cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ኢትyo 🇪🇹

ምርጥ ምርጥ አባባል👏 ምክር👨‍⚕ መጣጥፍ(ፅሁፍ)📖📚 ከፈለጉ join and share @tinsugt for any comment ኢትyo discussion group👈 ፨በቻላችሁት አቅም Left ላለማለት ሞክሩ ካላችሁም ያላችሁበትን ምክንያት ለ Adminoch Report አድርጉ 🙏

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
129
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

❝ብዙ ወንዶች አበቦችን ይሰጡሻል...ግን አንድ ቀን የምትወጂዉን አበባ..የምትወጂዉን ሙዚቃ..የምትወጂዉን ጣፋጭ የሚያዉቅ ወንድ ትተዋወቂያለሽ😘 እና አንዱንም ቢሆን ሊሰጥሽ ባይችል.. ምንም ደሃ ቢሆንም ጣጣ የለውም ምክንያቱም ጊዜዉን ወስዶ ማንም ሊያዉቅሽ ከሚችለው በላይ አዉቆሻልና። ለእሱ ብቻ ነው ልብሽን ልትሰጪው እሚገባው!♥️❞ @tinsugt
Показать все...
​​ሴና ♥️ ክፍል 37 ◈ አጭር እውነተኛ የፍቅር ታሪክ (ሴና)🌺 የመጨረሻው ክፍል! . . . አይኔን ስገልጥ ነጭ ኮርኒስ ነው የታየኝ፡፡ አልጋ ላይ እንደተኛው ይሰማኛል፡፡ አንገቴን ወደ ጎን ዞር ሳደርግ አጠገቤ አንድ ነጭ ጋወን የለበሰ ሰው ቆሞ የአይዞሽ አሁን ደና ነሽ" አለኝ ግንባሬን በመዳፉ እየዳበሰ፡፡ የተኛውት የሀኪም ቤት ክፍል ውስጥ እንደሆነ ገባኝ፡፡ ወዲያው የክፍሉ በር ተከፍቶ እነ ሚጣ ተከታትለው ገቡ፡፡ "አሁን እንዴት ነሽ?" እያሉ ጥያቄ ያከታትሉብኝ ጀመር፡፡ "አሁን ደና ስለሆነች ይዛቹሀት መሄድ ትችላላቹ ፡፡ትንሽ ድንጋጤው እንጂ ሌላ ምንም ችግር የለባትም" አለ ባለ ነጭ ጋወኑ ሀኪም፡፡ እነ ሚጣ ደግፈው ከአልጋ ካወረዱኝ ብሀላ ጫማዬን አድርገውልኝ ከተኛውበት ክፍል ይዘውኝ ወጡ፡፡ ከክፍሉ ስወጣ ከግቢ ውጪ ያለ ሀኪም ቤት እንደነበርኩ ገባኝ፡፡ አይኔ ያነባል፡፡ እነ ሚጣ አይዞሽ ይሉኛል ፣ ጥያቄ ይጠይቁኛል ፣ማብራሪያ ይሰጡኛል ፣ሊያረጋጉኝ ይሞክራሉ፡፡ እኔ ግን ማልቀሴን አላቆምኩም፡፡ ከሀኪም ቤቱ በር ላይ ስደርስ ያየውት ግራ ገባኝ ፡፡ የወንድሜ መኪና ቆሞአል፡፡ እንዴት እንደሰማ ግራ ገባኝ፡፡ "ቆይ ውስጥ ነው ይመጣል"አለችኝ ሚጣ በቀኝ በኩል ደግፋኝ እንደቆመች፡፡ እንዴት መጣ? ማን ነገረው? ቆይ እኔ እንዴት እዚ መጣው?' ጠየኳት ሚጣን እንባዬ አሁንም እንደወረደ ነው፡፡ ድምፄ ጉንፋን እንደያዘው ሰው ተዘግቶአል፡፡ "ቆይ ሁሉንም እናውራለን፡፡ አሁን ተረጋጊ"አለችኝ ሚጣ ጉንጬ ላይ የወረደውን እንባዬን በሹራቧ ጫፍ እየጠረገች፡፡ በዚ መሀል ወንድሜ መጣ "አይዞሽ ምንም አልሆንሽም"ብሎ አቀፈኝ፡፡ ጥያቄ ሆነብኝ፡፡ ወዲያው የመኪናውን ሁዋላ በር ከከፈተልኝ ብሀላ ወደ ውስጥ ገባው፡፡ ሚጣ ተከትላኝ ገባች፡፡ ሌሎቹ ከተሰናበቱኝ ቡሀላ ሄዱ፡፡ ወንድሜ ወኪናውን አስነስቶ መሄድ ሲጀምር 'ቆይ ምንድነው ነገሩ ግራ አጋባቹኝ እኮ 'አልኩኝ በደከመ ድምፅ፡፡ ማንም መልስ አልሰጠኝም፡፡ ወንድሜ መኪናውን እየነዳ ከከተማ ወጣ ወዳለ ቦታ ከወሰደን ብሀላ መኪናውን ከአንድ ሜዳማ ስፍራ አቁሞ ሞተሩን ካጠፋ ብሀላ ከመኪናው ወረደ፡፡ሚጣም ተከትላው ወረደች፡፡ ግራ ገባኝ እኔም ተከትያቸው ወረድኩኝ፡፡ ወንድሜ መኪናውን ተደግፎ ቆመ፡፡ ገና ከመኪና ከመውረዴ ሚጣ ማውራትጀመረች፡፡ "የውልሽ ሴና ያኔ ለ እረፍት ወደ ቤት የሄድን ሰአት ነበር ፍሬ በድንገተኛ አደጋ ያረፈው፡፡ እና የዛን እለት ላንቺ ይሄንን ልነግርሽ አስቤ ነገር ግን እንደዚ አይነት ነገር በስልክ ብነግርሽ ያለሽበት ሁኔታ ደሞ ጥሩ ባይሆን ይሄንን ስትሰሚ የሆነ ነገር ቢፈጠር ወይም የሆነ ነገር በራስሽ ላይ ብታደርሺ ብዬ ስለፈራው ለወንድምሽ ደወልኩለት፡፡ የሱን ስልክ ከየት አገኘሽው ካልሽኝ እኛ ግቢ ምትማረው የባልደረባችን ልጅ ያልሽኝ ከሷ ነው የተቀበልኩት፡፡ የሷን ስልክ ደሞ ያገኘውት እነሱ ዶርም የምትኖር ልጅ ጉዋደኛ እሱን ጠይቄ በሱ በኩል አድርጌ አፈላልጌ ነው፡፡ ያ አማራጭ ባይኖረኝ የዛኔ ቀጥታ ሀዋሳ ቤታቹ መጣ ነበር፡፡ ይሄንን አድርጌ ለወንድምሽ ደውዬ ሁሉንም ነገር ነገርኩት፡፡ የዛን እለት ወንድምሽ ሰበብ ፈልጎ ስልክሽን ተቀበለሽ፡፡ ያንን ያደረግነው ደሞ ከሌላ ሰው እንዳትገናኚ እና ከሌላ ሰው እንዳትሰሚው አስበን ነው፡፡" ሚጣ ይሄንን ስትነግረኝ ወንድሜን እየተመለከትኩት ማንባቴን ቀጠልኩ፡፡ ሚጣ ቀጠለች፡፡ " . . .