cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

መጽሐፈ ግጻዌ

ይህ ቻናል በየእለቱ በቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚባሉትን ምስባክና የሚነበቡትን የወንጌል ንባባት የሚያስተላልፍ ነው።

Больше
Рекламные посты
3 342
Подписчики
+1224 часа
+447 дней
+14230 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

1.05 KB
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ማቴ. 13:1-31፡ "ወበይእቲ ዕለት ወፂኦ ኢየሱስ" - "1፤በዚያን፡ቀን፡ኢየሱስ፡ከቤት፡ወጥቶ፡በባሕር፡አጠገብ፡ተቀመጠ፤ ርሱም፡በታንኳ፡ገብቶ፡እስኪቀመጥ፡ድረስ፡ብዙ፡ሰዎች፡ወደ፡ርሱ፡ተሰበሰቡ፥ሕዝቡም፡ዅሉ፡በወደቡ፡ቆመው፡ነበር። በምሳሌም፡ብዙ፡ነገራቸው፡እንዲህም፡አላቸው፦እንሆ፥ዘሪ፡ሊዘራ፡ወጣ። 4፤ርሱም፡ሲዘራ፡አንዳንዱ፡በመንገድ፡ዳር፡ወደቀ፥ወፎችም፡መጥተው፡በሉት። ሌላውም፡ብዙ፡መሬት፡በሌለበት፡በጭንጫ፡ላይ፡ወደቀ፤ ጥልቅ፡መሬትም፡ስላልነበረው፡ወዲያው፡በቀለ፥ ፀሓይ፡በወጣ፡ጊዜ፡ግን፡ጠወለገ፥ሥርም፡ስላልነበረው፡ደረቀ። ሌላውም፡በሾኽ፡መካከል፡ወደቀ፥ሾኽም፡ወጣና፡ዐነቀው። ሌላውም፡በመልካም፡መሬት፡ወደቀ፤አንዱም፡መቶ፥ አንዱም፡ስድሳ፥አንዱም፡ሠላሳ፡ፍሬ፡ሰጠ። የሚሰማ፡ዦሮ፡ያለው፡ይስማ። ደቀ፡መዛሙርቱም፡ቀርበው፦ስለ፡ምን፡በምሳሌ፡ትነግራቸዋለኽ፧አሉት። ርሱም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦ለእናንተ፡የመንግሥተ፡ሰማያትን፡ምስጢር፡ማወቅ፡ተሰጥቷችዃል፥ለእነርሱ፡ግን፡አልተሰጣቸውም። ላለው፡ይሰጠዋልና፥ ይበዛለትማል፤ከሌለው፡ግን፡ያው፡ያለው፡እንኳ፡ይወሰድበታል። ስለዚህ፥እያዩ፡ስለማያዩ፥ እየሰሙም፡ስለማይሰሙ፥ስለማያስተውሉም፡በምሳሌ፡እነግራቸዋለኹ። መስማት፡ትሰማላችኹና፡አታስተውሉም፥ማየትም፡ታያላችኹና፡አትመለከቱም። በዐይናቸው፡እንዳያዩ፥በዦሯቸውም፡እንዳይሰሙ፥ በልባቸውም፡እንዳያስተውሉ፥ተመልሰውም፡ እንዳልፈውሳቸው፥የዚህ፡ሕዝብ፡ልብ፡ደንድኗልና፥ዦሯቸውም፡ደንቍሯል፥ ዐይናቸውንም፡ጨፍነዋል፡የሚል፡ የኢሳይያስ፡ትንቢት፡በእነርሱ፡ይፈጸማል። የእናንተ፡ግን፡ዐይኖቻችኹ፡ስለሚያዩ፡ዦሮዎቻችኹም፡ስለሚሰሙ፡ብፁዓን፡ናቸው። እውነት፡እላችዃለኹ፥ብዙዎች፡ነቢያትና፡ጻድቃን፡የምታዩትን፡ሊያዩ፡ተመኝተው፡አላዩም፥ የምትሰሙትንም፡ሊሰሙ፡ተመኝተው፡አልሰሙም። እንግዲህ፡እናንተ፡የዘሪውን፡ምሳሌ፡ስሙ። የመንግሥትን፡ቃል፡ሰምቶ፡በማያስተውል፡ዅሉ፥ክፉው፡ይመጣል፥በልቡ፡የተዘራውንም፡ይነጥቃል፤በመንገድ፡ዳር፡የተዘራው፡ይህ፡ነው። በጭንጫ፡ላይ፡የተዘራውም፡ይህ፡ቃሉን፡ሰምቶ፡ወዲያው፡በደስታ፡የሚቀበለው፡ነው፤ ነገር፡ግን፥ለጊዜው፡ነው፡እንጂ፡በርሱ፡ሥር፡የለውም፥በቃሉ፡ምክንያትም፡መከራ፡ወይም፡ስደት፡ በኾነ፡ጊዜ፡ወዲያው፡ይሰናከላል። በሾኽ፡መካከል፡የተዘራውም፡ይህ፡ቃሉን፡የሚሰማ፡ነው፥የዚህም፡ዓለም፡ዐሳብና፡የባለጠግነት፡ መታለል፡ቃሉን፡ያንቃል፥የማያፈራም፡ይኾናል። በመልካም፡መሬት፡የተዘራውም፡ይህ፡ቃሉን፡ሰምቶ፡የሚያስተውል፡ነው፤ርሱም፡ፍሬ፡ያፈራል፡ አንዱም፡መቶ፡አንዱም፡ስድሳ፡አንዱም፡ሠላሳ፡ያደርጋል። ሌላ፡ምሳሌ፡አቀረበላቸው፡እንዲህም፡አለ፦መንግሥተ፡ሰማያት፡በዕርሻው፡መልካም፡ዘርን፡የዘራን፡ሰው፡ትመስላለች። ሰዎቹ፡ሲተኙ፡ግን፡ጠላቱ፡መጣና፡በስንዴው፡መካከል፡እንክርዳድን፡ዘርቶ፡ኼደ። ስንዴውም፡በበቀለና፡ባፈራ፡ጊዜ፥እንክርዳዱ፡ደግሞ፡ያን፡ጊዜ፡ታየ፡ የባለቤቱም፡ባሪያዎች፡ቀርበው፦ጌታ፡ሆይ፥ መልካምን፡ዘር፡በዕርሻኽ፡ዘርተኽ፡ አልነበርኽምን፧እንክርዳዱንስ፡ከወዴት፡አገኘ፧አሉት። ርሱም፦ጠላት፡ይህን፡አደረገ፡አላቸው።ባሮቹም፦እንግዲህ፡ኼደን፡ብንለቅመው፡ትወዳለኽን፧አሉት። ርሱ፡ግን፦እንክርዳዱን፡ስትለቅሙ፡ስንዴውን፡ከርሱ፡ጋራ፡እንዳትነቅሉት፡አይኾንም። ተዉአቸው፤ እስከ፡መከር፡ጊዜ፡ዐብረው፡ይደጉ፤በመከር፡ጊዜም፡ዐጫጆችን፦እንክርዳዱን፡አስቀድማችኹ፡ልቀሙ፡በእሳትም፡ለማቃጠል፡በየነዶው፡እሰሩ፥ስንዴውን፡ግን፡በጐተራዬ፡ክተቱ፡እላለኹ፡አለ። ሌላ፡ምሳሌ፡አቀረበላቸው፡እንዲህም፡አለ፦መንግሥተ፡ሰማያት፡ሰው፡ወስዶ፡በዕርሻው፡የዘራትን፡የሰናፍጭ፡ቅንጣት፡ትመስላለች።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
Показать все...
