ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 382 подписчиков, занимая 5 588 место в категории Религия и духовность и 2 193 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 382 подписчиков.

Согласно последним данным от 10 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 43, а за последние 24 часа — -3, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 23.36%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.42% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 592 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 449 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 23.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 11 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 382
Подписчики
-324 часа
-27 дней
+4330 день
Архив постов
ለምነና እንደወጡም ከሸዋ ተነሥተው ወደ ትግራይ ክፍለ ሀገር በአኵሱም አቅራቢያ ከሚገኘው ገዳም ደብረ በንኮል ከሚባለው ከአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ደረሱ፤ ብሉይ ከሐዲስ የጠነቀቁ ናቸውና የአባታቸውን ዙፋን (ልዑልነት) ስለ ፍቅረ ክርስቶስ ንቀውት እየዘመሩ ስለተጓዙ በዚህ ምክንያት 'መናኔ መንግሥት' ይባላሉ፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም አቡነ ያሳይ የእግዚአብሔር ጸጋ ያደረባቸው ሰው መሆናቸውንና ወደ እርሳቸውም እየመጡ መሆኑን በመንፈስ ዐውቀውት ስለነበር በደስታ ተቀበሏቸውና በረድእነት ከወንድሞቻቸው ጋር ጨመሯቸው፡፡ አቡነ ያሳይም የገዳም መነኮሳትን በማገልገል በመንፈሳዊ ተጋድሎ ብዙ ደከሙ፡፡ በደብረ በንኮል ገዳምም ብዙ አስገራሚ ተአምራትን አደረጉ፡፡ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ ወደ መካነ ገድላቸው በጣና አካባቢ እንደሆነ ነገራቸው፡፡ ‹‹ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን›› የተባሉ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም ቀደም ብለን የጠራናቸውን ‹‹ሰባቱን ከዋክብት›› ምግባር ሃይማኖታቸውን፥ ተጋድሎ ትሩፋታቸውንና ገቢረ ተአምራታቸውን አይተው ፈቃደ እግዚአብሔርን ጠይቀው በአንድ ቢያመነኩሷቸው በዚያው ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ገዳሙን በብርሃን አጥለቅልቆት ታይቷል፡፡ ከሰማይም የምስክርነት ድምፅ ተሰምቷል፡፡ አቡነ ያሳይ በረድእነት በቆዩበት ዘመንም ዛፎችን መትከል ይወዱ ነበር:: ከትሩፋት መልስም በልብሳቸው ውሃ እየቀዱ ያጠጡ ነበር:: በተለይ "ምዕራገ ጸሎት" የሚባለው ተአምረኛ ዛፍ ዛሬ ድረስም አለ፡፡ ከዚህም በኋላ ከሰባቱ ቅዱሳን ውስጥ ሦስቱ ቅዱሳን አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ አቡነ ያሳይ እና አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ሆነው ከደብረ በንኮል ገዳም አባታቸውን አቡነ መድኃኒነ እግዚእን ተሰናብተው ወደ ጣና ደሴት መጥተዋል፡፡ አቡነ ሳሙኤል ወደ ‎ዋልድባ፤ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ወደ ገሊላ ከዚያ ወደ ጐጉቤን ሲሔዱ አቡነ ያሳይ መንዳባ ውስጥ ገቡ:: አቡነ ያሳይ በ13ኛው መ/ክ/ዘመን በአባታቸው የዘመነ ንግሥና መጨረሻ ወደ አርባ ምንጭ ሄደው ከዚያው ሱባኤ ገብተው ፈጣሪያቸውን ቢማጸኑ እግዚአብሔርም ከዚያው አካባቢ የሚኖር አንድ ባሕታዊን የመድኀኔዓለምን ጽላት እንዲያወጣላቸው አዘዘላቸው፡፡ እርሳቸውም ጽላቱን ተቀብለው በጎጃም በኩል አድርገው ወደ ጣና ተመልሰው በዘጌ አከባቢ ሲደረሱ ከጣና ባሕር ዳር ቆመው በየብስ ያለውን ርቀትና በባሕሩ ያለውን ቅርበት አይተው አሁንም ወደ ፈጣሪያቸው በጸሎት ተማጸኑ፡፡ በዚህም ጊዜ ጌታችን ተገልጦላቸው ‹‹ወዳጄ ያሳይ ሆይ አትጨነቅ እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፣ ከጎንህ ያለውን ድንጋይ በባሕሩ ላይ ጫነው፤ ድንጋዩም ለልጅ ልጅ እኔ ዓለምን ለማሳለፍ እስከምመጣበት ሰዓት ድረስ መታሰቢያ ትሁንህ›› አላቸውና ተሰወረ፡፡ አቡነ ያሳይም የመድኀኔዓለምን ጽላት ይዘው በድንጋዩ ላይ እንደተቀመጡ ድንጋዩ እንደታንኳ በባሕሩ ላይ ተንሳፈፈ፡፡ ባሕሩም ከማዕበሉ ብዛት የተነሣ ይታወክ ነበር፡፡ አባታችንም ያለ ምንም ቀዘፋ ልብሳቸውም ውኃ ሳይነካው ቁጭ እንዳሉ ማን እንደአባ ወደ ተባለው ቦታቸው ደረሱ፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ ያሳይ ገዳማቸውን ገድመው ወንድሞቻቸውን ሰብስበው በተጋድሎ በመኖር ብዙ ቅዱሳንን አፍርተዋል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ፤ ✣ የጌታችንን እግር ያጠቡት የገዳመ መጕናው አቡነ አብሳዲ፤ ✣ እንደ ነቢዩ ኤልያስ ዝናብንና ነፋስን የከለከሉት አቡነ ያዕቆብ፤ ✣ እሬትን እንደ ማር ያጣፈጡት አቡነ ገብረ ኢየሱስ፤ ✣ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተሞሉት አቡነ ዳንኤል፤ ✣ እንደ ንጉሥ ሰሎሞን ጥበብን የተሞሉት አቡነ ፊቅጦርና ሌሎችም ብዙዎች ይጠቀሳሉ፡፡ በወቅቱም ብዙ የበቁ ቅዱሳን በአካባቢው ነበሩ፡፡ በአጽፋቸውና በእግራቸው በባሕሩ ላይ የሚሄዱ ነበሩ፣ በጸጋ ክንፍ ተሰጥቷቸውም የሚበሩ ነበሩ፡፡ የአቡነ ያሳይ ተአምራቶቻቸው ተነግረው አያልቁም፡፡ በወቅቱ የነበሩት ቅዱሳን ልጆቻቸው ‹‹ከቅዱሳን ማን እንደ አባ ያሳይ በከባድ ድንጋይ ላይ ተጭኖ በባሕር ላይ የተጓዘ አለና..