ለ ዴቭ ስትደውይለት አጠገቤ ነበር፡፡ ፍሬን እንዳላየው እና ሀዋሳ እንሆነ እንዲነግርሽ የነገርኩት እኔ ነበርኩኝ፡፡ ሰኞ ለምዝገባ መጥተሽ ምዝገባ አርብ ነው ሀሙስ እንመጣለን ያልኩሽ ግዜ እኔ ግቢ ነበርኩኝ፡፡ ሌሎቹም የዶርም ልጆች መጥተው ከተመዘገብን ብሀላ ወንድምሽ ንቺን ግቢ እንዳደረሰሽ በሌላ በር ገብቶ አንቺ መምጣት እንደማትችይ ነግሮ ግቢ ውስጥ በሚያውቀው ሰው አማካይነት እንድትመዘገቢ አደረግን፡፡ ከዛ እኔና የዶርም ልጆች እናንተ ቤት ነበርን፡፡ ምክንያቱም ሀሙስ ነው ምንመጣው ያልንሽ ብቻሽን እንድትሆኚ ነበር፡፡ ብቻሽን እንድትሆኚ ካደረግን ብሀላ ወንድምሽ ኪሩቤልን ላከው፡፡ ኪሩቤል በአጋጣሚ ካፌ ውስጥ የተዋወቅሽው ተማሪ ሳይሆን የስነልቦና ባለሙያ የሆነ የወንድምሽ ጉዋደኛ ነው፡፡ የፍሬ ስልክ ሲሙ የወጣው በዴቭ ስም ነው፡፡ስለዚ ፍሬ ሲያርፍ ዴቭ ሲሙን አውጥቶ ስለነበር በዛ ስልክ ሚደወሉ ጥሪዎችን በሙሉ ለፍሬ የተደወሉ ይሆናሉ ስለሚል አያነሳውም፡፡ እኔና ወንድምሽ ይሄንን ስናደርግ ሀሳቡ የኪሩቤል ነበር፡፡ እኛ ያሰብነው ፍሬን ቀስ በቀስ እንድትረሺው ነበር፡፡ ለዛ ነው ኪሩቤል ቢዚ ያደረገሽ፡፡ ያው ባልጠበቅነው መንገድ እውነቱን አወቅሽ እነጂ" ፡፡ ሚጣ ይሄንን ሁሉ ስታወራ እኔ እያነባው በግርምት አዳምጣት ነበር፡፡ ወንድሜ መኪናውን እንደተደገፈ ቆሞ ያዳምጣት ነበር፡፡ ወደወንድሜ እየተመለከትኩ ላወራ ስል "ሴና ከህፃንነችሽ ጀምሮ ሳደርግ የነበረው ነገር አንቺ እህቴን በጣም ሰለምወድሽ ነበር፡፡ ታላቅ እንደመሆኔ ደሞ አንቺን ከብዙ ነገር ጠብቄ ትልቅ ሰው ማድረግ ነበር እቅዴ ፡፡ እኔ ይህን ሳደርግ ደሙ ሙሉ ቤተሰባችን ስለሚቀበለኝ አንቺ ይሄንን ከጥላቻ ትቆጥሪያለሽ፡፡ በርግጥ እኔም አበዛውት ግን ላንቺው አስቤ የማደርገው ነገር ስለ. . . " አላስጨረስኩትም ወንድሜ ላይ ጥምጥም አልኩበት፡፡ ይሄንን ሁሉ ነገር ያደርግ የነበረው ለኔው ሲል መሆኑን ሳስብ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ፡፡ ወንድሜን ለቅቄ ሚጣን አቀፍኳት፡፡ ተቃቅፈን አለቀስን፡፡ ወደ ከተማ እየተመለስን በጭንቅላቴ ብዙ ሀሳቦች ተመላለሱ፡፡ ዠእውነት ለካ ቤተሰቦቼ ለኔ ፍቅር አላቸው፡፡ የተከተሉት መንገድ የጎዳኝ ቢመስለኝም ሁሉን ሚያደርጉት ለኔ ብለው ነው፡፡ የዶርሜ ልጆች እውነትም ለካ ከልባቸው ነው ጉዋደኝነታቸው፡፡ ለኔ ሰሜት ምን ያህል እንደሚጨነቁ አሰብኩኝ፡፡ እውነት እኛ ሰዎች ባሰቡልን ልክ እያሰብናቸው ነው?' ብዬ ራሴን ጠየኩት፡፡ ዶርም ስገባ ስለሁሉም ነገር ጉዋደኞቼን አመሰገንኳቸው፡፡ ከኪሩቤል ጋርም ጉወደኝነታችን ቀጠለ፡፡ ወንድሜና ጉዋደኞቼ ባደረጉት ነገር በጣም ብዙ ተማርኩኝ፡፡ ጉዋደኝነት ፣ቤተሰብ እውነተኛ ፍቅርን ከነሱ አገኘው፡፡ የፍሬ ህልፈት እጅጉን የከፋ ሀዘን ቢያደርስብኝም ቤተሰቦቼ እና ጉዋደኞቼ ከጎኔ በመሆናቸው ብርታት ሰጡኝ፡፡ ይሄ ታሪክ ከተፈጠረ አመት አለፈው፡፡ አሁን እኔ የሁለተኛ አመት ተማሪ ሆኛለው፡፡ ዶርም ስሄድ ቤቴ ቤት ስሄድ ዶርሜ ይናፍቀኝ ጀመር፡፡ በትምህርቴ ውጤታማ እየሆንኩኝ ነው፡፡እስካሁን የፍቀር ጉዋደኛ አልያዝኩም፡፡ ፍሬ ዛሬም በልቤ አለ፡፡ ነገር ግን ቤተሰቦቼና ጉዋደኞቼ አብረውኝ ስላሉ ደስተኛ ነኝ፡፡ ለሁሉም ነገር ደሞ ፈጣሪን አመሰግናለው፡፡ አምላክ የፍቅርን ጉልበት በቤተሰቦቼና በጉዋደኞቼ በኩል አስተምሮኛል፡፡ ይህንን ታሪክ ያነበባቹ በሙሉ ከዚህ እንደምትማሩ ተስፋ አደርጋለው፡፡ . . . ህይወት ይቀጥላል . . . ....... ተ ፈ ፀ መ...... ,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,, ••●◉Join us share◉●•• @tinsugt
Показать все...
❤️ 7
👏
አጭር እውነተኛ የፍቅር ታሪክ የመጨረሻው ክፍል በቅርቡ ይጠብቁን
Показать все...