👍 1
7/11/2016 ዓ.ም (፯/፲፩/፳፻፲፮ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ሣህሉ ለእግዚአብሔር መልዐ ምድረ። ወበቃለ እግዚአብሔር ጸንዐ ሰማያት። ወእምእስትንፋሰ አፉሁ ኵሉ ኃይሎሙ፡፡ መዝ 32፡ 🕯 ትርጉም የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች። በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ። ሰራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
Показать все...
07/11/2016 ዓ.ም (፯/፲፩/፳፻፲፮ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 አርውዮ ለትለሚሃ። ወአሥምሮ ለማዕረራ። ወበነጠብጣብከ ትበቊል ተፈሢሓ። መዝ. 64፥10 🕯 ትርጉም ትልሟን ታረካለህ። ቦይዋንም ታስተካክላለህ። በነጠብጣብ ታለሰልሳታለህ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
Показать все...
👍 3
1.82 KB
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ዮሐ. 1:1-6 "ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ" - "በመዠመሪያው፡ቃል፡ነበረ፥ቃልም፡በእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ነበረ፥ቃልም፡እግዚአብሔር፡ነበረ። ይህ፡በመዠመሪያው፡በእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ነበረ። ዅሉ፡በርሱ፡ኾነ፥ከኾነውም፡አንዳች፡ስንኳ፡ያለርሱ፡አልኾነም። በርሱ፡ሕይወት፡ነበረች፥ሕይወትም፡የሰው፡ብርሃን፡ነበረች። ብርሃንም፡በጨለማ፡ይበራል፥ጨለማም፡አላሸነፈውም። ከእግዚአብሔር፡የተላከ፡ስሙ፡ዮሐንስ፡የሚባል፡አንድ፡ሰው፡ነበረ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
Показать все...
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ማቴ. 24: 15-36 "ወይእተ ዓሚረ ይበጽሕ ሕልቀት " - "15፤እንግዲህ፡በነቢዩ፡በዳንኤል፡የተባለውን፡የጥፋትን፡ርኵሰት፡በተቀደሰችው፡ስፍራ፡ቆሞ፡ስታዩ፥አንባቢው፡ ያስተውል፥ 16፤በዚያን፡ጊዜ፡በይሁዳ፡ያሉት፡ወደ፡ተራራዎች፡ይሽሹ፥ 17፤በሰገነትም፡ያለ፡በቤቱ፡ያለውን፡ሊወስድ፡አይውረድ፥ 18፤በዕርሻም፡ያለ፡ልብሱን፡ይወስድ፡ዘንድ፡ወደ፡ዃላው፡አይመለስ። 19፤በዚያችም፡ወራት፡ለርጕዞችና፡ለሚያጠቡ፡ወዮላቸው። 