›› ብለው ይገረሙባቸው ነበር፡፡ ቦታቸውም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ‹‹ማን እንደ አባ›› ተባለ፡፡ ይህም የአቡነ ያሳይ ገዳም በሰሜን ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት በደንቢያ ወረዳ በጎርጎራ ጣና ሐይቅ አካባቢ ይገኛል፡፡ *** ገዳሙን ልዩ ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱ፤ በገዳሙ ውስጥ የሚገኙ መነኰሳት የሚጠሩበት የአባት ስማቸው በጻድቁ በአቡነ ያሳይ ስም ነው፡፡ ምንጭ፤ *የቃል አስረጅ የገዳሙ አበምኔትና የገዳሙ መነኰሳት (በተለይም አባ ኀይለሚካኤል ያሳይ)፤ *የቅዱሳን ታሪክ፣ ገጽ 152፤ *ሐመር 21ኛ ዓመት ቊ.11፣ 2006 ዓ.ም፤ *ከገድላት አንደበት-ke gedilat andebet እና Dn Yordanos Abebe መጽሐፈ ገጽ (Facebook) (ከቦታው ድረስ በመሄድና ከአበውና ከተለያዩ መጻሕፍት ይህንን ጽሑፍ ላዘጋጀልን የሰ/ትቤታችን አባል አቡነ ያሳይ ይስጡልን፡፡) አምላከ አበው(ያሳይ ዘመንደባ) በበረከት ረድኤት ይጠብቀን፤ ፍጻሜያችንን ያሳምረው፡፡ ከአበው በረከት፤ ከሥላሴ ልጅነት አያናውጠን፡፡ /የቀ/ደ/ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ፍ/ሕ/ሰ/ት/ቤት/

#አቡነ_ያሳይ_ዘማንዳባ_(ድንጋዩን እንደ ጀልባ ተጠቅመው የጣናን ሐይቅ ይጓጓዙ ስለነበር /ማን እንደ አባ የተባለላላቸው፤ ከ7ቱ ከዋክብት ቅዱሳንና ከ7ቱ ከዋክብተ ጣና ከኹለቱም ወገን የሚመደቡ) መስከረም 14 የዕረፍታቸው ዕለት ነው፤ መድኀኔዓለም አምላካችን ከጻድቁ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ /ስዕሉ 1ኛ አቡና ያሳይ በጣና ባሕር ላይ እንደሔዱ የሚያሳይ፣ 2ኛ ጻድቁ እንደ ታንኳ ይጠቀሙበት የነበረው ድንጋይ ዛሬ በገዳሙ ቅጽር ግቢ የሚገኝ፣ 3ኛ መንደባ መድኀኔዓለም ገዳም (የጻድቁ አጽም ያረፈበት) 4ኛ የአቡነ ኒቃላዎስ አጽም ያረፈበት ቤት/ 7ቱ ከዋክብት ቅዱሳንን የመላእክትን ሕይወት በምድር የኖሩ ታላላቅ የሀገራችንን ቅዱሳን በአንድ ጊዜ አስተምረውና አመንኵሰው ለጽድቅ ያበቋቸው አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡ ‹‹ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን›› የተባሉት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ የኢትዮጵያ ብርሃኗ በሆኑት በአቡነ ተክለ ሃይማኖት እጅ ከመነኰሱ በኋላና አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ለአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ‹‹ስፍር ቊጥር የሌላቸው ከዋክብት ቅዱሳንን›› በመንፈስ ቅዱስ እንደሚወልዱ ትንቢት በተናገሩላቸው መሠረት፤ ታላቁን ገዳም ደብረ በንኰልን (አኵሱም አጠገብ) መሥርተው፤ ኍልቈ መሳፍርት የሌላቸውን ቅዱሳንና መነኰሳት አመንኵሰዋል፡፡ ለአብነትም፤ የተንቤኑን አቡነ ዐቢየ እግዚእን፣ የዞዝ አምባውን አቡነ አብሳዲን፣ ሰባቱ ከዋክብትን ጨምሮ አመንኵሰዋል፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ሰባቱን ቅዱሳን በአንድ ጊዜ ሲያመነኵሷቸው በዚያው ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ (ገዳሙ የተቃጠለ እስኪመስል ድረስ ብርሃን ወርዶ) ገዳሙን በብርሃን አጥለቅልቆት ታይቷል ከሰማይም የምስክርነት ድምፅ ተሰምቷል፡፡ እንዲሁም እነዚሁ ቅዱሳን በአቡነ ተክለሃይማኖት በኋላ መላዋን ኢትዮጵያን በወንጌል ኮከብ ብርሃንነት አብርተዋታልና፤ በእነዚህ ምክንያት አንድ ላይ የመነኰሱት እነዚህ ሰባቱ ቅዱሳን ‹‹ሰባቱ ከዋክብት›› እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ ከላይ ካየናቸው ፯ቱ ከዋክብተ ጣና፥ ፯ቱ ቅዱሳንና፥ ፭ቱ ከዋክብት መካከል ባሕሩን በእግራቸውም እየረገጡ ጠቅጥቀው የተሻገሩ አሉ፣ በአጽፋቸው (በልብሳቸው) እንደጀልባ ተጠቅመው የሚጓዙ አሉ፤ በየብስ ላይ ኾነው መጻሕፍቶቻቸውን በአንበሳ ጭነው የተጓዙ አሉ፤ ……. ዛሬ መስከረም 14 ክብረ በዓላቸው የምናከብራለቸው አቡነ ያሳይ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይን እንደጀልባ ተጠቅመው በእርሱ ላይ ሆነው እንደ ጀልባ የሚጓጓዙ ናቸው፡፡ አቡነ ያሳይ፤ ቅዱስ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው›› (መዝ 67፡35) ብሎ እንደተናገረ ጻድቁ አቡነ ያሳይ ከእግዚአብሔር በተሰጣቸውም ጸጋ ጣና ሐይቅን የሚያቋርጡት በአንድ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ድንጋዩን እንደ ጀልባ ተጠቅመው ነበር፡፡ ያ ድንጋይ ዛሬም ድረስ በገዳማቸው ውስጥ በክብር ተቀምጦ ይገኛል፤ በዚህም ምክንያት በጣና ከተደረጉት ተዓምራት ማን እን አባ ያሳይ ይኾናል የሚሰጥመውን ድንጋይ ሳይሰጥም እንደ ጀልባ አድርጎ መጓዝ ብለው አበው ገዳሙን ‹‹ማን እንደ አባ ያሳይ /ማንዳባ(መንደባ)/ ብለው ሰየሙት፡፡ ጻድቁ ከአቡነ ሳሙኤል ጋር አብረው ወደዚህ ቦታ መጡ፡፡ ከዚያም የቦታው አቀማመጥ የብስ፥ መሬትና ደሴት መሆኑን አይተው ‹‹እግዚአብሔር ፈቅዶ ይችን ደሴት የጸሎት ቦታችን አድርጎ ቢሰጠን በጸሎት እንጠይቀው›› ተባብለው ሁሉቱም ቅዱሳን ሱባኤ ገቡ፡፡ ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንም ለአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ በገሃድ ተልጦላቸው ‹‹ወዳጄ ሳሙኤል ሆይ ይህ ቦታ የአንተ አይደለም የወንድምህ የያሳይ ቦታ ነው፡፡ እኔ ወዳዘጋጀሁልህ ቦታ ወደ ዋሊ(ዋልድባ) ሂድ›› ብሎ የዋልድባን ምድር አሳያቸው፡፡ አቡነ ሳሙኤልም የጌታችንን ትእዛዝ ተቀብለው ወንድማቸውን አቡነ ያሳይን ተሰናብተው ወደ ዋልድባ ሄደው ገዳማቸውን አቅንተው ተጋድሏቸውን በዚያ ፈጸሙ፡፡ ጌታችን ዳግመኛም ለአቡነ ያሳይ ተገለጠላቸውና ‹‹ወዳጄ ያሳይ ሆይ የአባትህን መንግሥትና የዓለሙን ክብር ከምኞቱ ጋር ለእኔ ብለህ ስለተውክ ይህንኑ ቦታ በዚህ ዓለም ሳለህ ለአንተ፣ ወደ ዘላለማዊ መንግሥቴ ከወሰድኩህ በኋላም ለልጆችህ ምንዳህ አድርጌ ሰጥቼሃለሁ፤ ምሕረቴንም በቦታህ አዘንባለሁ ቸርነቴም አይለያትም፣ ብዙ የመንፈስ ልጆችንም ታፈራለህ፤ ቦታህም እኔ ለፍርድ እስክመጣ ድረስ ትኖራለች›› በማለት ቃልኪዳኑን አቆመላቸውና ተሰወራቸው፡፡ ‹‹ምንዳህ›› ማለት ደመወዝ ማለት ነውና በዚህም ‹‹ማንዳባ›› ማለት ‹‹የአቡነ ያሳይ ምንዳ-ደመወዝ›› ማለት ነው ሲሉ አባቶች ገዳሙን ‹‹ማንዳባ-ምን እንደ አባ›› ብለው ሰየሙት፡፡ አቡነ ያሳይ የትውልድ ሀገራቸው ሸዋ ተጉለት ነው፡፡ አባታቸው ንጉሡ ዓምደ ጽዮን ቀዳማዊ ነው፡፡ ይኸውም ከ1296-1326 ዓ.ም. የነበረው ነው፡፡ አቡነ ያሳይ በልጅነታቸው በንጉሡ አባታቸው ቤት ሲኖሩ የገዳማት መነኰሳት ለመንፈሳዊ ሥራ ወደ ንጉሡ ዘንድ እየመጡ ደጅ ሲጠኑ ያዩዋቸዋል፡፡ በዚህም ጊዜ አባታችን ገና በልጅነታቸው የመነኰሳቱን እግር ያጥቡ ስለነበር በዚሁ አጋጣሚ መነኰሳቱን ስለምንኩስና ሕይወት ይጠይቋቸው ነበር፡፡ መነኰሳቱም ሕይወታቸውን ያስረዷቸዋል፡፡ አቡነ ያሳይም ብሉያትንና ሐዲሳትን ከልጅነታቸው ጀምሮ የተማሩ ስለነበር የአባቶችን ትምህርትና የወንጌልን ቃል በማገናዘብ የፈጣሪያቸው ፍቅር በልቡናቸው እንደ እሳት ነደደ፤ ይልቁንም ‹‹ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል›› የሚለውን የጌታችንን ቃል አሰቡ፡፡ ማቴ 16፥26፡፡ ከዚህም በኋላ የንጉሡ አባታቸውን የአልጋ ወራሽነት ማለትም የንጉሥነትን ክብር ፈጽመው በመናቅ ‹‹እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር እራሱን ይካድ፣ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ›› (ማቴ 16፡27) ያለውን የጌታችንን ቃል አስበው ንጉሣውያን ቤተሰቦቻቸውን ጥለው ለምነና ወጡ፡፡

ዘመኑን የዋጀ ተከታታይ መንፈሳዊ ትምህርት (Course)፤ ለወጣቶች (በቀንና በማታ) እና ለሕፃናት (በቀን)፤ ለምትፈልጉ ምዕመናን በሙሉ፤ ሰ/ት/ቤታችን የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል
ዘመኑን የዋጀ ተከታታይ መንፈሳዊ ትምህርት (Course)፤ ለወጣቶች (በቀንና በማታ) እና ለሕፃናት (በቀን)፤ ለምትፈልጉ ምዕመናን በሙሉ፤ ሰ/ት/ቤታችን የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ለወጣቶችና ሕፃናት ምዕመናን በ2012ዓ.ም. ልዩ ተከታታይ ትምህርቶችን አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል፡፡ የትምህርቶቹ ዓይነቶች፤ በወጣት ክፍል የሚሰጡ፤ ✤ #በቀዳማይ፤ * ትምህርተ ሃይማኖት (መግቢያ ሥነ ፍጥረትና አእማድ) * የቤተ ክርስቲያን ታሪክ መግቢያና በዓለም መድረክ * የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መግቢያና አዋልድ ቅዱሳት መጻሕፍት * ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ✤ #በካልዓይ፤ * ነገረ ማርያም ወነገረ ቅዱሳን * የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ (የቤ.ክ ታሪክ በኢትዮጵያ) * ብሉይ ኪዳን * ተግባራዊ ክርስትና (ክርስቲያናዊ ሕይወት) ✤ #በሣልሳይ * ነገረ ክርስቶስ ወነገረ ድኅነት * ልሳነ ግእዝ * ሐዲስ ኪዳን * ሥርዐት ወምሥጢራተ ቤ.ክ እንዲሁም በሕፃናት ክፍል የአብነት ትምህርትን ጨምሮ የተለያዩ ትምርቶች ይሰጣሉ፡፡ ትምህርቱ የሚሰጠው፤ * ለወጣቶች በቀን (ቅዳሜ ከ9-11 ና እሑድ ከ4፡30-6፡30) * ለወጣቶች በማታ (ሰኞ፣ ረቡዕና ዐርብ ከ12-2)፤ ለ6 ወራት * ለሕፃናት በቀን (ቅዳሜ ከ6፡30-8፡30 ና እሑድ ከ6፡30-8፡30) ✣✣ መመዝገቢያ፤ በሰ/ት/ቤቱ ጽሕፈት ቤትና ትምህርት ክፍል ✣ ከአኀት ሰንብት ትምህርት ቤቶችና ከግቢ ጕባኤ ለመማር የምትመጡ የተማራችኋቸውን ትምህርቶች የሚገልጽ ደብዳቤ (ምስክር ወረቀት /ካርድ (Certeficet)/ ማምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡ ✤✤ ትምህርቱ ጥቅምት 1 ይጀመራል፡፡ ‹‹የነፍስ ምግቧ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡›› ለበለጠ መረጃ፤ 0922 85 13 74 /0921 05 60 56/

?????? አንተ የምትተኛ ንቃ! /ሙሉ ጽሑፉን ሳያነቡ አስተያየት ባይሰጡ ይመከራል!/ ፩ ፨፨፨ ‹‹እስከ መቼ ድረስ በሁለት አሳብ ታነክሳላችሁ?›› ፨ መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ ፲፰፥፳፩ ‹‹ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን ገስጿቸው፡፡›› 1ተሰ. 5፥14 በጉለሌ ክፍለ ከተማ የእሬቻን በዓል በማስመልከት በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ /ቀሲስ?????