ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 383 подписчиков, занимая 5 582 место в категории Религия и духовность и 2 194 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 383 подписчиков.

Согласно последним данным от 09 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 38, а за последние 24 часа — -1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 21.91%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.42% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 370 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 449 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 25.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 10 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 383
Подписчики
-124 часа
-67 дней
+3830 день
Архив постов
ይናገራል ፎቶ!!፤ የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት አባላት #መስማት_ለተሳናቸው_ዝማሬ_ሲያቀርቡ፡፡ ኵሉ ነፍስ ይሴብሖ ለእግዚአብሔር፡፡ #እስትንፋስ_ያለው_ሁሉ_እግዚአብሔርን_ያመሰግናል፡፡ መዝሙረ ዳዊት
+7
ይናገራል ፎቶ!!፤ የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት አባላት #መስማት_ለተሳናቸው_ዝማሬ_ሲያቀርቡ፡፡ ኵሉ ነፍስ ይሴብሖ ለእግዚአብሔር፡፡ #እስትንፋስ_ያለው_ሁሉ_እግዚአብሔርን_ያመሰግናል፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ይናገራል ፎቶ!!፤ የፍኖተ ሕይወትና የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት አባላት #ከሰልፍ_አስተባባሪዎች_ጋር፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶
+9
ይናገራል ፎቶ!!፤ የፍኖተ ሕይወትና የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት አባላት #ከሰልፍ_አስተባባሪዎች_ጋር፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ይናገራል ፎቶ!!፤ የፍኖተ ሕይወትና የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት አባላት #ከዝማሬ_አስተባባሪዎች_ጋር፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶
+8
ይናገራል ፎቶ!!፤ የፍኖተ ሕይወትና የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት አባላት #ከዝማሬ_አስተባባሪዎች_ጋር፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ይናገራል ፎቶ!!፤ የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አባላት በዝማሬ ላይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ ht
+8
ይናገራል ፎቶ!!፤ የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አባላት በዝማሬ ላይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ይናገራል ፎቶ!!፤ የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አባላት በዝማሬ ላይ፤ #በዓለ_ጥምቀት #ከጃንሜዳ_መልስ_ያሉትን_ጕዞዎች_የሚያሳይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑ
+8
ይናገራል ፎቶ!!፤ የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አባላት በዝማሬ ላይ፤ #በዓለ_ጥምቀት #ከጃንሜዳ_መልስ_ያሉትን_ጕዞዎች_የሚያሳይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ይናገራል ፎቶ!!፤ የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አባላት በዝማሬ ላይ፤ #ከተራ_ከደብራችን_እስከ_ጃንሜዳ_ያሉትን_ጕዞዎች_የሚያሳይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑ
+8