​​💓 #ፍቅር 💗 "ሰው ስትሆን በህይወትህ ብዙ ነገሮችን ታገኛለህ ፣ታጣለህ ፤ብዙ መንገድ ትሄዳለህ ፣ትመጣለህ ፤ሀዘን እና ደስታ ይፈራረቁብሀል ፤ ብዙ ስቃይና መከራ ፣ብዙ ስኬት እና እረፍት በህይወትክ ከሚያጋጥሙህ ነገሮች መሀከል ናቸው፡፡ በነዚህ ውስጥ በሁሉም ቦታ ፍቅር አለ፡፡ ሲነጋም ፍቅር አለ ሲመሽም ፍቅር አለ፡፡ ፍቅር ማለት ፍቅረኛ አይደለም፣ፍቅር ሰው አይደለም ፤ፍቅር አንድ ትልቅ ሀይልን የተላበሰ የፈጣሪ ፀጋ ነው፡፡ ቀመና የለውም ፣አቅጣጫ አይቀመጥለትም፤ፍቅር መከላከያም ሆነ መቆጣጠሪያ ወይም ደሞ ሀይል መጨመሪያ የለውም፡፡ ፍቅር አያዳላም ለዛም ማሳያ እኛ አፍሪካዊያን እንሆናለን፡፡ በሀብት ፣በቀለም ሳያሳንሰን ከ አውሮፓ እና አሜሪካ ጋር ያለው የፍቅር ስሜት በኛ ልብ ውስጥም እንዲያድር ሆኗልና፡፡ እደግመዋለው ፍቅር ማለት ፍቅረኛ ማለት አይደለም፡፡ ፍቅር ትምህርት ነው ፣ፍቅረኛ መምህር! ትምህርት ከመምህሩ በላይ የሆነ ተሰፍሮ ፣ተቆጥሮ ማያልቅ ከተመገቡት የሁሉንም ጭንቅላት እንደሚሞላው ሁሉ ፍቅርም ከአፍቃሪው በላይ የሆነ ለተመገቡት ሁሉ ህይወትን በሀሴት የሚሞላ ተሰፍሮ ማያልቅ እጅጉን ፍፁም አስደሳች እና ሰላም ያለው የህይወት ምግብ ነው፡፡ ሁላችንም እኩል ፍቅር ተሰጥቶናል ተቀብለን ምናስቀምጥበት ቦታ ይለያያል እንጂ . . . ❤️ ,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,, ••●◉Join us share◉●•• @tinsugt
Показать все...
​​ሴና ❤️ ክፍል 36 . . . ዛሬ በጥዋቱ ነው የተነሳውት፡፡ ኪሩቤል ልክ በሰአቱ ሲደውል እኔ ቀድሜው መነሳቴን ነግሬው ጉዋደኞቼን ጨምሮ አብረን ቁርስ በላን፡፡ ዛሬ ምንመዘገብበት ቀን ነው፡፡ ኪሩቤል ሲቀር ሁላችንም ተያይዘን ሄድን፡፡ምዝገባ ቦታ ስንደርስ ማንም ተማሪ የለም፡፡ "ተማሪው ምን ነካው ? ቀኑ አልፍ ነው ወይስ እኛ ቀድመን ነው?" ስንባባል ሚጣ "መታወቂያ ነው አስቀምጠው ሚሄዱት መታወቂያቹን አምጡ እና እዚ ጠብቁኝ "ብላ መታወቂያችንን ሰብስባ ወደውስጥ ገባች፡፡ ትንሽ ቆይታ "በቃ መታወቂያ ነገ ነው ምንቀበለው" ብላን ተያይዘን ቡዙ ግዜ ተሰብስበን ምኅቀመጥበት ቦታ ሄድን፡፡ እስከ ምሳ ሰአት ከዛ ቦታ አልተነሳንም፡፡ ያለፋት ሳምንታት ምን ይመስሉ እንደነበር ተራ በተራ መጨዋወት ጀመርን፡፡ የኔ ተራ ሲደርስ 'ብዙም ደስ አይልም ይልቅ ተነሱ ወደ ምሳ ርቦኛል 'አልኩዋቸው ተጨማሪ ጥያቄ እንዳይጠይቁኝ ስል ከተቀመጥኩበት እየተነሳው፡፡ ሁሉም ተከትለውኝ ተነሱ ፡፡ ማንም ምንም አልተናገረኝም፡፡ በፊትም ቤት ውስጥ ያለውን ነገር የተወሰነ ያህል ስለሚያውቁ ይረዱኛል፡፡ ምሳ ልንበላ ወደ ካፌ እየሄድን ኪሩቤል ደወለ "እስኪ አምስት ብር ሙይልኝ የምሳ " አለኝ በአሳዛኝ ድምፅ፡፡ በጣም ነው ያሳቀኝ፡፡ ከጉዋደኞቼ ጋር እየመጣው እንደሆነ እና እዛው ካፌ እንዲጠብቀኝ ነግሬው ስልኩን ዘጋውት፡፡ በስልክ ያለኝን ለጉዋደኞቼ ስነግራቸው ሁሉም ሳቁ፡፡ ኪሩቤል ከሁሉም ጋር ተግባብቶአል፡፡ ገና በመጀመሪያ ቀን እንደዛ ሲጫወት ሳየው ጉዋደኞቼን ከድሮ ጀምሮ ሚያውቃቸው ነው ሚመስለው፡፡ካፌ ስንደርስ ኪሩቤል ዝርዝር ብር ይዞ ካፌው በር ላይ ተቀምጦአል፡፡ ገና አንዳየነው ሁላችንም ሳቅን፡፡ ተሰብስበን ምሳ አብረን በላን፡፡ ከምሳ ብሀላ ሌሎቹ ጉዋደኞቼን ከ ኪሩቤል ጋር ትተን እኔ እና ሚጣ ወደ ዶርም እየሄድን ሳለ አንድ ልጅ መጥታ ሚጣን ተጠምጥማባት ካቀፈቻት ቡሀላ እኔን ጨበጠችኝ፡፡ ወዴት እየሄድን እንደሆነ ጠይቃን ሚጣን "እንዴት ነው በረታቹ ? እኔም እኮ ወደ ግቢ መጣው ተመልሼም ሳልጠይቃቹ፡፡ ወይዘሮ አዲስ እንዴት ናቸው? በረቱ ? " አለች፡፡ ሚጣ በጣም ደነገጠች ምትመልሰው መልስ አጣች፡፡ "ሴና እኔ መጣለው እየሄድሽ ጠብቂኝ" አለችኝ፡፡ ግራ ገባኝ የሆነ ነገር ውርር ሲያደርገኝ ይሰማኛል፡፡ እሺ ብዬ መንገዴን ቀጠልኩ፡፡ ትንሽ ከሄድኩኝ ብሀላ አንድ ጥግ ቆሜ ማጣን መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ ሚጣና ልጅቱዋ ሚያወሩትን ባልሰማም ግን በደንብ ይታዩኛል፡፡ ሚጣ እያለቀሰች ነው፡፡ ከእጅ ቦርሳዋ ውስጥ ሶፍት አውጥታ እንባዋን ትጠራርጋለች፡፡ ቡዙ ቆመው ካወሩ ቡሀላ ሚጣ ወደኔ መጣች፡፡ በጣም ደንግጫለው ሚጣ አይኗ ቀልቶአል፡፡ ምን እንደሆነች ብጠይቃትም ምንም መልስ አትሰጠኝም አይኗን በሶፍት እየጠረገች ዶርም ደረስን፡፡ ምን ተፈጥሮ እንደሆነ ስጠይቃት "ጎረቤት ለቅሶ ነበር አብሮ አደጋችን አርፎ ለቅሶ ላይ ነበር የቆየውት ስለሱ ነው ያነሳችብኝ፡፡ "አለችኝ ሚጣ እንባዋን እያፈሰሰች፡፡ ደነገጥኩኝ! . . . እግሬ ተንቀጠቀጠ . . . ቅድም ልጅቷ "ወይዘሮ አዲስ በረቱ?" ያለችው ትዝ አለኝ፡፡ የሆነ ግዜ ፍሬ ስለቤተሰቦቹ ሲነግረኝ የእናቱ ስም አዲስ እንደሚባል ነግሮኝ ነበር፡፡ መናገር አቃተኝ የሙት የሙቴን "ፍሬስ?" አልኳት ሚጣን፡፡ "ፍሬ ምንም አልሆነም አለ" አለችኝ እያነባች፡፡ "ሚጣ አትዋሺኝ! ፍሬ የታለ? ስልኩን አያነሳ ! ግቢ አልመጣ ! ፍሬ ምን ሆኖ ነው! ሚጣ በፈጠረሽ አትዋሺኝ ፍሬ ምን ሆነ!?" የሚጣን ትከሻ ይዤ በጩኸት ጠየኩዋት፡፡" ፍሬ ምንም አልሆነም ተረጋጊ "አለችኝ ሚጣ ራሱዋን ለማረጋጋት እየሞከረች፡፡ "ሚጣ አትዋሺኝ የቅድሙዋን ልጅ ጠይቃታለው ፍሬ ምን ሆነ!? ሚጣ በምትወጂው ይሁንብሽ ! በፈጠረሽ ፍሬ ምን ሆኖአል?" እንባዬ መውረድ ጀመረ፡፡ መጠየቁ አልሆን ሲለኝ መለመን ጀመርኩ "ሚጣ ፍሬ የት ነው ያለው? ፍሬ ምን ሆኖ ነው የጠፋው?" "ሴና ፍሬ አርፎአል" አለችኝ ሚጣ ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች፡፡ አላመንኩም በሁለት አጄ ጭምድድ አድርጌ የያዝኩትን የሚጣን ትከሻ ለቀኩት፡፡ ከዚሁ ብሀላ ማስታውሰው የሆነ ነገር ኩሀላ ጭንቅላቴን ሲመታው ነው . . . @tinsugt
Показать все...
​​ሴና ❤️ ክፍል 35 . . . ዛሬም እንዳለፉት ቀናት የኪሩቤል ስልክ ነው የቀሰቀሰኝ፡፡ ቁርሳችንን ከበላን ብሀላ ትንሽ ተጨዋውተን ወደ ዶርሜ ተመለስኩ፡፡ ጉዋደኞቼ ይመጣሉ ፤ዶርሙን አስተካከልኩ፡፡ ዶርም እንደተቀመጥኩኝ ጉዋደኞቼ ደወሉልኝ፡፡ ሁሉም አንድ ቦታ ተገናኝተው ወደ ግቢ እየመጡ እንደሆነ ነገሩኝ፡፡ በጣም ደስ ቡሎኛል፡፡ ከዛሬ ቡሀላ ብቻዬን አላድርም ማለት ነው፡፡ በርግጥ ባለፉት ቀናት ሙሉ ሰአት አብሮኝ የነበረው ኪሩቤል ምንም ብቸኝነት እንዳይሰማኝ አድርጎኛል፡፡ ድንገት የዶርሜ በር ተንኳኳ፡፡ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ከፈትኩት፡፡ በሩን ከፈት ከማድረጌ ሚጣ ፈገግ ብላ እያየችኝ በሩ ላይ ቆማለች፡፡ በጣም ደስ አለኝ፡፡ ሁሉንም አንድ በአንድ አቅፌ ሰላም እያልኩኝ ወደ ውስጥ አስገባዋቸው፡፡ ገና እየመጣን ነው ያሉኝ ለካ ደርሰው ነው፡፡ እየተሳሳቅን እና እየተጨዋወትን ናፍቆታችንን እንገልፅ ጀመር፡፡ ሁሉም ስለደከማቸው ሻወር እንዲወስዱ ነግሬያቸው መጣው ብዬ ከዶርም ወጣው፡፡ ለኪሩቤል ደወልኩለት፡፡ የጠራሁት ቦታ መጣ፡፡ ጉዋደኞቼ ከመንገድ ስለመጡ ስለደከማቸው ከዶርም ከሚወጡ ምግብ እንድንገዛላቸው እኔ ቴካዌ አዝዤ ስለማላውቅ እንዲያጋዛኝ ነገርኩት፡፡ "አረ አንቺም ባትመጪ ብታዢኝ ይዤ መጣ ነበር ብር የለኝም እንጂ ፡፡ "አለኝ እየሳቀ፡፡ ገዛዝተን ከመጣን ቡሀላ ዶርም መግቢያ ድረስ ሸኝቶኝ ተመለሰ፡፡ ዶርም ስገባ ከ ሁለቱ በስተቀር ሌሎቹ ሻወር ሊወስዱ ወጥተዋል፡፡ ምግቡን ካቀራረብኩ ቡሀላ ሁሉም ሲመለሱ ተሰብስበን ምሳችንን በላን፡፡ ምናልባት ከደከማቸው ብዬ እንዳደረኩት ስለገባቸው በጣም አመሰገኑኝ፡፡ ጨዋታችን ቀጠለ፡፡ ስለገጠመኞቻችን እያወራን መሳሳቅ ጀመርን፡፡ በመሀል ስለ ፍሬ ጠየኩዋቸው፡፡ ሁሉም ዝም ዝም አሉ፡፡ "ምነው አግኝታቹት አታውቁም?" አልኩኝ ወደ ሚጣ እያየው፡፡ 'አረ ከዚ እንደሄድን እኮ በስንተኛው ቀን አጎቴጋር ምናምን ብሎ ወደ ባህርዳር ሄደ ከዛን ቡሀላ አንድ ቀን ነው እንዲሁ ለሰላምታ የተገናኘነው፡፡" አለችኝ፡፡ 