/በላይ በመገኘት ስለ በዓሉ ሃይማኖታዊ???? አከባበር መግለጫና ማብራሪያ ሰጥተዋል፤ በመጨረሻም ቀሲሱ????? በሰጡት ቃለ ምዕዳን የፓናሉ ፍጻሜ ሆኗል፡፡ ፪ ፨፨፨ /#ዋዜማ_ቅኔ_ዘሊቁ_ክፍለ_ዮሐንስ/ #ለመልአክ ኢናከብሮ፣ ለእመ አስረጸ ቈጽለ በመጠነ ነዊኀ ቆሙ፤ ለዖፍ ወለትንንያ እስመ ክንፍ ቦሙ፡፡ ወበሲበቱ ለሰብእ ኢናከብሮ ቀዲሙ፤ ፀዐዳ ሲበት እስመ ሀለወሙ፤ ለዕፀው ወአዕባን ኵሎሙ፡፡ #ትርጕም፤ ፠፠ #በረጅም_ቁመቱ_ክንፍን_ቢያበቅል_በክንፍ_ቢሸፈን_መልአኩን_አናከብረውም_፤ (ቀሲስ በላይ የክህነት ልብስ ስለለበሰ፥ መስቀል ስለያዘ፥ የእግዚአብሔርን ስም ስለጠራ አናከብረውም) ለወፍና ለትንኝ ክንፍ አላቸውና፤ መልአኩን በክንፍ አናከብረውም፡፡ (ለጣዖት ቤት /ለመተተኞች ፥ ለጠንቋዮች፥ ለካዳሚዎች ……/ ልብስ አላቸውና፥ በቅብዐ ሜሮን ያልከበረ መስቀል የሚይዙ አሉና፥ ዲያብሎስም እግዚአብሔርን ያምናልና …..) ፠፠ #ሰውንም በሽበት አናከብረውም፤ (በላይም ስሙ ቀሲስ ስለተባለና ከመንግሥት አካላት ጋር ስለተጠጋ አናከብረውም) ለድንጋይና ለእንጨቶች ሁሉ ነጭ ሽበት አላቸውና፤ ሰውን በእውቀቱ እንጂ በሽበቱ አናከብረውም፡፡ (በስመ ቀሲስ የሚነግዱና የሚያጨናብሩ፤ ቆብ ያደረጉ፥ ጥምጣም የጠመጠሙ አሉና)፨ ፫ ፨፨፨ #ፍቅር ያጌብረኒ ነጊረ ነጊረ ዜናሆሙ ለቅዱሳን፤ የቅዱሳንን ዜናቸውን ለመናገር ፍቅር ግድ ይለኛል ወቅንዐት ያጌብረኒ ከመ እዝልፎሙ ለዕልዋን፤ #ቅናትም_ዝንጉዎችን_እንድሸሻቸው_ግድ_ይለኛል፤ #ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እሰብሖ ለኢየሱስ ክርስቶስ፤ ፍቅር ክርስቶስን እንዳመሰግነው ግድ ይለኛል፤ ወቅንዐት ያጌብረኒ ከመ አውግዞ ለሰይጣን፤ ቅናትም ሰይጣንን አወግዘው ዘንድ ያስገድደኛል፤ #ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እትልዎሙ ለሐዋርያተ ክርስቶስ፤ ፍቅር የክርስቶስን ሐዋርያት እንድከተላቸው ያስገድደኛል፤ ወቅንዐት ያጌብረኒ ከመ አጕይዮሙ ለረሲዓን፤ #ቅንዐትም_ከሀዲዎችን_እነቅፋቸው_ዘንድ_ያስገድደኛል፤ #ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እወድሶሙ ለሰማዕት፤ ፍቅር ሰማዕታትን አውድሳቸው ዘንድ ግድ ይለኛል፤ ወቅንዐት ያጌብረኒ ከመ እጽአሎሙ ለማርያን፡፡ ቅናትም ጠንቋዮችን እንድዘልፋቸው ያስገድደኛል፡፡ /ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፥ መጽሐፈ ምሥጢር ዘደብረ ዘይት ምንባብ፡፡/ ፬ ፨፨፨ የቄሣርን ለቄሣር፤ የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር፡፡ ‹‹ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዐት ይሁን፡፡›› 1ቆሮ. 14፥40 #አድኅነኒ እግዚኦ እስመ ሀልቀ ሔር፤ ወውኅደ ሃይማኖት እም እጓለ እመሕያው፡፡

እንኳን ለሰ/ት/ቤታችን #፶፬ኛ#ዓመት_የምሥረታ_በዓል_ለተማሪዎች_ምረቃና_ለዝክረ_ቅዱስ_ያሬድ_አደረሳችሁ_አደረሰን፡፡ ፎቶ 1፤ በ1962 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ደብራችንንና ሰ/ት/ቤታችንን በጎጉበት ወቅት፡፡ ‹‹የሰ.ት.ቤት አገልግሎት ለቤ.ክ ሐዋርያዊ ተልዕኮ›› የሰንበት ትምህርት ቤታችን የ54ዓመታት ታሪክ በአጭሩ፤ ፠ ምንም እንኳን አስቀድሞ ብዙ እንቅስቃሴዎች ቢኖሩም፤ ሰንበት ትምህርት ቤታችን ራሱን ችሎ በመዋቅር ተዋቅሮ አካል ገዝቶ፥ ስያሜ አግኝቶ የተዋቀረው የደብራችን አስተዳዳሪ በኾኑት በንቡረ ዕድ በየነ ዓሊ ከፍተኛ ድጋፍ በጥቂት ወንዶችና ሴቶች (ወጣትና ሕፃናት) ነሐሴ ፳፮ና ፳፯/፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ነው፤ ፠ ሲመሠረት የሰ/ት/ቤታችን ስያሜ ‹‹የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ.ክ. ሰንበት ትምህርት ቤት›› በሚል ነበር፤ ፠ ሲመሠረትም ከነበሩት መሥራች አባላት መካከል ለአብነት (እማሆይ ተስፋዬ (እኅተ ጊዮርጊስ)፣ አቶ አየለ…፣ አርቲስት የሻሽወርቅ በየነ፣ ሐና በለጠ፣ …..….) እዲሁም ከጥቂት ቆይታ በኋላ ከተቀላቀሉት መካከል እነ አርቲስ ችሮታው ከልካይ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ በተለይም እማሆይ ተስፋዬ ፀጋ ሰንበት ትምህርት ቤታችንን ከመመሥረት ጀምሮ ለብዙ ዘመናት በሰንበት ትምህርት ቤታችን አገልግሎት ላይ እጅግ ከፍተኛውን አስተዋጽዖ ያደረጉና በሰ/ት/ቤታችን ታሪክ ላይ የአንበሳውን ድርሻ የተወጡ እናታችን ናቸው፡፡ ✤✤ ሰ/ት/ቤታችን መነሻ አድርጎ የተመሠረተበት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ቃልም ‹‹አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥትና ጽድቁንም ፈልጉ፤ ሌላው ኹሉ ይጨመርላችኋል፡፡›› ማቴ. ፮፥፴፫ የሚለው ሲኾን፤ ዋና ዓላማው መጽሐፍ ቅዱስን መማርን ቤተ ክርስቲያንን ማወቅ ሲኾን ዝርዝር ዓለማው ደግሞ ወጣቶች ከሕፃንነታቸው ጀምረው እግዚአብሔርን በፍፁም ልባቸውና በፍፁም ነፍሳቸው እንዲያመልኩት፤ ወላጆቻቸውንና ከእነርሱ በእድሜ ከፍ ያሉትን እንዲያከብሩ፣ በኑሮ ዝቅ ላሉት ወንድሞቻቸውና እኅቶቻቸው በራሳቸው ሊደረግላቸው የሚወዱትን ኹሉ ለእነርሱም እንዲያደርጉላቸው፤ ትምህርተ ሃይማኖትና ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ነበር፡፡ ፠ ከሰ/ት/ቤታችን ምሥረታ ከ2 ዓመታት በኋላ ጥቅምት 11/1960ዓ.ም. ‹ፍኖተ ሕይወት› (‹‹የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወት››) የሚል ስያሜን ያገኘችበት ነው፡፡ ‹ፍኖተ ሕይወት› ቃሉ የግእዝ ሲኾን ትርጓሜው የሕይወት መንገድ ማለት ነው፤ ይኸውም እውነተኛ መንገድ የተባለው መድኀኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ‹‹እኔ እውነተኛ መንገድና ሕይወት ነኝ፡፡›› እንዲል፡፡ ✤፠✤ በ1962ዓ.