ይናገራል ፎቶ!!፤ የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አባላት በዝማሬ ላይ፤ #ከተራ_ከደብራችን_እስከ_ጃንሜዳ_ያሉትን_ጕዞዎች_የሚያሳይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

[ Album ] የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሕፃናት ክፍል በዝማሬ ላይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤
+6
[ Album ] የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሕፃናት ክፍል በዝማሬ ላይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

የማኅበረ ቅዱሳን አባላት የጥምቀት ተሰላፊዎች በዝማሬ ላይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https:/
+1
የማኅበረ ቅዱሳን አባላት የጥምቀት ተሰላፊዎች በዝማሬ ላይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

የተለያዩ አድባራት ሰንበት ትምህርት ቤት በዝማሬ ላይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://ww
+8
የተለያዩ አድባራት ሰንበት ትምህርት ቤት በዝማሬ ላይ፡፡ ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

በቀጨኔ ደብረ ሰላም አጥቢያ ከሚገኙና ለጥምቀት ከሚሰለፉ ማኅበራት በጥቂቱ፡፡ ፠ ሰብሕዎ በቃለ ቀርን፤ ሰብሕዎ በመዝሙር ወበሰንቆ፤ #እግዚአብሔርን_በመዝሙርና_በመሰንቆ_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻
+7
በቀጨኔ ደብረ ሰላም አጥቢያ ከሚገኙና ለጥምቀት ከሚሰለፉ ማኅበራት በጥቂቱ፡፡ ፠ ሰብሕዎ በቃለ ቀርን፤ ሰብሕዎ በመዝሙር ወበሰንቆ፤ #እግዚአብሔርን_በመዝሙርና_በመሰንቆ_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

፠ ወበመዝሙር ዘ ፲ቱ አውታሪሁ ዘምሩ ሎቱ፡፡ (#ዐሥር_አውታር_ባለው_በገና_ዘምሩለት_፡፡) መዝሙረ ዳዊት ፴፪፥፫ ፠ ንፍሑ ቀርነ በዕለተ ሠርቅ፥ በዕምርት ዕለት በዓልነ፡፡ (#በከፍተኛው_በዓላችን_ቀ
+5
፠ ወበመዝሙር ዘ ፲ቱ አውታሪሁ ዘምሩ ሎቱ፡፡ (#ዐሥር_አውታር_ባለው_በገና_ዘምሩለት_፡፡) መዝሙረ ዳዊት ፴፪፥፫ ፠ ንፍሑ ቀርነ በዕለተ ሠርቅ፥ በዕምርት ዕለት በዓልነ፡፡ (#በከፍተኛው_በዓላችን_ቀን_መለከትን_ንፉ፡፡) መዝሙረ ዳዊት ፹፥፫ ፠ ሰብሕዎ በቃለ ቀርን፤ ሰብሕዎ በመዝሙር ወበሰንቆ፤ ሰብሕዎ በአውታር ወበዕንዚራ፡፡ (#እግዚአብሔርን_በመለከት_በነጋሪት_ድምፅ_አመስግኑት፤ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_በበገናና_በመሰንቆ_አመስግኑት፤ #እግዚአብሔርን_በአውታርና_እምቢልታ_አመስግኑት፡፡) መዝሙረ ዳዊት ፻፶ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ወይሴብሑ ለስሙ በትፍሥሕት፡፡ (#ስሙን_በደስታ_ያመሰግናሉ_፡፡) መዝሙረ ዳዊት ፻፵፱፥፫ (ለታቦታቱ ምንጣፍ በማንጠፍና መንገዶቹን በመጥረግ የሚያገለግሉ ወንድሞችና እኅቶች) ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈ
+7
ወይሴብሑ ለስሙ በትፍሥሕት፡፡ (#ስሙን_በደስታ_ያመሰግናሉ_፡፡) መዝሙረ ዳዊት ፻፵፱፥፫ (ለታቦታቱ ምንጣፍ በማንጠፍና መንገዶቹን በመጥረግ የሚያገለግሉ ወንድሞችና እኅቶች) ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ለአሰተርዕዮ_ማርያም_ጕዞ_ወደ_መጠቆሚያ_ማርያም_፡፡ ፠የጕዞ ቀናት፤ ረቡዕና ሐሙስ (ጥር 20-21) 2012 ዓ.ም. ፠ለመመዝገብ፤ የሰ/ትቤታችን ልማት ክፍል፣ ጽ/ቤት ወይም መዝሙርና ኪነ ጥበባት ክ
+1
#ለአሰተርዕዮ_ማርያም_ጕዞ_ወደ_መጠቆሚያ_ማርያም_፡፡ ፠የጕዞ ቀናት፤ ረቡዕና ሐሙስ (ጥር 20-21) 2012 ዓ.ም. ፠ለመመዝገብ፤ የሰ/ትቤታችን ልማት ክፍል፣ ጽ/ቤት ወይም መዝሙርና ኪነ ጥበባት ክፍል እንዲሁም በ0910 61 72 58 ወይም 0902 50 39 54 ብለው ይደውሉ፡፡ ፠የጕዞ ዋጋ፤ 250 ብር (ምግብን ጨምሮ) ፠የመመዝገቢያ ቀናት፤ እስከ ጥር 17/2012 ዓ.ም. /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#የጥምቀት_በዓል_አከባበር_በአዲስ_አበባ_ከእንጦጦ_ጋራ_ጥግ_እስከ_ጃንሆይ_ሜዳ_ በአዲስ በአበባ ያሉ ገዳማትና አድባራትም በቦታ ርቀት እስከ ተለያዩበት ቀን ድረስ በእንጦጦ ጋራ ጥግ በአንድ ላይ በመፈናኘት ያድሩ ነበር፤ ኋላ ከቦታ ርቀት በኋላ የተቀሩት በጃንሆይ ሜዳ ማደር ጀምረዋል፡፡ እያደረም ሌሎች ገዳማትና አድባራት ሲመሠረቱ ከጃንሆይ ሜዳ በተጨማሪ ለአጥቢያቸው በሚቀርብ ቦታ ማደር ጀመሩ፡፡ ፠ በዓለ ጥምቀት በጃን ሜዳ (ጃንሆይ ሜዳ) መከበር የጀመረው ከ1887 ዓ.