊስ ተጠቅመዋል ባንቺ በስጋም በነፍስ #አዝ... አባትህን ጠይቅ ስለሚለን ቃሉ ብንጠይቃቸው ቅዱሳኑን ሁሉ ስለአንቺ ነገሩን ክብር ታምራትሽን ለሰው ዘር በሙሉ አማላጅ መሆንሽን #አዝ... ገብርኤል ከሰማይ ኤልሳቤጥ ከምድር በአንድ መሰከሩ ስለድንግል ክብር ሰዓሊለነ ብሎ ተማጽኖ ባንቺ ስም የተጠቀመ እንጂ የተጐዳ ይለም 🌺🕊🌺🕊🌺🕊🌺 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥      ⬇️ ለመቀላቀል⬇️        ⬇️⬇️⬇️⬇️             #ሼር     🙏 🙏 🙏 @ney_ney_emye_maryam      ➡️ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ

Selam yezih channel beteseboch meteyek yemtfelgut tyake kale yemchlew yemawkew kehone emelslachuhalehu endeza eyaderegn entegagezalen Ena Yemtfelgut mezmur kale teykul elkalehu

እንኳን አደረሰን አደረሳቹ ውሉደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት የተመሰረተችበትን 19ኛ ዓመት የልደት በዓል ኑና አብረን እናክብር። መስከረም 8 - 1998 ዓ/ም የተመሰረተችው ሰንበት ት/ቤቷ የፊታች
እንኳን አደረሰን አደረሳቹ ውሉደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት የተመሰረተችበትን 19ኛ ዓመት የልደት በዓል ኑና አብረን እናክብር። መስከረም 8 - 1998 ዓ/ም የተመሰረተችው ሰንበት ት/ቤቷ የፊታችን እሁድ መስከረም 26 ቀን ከ10፡00 ሰዓት ጀምሮ ሁላችንም ተገኝተን ሰንበት ት/ቤቷን በሚዘክሩ በተለያየ መርሃግብር እናክብር ስትል ጠርታናለች፤ በመሆኑም በተለያየ አጋጣሚ እርቃቹ ያላቹ ልጆቿ በእለቱ ተገኝታቹ ከበዓሉ ተካፋይ እንድትሆኑ ተጋብዛቹዋል።

አይቀርም❗️❗️❗️❗️

እንኳን ለ2️⃣0️⃣1️⃣7️⃣ ዓመተ ምህረት በሠላም አደረሳችሁ መልካም አዲስ ዓመት ይሁንልን _ የዘመን መለወጫ ዘመን መለወጫ ምንድ ነው.❓ እንቁጣጣሽ ምንድነው..❓ አዲስ ዓመት ለምን ቅዱስ ዮሐንስ ይባላል❓ ኢትዮጵያ የወራት ሁሉ መጀመሪያ መስከረም ነው፡፡ ይህ ወር ዘመን መለወጫ፣ ዕንቁጣጣሽ፣ ቅዱስ ዮሐንስ እየተባለ ይጠራል፡፡ ስለ አዲስ ዓመት በተለያየ ስም የመጠራቱ ታሪካዊ አመጣጥና ስያሜ መነሻ አሳቡ ምን እንደሆነ እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡ ዘመን መለወጫ ዘመን መለወጫ መስከረም ወር የሆነበት ምክንያት “ብርሃናት /ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት/ የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜ ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው፡፡ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር ይተካከላል፡፡ ዓመቱን ጠንቅቀው ቢቆጥሩ 366 ቀናት ይሆናል፡፡ “ሌሊቱም ከቀኑ ጋራ ይተካከላል፡፡ ዓመቱም ጠንቅቆ ቢቆጥሩት ሦስት መቶ ስልሳ አራት ቀን ይሆናል፡፡ /ሄኖክ.26፥44/ “ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድሱ” /ሰ.