ም. የሰንበት ትምህርት ቤታችን ሌላኛው ትልቁ ምዕራፍ፤ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ደብራንችንና ሰንበት ትምህርት ቤታችንን መጎብኘት /ፎቶውን ይመልከቱ …../ ፠ ብፁዕ አባታችን ሰንበት ትምህርት ቤታችንን ባልታሰበ ጊዜ መጎብኘታቸው፤ አዳራሻችን ድረስ መጥተው ማስተማራቸውና አባላቱን ኹሉ እቅፍ አድረገው ማበረታታቸው፤ አዳራሻችንን ለማደስ ተሥፋ መስጠታቸው፤ ማኅበረ ካህናት ለሰንበት ትምህርት ቤት እንዲራዱ መመሪያ መስጠታቸው ከሰንበት ትምህርት ቤቱ ምሥረታ በኋላ ዳግመኛ በአባላቱ ሁሉ ልቡና ላይ እንደ ሰሌዳ ተቀርጾ በብርታትና በፍቅር፤ በንቃትና በትጋት አገልግሎትን እንድናከናውን መሠረት ሆነን፤ ይህችም ቀን ዳግመኛ ሰንበት ትምህርት ቤታችን የተመሠረተችበት ዕለት ሆነች፡፡ ✤✤✤ ሕፃናት ክፍል  መምህር አባ ምክረ ማርያም ሠይፈ ሥላሴ የደብራችን አስተዳዳሪ ከኾኑ በኋላ መጋቢት 29/1965ዓ.ም. ድረስ በመምጣጥ የሕፃናት ክፍል ለብቻቸው እንዲማሩ ወንድ በአንድ ረድፍ ሴቶች በሌላኛው ረድፍ እንዲቀመጡ ባስተላለፉት መመሪያ መሠረት፤ በሳምንቱ ከሚያዝያ 6/1965ዓ.ም. ጀምሮ ሕፃናት ክፍል ራሱን ችሎ መዋቀሩ የመጀመሪያዋ የሕፃናት ክፍል ሰብሳቢም የ13ት ዓመቷ የሻሽ ወርቅ በየነ መኾኗ፡፡  በ1980ዋቹና 90ዎቹ መጀመሪያ ድረስ የሕፃናት ክፍል ‹‹እምነት ተስፋ ፍቅር›› በሚል በተሰየሙ በ3ት ምድቦች የተለያዩ መርሐ ግብሮችን በአዳራሽና በዐውደ ምሕረት ሲያቀረብ መቆየቱ፡፡  በ1990ዎቹ መጀመሪያ የፊልጶስና ናትናኤል ክፍል በሚል ስያሜ ተሰይሞ ለ2ት ተከፍሎ መቆየቱ፤ የሕፃናት ክፍል አባላት ከጊዜ ወደ ጊዜ በመጨመራቸውና በተለያዩ የእድሜ ክልሎች ከፍሎ ማስተማር በማስፈለጉ ተጨማሪ 2ት ክፍሎች ‹‹የታሪክ ሀ›› እና ‹‹የታሪክ ለ›› ክፍል በሚባሉ የተሰየሙ ክፍሎች መጨመራቸው፡፡ ያተሪክ ሀ እና ለ የሚሉት ስያሜዎች አሁን የጳውሎስና የጴጥሮስ ክፍል ተብለው የተሰየሙት ናቸው፡፡  በ2000ዎቹ መጀመሪያ ላይ የመድኀኔዓለም ዝክር (ጽዋ) ስያሜው ‹‹ዝክረ አበው›› በሚል መከበር መጀመሩ፡፡ አንዲሁም የወላጅ ኮሚቴ በሕፃናት ክፍል መዋቀሩ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን፤ የፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡/

#አጋፔ_ ለተማሪዎችና ለአባላት በሙሉ፤ የአጋፔ (የፍቅር ማዕድ) መርሐ ግብር ቅዳሜ መስከረም 10/2012 ዓ.ም. በ12፡00 ሰዐት ይካሄዳል፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱ
+1
#አጋፔ_ ለተማሪዎችና ለአባላት በሙሉ፤ የአጋፔ (የፍቅር ማዕድ) መርሐ ግብር ቅዳሜ መስከረም 10/2012 ዓ.ም. በ12፡00 ሰዐት ይካሄዳል፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያናችን ፈተናዎች ምንድን ናቸው?፤ የእኛስ ድርሻ? መስከረም 10/2012 ዓ.ም. በ10፡30 በመርካቶ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል ቤ/ክ በትልቁ ት/ቤት ሰገነት ላይ እንገናኝ፡፡
+2
ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያናችን ፈተናዎች ምንድን ናቸው?፤ የእኛስ ድርሻ? መስከረም 10/2012 ዓ.ም. በ10፡30 በመርካቶ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል ቤ/ክ በትልቁ ት/ቤት ሰገነት ላይ እንገናኝ፡፡

እንኳን ለአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ (ፀሐየ ዋሊ ፀሐየ ኢትዮጵያ) ፍልሰተ ሥጋ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ /ስዕሉ/- አቴና(መቃብረ ሳሙኤል)ይባላል፤ በዋሊ(ዋልድባ) የሚገኝ፤ አቡነ ማር ሳሙኤል ዘዋልድባ ለበርካታ ዘመናት በጾም፣ በጸሎት፣ በትህርምት፣………የኖሩበት እና በስተመጨረሻም፤ ማክሰኞ ታኅሣሥ 12 ያረፉበት፤ ጌታችን ከእናቱና ከቅዱሳን መላእክቶች ጋር የወረዱበት ቅዱስ ቦታ፤ ከካረፉም በኋላ ቅዱስ ሥጋቸው ለበርካታ ዘመናት የኖረበት ቦታ ነው፡፡ አቡነ ኣሙኤል በኪደተ እግር በወንጌል ገበሬነት አዲስ አበባንና አካባቢዋን ያስተማሩ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ዛሬ መስከረም 6 የአቡነ ማር ሳሙኤል(ፀሐይ ዘዋሊ፤ ፀሐይ አዚትዮጵያ) ቅዱስ ሥጋ ከአቴና(መቃብረ ሳሙኤል) የፈለሰበት ነው፤ ልክ የእመቤታችን ሥጋ በነሐሴ (14) እንደፈለሰ፤ የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋ (ሚያዝያ 23 አርፎ) በነሐሴ 16 ወደ ልዳ እንደፈለሰ፤ የአቡነ ተክለሃይማኖት ሥጋ (በነሐሴ 24 አርፎ) በግንቦት 12 ከደብረ አስቦ ወደ ደብረ ሊባኖስ እንደፈለሰ ሁሉ፤ ዛሬም የአቡነ ማር ሳሙኤል ሥጋ ከአቴና የፈለሰበት ነው፡፡ አቡነ ማር ሳሙኤል (ፀሐይ ዘዋሊ፤ ፀሐይ አዚትዮጵያ) ከሚታወቁበት ብዙ ነገሮች መካከል ከአቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግና ከአቡነ ብንያሚ ጋር ወደ ታላቁ አባት አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ለበረከት በመጡበት ወቅት አዲስ አበባንና አካባቢዋና በወንጌል ገበሬነት አርሰዋታል፤ ለዚህም ምስክሩ፤ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ የተሠራበት/አቡነ ሳሙኤል የኤልክትሪክ ኃይል ማመንጫ በመባል የሚታወቀው/ (ከአቃቂ 30ኪ.ሜ አካባቢ ርቀት ላይ የሚገኘው) በወቅቱ ራሳቸው የመሠረቱት(ያስፋፉት) ገዳም (ደብረ ገነት አቡነ ሳሙኤል የሴቶች አንድነት ገዳም በመባል የሚጠራው) ምስከር ነው፡፡ ሰላም ለከ ኵነነ ሐመረ፤ እንበለ አስጥሞ ኅቡረ፥ ታዕድወነ ባሕረ፡፡ አምላከ አበው(ሳሙኤል) በረድኤት ይጠብቀን፤ ፍጻሜያችንን ያሳምረው፡፡ ከአበው በረከት፤ ከሥላሴ ልጅነት አያናውጠን፡፡ /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/

‹‹ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በወርኀ ነሐሴ ፳፬/፳፻፲፩ ዓ.