ም. አንስቶ መሆኑ ይነገራል፡፡ ስያሜውምና አጀማመሩም ጃንሜዳ የሚለው ጃን፥ ጃኖ ከሚለው ጋራ የተዛመደ ሲሆን ነገሥታት ለመሾም ለመሻር፣ ዳኝነት ለመስጠት፣ ሊቃውንትን ለመሾምና፣ ዐዋጅ ሲያስነግሩ በቤተ መንግሥታቸው አቅራቢያ በሚገኝ ሜዳ ላይ የጃኖ ድንኳን ተክለው ያስነግራሉ፤ ይህም ሜዳ ከጃኖ ጋራ እየተናበበ የቦታ መጠሪያ ሁኗል፡፡ ለምሳሌ፤ ‹‹ጃን ተከል›› በጎንደር ነገሥታት፤ ‹‹ጃን መራቂ›› በላስታ ነገሥታት፤ ‹‹ጃን ተራራ›› በአማራ ሳይንት በአፄ በዕደ ማርያም ‹‹ጃን ሜዳ›› በደብረ ታቦርና በአዲስ አበባ ናቸው፡፡ ፠ አዲስ አበባ መዲና በሆነችበት ሰዓት ‹‹መሐል ሰፋሪ‹‹ የሚባሉ የመኳንንት ጕባኤ በዚሁ በጃንሜዳ በስውር ዐድማ የሚያደርጉበት ሆነ አድማውን ሲያደርጉም በጃን ሜዳ ያለው የጃኖው ድነኳን ከሩቅ እንዳይታይ በማቅ ይሸፈን ነበር፡፡ እቴጌ ጣይቱ ይህን የመሰለ ሜዳ የክፉ ምክር መምከሪያ ሆኖ ከሚኖር ተባርኮ ለጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቢሆን ብለው ለአፄ ምኒልክ ሃሳብ አቀረቡላቸው፤ አፄ ምኒሊክም ማለፊያ ብለው ሐሳባቸውን በመቀበል ጃን ሜዳ የጥምቀት በዓል ማክበሪያ እንዲሆን አዘዙ፡፡ እንዲሁም የአፄ ምንሊክ አልጋ ወራሻቸው ልጅ ኢያሱ መሆኑን በግንቦት 10 ቀን 1901ዓ.ም. ዐዋጅ ያስነገሩበት፤ ‹‹ንሥረ ተፈሪ›› የተባለው የመጀመሪያው አውሮፕላንም በ12921ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ያረፈውም በዚሁ ሜዳ በመሆኑ ጭምር ስያሜው ጃንሆይ ሜዳ ተባለ፡፡ ፠ በ1887ዓ.ም. በዓለ ጥምቀትን ለመጀመሪያ ጊዜ በጃን ሜዳ በሕብረት ያከበሩት የመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተክርስቲያን፣ የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ነበሩ፡፡ ፠ እስከ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ መን ድረስ ግን ታቦታቱ ወደ ቀበና ወንዝ (አፈ ንጉሥ ጥላሁን ሰፈር፤ ከፈረንሳይ ኤምባሲ በታች) ከከተራው አንስቶ አድረው በጥምቀት ዕለት ወደ ጃንሜዳ ይመለሱ ነበር፡፡ ሌሎችም በየሰበካቸው በሚገኝ አምች ቦታ ሲያከብሩ ቆይተው በ1939ዓ.ም. ከንሜዳ እጅግ በጣም ብዙ ያልራቁት (የካ ሚካኤልና ቅዱስ ዑራኤል) በንጉሠ ነገሥቱ ጥሪ ተደርጎ ወደ ጃናሜዳ እንዲመጡ ተደርጎ ነበር፤ ሆኖም ሕዝብ እየበዛ ስላስቸገረ በየአቅራቢያቸው እንዲያድሩ ተድርጓል፡፡ ፠ ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኀይለ ሥላሴ በ1936 ዓ.ም በስፍራው የውኃ ቧንቧ እንዲዘረጋ፣ ባሕረ ጥምቀት ገንዳ በግንብ እንዲሰራ፣ የኤሌክትረክ መብራት በቦታው እንዲገባ አድርገዋል፡፡ ዙሪያውን በግንብ ተሰርቶ በቧንቧ የብረት ማገር ውብ ሆኖ እንዲታጠርና በዐፀድና በአበባዎች እንዲያጌጥ አድርገዋል፡፡ ይህ ቦታ ኋላ በ1994ዓ.ም. እድሳት ተደርጎለታል፡፡ ፠ እስከ ቅርብ ጊዜያትም ድረስ ወደ ባሕረ ጥምቀት የሚወርዱ ታቦታት ከነድርባቸው ነበር፤ ለምሳሌ ቀቀጨኔ ደብረ ሰላም ከቅዱስ ገብርኤል ጋራ ነበረ፤ ኋላ ግን ድርብ ታቦታት ቀርተው ዋናውን ይዘው የሚወርዱ ሆኗል፡፡ በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ ውስጥ እስከ 2010ዓ.ም ድረስ ….. ባሕረ ጥምቀት (አብሕርተ አጥማቃት) አሉ፡፡ ፠ እስከ 1958ዓ.ም. በምስካየ ኅዙናን ተምሮ ማስተማር ማኅበርና በጠቅላይ ቤተ ክህነት የታሪክ ድርሰትና ስብከት ክፍል አስተባባሪነት ከኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ. ሐዋርያዊ ድርጅት፣ ከሊቃውንትና ከመምህራን፣ ከሰዋስወ ብርሃንና ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በተውጣጡ መምህራን በባሕረ ጥምቀቱ የስብከተ ወንጌልና፣ የመዝሙርና የድራማ መርሐ ግብር ያቀርቡ ነበር፡፡ በ1959ዓ.ም. አካባቢ ጥቂት ሰንበት ት/ቤቶች የደንብ ልብስና ነጠላ በማድረግ ታቦታቱን አጅበው አውጥውና አጅበው በመመለስ የበዓሉ ድምቀት እየሆኑ መጡ፡፡ በአሁኑ ወቅት በጃንሜዳ የሚያድሩ ታቦታት 12 ናቸው እነርሱም፤ 1ኛ. መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ.ክ.፤ 2ኛ. ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም፤ 3ኛ. መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ 4ኛ. መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ.፤ 5ኛ. ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.፤ (የምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ታቦተ ወደ ጥምቀተ ባሕር ስለማይወጣ ሕዝቡና ሰ/ት/ቤቱ አብሮ ነው የሚያከብረው) 6ኛ. መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም 7ኛ. ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ.፤ 8ኛ. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (አብሮም ቅዱስ ሚካኤል ይወርዳል)፤ 9ኛ. ቀበና መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ.፤ 10ኛ. ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ.ክ.፤ 11ኛ. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ.፤ 12ኛ. ፈለገ ሰላም ቤላ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና አቡተ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ (ቀበና 18 ፓርክ አጠገብ)፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ጥምቀት_በኢትዮጵያ፤ ፠ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠመቀው የንግሥት ሕንደኬ በጅሮንድ አቤላክ(ባኮስ) ‹‹እነሆ ውኃ አለ፣ ታድያ መጠመቅን ማን ይከለክለኛል?›› /የሐዋ. ፷፥፳፱-፴፮/ ብሎ በሐዋርያው ፊልጶስ በተጠመቀ ጊዜ ነው፡፡ ይህ ሥርዐት ግን ተስፋፍቶ የቀጠለው በነገሥታቱ በአብርሃ ወአጽብሐ (315-351ዓ.ም.) የቤተ መንግሥቱ ጃንደረባ በነበረውና ኋላ ጳጳስ በሆነው በፍሬምናጦስ(አባ ሰላማ) ዘመን ነው፡፡ በዓሉ ግን አሁን በምናከብረው ዓይነት ስዕላዊ በሆነ መልኩ መከበር የጀመረው ከማኅሌታዊው ቅዱስ ያሬድ ዜማ መስፋፋት ጋራ በአፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት (530-544ዓ.ም.) እንደሆነ ይነገራል፡፡ ፠ ገዳማቱና አድባራቱም በአቅራቢያቸው ወደሚገኙ የውኃ ምንጮች በተናጥል በመውረድ በዓለ ጥምቀትን ያከብሩ ነበር፡፡ ተቀራርበው የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ታቦታቸውን በአንድ ቦታ እንዲያሳድሩ ዐዋጅ የታወጀው፥ ትእዛዝ የተላለፈው በጻድቁና በጠቢቡ ንጉሥ ላልይብላ(1140-1180ዓ.ም.) ዘመነ መንግሥት ነው፡፡ በዚሁ ዘመን የነበሩት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአኵሱም በመቀለና በመርጡለ ማርያም ያሉ ጥምቀተ ባሕሮችን ባርከዋል፤ በአፄ ይኩኖ አምላክ ዘመን ደግሞ በአቡነ ተክለሃይማኖት አሳሳቢነት ሥርዐተ ጥምቀቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ዐዋጅ ታውጇል፡፡ እስከ አጼ ዘርዐ ያዕቆብ ድረስም ታቦታቱ ዕለቱን ጠዋት ወጥተው ማታ መለሱ ነበር፤ አፄ ዘርዐ ያዕቆብ ግን ታቦታቱ በዋዜማው ጥር 10 ከሰዐት በኋላ ወደ ትምቀተ ባሕር ወርደው እንዲያድሩ፤ አገሩንም በኪደተ እግር እንዲባርኩ፤ በሄዱበት መንገድም እንዳይመለሱ በዐዋጅ ወሰኑ፡፡ ቀጥሎም አፄ ናዖድ ሕዝቡ ታቦታቱን አጅቦ ወደ ጥምቀተ ባሕር እንዲሄድ በዐዋጅ አስነገሩ፡፡ ይህ ሥርዐትም እስካሁን ከኛ ዘንድ ደርሷል፡፡ በዘመናት ውስጥም የጥምቀት በዓል ሲከበርባቸው ከነበሩ ቦታዎች ዐበይቶቹን ለመጥቀስ ያህል፤ #በአኵሱም_የንግሥተ_ሳባ_መዋኛ_ ‹‹#ማይ_ሹም›› #በጎንደር_የአፄ_ፋሲል_መዋኛ_ገንዳ #በቅዱስ_ላሊበላ_የዮርዳኖስ_ወንዝ #በሸዋ_የአፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ_ፍርድ_መስጫ_አደባባይ #44ት #ታቦታት_የሚያድሩበት_የሸንኮራ_ሜዳ ‹‹#ኢራንቡቴ_ጥምቀተ_ባሕር›› #በአዲስ_አበባ_የጃንሆይ_ሜዳ_ (ጃንሜዳ) #በአዲስ_አበባ_የእንጦጦ_ማርያምና_ቅዱስ_ራጕኤል_ታቦት_ማደሪያ #ኀሙስ_ገበያ_ሜዳ ዐበይቶቹ ናቸው፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ከተራ_፤ ትርጕሙ ውሃን መከተር ወይም ውሃ መገደብ (መዝጋት፥ ማቆም፥ ማገድ፥ ማጠር፥ ዙሪያውን መያዝ፥ መክበብ፥ መከልከል) ማለት ነው፡፡ #ከተራ_ለምን_ተባለ? በጥምቀት በዓል ዋዜማ በጥር 10 ቀን ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውሃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ወይም