ኤር.5፥21/ከቆየ እንዲል፡፡ በዘመነ ኖኅ ዓለምን ንፍር ውኃ አጥለቅልቆት በኋላ ዳግመኛ ውኃው የጎደለበት በመሆኑ /ኩፋሌ 7፥1/ “በመጀመሪያው ወር መባቻም ምድር ታየች” እንዲል፡፡ ዕንቁጣጣሽ ዕንቁጣጣሽ የተባለበት ምክንያት አንደኛ “ዕንቁ - ዕፅ አመጣሽ” ብሎ የአበባውንአህጉራትን መፈንዳት ያመለክታል፡፡ ሁለተኛ ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ በእጣ ሲያካፍላቸው አፍሪካ ለካም ደረሰችው፡፡ በአፍሪካ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ ያረፈው በኢትዮጵያ ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ አሸብርቃ ነበር፡፡ ወሩ ወርኀ መስከረም በመሆኑ ደስ ብሎት ዕንቁ ዕጣ ወጣሽልኝ ይህችን ወቅት እንቁጣጣሽ ብሏታል፡፡ ሦስተኛው /1ነገ.10፥1-10/ ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሣባ /መንሻ አዜብ የንጉሡን ጥበብ ከመስማት ማየትን መርጣ ወደ ንጉሥ ሰሎሞን ከብዙ ሠራዊቶቿ ጋር የእጅ በመያዝ ሄደች፡፡ ንጉሡም በደስታ ተቀብሎ እርሱም “እንቁ ለጣትሽወርኀ ጌጥ ይሁንሽ” በማለት አራት አይነት ቀለም የሚታይበት በቀንና በሌሊት የምታበራ ቀለበት ሰጥቷታል፡፡ ወሩም መስከረም ነበር፡፡ ከዚህ በመነሣት እንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜ ወጥቷል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ሦስተኛው የአዲስ ዘመን ስያሜ ቅዱስ ዮሐንስ ነው፡፡ የመጥምቁ ዮሐንስ ተግባር ለዘመነ ወንጌል በር ወይም መነሻ እንዲሆን ለኢትዮጵያ ዐውደ ዓመት መስከረም አንድ ቀን እንዲከበር አባቶች ወስነዋል፡፡ /ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 1-3/ መጽሐፈ ስንክሳር “የመስከረም ወር የተባረከ ነው፡፡ እርሱም የግብጽና የኢትዮጵያ ዓመቶች መጀመሪያ ነው፡፡ በአጠቃላይ ዘመን መለወጫ ከላይ ባየናቸው የተለያየ ስያሜ ይጠራ እንጂ ዘመኑ አዲስ እየተባለ ቢጠራም አዲስ መሆን ያለበት ወርና ወቅቱ ብቻ ሳይሆን የእኛ የክርስቲያኖች ሥርዓት ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውነታችሁን አታርክሱ የእግዚአብሔር ማደሪያ ነውና እያለ በመዋዕለ ሥጋዌው ያስተምር ነበር፡፡ አዲስ ዓመት ሲመጣ በኀጥያት፣ በተንኮል፣ በክፋት የቆሸሸው ሰውነታችን በንስሓ፣ በቅዱስ ቊርባን፣ በመልካም ተግባር አዲስ ልናደርገው ይገባናል፡፡ መልካም አዲስ ዓመት።     ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮       @Yemezmur_Gitimoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯

#ጳጉሜን_ለምን_እንጾማለን_? #ጳጉሜን_ለምን_እንጠመቃለን_? #ጳጉሜን_በመጠመቃችን_የምናገኘው_ጥቅም_ምንድን_ነው? #ጳጉሜን_መጠመቅ_መተት_እና_ድግምትን_ይሽራል፡፡ #ጳጉሜ_ሦስት_ርኅወተ_ሰማይ_ነው_ሰባቱ_ሰማያት_ይከፈታሉ ጸሎታችን በሙሉ ያርጋል፡፡ /ዩ ትዩብ ላይ የለቀኩትን ትምህርት በጽሑፍ ቃል በቃል አቅርቤላችኃለሁ/ ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ! የወለላይቱ እመቤት ልጆች እንደሚታወቀው ወርኃ ጳጉሜ፤ ኢትዮጲያን ብቸኛዋ ባለ አሥራ ሦስት ወራት ሀገር ያደርገች ልዩ ወር ናት፡፡ ታዲያ ይህች በሦስቱ ወንጌላውያን አምስት ፣ በዘመነ ዮሐንስ በአራት ዓመት ስድስት ቀን የምትሆነው ጳጉሜ፣ ብዙ ምስጢር እና ልዩ ጥቅም የላት ወር ናት፡፡ #ጳጉሜን_ለምን_እንጾማለን? የጳጉሜ ወር በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት የዓለም ፍጻሜ መታሰብያ ወር ተደርጋ ትታሰባለች፡፡ ጳጉሜ የዓመታት መሸጋገሪያ፤ ጨለማው የክረምት ወቅት፤ ወደ ማብቂያው እና የሚያልፍበት፤ እንደ ሆነ ሁሉ፤ ዳግም ምጽዓትም ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ፤ ከጊዜያው ወደ ዘላለማዊ መሻጋገሪያ በመሆኑ ጳጉሜ የእለተ ምጽአት ምሳሌ የሆነችው፡፡ በዚህም ምክንያት የኦርቶዶክስ አማኞች የጳጉሜን ወር በሱባኤ በጾም በጸሎት ያሳልፋሉ፡፡ በገዳም ያሉ አባቶች ጳጉሜን በዝግ ሱባኤ ያሳልፋሉ፡፡ በእርግጥ ጳጉሜ ከሰባቱ አጽዋማት ውስጥ ባትካተትም፤ ጳጉሜን በግዴታ ሳይሆን በውዴታ ብንጾም የበረታን ሱባኤ ብንይዝባት፣ የቻልን በተዐቅቦ ብናሳልፋት ትልቅ ጥቅም አለው፡፡ አንደኛ በፈቃዳችን በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ በሱባኤ ብናሳልፍ ጸጋና በረከት ያሰጠናል፡፡ ሁለተኛው ጳጉሜ የአዲስ ዓመት መቀበያ የዋዜማ ቀናት በመሆኗ፤ አዲሱን ዓመት በጾም፣ በጸሎት በሱባኤ ብንቀበል አዲሱ ዓመት የበረከት፣ የረድኤት ይሆንልናል፡፡ አዲሱን ዓመት በተለይም በዋዜማው በመዝናናት፣ በመጨፈር፣ በመጠጣት እና በመዘሞት ከምንቀበል፤ በጸሎት ብንቀበል አዲሱ ዓመት የበረከት ዓመት፣ ያሰብነው ያቀድነው እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሚሳካበት ይሆናል፡፡ ቅድም እንዳልኩት የገዳም አባቶቻችን የጳጉሜን ወር፤ መንፈሳዊ ጥቅም ስለሚያውቁ፤ በፈቃዳቸው በታላቅ ሱባኤ ሆነው ስለ ሀገር፣ ስለ መጪው አዲስ ዓመት መልካምነት ፈጣሪን ይማጸኑበታል፡፡ እኛ የአባቶቻችን ልጆች ነን እና፣ እነሱ የሄዱበትን መንገድ ተከትለን፤ እንደ እነሱ ልንጠቀም ያስፈልጋልና፤ ወርኃ ጳጉሜን በጾም በጸሎት እና በሱባኤ ብናሳልፍ እንጠቀማለን፡፡ በተለይ በአሁኑ ጊዜ እኛም፣ ሀገራችንም ቅድስት ቤተ-ክርስትያናችንም የገጠመን ፈተና፣ እጅጉን ከባድ ነውና እግዚአብሔር እንዲታረቀን፣ ገጸ ምሕረቱን እንዲመልስልን፣ ወረርሽኙን እንዲያጠፋልን፣ ለቅድስት ቤተ-ክርስትያናችንና ለሀገራችን ጽኑ ሰላም እና አንድነት እንዲሰጥልን ወርኃ ጳጉሜን እንደ በፊቱ በመብላት በመጠጣት ሳይሆን በጾም በጸሎት ብናሳልፍ ጥቅሙ ለእኛው ነው፡፡ #ጳጉሜን_ለምን_እንጠመቃለን? #በመጠመቃችን_ምን_ጥቅም_እናገኛለን? እንደሚታወቀው ብዙዎቻችን ወርኃ ጳጉሜን እንጠመቃለን፡፡ ጳጉሜን የምንጠመቅበት ዋናው ምክንያት ከሊቀ መልአኩ ከቅዱስ ሩፋኤል ጋር የተያያዘ ነው፡፡   በዚህ በጳጉሜ ወር በዓለም ላይ ያሉ ውቅያኖሶች፣ ባህሮች፣ ወንዞች፣ ኩሬዎች ጸበሎች በአጠቃላይ ውሃዎች ሰማይ ተከፍቶ፣ በመላክእት የሚባረኩበት ስለሆነ፤ ጳጉሜን የቻልን ጸበል ቦታ ሄደን፣ ወይም በአከባቢያችን ጸበል ካለ እዛም ሄደን፤ መሄድ ባይመቸን፣ ቤታችን ውስጥ ባለው ውኃ ብንጠመቅ እንባረክበታለን፣ ከበሽታችንም እንድንበታለን፡፡ በጳጉሜ ጸበል፣ እንኳን የሰው በሽታ፤ በሽታ ያለው እህል፣ በሽታው ይለቀዋል፡፡  ገበሬው ከጳጉሜ ወዲያ ነው የሚጠፋውንና የማይጠፋውን እህል የሚለየው፤ በተለይ ዘንጋዳ ጳጉሜ ላይ ነው በደንብ የሚያስታውቀው፡፡ በአባባልም ‹‹ዘንጋዳ እና ቡዳ ከመስከረም ወዲያ›› ነው የሚያስታውቀው ይባላል፡፡ የሚገርመው አባቶቻችን ጳጉሜ ሦስት ሌሊት ስድስት ሰዓት በተለይ ፏፏቴ ያለው ወንዝ፤ ውሃው ሲቆም ያዩታል፡፡ ቀድሞ አባቶቻን ይህንን ተአምር ለማየት ጳጉሜ ሦስት ሌሊት በተለይ ፏፏቴ ያለበት፣ ትልቅ ወንዝ ዳር ሄደው ያድሩ ነበር፡፡ ውሃው ቀጥ ብሎ ሲቆም ሰማይ ሲከፈት ያዩ ነበር፡፡ ጳጉሜን በተለይም ጳጉሜ ሦስት፣ የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በአሉ ስለሆነ፤ በዚህ ቀን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ውሆችን የሚባርክበት፤ እና ለሰው ልጆች በፈጣሪው ጸጋ፤ ድህነት እና ፈውስ የሚያሰጥበት ቀን ስለሆነ ብንጠመቅ ከበሽታችን እንድናለን፡፡ በመጸሐፍ ቅዱስ በዮሐንስ ወንጌል በምዕራ 5 ቁጥር 4 ላይ ‹‹አንዳንድ ጊዜ  የጌታ መልአክ ወደ መጠመቂያይቱ ወርዶ፣ ውኃውን ያናውጥ ነበርና፤ እንግዲህ ከውኃው መናወጥ በኃላ በመጀመሪያ የገባ ከማናቸውም ካለበት ደዌ ጤናማ ይሆን ነበር›› ይላል፡፡ የጌታ መልአክ ‹‹ውኃውን ያናውጥ ነበር›› የተባለው፤ ከሰማይ ወርዶ ውኃውን ይባርከው ነበር ለማለት ነው፡፡ ውኃውም የሚናወጠው የእግዚአብሔር መልአክ ውኃውን ሲባርከውና እና በመጠመቂያው፣ ለፈውስ ደጅ የሚጠኑት፣ ህሙማን ውሃው በመልአኩ መባረኩን የሚያውቁት ውኃው ሲናወጥ ነው፡፡ ዛሬም እንደ ቀድሞ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል፤ በዓለም ላይ ያሉትን ውሃዎች ሁሉ ስለሚባርካቸው፤ ብንጠመቅባቸው እንፈወሳለን፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ብቻ ሳይሆን ሌሎች ቅዱሳን መላእክትም ውኃውን ይባርኩታል፡፡ ጳጉሜ ሦስት ይህ ብቻ አይደለም ሊቀ መልአኩ ያስለመደን ነገር አለ፡፡ ይህም ሁል ጊዜ ጳጉሜ ሦስት ሌሊት፣ ጠዋት፣ ከሰዓት አልያም ማምሻ ላይ ይዘንባል፡፡ ይህ ከሰማይ የሆነ የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ጸበል ነው፡፡ በልጅነታችን ጳጉሜ ሦስትን ‹‹ሩፋኤል አሳድገኝ›› እያልን እንጠመቃለን፡፡ ጳጉሜ ሦስት በዘነበው ውኃ መጠመቅ ትልቅ መታደል እና ፈውስ ነው፡፡ በደዌ ይሰቃይ የነበረው ኢዮብም በዚህ ሳምንት ነው ተጠምቆ ነው የዳነው፡፡ የሚገርማችሁ በዚህ በከተማ ብዙም ስለማይታወቅ ነው እንጂ፤ በገጠር እና በክፍለ ሀገር የቅዱስ ሩፋኤል እለት የዘነው ዝናብ በእቃ ይቀዳና ይቀመጣል፡፡ በተቀዳው ጸበል ቦሃቃው ይረጭበታል፣ በውሃው እህሉ ይቦካበታል፣ ቤቱ ደጁ ይረጭበታል፡፡ ይህም የሚሆነው የቅዱስ ሩፋኤል እለት የዘነበው ውኃ የሰላቢ መንፈስን ስለሚያርቅ ነው፡፡ የሰላቢ መንፈስ ከቤታችን የእህል በረከት የሚያሳጣ፣ ለአንድ ወር ያሰብነውን ለሳምንት የማያዳርስ፣ ለዓመት ያልነው በሦስት ወር እንዲያልቅ የሚያደርግ፤ ክፉ መንፈስ ስላለ ይህን ያርቅልናል፣ በጸበሉ በረከት እህል አስቤዛውን ያበረክትልናል፡፡ እንደምታውቁት ቅዱስ ሩፋኤል ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሦስተኛው ነው፡፡ በመጀመሪያዋ እለተ ፍጥረት እግዚአብሔር መቶ ነገደ መላእክት ፈጥሮ በአሥር ከተማ ሲያኖራቸው ቅዱስ ሩፋኤል ራማ ላይ ነው ከነ ሠራዊቱ ያረፈው ወይም የከተመው፡፡ በራማም መናብርት ተብለው ለሚጠሩት አሥሩ ነገድ አለቃ ወይም መሪ ሆኖ በእግዚአብሔር ተሹሟል፡፡ በኃላም መጋብያን በሚባሉ በሃያ ሦስቱ ነገድ ላይ ተሹሟል፡፡ ስለዚህ ጳጉሜ ሦስት የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል በዓለ ሲመት ወይም የሹመት በዓሉ ነው፡፡ ይህንንም እራሱ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል በመጽሐፈ ጦቢት ምዕራፍ 12 ቁጥር 15 ላይ ‹‹ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ›› በማለት ተናግሯል፡፡ የስሙንም ትርጉም ስንመለከት ‹‹ሩፋ›› ማለት ሐኪም ማለት ነው፡፡ ኤል ማለት እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሩፋኤል ማለት የእግዚአብሔር ሐኪም ማለት ነው፡፡

" ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል:: ክንድህ ከኃይልህ ጋር ነው:: እጅህ በረታች: ቀኝህም ከፍ ከፍ አለች:: "(መዝ. 88:12) እንኳን አደረሳችሁ!
" ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል:: ክንድህ ከኃይልህ ጋር ነው:: እጅህ በረታች: ቀኝህም ከፍ ከፍ አለች:: "(መዝ. 88:12)            እንኳን አደረሳችሁ!

✧ ሆያ ሆዬ  ✧ ሆያ ሆዬ  ሆ ሆያ ሆዬ (7) በግዕዝ በዕዝል ሆ በአራራ ዜማ ለአምላኳ ቅኔ    ሆ የምታሰማ የምታስተምር  ሆ  ፈጣሪን መፍራት የአለም መፀሀፍት ሆ ተዋሕዶ ናት ቤተ ክብርት የእግዚአብሔር ቤት (2) አትናወጥም ሆ በሲኦል ደጆች ስለ ታነፀች ሆ  በእግዚአብሔር  እጆች የፍቅር ደሴት ሆ ንፄት ሙሽራ አምላክ አለባት ሆ ከእናቱ ጋራ ቤተ ክርስቲያን ንፄት ሰማያዊት (2) ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ የአታናቲዎስ   ሆ ህያዋ ብርቱ የዲኦስቆሮስ ሆ  ፅና እርስቱ የቅርስ ማህደር ሆ የአለም ጥላ የያሬድ እናት  ሆ  የላሊበላ ቤተ ክርስቲያን እናታችን መማፀኛችን (2) ✥•┈┈•●◉አዝ◉●•┈┈•✥ ስርዓትቷን እዩ  ሆ ማህሌቷን ሳቷቷን ስሙ ሆ ቅዳሴዋን በመንፈስ ቅዱስ ሆ የተረቀቀች አበዉ ቅዱሳን  ሆ የተዘከረች ቤተ ክርስቲያን ሆ ሰማያዊት ነሽ የኛ ተዋህዶ ሆ እር ፅይት ነች ቤተ ክርስቲያን እናታችን መማፀኛችን ቤተ ክርስቲያን ክብርት የእግዚአብሔር ቤት ቤተ ክርስቲያን ነፅይት ሰማያዊት ቤተ ክርስቲያን ከብርት የእግዚአብሔር ቤት  ✥•┈•●◉ ◉●•┈•✥