'እና ለምንድነው ስልክ ማያነሳው?' አልኩኝ በድንገት ተናደድኩ፡፡ "የደወለልኝ ግዜ ስልኩን ሌላ ቦታ ረስቶት እንደሄደ እና ወደ ቤት ሲመለስ በዛው ተቀብሎ እንደሚመጣ ነው የነገረኝ፡፡ የዛን ቀንም የደወለልኝ በሰው ስልክ ነበር፡፡ "አለችኝ፡፡ እንደመንተባተብ እያለች፡፡ ሌሎቹ እንዳለ ዝም ብለው ያዪኛል፡፡ ምክንያቱ ምንም አልተዋጠልኝም፡፡ ግን ምንም ማለት አልፈልግም በይሁንታ ራሴን ነቅንቄ ወደ ሌላ ጨዋታ ገባን፡፡ በመሀል ስለ ኪሩቤል ማውራት ጀመርኩ፡፡ ከቀልዶቹ እያካፈልኩዋቸው ያደረግናቸውን ነገሮች እየነገርኳቸው ዶርሙን ሳቅ በሳቅ አደረግነው፡፡ እየተጫወትን ሳናስበው መሸ፡፡ መምሸቱንም ያወቅነው ኪሩቤል ሲደውል ነው፡፡ "ዛሬ ቀጣሽኝ አይደል? አይ ሰው ገና ለገና ጉዋደኞቼ መጡ ብለሽ ነዋ? እሺ እራት አንበላም ወይስ እሱንም ቴካዌ ላስመጣላቹ?" አለኝ ገና ስልክ ከማንሳቴ፡፡ ጉዋደኞቼ እራት ወጥተን እንድንበላ ስነግራቸው ተስማሙ፡፡ "እንደውም ጊቢውም ናፍቆናል እራት ብቻ ሳይሆን ጉብኝትም ጭምር ነው፡፡" እያሉ እየተሳሳቅን ልብሳችንን ቀያይረን ወጣን፡፡ ካፌ ስንደርስ ኪሩቤል በቁጥራችን ልክ ወንበር አስተካክሎ ጠበቀን፡፡ ከሁሉም ጋር ካስተዋወኩት ቡሀላ ሁላችንም ተቀመጥን፡፡ በኪሩቤል አቀባበል ሁሉም ተደስተዋል፡፡ ከግቢ ውጪ ሌላ ሆቴል ያለን ነው የመሰለን፡፡ እራት ከተመገብን ቡሀላ ጨዋታ ተጀመረ፡፡ ኪሩቤል አልተቻለም፡፡ ክብ ሰርተን ስንስቅ ካፌ ውስጥ ያሉት ተማሪዎች አይን በሙሉ እኛ ላይ ሆነ፡፡ በጣም ተጫወትን፡፡ ኪሩቤል ከጉዋደኞቼ ጋር በጣም ነው የተግባባው፡፡ ደስ የሚል ምሽትን አሳለፍን፡፡ ዶርም ከገባው ቡሀላ እንደለመድኩት ከኪሩቤል ጋር በስልክ አወራና እስቅ ጀመር፡፡ በድምፅ ካወራን ቡሀላ በፅሁፍ ማውራት ቀጠልን፡፡ አሁንም ግን የፍሬን ስልክ ሞክራለው፡፡ ይጠራል . . . አይነሳም፡፡ ጉዋደኞቼ ሁሉም ተኝተዋል፡፡ እኔ ግን በፍሬ ትዝታውስጥ ኪሩቤልን እያወራሁት ነው፡፡ ,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,, ••●◉Join us share◉●•• @tinsugt
Показать все...
​​ሴና ❤️ ክፍል 34 . . . በፍጥነት ከአልጋው ላይ ወርጄ የደወለውን ሳይ ኪሩቤል ነው፡፡ የፍሬን ስልክ እየጠበኩ ስለነበር ነው መሰለኝ አለመሆኑን ሳይ በጣም ቅር አለኝ፡፡ ኪሩቤልን ማውራት ጀመርኩ፡፡ በጣም ብዙ ሰአት ከኪሩቤል ጋር በስልክ አወራው፡፡ በጣም ተጫዋች ልጅ ነው፡፡ ቀልዶቹ ደሞ በእውቀት ላይ የተመሰረቱ ናቸው፡፡ አንዳንድ ሚያወራቸው ነገሮች እኔ ሚሰማኝን ስሜት በቀልድ አድርጉ ስለሆነ በጣም ተመችቶኛል፡፡ እንደዚ በአንድ ቀን መቀራረባችን በጣም ነው የገረመኝ፡፡ በመጨረሻም 'አረ ይቆጥርብካል በቃ ነገ ጥዋት ካቆምንበት እንቀጥላለን 'ስለው "አታስቢ ካርዱን በቁማሩ ብር ነው የሞላውት ከእራት በተረፈው "አለኝ፡፡ 'ይሄ ቁማር እውነትም አዋጪ ነው ነገም አስይዝ ከዛ ሙሉ ቀን እንንበሸበሽበታለን'አልኩት መልሼ፡፡ የሳቅ ብዛት ሆዴን አቁስሎታል፡፡ እኔም በአንድ ቀን ቀልደኛ ሆኛለው፡፡ ስልኩን ስዘጋው ጥዋት መልሼ እስካገኘው ቸኮልኩ፡፡ ልብሴን ቀያይሬ መብራት አጥፍቼ ተኛው፡፡ ጥዋት ከእንቅልፍ የቀሰቀሰኝ የኪሩቤል ስልክ ጥሪ ነበር፡፡ ገና አንድ ሰአት ነው፡፡ ገና ስልክ በማንሳቴ በተለመደው ጨዋታው ተቀበለኝ፡፡ አጣድፍ ከድርም እንድወጣ ካደረገኝ ብሀላ ካፌ ወሰደኝ፡፡ ካፌ ስንደርስ የመጀመሪያዎቹ ሳንሆን አንቀርም፡፡ ለምን በጥዋት እንደዚ እንደጠራኝ ስጠይቀው "ርቦኝ ነው "ሲል የመለሰልኝ መልስ በጣም አሳቀኝ፡፡ ትልቅ ቁምነገር እንደሚነግረኝ ሰው እንደዚ አሩዋሩጦ ያመጣኝ ለመብላት መሆኑን ሳስበው ሳቄን ማቁዋረጥ አልቻልኩም፡፡ ከጨዋታው በላይ ድፍረቱም ተመችቶኛል፡፡ ቁርስ ከጨረስን ቡሀላ ዛሬ ምሄድበት ከሌለ አብረን እንድንውል ጠየቀኝ፡፡ ምንም መሄጃ ስለሌለኝ አብሬው ለመዋል ተስማማው፡፡ ቀኑን ሙሉ ቦታ እየቀያየርን ስንስቅ እና ስንጫወት ጊቢውን ሳቅ በሳቅ አደረግነው፡፡ ኪሩቤል ለሳቅ የተፈጠረ ሰው እስኪመስለኝ ድረስ ባየው ነገር በሙሉ ሳቅ መፍጠር ይችላል፡፡ በደረስንበት ቦታ ሁሉ ጨዋታ ያመጣል፡፡ ያለፉትን አመታት በሙሉ ሳቅ በሳቅ ያደረጋቸው እስኪመስል ድረስ ነው ያዝናናኝ፡፡ ማታ ላይ እራት በልተን ተጨዋውተን ዶርም ከሸኘኝ ብሀላ "ዛሬ ግን አልደውልልሽም" አለኝ፡፡ 'ለምን 'ብዬ ስጠይቀው "እሱን ደውይና በስልክ ነግርሻለው" ብሎኝ አቅፎ ከሳመኝ ብሀላ ቻው ብሎኝ ሄደ፡፡ ዶርም ከገባው ቡሀላ ልብሴን ቀያይሬ አልጋዬ ላይ ከወጣው ቡሀላ ለኪሩቤል ደወልኩለት 'ለምንድነው ቆይ አልደውልም ያልከኝ? ' አልኩት ዝቅ ባለ ድምፅ፡፡ "እንዴ እኔ አልደውልም ያልኩት አንቺ እንድትደውይ ነዋ "አለኝ እየሳቀ፡፡ አይ ኪሩቤል በነዚ ቀናት ልቤን ሚነካ ደስታን የፈጠረ ሰው ነው፡፡ ጉዋደኞቼን ረሳዋቸው፡፡ የፍሬን ናፍቆት በትንሹም ቢሆን አስታገሰልኝ፡፡' ብቻዬን መሆኔን አይቶ ፈጣሪ ያመጣልኝ ጉዋደኛዬ ነክ 'ስል በጨዋታ መሀል ነገርኩት፡፡ ከዛም በመቀጠል ግቢ ከገባው ግዜ ጀምሮ ስላለው የግቢ ህይወቴ በአጠቃላይ ነገርኩት፡፡ ባገኘውት በሁለት ቀን ውስጥ እነዴት እንዲ አምኜ ስለራሴ እንደነገርኩት አላውቅም ግን በውስጤ ስለሱ የሆነ እምነት አደረብኝ፡፡ ስለኔ በነገርኩት ግዜ የነገረኝ ምክር አዘል ነገር ልክ እኔ ምፈልገውን እና ማስበውን አይነት ነገር ነበር፡፡ ውስጤን ሚያነበው ያህል ነው የተሰማኝ፡፡ ቀልዱንም ሆነ ቁምነገሩን ይችልበታል፡፡ በስልክ በጣም ብዙ ሰአት ካወራን ብሀላ ጥዋት እንገናኝ ተባብለን ተሰነባበትን፡፡ ኪሩቤል የመከረኝን ደግሜ ደጋግሜ ማሰላሰል ጀመርኩ፡፡ የነገረኝ ነገሮች በሙሉ በትክክል አስባቸው የነበሩትን ነው፡፡ እሱን እያሰላሰልኩ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡ ጥዋት እንደትናንቱ የኪሩቤል ስልክ ቀሰቀሰኝ፡፡ አብረን ቁርስ መብላት ፣መጫወት ፣መሳሳቅ ብቻ ጥሩ ጊዜን እያሳለፍን ነው፡፡ እመኛቸውው የነበሩ ቀናቶችን ማሳለፍ ጀመርኩኝ፡፡ ሀሳብ ጭንቀት የሌለባቸውን ቀናት ማሳለፍ ጀመርኩኝ፡፡ ኪሩቤል በነዚህ ሶስት ቀናት ብዙ ነገሮችን በሳቅ እያወዛ የሞራል ግንባታን ጨምሮ ብዙ ትምህርት ሰጠኝ፡፡ ነገ ጉዋደኞቼ ይመጣሉ፡፡ እሱንም ያወኩት ሚጣ በመደወሉዋ እንጂ ረስቼው ነበር፡፡ ከሁንም ለፍሬ ስልክ መደወሉን አላቆምኩም ፡፡ በሌላ ስልክም ብደውል አይነሳም፡፡ ዴቭን ስጠይቀው ሰላም ነው ይለኛል፡፡ ምን አድርጌው እንደዘጋኝ አላውቅም፡፡ ወይ ትምህርት ሲጀመር መምጣቱ ስለማይቀር የዛኔ አገኘዋለው ስል አሰብኩ፡፡ ከኪሩቤል ጋር ግቢ ውስጥ ያልረገጥነው ቦታ የለም ማለት ይቻላል፡፡ ሙሉ ቀን ሳቅ እና ጨዋታ፡፡ ጉዋደኞቼ ሲመጡ እንደማስተዋውቀው ቃል ገባውለት፡፡ ,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,, •●◉Join us share◉●•• @tinsugt
Показать все...
​​ሴና ❤️ ክፍል 33 . . . እኔ ሳቅ በሳቅ ሆኛለው፡፡ ኪሩቤል በጣም ነው ያዝናናኝ፡፡ ብዙ ከሳኩኝ ብሀላ " አንዴ ላቁዋርጥሽ እና ምን እንዘዝ?" አለኝ ሳቄ አላልቅ ሲለው፡፡ እሱ የተመቸውን እንዲያዝ ከፈቀድኩለት ቡሀላ ምግብ ቀርቦ መመገብ ጀመርን፡፡ ምግቡን እስክንጨርስ እንኳ ሳቅ አልተለየኝም ነበር፡፡ ምሳችንን ከጨረስን ብሀላ አንድ ቦታ ላሳይሽ ብሎኝ ይዞኝ ከካፌው ወጣ፡፡ በመንገዳችን ላይ በሚያወራው ወሬ እና በሚያደርገው ድርጊት በጣም ነበር ሚያዝናናኝ፡፡ ብዙ ከሄድን ብሀላ የግቢው ዋና መውጫ በር ጋ ደረስን፡፡ "እንዴ ምታሳየኝ ቦታ የት ነው?" አልኩት ወደ መውጫ በር ጋ ቆሜ፡፡ "እዚሁ ቅርብ ነው በእግር የ3ደቂቃ መንገድ "አለኝ፡፡ ከግቢ ውጪ የትም እንደማልሄድ ከታላቅ ይቅርታ ጋር ገለፅኩለት፡፡ ትንሽ ቢወተውተኝም እሺ ልለው አልቻልኩም፡፡ "በቃ አንቺ ካልሄድሽ እኔ ደርሼ መጣለው እና ቡሀላ እራት ላይ ይመችሻል?" አለኝ፡፡ "እኔንጃ ከተመቸኝ ደውልልካለው"ብዬው ከተሰነባበትን ቡሀላ እሱ ከግቢው ወጥቶ ሄደ፡፡ እኔም