+3
‹‹ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በወርኀ ነሐሴ ፳፬/፳፻፲፩ ዓ.ም. ጋብቻሽን በዩናይትድ ኪንግደም ሎንዶን ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ የፈጸምሽው የሰ/ት/ቤታችን አባል እኅታችን፤ #ሰላማዊት(ይልፋሸዋ)#ጌታቸው_ከሠራዊት_ወንድማገኘው ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#አስቸኳይ_፤ +++ነገ መስከረም 4/2012 ዓ.ም. * ሁላችንም እናስቀድስ፥ አቡነ ዘበሰማያት እናድርስ፤ ሁላችንም፤ የተቻለን 151 መዝሙረ ዳዊት እንጸልይ (በገዳም ያሉ እንዲጸልዩ መልዕክት እናድርስ) * ውዳሴ ማርያም፥ ሰላም ለኪ እንድገም። * ሰላማዊ ሰልፉን ያጨናገፉ 3ቱ .... ከለባትን ሌላ ጊዜ እንመለከታቸዋለን። /shareeeeeeee/

እንኳን ✤ ለ7512 ዓመተ ዓለም፥ ✤ ለ2012 ዓመተ ምሕረት፥ ✤ ለ64 ዐውደ ቀመር፥ ✤ ለ7 ዐውደ ወርኅ፥ ✤ ለ6 ዐውደ ወንበር፥ ✤ ለዐውደ ዓመት ዮሐንስ (መስከረም 1 /መባቻ/) ኀሙስ፥ ✤ ለዐ
+9
እንኳን ✤ ለ7512 ዓመተ ዓለም፥ ✤ ለ2012 ዓመተ ምሕረት፥ ✤ ለ64 ዐውደ ቀመር፥ ✤ ለ7 ዐውደ ወርኅ፥ ✤ ለ6 ዐውደ ወንበር፥ ✤ ለዐውደ ዓመት ዮሐንስ (መስከረም 1 /መባቻ/) ኀሙስ፥ ✤ ለዐውደ ዓመት ወንጌላዊ ዮሐንስ፥ ✤ ለ2 ጥንተ ዮን፥ ለ4 እንድክትዮን ✤ ለ6 አበቅቴ፥ ✤ ለ24 መጥቅዕ፤ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡ ሥርዐተ ማኅሌት ዘመስከረም 1፤ በዓለ ርዕሰ ዐውደ ዓመት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅዱስ ራጕኤል፡፡ የመስከረም 1 ርዕሰ ዐውደ ዐመት ክብረ በዓል በሃገራችን የሚከበርባቸው ዋና ዋና ቦታዎች፤ ✣ ጋራ መናገሻ መድኀኔዓለም (የቅዱስ ራጕኤል ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት ይከብራል) ✣ ርዕሰ አድባራት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጕኤል ወኤልያስ ቤ.ክ. ✣ መርካቶ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጕኤል ቤ.ክ. ✣ ዘንሥር ዮሐንስ ማዕከላ ለጎንደር (የቅዱስ ራጕል ታቦት በድርብነት ይከብራል) እንኳን ለ፳፻፲፪ዓ.ም. (ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ፎቶ፤ መጋቤ ብርሃናት ቅዱስ ራጕኤል (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት)

/የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

በየዓመቱ ጳጕሜን 5ት፤ በየዓራት ዓመቱ ጳጕሜን 6ት፤ በስድስት መቶ ዓመት ጳጕሜበን 7ት ለምን? #ጳጕሜን_፭_ዕለተ_ምሪያ_(#ዕለተ_መድኀኒት_ብርሃን_ልደት_) ‹‹ምርያ›› ማለት ‹የተመረጠች ቀን› ማለት ሲሆን የምታዘዋውር ማለትም ነው፤ ይህች ዕለት ዓመቱ በዋለበት እንዳይውል የምታደርግ ናት፡፡ /ለምሳሌ መስከረም 1/2010 ሰኞ ውሎ የዘንድሮ መስከረም 1/2011ዓ.ም. ማክስኞ እንዲውል የምታደርገው ጳጕሜን 5 ናት/፡፡ ጳጕሜን ፭ የሚትውልበት ዕለት ሁልጊዜም ከቀጣዩ የገና(የልደት) በዓል ዕለት ጋር ተመሳሳይ ነው (በዓለ ልደት የሚውለውም ጳጕሜን 5 በዋለበት ቀን ነው)፡፡ በዚህም የጌታችንን የመድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ልደቱን ስለምታሳውቅ (ስለምትመራ) ጳጕሜን 5 ዕለተ ምሪያ ከሚል ስያሜ በተጨማሪ ዕለተ መድኀኒት ዕለተ ልደት በመባል ትታወቃለች፡፡ /ለምሳሌ ጳጕሜን 5/2010 ዓ.ም. ሰኞ ዋለ፣ ታኅሣሥ 29, 2011 ሰኞ ዋለ፡፡ #ጳጕሜን_፮_ዕለተ_ሠግር_(#ሠግረ_ዮሐንስ_6ኛ_ጳጉሜን_) (leap year) ዮሐንስ ተሻግሮ የሚውልባት ቀን ማለት ነው፡፡ የ2012 ዓ.ም. መባቻ (መስከረም 1) ረቡዕ እንዳይሆን ወደ ኀሙስ የተሻገረው በሠግር በተሰኘችዋ ጳጉሜን 6 አማካይነት መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ በአራት ዓመት አንድ ጊዜ ጳጕሜን 6 ቀን የምትኾነውም እነዚህ በየዓመቱ የተሰባሰቡ 15 ኬክሮሶች አንድ ላይ መጥተው በአራት ዓመት አንድ ጊዜ አንድ ዕለት ስለሚኾኑ ነው፡፡ ጎርጎርዮሳውያኑ ይህቺን ሠግር በፌቡርዋሪ ወር ላይ ጨምረው ወሩን በየአራት ዓመቱ አንድ ጊዜ 29 ቀን ያደርጉታል፡፡ 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ተደምረው አንድ ዕለት መጡና በአራት ዓመት አንድ ጳጕሜን ስድስት ቀን እንድትኾን አድርገዋታል፡፡ የቀረችው 6 ካልዒትስ የት ትግባ? ከተባለ ካልዒት አንዲት ዕለት ትኾን ዘንድ 3600 ካልዒት ያስፈልጋሉ፡፡ ይህንን ያህል ካልዒት ለማግኘት 600 ዓመታት ያስፈልጉናል፡፡ ለዚህ ነው ጳጕሜን በየስድስት መቶ ዓመታት ሰባት የምትኾነው፡፡ በዘመነ ዮሐንስ ግን ስድስተኛዋ የጳጕሜን ቀን በዓለ ልደትን በአንድ ቀን ዝቅ ብሎ እንዲከበር ስለምታደርገው ልደትን ታኅሣሥ 28 ቀን እናከብራለን፡፡ ታድያ ምነው ጥምቀት፣ ግዝረትና ሌሎችም በዓላት አይለወጡም? ቢሉ ሊቃውንቱ የሚሰጡት ምላሽ ‹‹ትውልድ ሱባዔ እየቈጠረ በተስፋ የጠበቃት ዕለተ ልደትን ስለ ኾነ ነው፤ ሌሎቹ በዓላትም የመጡት በልደቱ ምክንያት ነው›› የሚል ነው፡፡ በጎርጎርዮሳውያንም ቢኾን በአራት ዓመት አንድ ጊዜ በዓለ ልደት ዝቅ ብሎ ይከበራል፡፡ የእነርሱ የማይታወቀው ጭማሪዋ ፌብርዋሪ ላይ ስለ ኾነች ነው፡፡ ያ ደግሞ አዲሱን ዓመት ካከበሩ በኋላ ስለሚመጣ ነው፡፡ የእኛ ግን የምትወድቀው ጳጕሜን መጨረሻ ላይ በመኾኗና ከአዲስ ዓመት በፊት ስለምትጨመር ቍጥሯ ጐልቶ ይታወቃል፡፡ #ተጨማሪ_ማብራሪያ_/#ከባሕረ_ሐሳብ_መጻሕፍት_/ ፠ዓመቱ በዐውደ ፀሐይ ሲለካ 365 ቀናት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ነው፣ ፠ዓመቱ በጨረቃ ሲለካ ደግሞ 354 ቀናት ከ22 ኬክሮስ፣ ከ1 ካልዒት፣ ከ36 ሣልሲት፣ ከ52 ራብዒት፣ ከ48 ኀምሲት ነው፡፡ **በሁለቱ አቈጣጠር መካከል (በፀሐይና በጨረቃ) በዓመት ውስጥ ያለው ልዩነት 11 ቀናት ከ7 ኬክሮስ ይኾናል፡፡ በዘመን አቈጣጠራችን ውስጥ ከዕለት በታች የምንቈጥርባቸው ስድስት መለኪያዎች አሉ፡፡ እነዚህም ኬክሮስ፣ ካልዒት፣ ሣልሲት፣ ራብዒት፣ ኀምሲትና ሳድሲት ናቸው፡፡ 60 ሳድሲት 1 ኀምሲት፣ 60 ኀምሲት 1 ራብዒት፣ 60 ራብዒት 1 ሣልሲት፣ 60 ሣልሲት 1 ካልዒት፣ 60 ካልዒት ደግሞ 1 ኬክሮስ ይኾናል፡፡ 60 ኬክሮስ ደግሞ 1 ዕለት፤ 1 ኬክሮስ 24 ደቂቃ ነው፡፡ ወርኀ ጳጕሜንን ለማግኘት የሚረዳንም የየዕለቱን ልዩነታቸውን መመልከቱ ነው፡፡ በየዕለቱ በጨረቃና በፀሐይ መካከል 1 ኬክሮስ ከ52 ካልዒት ከ31 ሣልሲት ይኾናል፡፡ ይህም ማለት 5 ሰዓት ከ48 ደቂቃ ከ46 ካልዒት (ሴኮንድ?) ነው፤ ይህ ልዩነት በአንድ ወር ምን ያህል እንደሚደርስ ለማወቅ በ30 ብናበዛው 30 ኬክሮስ ከ1560 ካልዒት፣ ከ930 ሣልሲት ይኾናል፡፡ የዓመቱን ለማግኘት ደግሞ በ12 ብናበዛው 360 ኬክሮስ ከ18720 ካልዒት፣ ከ11160 ሣልሲት ይመጣል፡፡ ቀደም ብለን 60 ኬክሮስ አንድ ዕለት ይኾናል ባልነው መሠረት 360 ኬክሮስ ለ60 ሲካፈል 6 ዕለታትን ይሰጠናል፡፡ 18720 ካልዒትን በስድሳ በማካፈል 312 ኬክሮስን እናገኛለን፡፡ ያም ማለት ትርፉን 12 ኬክሮስ ትተን 300ውን ኬክሮስ ለ60 በማካፈል 5 ዕለት እናገኛለን ማለት ነው፡፡ ይኼም 5 ዕለት ከ12 ኬክሮስ ይኾናል፡፡ 11160 ሣልሲትን ለ60 ብናካፍለው 186 ካልዒት ወይም ደግሞ 3 ኬክሮስና 6 ካልዒት ይኾናል ማለት ነው፡፡ ከላይ ኬክሮስን በዓመቱ ቀናት አባዝተን ያገኘነው 6 ዕለት ሕጸጽ ይባላል፡፡ ፀሐይና ጨረቃን እኩል መስከረም አንድ ላይ ዓመቱን ብናስጀምራቸው ፀሐይ የወሯ መጠን ምንጊዜም 30 ሲሆን ጨረቃ ግን በአንደኛው ወር 29 በሌላኛው ወር ደግሞ 30 ስለምትኾን ዓመቱ እኩል አያልቅም፤ የጨረቃ ዓመት የሚያልቀው ነሐሴ 24 ቀን ነው፡፡ ይህም ማለት ጨረቃ በሁለት ወር አንድ ጕድለት ታመጣለች ማለት ነው፡፡ ይህንን ነው ሊቃውንቱ ሕጸጽ (ጕድለት) ያሉት፡፡ በዚህም መሠረት ከላይ ኬክሮሱን በዓመቱ ቀናት አባዝተን ያገኘነውን 6 ዕለት ለጨረቃ ሕጸጽ ስንሰጠው የመስከረም /ጥቅምት 1፣ የጥቅምት /ኅዳር 2፣ የጥር /የካቲት 3፣ የመጋቢት /ሚያዝያ 4፣ የግንቦት /ሰኔ 5፣ የሐምሌ /ነሐሴ 6 ኾነው ተካፍለው ያልቃሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በጨረቃና በፀሐይ ዑደት መካከል በዓመት ያለው ልዩነት 11 ቀናት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ይኾናል፡፡ ስድስቱን ዕለታት ጨረቃ ለምታጋድልበት ሕጸጽ ብንሰጠው ቀሪ 5 ዕለት ይኖረናል፡፡ ወርኀ ጳጕሜን ማለት እነዚህ 5 ቀናት ናቸው፡፡ አሁን የዐሥራ አንዱን ዕለታት ከፈጸምን ሽርፍራፊዎቹን (15 ኬክሮስና 6 ካልዒት) እንመልከት፤ ከላይ እንደ ተመለከትነው በፀሐይና ጨረቃ ዓመታት መካከል የተፈጠሩትን 11 ቀናት ስድስቱ ለሕጸጽ ማሟያ ሲገቡ የቀሩት 5 ዕለታት ናቸው ጳጕሜን የምትባለውን ወር ያስገኟት፡፡ በጎርጎርዮሳውያኑ አቈጣጠር እነዚህ 5ቱ ዕለታት በጃንዋሪ፣ ማርች፣ ሜይ፣ ጁላይና ኦገስት ላይ ስለ ተጨመሩ ወሮቹ 31 ሊኾኑ ችለዋል፡፡ ይህንን የከፈለው በ46 ቅልክ የነበረው ዩልየስ ቄሣር ነው፡፡ ለአራቱ ወሮች 30 ቀን፣ ለአንዱ 28/29 (በየአራት ዓመቱ)፣ ለቀሩት ሰባት ወሮች ደግሞ 31 ቀን ሰጥቷቸዋል፤ ለአምስቱ ወሮች 31 ያደረጋቸው ከጳጕሜን ወስዶ ሲኾን ለሁለቱ ወሮች አንዳንድ ቀን የጨመረላቸው ደግሞ ከፌቡርዋሪ 2 ቀናት ወስዶ ወሩን 28 በማድረግ ነው፡፡ ከእንግዲህ የሚተርፉት ከላይ የየዕለቱን ልዩነት በዓመት ስናባዛ የቀሩት 15 ኬክሮስና 6 ካልዒት ናቸው፡፡ ሁለቱን ከላይ ያየናቸውን ስንደምራቸው (12 ኬክሮስ + 3 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት) 15 ኬክሮስ ከ 6 ካልዒት ይመጣሉ፡፡ 1 ዕለት 60 ኬክሮስ በመኾኑ 1 ዕለትን (60 ኬክሮስን) ለማግኘት ከላይ ያገኘነውን 15 ኬክሮስ በ4 ማባዛት ይኖርብናል፡፡ #ምንጭ_፤ **ስለ ባሕረ ሐሳብ የአባቶች የቃል ትምህርት **መልአከ ሰላም ዐምደ ብርሃን (የቀድሞ የደብራችን አስተዳደሪና አሁን የሊቃውንት ጕባኤ አባል፤ በደብራችን ‹‹በዕለተ ኅሪት ሰማዕኩከ፥ በዕለተ መድኀኒት አድኀንኩከ›› በሚል ካስተማሩት ትምህርት/ **ወልደ ያሬድ ሔኖክ **የዳንኤል ክብረት እይታዎች

አዋጅ፥ አዋጅ፥ አዋጅ፡፡ የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም፡፡ *** እንደ አምለከ አበው መድኀኔ ዓለም ፈቃድ #ለመስከረም_፬/ ፳፻፲፪ ዓ.ም. #የሚካሄደውን_ሰልፍ_በተመለከተ_የወጣ_መርሐ_ግብር_፤ *** ሰልፉ በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገራት መስከረም ፬ በአደባባዮች ይካሄዳል፡፡ *** በዕለቱም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ይገኛሉ፡፡ ሰልፉን ሁሉም ምዕመን በኀላፊነት የሚያስተባብረው ሲሆን፤ በግንባር ቀደምትነት ግን የሰ/ት/ቤቶች አንድነት፤ የመንፈሳዊ ኰሌጅ ተማሪዎችን ምሩቃን፤ በሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን፤ የወጣቶችና ጎልማሶች ማኅበራት ኅብረት፤ የሠለስቱ ምዕት ማኅበራት ኅብረት፤ የአእላፋት ድምፅ የካህናትና ምእመናን ተናሥኦት ኅብረት፤ የጽዋ ማኅበራት ሙሴና ደርገ ሙሴዎች ናቸው፡፡ *** መስከረም 4 ጠዋት 2.30-3፡30 ሰዐት ቅዳሴ እንዳበቃ ከየአብያተ ክርስቲያናቱ እስከ ተመደበላቸው መሰባሰቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ (ለምሳሌ የሰሜን አቅጣጫ እኛን ጨምሮ ገነተ ጽጌ ላይ ነው የምንገናኘው)፤ በሚከተለው ሁኔታ ጕዞ ይካሄዳል፡፡ ፠ ባለ መለከቶችና ባለ ጥሩንባዎች ድምፅ እያሰሙ ባንዲራን እያውለበለቡ ከፊት ይመራሉ፤ ፠ በመከተልም የበገና ዝማሬ የሚያቀርቡ ይከተላሉ፡፡ ፠ ማዕጠንት የያዙ ካህናት እያጠኑ ይመራሉ፤ ፠ የየሰንበት ትምህርት ቤት መለያ ልብስ(ዩኒፎርም)ና ጥንግ ድርብ የለበሱ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትና ተማሪዎች በዝማሬ ጭምር ይከተላሉ፤ /የሰ/ትቤቶች አመራር ያስተባብራሉ/ ፠ የጽዋ ማኅበራት በነጭ ልብስ (በማኅበራቸው መለያ ልብስ) ይከተላሉ /የየማኅበሩ ሙሴና ደርገ ሙሴ ያስተባብራሉ/ ፠ ጥንግ ድርብ የለበሱ መዘምራን ማኅሌታውያን ይከተላሉ /አጋፊሪና መጨኔ ያስተባብራሉ/ ፠ መስቀል የያዙ ዲያቆናትና ካህናት፤ ልብሰ ተክህኖ የለበሱ፥ ጥላና ድባብ የያዙ ካህናት ይከተላሉ፤ /ሊቀ ዲያቆንና ቄሰ ገበዝ ያስተባብራሉ/ ፠ ምዕመናን ነጭ ልብስ፣ ነጠላ (ቲሸርት) በመልበስ ይከተላሉ፡፡ /የሰባካ ጕባኤ አባላት ያስተባብራሉ/ * ** በተመደበልን ቤተ ክርስቲያን ከተገኘን በኋላ ጠዋት ከ3፡30-4፡30 በሊቃነ ጳጳሳት እየተመራን ወደ መስቀል አደባበይ ጕዞ ይካሄዳል፤ *** ከ4፡30-7፡30 በመስቀል አደባባይ ሰልፉ ይካሄዳል፡፡ *** የመንፈሳዊ ኰሌጅ ተማሪዎችና ምሩቃን /አስተባባሪዎች ያስተባብራሉ/ *** የማኅበረ ቅዱሳን አባላትና ተማሪዎችንም /የተመደቡላቸው አስተባባሪዎች ያስተባብራሉ፡፡/ ስለ ጽዮን ዝም አንልም፠ * ልዩ ማስታወሻ፤ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ተቃውሟቸውን ድጋሚ መስከረም 16 በደመራ ዕለት በትርዒቶቻቸው እንደ የሁኔታው ሊያቀርቡ ይችላሉ፡፡ * ተጨማሪ የሰልፉን ማብራሪያዎች በተመለከተ ነገ ይጠብቁ፡፡ #ላልሰሙት_ያሰሙ_ላልደረሰው_Like_Share_ያድርጉ_፡፡