20፤ነገር፡ግን፥ሽሽታችኹ፡በክረምት፡ወይም፡በሰንበት፡እንዳይኾን፡ጸልዩ፤ 21፤በዚያን፡ጊዜ፡ከዓለም፡መዠመሪያ፡ዠምሮ፡እስከ፡ዛሬ፡ድረስ፡ያልኾነ፡እንግዲህም፡ከቶ፡የማይኾን፡ ታላቅ፡መከራ፡ይኾናልና። 22፤እነዚያ፡ቀኖችስ፡ባያጥሩ፡ሥጋ፡የለበሰ፡ዅሉ፡ባልዳነም፡ነበር፤ነገር፡ግን፥እነዚያ፡ቀኖች፡ ስለተመረጡት፡ሰዎች፡ያጥራሉ። 23፤በዚያን፡ጊዜ፡ማንም፦እንሆ፥ክርስቶስ፡ከዚህ፡አለ፡ወይም፦ከዚያ፡አለ፡ቢላችኹ፡አትመኑ፤ 24፤ሐሰተኛዎች፡ክርስቶሶችና፡ሐሰተኛዎች፡ነቢያት፡ይነሣሉና፥ቢቻላቸውስ፡የተመረጡትን፡እንኳ፡እስኪያስቱ፡ ድረስ፡ታላላቅ፡ምልክትና፡ድንቅ፡ያሳያሉ። 25፤እንሆ፥አስቀድሜ፡ነገርዃችኹ። 26፤እንግዲህ፦እንሆ፥በበረሓ፡ነው፡ቢሏችኹ፥አትውጡ፤እንሆ፥በዕልፍኝ፡ነው፡ቢሏችኹ፥አትመኑ፤ 27፤መብረቅ፡ከምሥራቅ፡ወጥቶ፡እስከ፡ምዕራብ፡እንደሚታይ፥የሰው፡ልጅ፡መምጣት፡እንዲሁ፡ይኾናልና፤ 28፤በድን፡ወዳለበት፡በዚያ፡አሞራዎች፡ይሰበሰባሉ። 29፤ከዚያች፡ወራትም፡መከራ፡በዃላ፡ወዲያው፡ፀሓይ፡ይጨልማል፥ጨረቃም፡ብርሃኗን፡ አትሰጥም፥ከዋክብትም፡ከሰማይ፡ይወድቃሉ፥ 30፤የሰማያትም፡ኀይላት፡ይናወጣሉ።በዚያን፡ጊዜም፡የሰው፡ልጅ፡ምልክት፡በሰማይ፡ይታያል፥በዚያን፡ ጊዜም፡የምድር፡ወገኖች፡ዅሉ፡ዋይ፡ዋይ፡ይላሉ፥የሰው፡ልጅንም፡በኀይልና፡በብዙ፡ክብር፡በሰማይ፡ደመና፡ ሲመጣ፡ያዩታል፤ 31፤መላእክቱንም፡ከታላቅ፡መለከት፡ድምፅ፡ጋራ፡ይልካቸዋል፥ከሰማያትም፡ዳርቻ፡እስከ፡ዳርቻው፡ከአራቱ፡ ነፋሳት፡ለርሱ፡የተመረጡትን፡ይሰበስባሉ። 32፤ምሳሌውንም፡ከበለስ፡ተማሩ፤ጫፏ፡ሲለሰልስ፡ቅጠሏም፡ሲያቈጠቍጥ፥ያን፡ጊዜ፡በጋ፡እንደ፡ቀረበ፡ ታውቃላችኹ፤ 33፤እንዲሁ፡እናንተ፡ደግሞ፡ይህን፡ዅሉ፡ስታዩ፡በደጅ፡እንደ፡ቀረበ፡ዕወቁ። 34፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ይህ፡ዅሉ፡እስኪኾን፡ድረስ፡ይህ፡ትውልድ፡አያልፍም። 35፤ሰማይና፡ምድር፡ያልፋሉ፥ቃሌ፡ግን፡አያልፍም። 36፤ስለዚያች፡ቀንና፡ስለዚያች፡ሰዓት፡ግን፡ከአባት፡ብቻ፡በቀር፡የሰማይ፡መላእክትም፡ቢኾኑ፡ልጅም፡ ቢኾን፡የሚያውቅ፡የለም።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
Показать все...
1.24 KB
3
06/11/2016 ዓ.ም (፭/፲፩/፳፻፲፮ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 እስመ አድኀንካ ለነፍስየ እሞት። ወለአእይንትየኒ እምአንብዕ። ወለአገርየኒ እምዳህፅ። መዝ 55፥13 🕯 ትርጉም ነፍሴን ከሞት እግሮቼን ከመውደቅ አድነኻልና። በሕያዋን ብርሃን እግዚአብሔርን ደስ አሠኘው ዘንድ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
Показать все...