ወደ ሁዋላ ተመልሼ ወደዶርም ማቅናት ጀመርኩ፡፡ ደስ ሚል ግዜ ነበር ያሳለፍኩት፡፡ ዶርም እንደገባው አልጋዬላይ በጀርባዬ ተጋድሜ ለፍሬ ስልክ መደወል ጀመርኩ ፡፡ ይጠራል ግን አያነሳም፡፡ ሁለት ግዜ ሞክሬ ተውኩ፡፡ ስልኬን አሰቀምጬ ጋደም ባልኩበት የኪሩቤልን ጨዋታና ቀልዶች እያስታወስኩ ደግሜ እንዳዲስ እስቅ ጀመር፡፡ ትንሽ እንደቆየ ጋደም ባልኩበት እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡ ከእንቅልፌ ስነቃ አስራሁለት ሰአት አልፎአል፡፡ ከአልጋዬ ወርጄ በመስኮት ወደውጪ ሳይ እየጨለመ ነው፡፡ ወዲያው ስልኬን አንስቼ ለ ኪሩቤል ደወልኩለት፡፡ ገና ከመጥራቱ ኪሩቤል ስልኩን አንስቶ መጮህ ጀመረ" በፈጣሪ ስም ሀያ ደቂቃ ብታረፍጂ ኖሮ መቶ ብር አስበልተሽኝ ነበር፡፡ ለትንሽ አተረፍሽኝ፡፡ በቃ የእራት ብር ሸቅያለው በሱ እንበላለን መጣው "ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡ ለማለት የፈለገው አልገባኝም ግን ልብሴን እና ፀጉሬን አስተካክዬ ልወጣ ስል ለካ የት እንደምንገናኝ አልነገረኝም ፡፡ መልሼ ደወልኩ አሁንም እንደቅድሙ በፍጥነት አንስቶት "የት እንደምንገናኝ ነዋ ልትጠይቂኝ የፈለግሽው የቅድሙ ካፌ በር ላይ ነይ፡፡ መልሰሽ በመደወልሽ ቦነስ አግኝተናል በዚ ደሞ ሻይ እንጠጣለን" ብሎ ስልኩን መልሶ ዘጋው፡፡ በጣም ግራ አጋባኝ ምን እንዳገኘን ምን እንዳወራ ምንም አልገባኝም፡፡ ቢሆንም ተስተካክዬ ስጨርስ ከዶርም ወጥቼ ወደ ካፌው አቀናው፡፡ ከካፌው ስደርስ ኪሩቤል ቀድሞኝ ወደ በሩ ጋር ቆሞ እየጠበቀኝ ነበር፡፡ እንደተገናኘን ሰላምታ ከተለዋወጥን ብሀላ ምንም ሳያወራኝ ወደውስጥ ገባን፡፡ውስጥ ቦታ ይዘን ከተቀመጥን ብሀላ "ቆይ ቅድም ምንድነው በስልክ ያልከኝ? ምንድነው ማስበላክ? ምንድነው የሻይ ተጨመረልን ያልከኝ?" ስል ጥያቄ አከታተልኩበት፡፡ "ነግርሻለው ቆይ እራት አዝዤ ልምጣና የአሁኑ የኔ ግብዣ ስለሆነ አንቺ እንድትመርጪ አልፈቅድልሽም" ብሎ በተቀመጥኩበት ትቶኝ ሄደ፡፡ ትንሽ ቆይቶ እንደተመለሰ ስለሁኔታው ያስረዳኝ ጀመር፡፡" የውልሽ ቅድም እራት እንብላ ብለሽ እስከ 1 ሰአት እንደምትደውይ ከጉዋደኞቼ ጋር ተወራርጄ ነበር፡፡ ለአንድ ሀያ ጉዳይ በመደወልሽ ይኸው መቶ ብር ሸቀልን፡፡ እንደገና ደግሞ ወዲያው ስልኩን እንደዘጋውት የት እንደምንገናኝ ልትጠይቂኝ መልሰሽ እንደምትደውይ ወዲያው በሀያ ብር አስያዝኩ፡፡ እንደፈራውትም መልሰሽ ደወልሽ፡፡ ይኸው ተጨማሪ ሀያ ብር ሸቀልን ማለት ነው፡፡" አለኝ ዝርዝር ብሮች እያሳየኝ፡፡ ነገረ ስራው በሙሉ አስቂኝ ነው፡፡ ለምን እንዴት ሚሉ ሌሎች ጠሸያቄዎችን ላነሳበት አልፈለኩም፡፡ ያዘዝነው እራት መጥቶ እየተመገብን መጨዋወት ጀመርን፡፡በመሀል በመሀል ማውቃቸው ልጆችን ሰላም ስል አይቶ "የዲን ልጅ ነሽ እንዴ?" አለኝ፡፡ ንግግሩ እና መልሱ እንዳለ የተጠና ነው ሚመስለው፡፡ ምሽት ላይ አሪፍ ግዜ ካሳለፍን ቡሀላ በጣም ስለመሸ እንሂድ ተባብለን ከካፌ ወጣን፡፡ ኪሩበል በተለመደው ጨዋታው እያዝናናኝ ዶርም ድረስ ሸኝቶኝ ሊሄድ ሲል 'አትገባም?' ስል ጠየኩት፡፡ "እሺ "ብሎ ተከተለኝ፡፡ ሳቄን መቆጣጠር አልቻልኩም፡፡ እንደምንም ሳቄን አቁሜ 'ሆሆሆ ወንድሜ አንተ አታደርገውም አይባልም 'አልኩትና መልሼው እኔ ወደዶርሜ ገባው፡፡ዶርም እንደደረስኩ የመጀመሪያው ስራዬ ለፍሬ ስልክ መደወል ነበር፡፡ ነገር ግን አሁንም ስልኩ አይጠራም፡፡ በጣም ተናደድኩኝ ስልኬን ጠረቤዛው ላይ ወርውሬ ልብሴን እንኳ ሳልቀይር አልጋዬላይ ወጥቼ በጀርባዬ ጋደም አልኩ፡፡ 'ፍሬ ምን ሆኖ ነው? የኔን ስልክ ብቻ ነው ማያነሳው ወይስ? ነገ በሌላ ስልክ እደውልለታለው ቆይ 'ብዬ ከራሴ ጋር እያወራው ስልኬ ጠራ ፡፡ በፍጥነት ከአልጋው ወርጄ የደወለውን ሳይ . . . ,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,, ••●◉Join us share◉●•• @tinsugt
Показать все...