ጉድጓድ ተቆፍሮ፤ ድንኳን ይተክላል፥ ዳስ ሲጣል ይውላል (ምክንያቱም ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናምና የበረዶ ወራት ስለሆነ ቅዝቃዜውም በወንዞች አጠገብ ስለሚያይል በባሕረ ዮርዳኖስ፥ በዕደ ዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ ሰዎች ድንኳን ተክለው፥ ዳስ ጥለው ያድሩ ስለነበረ ነው)፡፡ ነገር ግን በዚህ ወቅት የምንጮች ውሃ ደካማ በመሆኑ ውሃው እንዲጠራቀም ወንዶች ጉድጓድ እየቆፈሩ፥ ሴቶች ውኃ በእንስራ እየቀዱ ከወንዞችና ከምንጮች ውኃውን ይከትራሉ፥ ይገደባሉ (አሁን በከተሞች ሰው ሰራሽ ግድብ ይገደባል)፡፡ የምዕመናኑ አብዛኛው ስራ ውሃውን መከተርና መገደብ በመሆኑ ዕለቱ #ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ #አንድም በኢያሱ መሪነት እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ባሕር ሲሻገሩ ታቦቱን ያከበሩ (የያዙ) ካህናት ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ከወንዙ መሃል ቆመው ነበር ውኃውም እንደ ባሕረ ኤርትራ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ቆሞ ነበርና ይህንንም ለማስታወስ ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡ #አንድም ጌታችን በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የላይኛው ሸሽቶ እንደ ክምር ተቆልሏል (ከአዳም ጀምሮ እስከ መድኅን መወለድ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ተቋርጦ ለመቅረቱ፥ ከአበው ወደ ውሉድ ላለመተላለፉ ምሳሌ)፤ የታችኛውም ወደ ታች ሸሽቶ በመድረቁ (የአዳም ኀጢአት ከሥሩ እንደተነቀለ ዛፍ ሆና ለመውደቋ ምሳሌ) ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡ ፠ውኃ የሚከተርበት ቦታ ‹‹#ባሕረ_ጥምቀት(#ጥምቀተ_ባሕር_››) (#የታቦት_ማደሪያ) እየተባለ ይጠራል፡፡ ውኃው የሚከተረውም በማግስቱ ጥር 11 ቀን ለሚከበረው የጥምቀት በዓል መጠመቂያና የጥምቀትን በዓል ለማክበር እንዲሆን ነው፡፡ ሌሊት ማኅሌት ተቁሞ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ፥ ጠዋት ጸሎት ተደርሶ የሚጠመቅ ሕፃን ካለ እዚያው ውስጥ ይጠመቃል፡፡ ጐበዛዝትም ለቡራኬ ይዋኙበታል ምዕመናንም እንዲሁ ለቡራኬ ይረጩታል፡፡ ያ ስፍራ በዘልማድ ጥምቀተ ባሕር ተብሎ ይጠራል፡፡ #ሥርዐተ_ከተራ ፠ ታቦተ ሕግ ይዞ መጓዝና ወደ ወንዝ መውረድ የተጀመረው በአሮን ልጅ በአልዓዛር ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ቀድሞ በሙሴ ኋላ በኢያሱ መሪነትም ታቦተ ሕጉን ይዘው የዮርዳኖስን ባሕር መሻገራቸውንም ልብ ይሏል፡፡ የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁት ጊዜ ከስፍራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት፡፡ /ኢያ.3፥3/ እንዲል፡፡ ፠ የከተራ ዕለት ድንኳኑ ተተክሎ፥ ዳሱ ተጥሎና ውሃው ተከትሮ ሁሉም ነገር ከተስተካከለ በኋላ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ የደወል ድምፅ እንደተሰማ ከልጅ እስከ አዋቂ በነቂስ ተወጥቶ በዐፀደ ቤተ ክርስቲያንና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች ይሰበሰባሉ፤ የየአድባራቱና የገዳማቱ ታቦት በካህናት አማካይነት በወርቅና በብር በተንቈጠቆጠ መጐናጸፊያ እየተሸፈኑ በታቦት ጉዞ (በዝግታ) ወደ ጥምቀተ ባሕሩ ይጓዛሉ፡፡ በዚህም ጊዜ፤ *ባለ መስቀል መፆር ሰንደቅ ዓለማና ዓርማ የያዘው ግን ከሁሉም ፊት ፊት እያለ ቀድሞ ይሄዳል፡፡ *የወርቅ (ወርቀዘቦ) ካባና ላንቃ የለበሱና ጥላ የያዙት ቀሳውስትና መነኰሳት ከታቦቱ ጐን፤ *መስቀልና ጽንሐሕ የያዙት ከታቦቱ በፊት ማዕጠንት እያጠኑ ይሄዳሉ፡፡ *እንደ ቀሳውስቱ ተመሳሳይ ልብስ ተክህኖ የለበሱት ዲያቆናት ጥላ፣ ድባብ፣ መስቀልና ቃጭል ይዘው እያቃጨሉ ከቀሳውስቱ በፊት በመሆን ያጅቧቸዋል፡፡ *ወደ ባሕረ ጥምቀቱም ሲወረድ ካባ ላንቃ፥ ጥንግ ድርብ በለበሱ፥ የብር፣ የነሐስ፣ የወርቅ መቋሚያና ጽናጽል በያዙ በማኅሌታውያን መዘምራን ደባትር ሃሌታ፣ በሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ዝማሬና ሽብሸባ፣ በወጣት መዘምራን ደስታ፣ በወንዶች ሆታ፣ በሴቶች እልልታ ዲያቆናቱን