👍 2👏 1
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ዮሐ. 15:1-17 "አነ ውእቱ ሐረገ ወይን" - "እውነተኛ፡የወይን፡ግንድ፡እኔ፡ነኝ፤ገበሬውም፡አባቴ፡ነው። ፍሬ፡የማያፈራውን፡በእኔ፡ያለውን፡ቅርንጫፍ፡ዅሉ፡ያስወግደዋል፤ፍሬ፡የሚያፈራውንም፡ዅሉ፡አብዝቶ፡እንዲያፈራ፡ያጠራዋል። እናንተ፡ስለነገርኋችሁ፡ቃል፡አሁን፡ንጹሓን፡ናችሁ፤ በእኔ፡ኑሩ፡እኔም፡በእናንተ። ቅርንጫፍ፡በወይኑ፡ግንድ፡ባይኖር፡ከራሱ፡ፍሬ፡ሊያፈራ፡እንዳይቻለው፥እንዲሁ፡እናንተ፡ደግሞ፡በእኔ፡ባትኖሩ፡አትችሉም። እኔ፡የወይን፡ግንድ፡ነኝ፡እናንተም፡ቅርንጫፎች፡ናችሁ።ያለእኔ፡ምንም፡ልታደርጉ፡አትችሉምና፡በእኔ፡የሚኖር፡እኔም፡በእርሱ፥እርሱ፡ብዙ፡ፍሬ፡ያፈራል።;በእኔ፡የማይኖር፡ቢሆን፡እንደ፡ቅርንጫፍ፡ወደ፡ውጭ፡ይጣላል፡ይደርቅማል፤እነርሱንም፡ሰብስበው፡ወደ፡እሳት፡ይጥሏቸዋል፥ያቃጥሏቸውማል። በእኔ፡ብትኖሩ፡ቃሎቼም፡በእናንተ፡ቢኖሩ፡የምትወዱትን፡ሁሉ፡ለምኑ፡ይሆንላችሁማል። ብዙ፡ፍሬ፡ብታፈሩና፡ደቀ፡መዛሙርቴ፡ብትኾኑ፡በዚህ፡አባቴ፡ይከበራል። አብ፡እንደ፡ወደደኝ፡እኔ፡ደግሞወደድዃችኹ፤በፍቅሬ፡ኑሩ። እኔ፡የአባቴን፡ትእዛዝ፡እንደ፡ጠበቅኹ፡በፍቅሩም፡እንደምኖር፥ትእዛዜን፡ብትጠብቁ፡በፍቅሬ፡ትኖራላችኹ። ደስታዬም፡በእናንተ፡እንዲኾን፡ደስታችኹም፡እንዲፈጸም፡ይህን፡ነግሬያችዃለኹ። እኔ፡እንደ፡ወደድዃችኹ፡ርስ፡በርሳችኹ፡ትዋደዱ፡ዘንድ፡ትእዛዜ፡ይህች፡ናት። ነፍሱን፡ስለ፡ወዳጆቹ፡ከመስጠት፡ይልቅ፡ከዚህ፡የሚበልጥ፡ፍቅር፡ለማንም፡የለውም። እኔ፡ያዘዝዃችኹን፡ዅሉ፡ብታደርጉ፡እናንተ፡ወዳጆቼ፡ናችኹ። ከእንግዲህ፡ወዲህ፡ባሪያዎች፡አልላችኹም፤ባሪያ፡ጌታው፡የሚያደርገውን፡አያውቅምና፤ወዳጆች፡ግን፡ብያችዃለኹ፥ ከአባቴ፡የሰማኹትን፡ዅሉ፡ለእናንተ፡አስታውቄያችዃለኹና። እኔ፡መረጥዃችኹ፡እንጂ፡እናንተ፡አልመረጣችኹኝም፤አብም፡በስሜ፡የምትለምኑትን፡ዅሉ፡እንዲሰጣችኹ፥ ልትኼዱና፡ፍሬ፡ልታፈሩ፡ፍሬያችኹም፡ሊኖር፡ሾምዃችኹ። ርስ፡በርሳችኹ፡እንድትዋደዱ፡ይህን፡አዛችዃለኹ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
Показать все...
2
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.