​​ሴና ❤️ ክፍል 32 . . . ልክ ዶርም እንደደረስኩ በሩን ልከፍተው ስል ቁልፍ ነው፡፡ ማንም የለም ማለት ነው፡፡ የኔን ቁልፍ አውጥቼ በሩን ከፍቼ ገባው፡፡ ዶርሙ ያኔ ስንሄድ ትተነው እንደሄድነው ነው፡፡ ደነገጥኩኝ! ማንም አልመጣም ማለት ነው? ቦርሳዬን ካስቀመጥኩ ቡሀላ ስልኬን አውጥቼ ለሚጣ ደወልኩላት፡፡ ስለተነፋፈቅን ብዙ አወራን፡፡ ሰሞኑኑን ስልኬ ተበላሽቶ እንደተዘጋ እና አሁን ዶርም እንደሆንኩ ስነግራት ብዙ ቀን ደውለው እንዳጡኝ ነግራኝ" ምዝገባ ሀሙስ ስለሆነ እሮብ እንግባ ተባብለን ነው " አለችኝ፡፡ በጣም ተበሳጨው፡፡ ግን ወደቤት ከምመለስ ሁለት ቀን ዶርም ብቻዬን ባድር ይሻለኛል ብዬ ወሰንኩ፡፡ አልጋዬ ላይ ጋደም ብዬ ለፍሬ ደወልኩለት ፤አያነሳም፡፡ ደጋገምኩ መልስ የለም፡፡ ለ ዴቭ ደወልኩለት ገና ከማንሳቱ በወሬው ሳስቀኝ ጀመር፡፡ በመደወሌ በጣም ነው የተገረመው፡፡ ትንሽ ካወራውት ብሀላ ስለ ፍሬ ጠየኩት፡፡እሱ ሀዋሳ እንዳለና ፍሬን በስልክ እንጂ በአካል እንዳላገኘው ነገረኝ፡፡ ለመጨረሻ ግዜ ከሰአታት በፊት መደዋወላቸውን ገልፆ ደህና እንደሆነ ሲነግረኝ ተረጋጋው፡፡ ጊቢ ከመጣ እንዲደውልልኝ ነግሬው ስልኩን ዘጋውት፡፡ ዶርም ውስጥ ብቻዬን መቀመጡ ሲጨንቀኝ ራሴን ዘና ለማድረግ ወደ ካፌ ሄጄ ሻይ እየጠጣው ቲቪ ማየት ጀመርኩ፡፡ ካፌው ውስጥ ብቻዬን የተቀመጥኩት እኔ ብቻ ነኝ፡፡ከአንድ ጥግ ተቀምጬ ቲቪ እያየው ሻይ ጠጣለው፡፡ በመሀል በመሀል ስልኬን እያነሳው ለፍሬ ደውላለው፡፡ አሁንም አያነሳም፡፡ምናልባት ስራ ላይ ይሆናል ስል አሰብኩ፡፡ስልኬን አስቀምጬ ቲቪውን መመልከቴን ቀጠልኩ፡፡ ብቻዬን ቁጭ በማለቴ ጨንቆኛል፡፡ ግን ዶርም ገብቼ ከምተኛ አዚህ ብቀመጥ ይሻለኛል ስል አሰብኩ፡፡ ቲቪውን እየተመለከትኩ ድንገት "ቲቪ ውስጥ ማንን እየፈለግሽ ነው? እንደዚ ያፈጠጥሽበት?" አለኝ አንድ ወንድ አጠገቤ ቆሞ፡፡ ቀና ብዬ አየውት፡፡ ምንም መልስ ሳልሰጠው አይኔን ወደ ቲቪው መለስኩኝ፡፡ " ከቅድም ጀምሮ እያየውሽ ነበር ብቻሽን ሆነሽ የቀጠርሽው ወይ የቀጠርሻት አሊያም የቀጠርሻቸው ቀሩ መሰለኝ፡፡ ቅር ካላለሽ ልቀመጥ? እኔም የቀጠርኳት ቀርታ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ከምቆዝም ይሻላል" አለኝ አጠገቤ እንደቆመ፡፡ በእርግጥ ለኔም ብቻዬን ከመቀመጡ የተሻለ ነው፡፡ "እና ለምን ቆምክ አትቀመጥም?" አልኩት፡፡ "አረ ሳላስፈቅድ የመቀመጥ ልምዱም ስርአቱም ድፍረቱም ወጉም የለኝም፡፡ አስፈቅዶ በመቀመጥ አንቱታን ያተረፍኩ ተቀማጭ ነኝ፡፡ የቱጋ ልቀመጥ ታዲያ አንቺ የመረጥሽልኝ ወንበር ይመቸኛል?" አለኝ ፈገግ እያለ፡፡ ንግግሩ አዝናንቶኛል፡፡ የፈለከው አልኩት ፈገግታዬን ሳልደብቅ፡፡ ፈገግ ስል ይበልጥ ቀለል አለው መሰለኝ ከፊት ለፊቴ ያለውን ወንበር እየሳበ ወሬውን ካቆመበት ቀጠለ፡፡ "እናም እልሻለው ባትመጪም ቅጠሪኝ ብያት ላትመጣ ቀጥራኝ ይኸው ጠብቃታለው " አለኝ ወንበሩ ላይ ተስተካክሎ እየተቀመጠ፡፡ ታሪኩን ከመሀል ጀምሮ መሀል ላይ አቆመው፡፡ ምንም አላልኩትም ፈገግ ብዬ ተቀበልኩት፡፡ "ኪሩቤል እባላለው "አለኝ ቀኝ እጁን እየዘረጋልኝ፡፡ "ሴና እባላለው "አልኩት እየጨበጥኩት፡፡ ጠይም ረዘም ያለ ተጫዋች ቆንጅዬ ነገር ነው፡፡ ገና ከመምጣቱ ጀምሮ ፈገግታ ከፊቱ አልተለየውም፡፡ ከኪሩቤል ጋር ብዙ ተጨዋወትን፡፡ እሱ እየተናገረ እኔ እያዳመጥኩ አልፎ አልፎ እኔም እየተናገርኩ እየተሳሳቅን ሳናስበው ብዙ ቆየን፡፡ ምሳ ሰአት ሲደርስ ኪሩቤል የእጅ ሰአቱን ከተመለከተ ብሀላ "ካፌ ሳይዘጋ ልሂድ ምሳ ትሄጃለሽ ወይስ እዚ ነሽ?" አለኝ፡፡ አይ እኔ እዚሁ ነኝ አልኩት፡፡ "እንደዛ ከሆነ በቃ እዚሁ በላለው" አለኝ "እንዴ ታዲያ ለምን መጀመሪያ ልሂድ አልክ?" ስለው "አይ ምሳ እዚ ልብላ ምናምን ስል ጉራ እንዳይመስል ነው ለዛሬ እዚ ለመብላት ሚሆን አላጣም" ብሎ ከኪሱ ብዙ ዝርዝር ብር አወጣ፡፡ ነገረ ስራው አሳቀኝ፡፡ "አትሳቂ ይደርስብሻል እኔም ደርሶብኝ ነው" አለኝ ከሌላኛው ኪሱም ዝርዝር ሳንቲም እያወጣ፡፡ "ምንድነው የደረሰብክ?" አልኩት ሳቂን በግድ እያፈንኩ፡፡ "ብዙ ብር የያዝኩ እንዲመስለኝ ከቤት የተሰጠኝን 100ብሩ በሳንቲም እና በአንዳንድ ብር ዘርዝሬ ነው" አለኝ ጠረቤዛላይ የዘረገፈውን ሳንቲም እያስተካከለ፡፡ ከዚ በላይ ሳቄን መቆጣጠር አቃተኝ . . .ለቀኩት 'ይሄሁሉ 100ብር ነው? አልኩት፡፡ አዎ አለኝ በጭንቅላቱ አነቃንቆ፡፡ ሳንቲሙን አስተካክሎ ከጨረሰ ብሀላ ወደ ኪሱ እየመለሰ "በቃ አንዳንድ ምግብ አዘን በአንድ ላይ አድርገን እንብላ ?" አለኝ ፈገግታ በማይለየው ፊቱ፡፡ እኔ ሳቅ በሳቅ ሆኛለው . . . ,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,, •●◉Join us share◉●•• @tinsugt
Показать все...
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.