ቀድመው እያጀቡ ይሄዳሉ፡፡ *የደብር አለቆችና አበው ካህናት ታቦቱን ተከትለው ይጓዛሉ፡፡ *ሕዝቡም ደግሞ ‹‹#ለጥምቀት_ያልሆነ_ቀሚስ_ይበጣጠስ›› እንዲሉ እንደየችሎታው ያለውን ልብስ (ጃኖ፣ ለምድ፣ በርኖስና የመሳሰለውን) ለብሶና አጊጦ፥ የጀብዱነት ሽልማት ያለው በሽልማቱ አጊጦ፥ ሽማግሌዎችና የጐበዝ አለቃዎችን በማስቀደም ታቦቱን በመከተል በስተኋላ ይሄዳሉ፡፡ **ነገር ግን ሴቶችና ልጆች እንደፈለጋቸው ከፊትም ከኋላም ሆነው ይሄዳሉ፡፡ ባሕረ ጥምቀትም እንደደረሱ ታቦቱ በድንኳን አጠገብ ቆሞ የዓመቱ #ተረኛ_ደብር (#የምራት_ባለተረኛ) “#ወረደ_ወልድ_እምሰማያት_ውስተ_ምጥምቃት_፤ #በፍሥሓ_ወበሰላም” (እግዚአብሔር ወልድ በሰላምና በደስታ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከሰማያት ወደ መጠመቂያው ወረደ) የሚለው #ሰላም ተመርቶ በአግባቡ ከተለዘበ በኋላ ጸሎት ተድርጐ ሲያልቅ ታቦቱ ወደ ድንኳኑ ይገባል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ግሱን ለመቃኘትና ለማሸብሸብ፣ ማኅሌት ለመቆም፣ ቅዳሴ ለመቀደስና ሌላውንም ሥርዐት ለመፈጸም ኃላፊነት ያለባቸው ተረኛ ደብር (የምራት ባለተረኞች) ሲሆኑ ለቀጣዩ (ለከርሞ) ዓመት ተረኞች የሚሆኑና በአሁኑ ዓመት የምራት ባለተረኞችን የሚረዱት ገዳማትና አድባራት ደግሞ ‹‹#አንሺዎች_›› ይባላሉ፡፡ የከተራ ዕለት የየአጥቢያው ሕዝብ በየዓመቱ ተራ እየገባ ራት ከየአካባቢው ስለሚያመጣ ያ ሲበላና ሲጠጣ ከቆየ በኋላ ወዲያው የሌሊቱ ጸሎት(ስብሐተ ማኅሌቱ) በተረኛው ደብር ካህናት ተጀምሮ አገልግሎቱ መላ ሌሊቱን ሲካሄድ ያድራል (እንደ ቀጨኔ ባሉ ታላላቅና የሊቃውንት መፍለቂያ አድባራት ተረኛ ቢሆኑም /በጥምቀተ ባሕሩና በቤተ ክርስቲያናቸው ጭምር/ ባይሆኑም በቤተ ክርስቲያናቸው ማኅሌቱን ቆመውና ቅዳሴውን ቀድሰው ያድራሉ)፡፡ ቅዳሴው የሚቀደሰው ከሌሊቱ 7-9 ሰዐት ነው፡፡ #በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት_አላቸው_እነዚሁም_፤ #ታቦቱ_የጌታችን ምሳሌ #ታቦቱን_አክብሮ_ይዞ_የሚሄደው_ካህን_የቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_ምሳሌ #ባሕረ_ጥምቀቱ_የዮርዳኖስ_ወንዝ_ምሳሌ #ታቦታቱን_አጅበው_የሚሄዱት_ምዕመናን_ወደ_ቅዱስ_ዮሐንስ_እየመጡ_የንስሐ_ጥምቀት_ሲጠመቁ_የነበሩ_ሰዎች_ምሳሌ #ታቦታቱ_በከተራ_ዕለት_ከመንበራቸው_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_መውረዳቸው_መድኀኔ_ዓለም_ክርስቶስ_በእደ_ዮሐንስ_በፈለገ_ዮርዳኖስ_ለመጠመቅ_ከገሊላ_ወደ_ዮርዳኖስ_ከማታው_ጀምሮ_መውረዱንና_ተራውን_ሲጠብቅ_አድሮ_መጠመቁን_ያጠይቃል፡፡ ‹‹ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡›› /ማቴ፡ 3፥13/ #ጥምቀቱ_የሞቱ፤ አርአያ፤ የመቃብሩ አምሳል ነው፡፡ ፠ በዓለ ጥምቀት ሰንበት (ቅዳሜና እሑድ ላይ) ካልዋለ የሚታረሰው መሬት ረድኤት በረከት ስለሚገኝበት ገበሬው አንድ ሁለት ፈር ያርሳል፡፡ ፠ በዓለ ጥምቀት ዐቢይ በዓል ስለሆነ የጥሉላት (የፍስክ) ምግብም ጭምር ስለምንመገብበት ዘንድሮ ሰኞ ስለሚውል ዋይዜማውን እሑድን የጋድ ጾም (ከጥሉላት መባልዕት) እንጾማለን፡፡ የሚቈርብ ሰው ግን አክፍሎ ያድራል፡፡ /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#፴፪ኛ) #ወረዳ_1_ #በቴል_አጠገብ_(ኳስ ሜዳ) 1ኛ. ቤቴል ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል 2ኛ. አንፎ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል #፴፫ኛ) #በላፍቶ_ክፍለ_ከተማ_ወረዳ_4 #ገብርኤል_ጠበል 1ኛ. ሰፈረ ገነት ቅድስት ሥላሴ #፴፬ኛ) #ወረዳ_2_ #ሮል_ሳሙና_ፋብሪካ_ፊት_ለፊት 1ኛ. ረጲ ደብረ ጎልጎታ መድኀኔ ዓለም 2ኛ. ካራ ቆሬ ቅዱስ ሩፋኤል 3ኛ. ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል 4ኛ. ግራር ደ/አ/ቅድስት አርሴማ 5ኛ. ወይብላ ደብረ ጽዮን ማርያም ፠ ፠ ፠ #ነፋስ_ስልክ_ላፍቶ_ክፍለ_ከተማ_ (13ት ጥምቀተ ባሕር) #፴፭ኛ) #ደብረ_ኢያሪኮ_መድኀኔ_ዓለም_ቤተ_ክርስቲያን_አጠገብ 1ኛ. ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል 2ኛ. ፉሪ ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ማርያም 3ኛ. ደብረ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለም 4ኛ. ደብረ ወርቅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 5ኛ. ፈለገ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ 6ኛ. ፉሪ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል #፴፮ኛ) #ጎፋ_ሠፈር 1ኛ. ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ቤዛ ብዙኃን ኪዳነ ምሕረት 3ኛ. ቄራ መብራት ኀይል ደብረ መዊዕ ቅዱስ መርቆሬዎስና ዮሐንስ መጥምቅ #፴፯ኛ) #ጀሞ_መድኀኔ_ዓለም 1ኛ. ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት 2ኛ. ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል #፴፰ኛ) #ቻይና_ካምፕ 1ኛ. ፈለገ ዮርዳኖስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና ቅድስት ማርያም #፴፱ኛ) #ጀሞ_ቊጥር_3_አደባባይ 1ኛ. ጀሞ ቊጥር 3 ቅዱስ ገብርኤል #፵ኛ) #ቶታል_አደባባይ 1ኛ. ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. መካኒሳ ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፵፩ኛ) #መካኒሳ_ኮንዶሚንየም 1ኛ. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል #፵፪ኛ) #ዮሴፍ_አካባቢ 1ኛ. ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 2ኛ. ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ 3ኛ. ብሔረ ጽጌ ቅድስት ማርያም 4ኛ. አዲስ አምባ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 5ኛ. ሐመረ ወርቅ ቅድስት ማርያም #፵፫ኛ) #ብሥራተ_ወንጌል 1ኛ. ደብረ ቢ/ያ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፵፬ኛ) #ደብረ_ዕንቊ_ቅዱስ_ገብርኤል 1ኛ. ደብረ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል #፵፭ኛ) #ፉሪ_ኆኅተ_ብርሃን_ቅድስት_ማርያም 1ኛ. ፉሪ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም #፵፮ኛ) #ፉሪ_ደብረ_ገነት_ቅዱስ_ዑር(ራ)ኤል 1ኛ. ፉሪ ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል #፵፯ኛ) #ቡልቡላ_ ኤምባሲ_አጠገብ 1ኛ. ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ለቡ በዓለ ወልድ ፠ ፠ ፠ #አቃቂ_ቃሊቲ_ክፍለ_ከተማ_ (9ኝ ጥምቀተ ባሕር) #፵፰ኛ) #ወረዳ_1 #አቃቂ_በሰቃ_ወንዝ 1ኛ. ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ 3ኛ. ጃቲ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 4ኛ. ሰርጢ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም 5ኛ. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔ ዓለም 6ኛ. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል 7ኛ. ፈንታ ደ/ጽ/ቅዱስ ሩፋኤልና ቅድስት አርሴማ 8ኛ. ቀርሣ ፈለገ ብርሃን ቅድስት ልደታ ለማርያም #፵፱ኛ) #ወረዳ_5 #ከቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ቃሊቲ ደብረ ቊስቋም ማርያምና ቅዱስ ሚካኤል #፶ኛ) #ወረዳ_4 #ሰርቲ_መድኀኔ_ዓለም_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ሰርቲ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም #፶፩ኛ) #ወረዳ_9 #ገብረ_መንፈስ ቅዱስ_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ኮዬ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፶፪ኛ) #ቃሊቲ_አካባቢ 1ኛ. ሠፈረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል #፶፫ኛ) #ወረዳ_9 #ሥላሴ_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ቂሊንጦ ቅድስት ሥላሴ #፶፬ኛ) #ወረዳ_10 #ገላን_ጉራራ_ገብርኤል_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ገላን ጉራራ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል #፶፭ኛ) #ወረዳ_11 #ገላን_ኢዶሮ_ገብርኤል_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ገላን ኢዶሮ ቅዱስ ገብርኤል #፶፮ኛ) #መጠሊ_ገብርኤል_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. መጠሊ ደ/አ/ቅዱስ ገብርኤል ፠ ፠ ፠ #ቦሌ_ክፍለ_ከተማ_ (19ኝ ጥምቀተ ባሕር) #፶፯ኛ) #ጉምሩክ_ወረዳ_3 1ኛ. ቦሌ ደብረ ሳሌም መድኀኔ ዓለም ወመጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ወአቡነ አረጋዊ #፶፰ኛ) #ወረዳ_23 #አየር_መንገድ 1ኛ. ደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ክርስቶስ ሰምራ #፶፱ኛ) #ወረዳ_06 #መገናኛ 1ኛ. መገናኛ መንበረ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ #፷ኛ) #ወረዳ_02 #ሩዋንዳ_አካባቢ 1ኛ. ቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 2ኛ. ቦሌ አየር ማረፊያ መንበረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ #፷፩ኛ) #ወረዳ_13 #አድዋ_ፓርክ 1ኛ. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም 2ኛ. ገርጂ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ 3ኛ. ኤ(የ)ረር ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ዑርኤል #፷፪ኛ) #ወረዳ_9 #ሰሚት_አደባባይ 1ኛ. ቦሌ ሰሚት መካነ ሰላም መድኀኔ ዓለም 2ኛ. ቦሌ ሰሚት ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ 3ኛ. ቦሌ ሰሚት ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 4ኛ. በሻሌ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም #፷፫ኛ) #ወረዳ_12 #ቡልቡላ 1ኛ. ቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም 2ኛ. ቦሌ ቡልቡላ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ሳሙኤል ወቅዱ አማኑኤል 3ኛ. ቦሌ ቡልቡላ ፍኖተ ሕይወት ቅድስት ማርያም #፷፬ኛ) #ወረዳ_9 #ጎሮ_ሰፈር_ባሕረ_ጥምቀት 1ኛ. ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብኤል 2ኛ. ኤረር ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ 3ኛ. ኤረር መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል #፷፭ኛ) #ወረዳ_13 #አያት_አደባባይ_ #4_ኪሎ_ሰፈር 1ኛ. አያት መ/ሕ/መድኀኔ ዓለም #፷፮ኛ) #ወረዳ_13 #መሪ_አያት 1ኛ. መሪ ምሥራቀ ፀሐይ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 2ኛ. አያት ጌቴ ሴማኒ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 3ኛ. መሪ ቅዱስ ፋኑኤል 4ኛ. መሪ ቅድስት ሥላሴ #፷፯ኛ) #በሻሌ 1ኛ. ቦሌ በሻሌ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ እስጢፋኖስ 2ኛ. የቃጥላ ደብረ ፀሐይ ቅድሰት ማርያም #፷፰ኛ) #ወቄ_አካባቢ 1ኛ. ወረገኑ ቅዱስ ሚካኤል #፷፱ኛ) #አያት_ጨፌ 1ኛ. አያት ጨፌ ደብረ ኢያሪኮ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ #፸ኛ) #ወረዳ_11 #ለሚ_ኮንዶሚኒየም 1ኛ. ቦሌ ሰሚት ቅዱስ ሩፋኤልና ኤዎስጣቴዎስ #፸፩ኛ) #ወረዳ_11 #አራብሳ 1ኛ. አራብሳ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ዋሻው አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፸፪ኛ) #ለሚ 1ኛ. ቦሌ ለሚ አቡነ ተክለ ሃይማኖት 2ኛ. ቦሌ ለሚ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፸፫ኛ) #አያት_ኮንዶሚኒየም 1ኛ. አያት ጨፌ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. አያት ፈለገ ሕይወት ቅዱስ ዮሐንስ #፸፬ኛ) #ቦሌ_ቡኒ 1ኛ. ቦሌ ቡኒ ደብረ ቤቴል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ #፸፮ኛ) #ሪፈንቲ 1ኛ. ሪፈንቲ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ቦሌ ሰሚት መካነ ሕያዋን ዋሻው ቅዱስ ገብርኤል #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem