ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 368 подписчиков, занимая 5 631 место в категории Религия и духовность и 2 191 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 368 подписчиков.

Согласно последним данным от 20 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -39, а за последние 24 часа — -5, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 22.39%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 7.98% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 441 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 226 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 22.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 21 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 368
Подписчики
-524 часа
+297 дней
-3930 день
Архив постов
ወይም ከደሴ → ወልድያ → ደብረ ታቦር → ወረታ → ፎገራ፤ ፲፰. ሐዋሳ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ሐዋሳ ሃገረ ስብከት ፥ ሐዋሳ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ሐዋሳ፡፡ ፲፱. ሆሳዕና ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሃገረ ስብከት፥ ሆሳዕና፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ሆሳዕና፡፡ ፳. ማፌድ ጓረባ ጠብረሪ ደብረ ዕንቊ ቅድስት ልደታ ወዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሃገረ ስብከት፥ ማፌድ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ሆሳዕና → ማፌድ፡፡ ፳፩. እዣ ስራይ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሃገረ ስብከት፥ እዣ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ሆሳዕና → እዣ፡፡ ፳፪. ደብረ ዘይት ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ፤ አድራሻ፤ ምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ አድአ ወረዳ → ደብረ ዘይት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ዘይት፡፡ ፳፫. አለም ገና ቤ/ን (ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ በድርብነት ይከብራል)፤ አድራሻ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ አለም ገና፤ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → ጀሞ → አለም ገና፡፡ አቅጣጫ ምንጭ ገዳማት ገጽ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com

#ጥር ፬፤ #በዓለ_ስዋሬሁ_ለዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ_፡፡ #በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የቅዱስ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ_በዓለ_ስዋሬ_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው #ገዳማትና_አድባራት፡፡ #በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፫ #ገዳማትና_አድባራት_፡፡ ፩. ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ማርያም ቤ.ክ. ታቦተ ሕጉ ከኢየሩሳሌም የመጣ፥ ከዐፄ ዮሐንስ ጋር በመቀለ፤ ከራስ ጉግሳ ወሌ ጋር በደብረ ታቦር፤ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ከደብረ ታቦር ወደ አዲስ አበባ መናገሻ ገተ ጽጌ ያመጣችው፤ አፄ ኀይለ ሥላሴ ደግሞ አሁን ያለውን ሕንፃ ያሠሩት፤ በአዲስ አበባ በወልደ ነጐጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም በመሰየም ብቸኛው ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ አራዳ ክፍለ ከተማ፥ ሰባራ ባቡር፥ አባ ኮራን፥ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ታክሲ፤ ከፒያሳ ጴጥሮስ ዐደባባይ → ዊንጌት አስኮ በሚለው ታክሲ ተሳፍረው ቤተ ክርስቲያኑን ያገኛሉ፡፡ ወይም ከመርካቶ ጎጃም በረንዳ → አዲሱ ገበያ (ቀጨኔ) በሚሉ ታክሲዎች ተሳፍረው ቤተ ክርስቲያኑን ያገኛሉ፡፡ ፪. ብሔረ ጽጌ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያምና መድኀኔዓለም ቤ/ክ (የሐዋርያው ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ታቦት ቤተ ክርስቲያኑ ከተመሠረተበት ከ፲፱፻፹፮ ዓ.ም ጀምሮ በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ፥ ብሔረ ጽጌ፤ ከብሔረ ጽጌ መናፈሻ 100 ሜትር ያህል ገባ እንዳሉ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሰታዲየም)(መርካቶ)(መገናኛ)→ አደይ አበባ/ሳሪስ/ → ብሔረ ጽጌ፡፡ ፫. ምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም (ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ባይከብርም፥ ከቀድሞ ጀምሮ በኪዳንና በሰዐታት፤ በውዳሴ፥ በቅዳሴ ይከበራል፡፡) አድራሻው፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ 6 ኪሎ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4 ኪሎ) → ሽሮሜዳ በሚለው ታክሲ (ምስካየ ኅዙናን ጋር) ወይም ከመርካቶ ራጕኤል (ከጊዮርጊስ)→ ሽሮሜዳ በሚለው → መነን (የካቲት 12 ት/ቤት) ተወርዶ → ምስካየ ኅዙናን፡፡ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፳፫ #ገዳማትና_አድባራት_፡፡ ፩. መአቁዲ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ (ጥንታዊው ደብር፤ ለአንድ ቀን ብቻ ጠበል የፈለቀበት)፤ አድራሻ፤ ትግራይ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ወልድያ → መአቁዲ፡፡ ፪. ደቡብ ወሎ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ (ጥንታዊው ደብር፤ ከመካነ ሥላሴ አጠገብ የሚገኝ)፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → መካነ ሥላሴ፡፡ ፫. ሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ሐይቅ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ደሴ → በወልድያ መስመር (ሐይቅ ከተማ) ፬. ደብረ በንኰል ገዳም አጠገብ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ አድራሻ፤ ትግራይ፥ ሰለኽላኻ፥ ከታላቁ ገዳም ደብረ በንኰል አጠገብ ትራንስፖርት፤ ከመቀለ(አኵሱም) → ሽሬ → ሰልኽላኻ → ደብረ በንኰል መስመር የቅ/ዮሐንስን ደብር ያገኙታል፡፡ ወይም ከጎንደር በሊማሊሞ ሽሬ (ዳንሻ፤ ሁመራ፤ ሽሬ) መስመር → ሰልኽላኻ → ደብረ በንኰል መስመር የቅ/ዮሐንስን ደብር ያገኙታል፡፡ ፭. አደቁዋረክ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ አኵስም (ማዕከላዊ ትግራይ) ሃገረ ስብከት፥ ማኅበረ ዴጎ አጠገብ/፤፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → በደሴ → ወልድያ → መቀለ → አኵስም → ማኅበረ ዴጎ → አደቁዋረክ፤ ወይም ከአ.አ. (በአውሮፕላን ) → አኵስም → ማኅበረ ዴጎ → አደቁዋረክ፤ ወይም ወይም ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በቡሬ/በሞጣ/ ባህርዳር → ጎንደር → ከጎንደር በሊማሊሞ ሽሬ (ዳንሻ፤ ሁመራ፤ ሽሬ) መስመር → ሽሬ → አኵስም → ማኅበረ ዴጎ → አደቁዋረክ፤ ፮. ገደፈና_ዮሐንስ /ማይጨው አጠገብ/፤ አድራሻ፤ ትግራይ፥ ማይጨው ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → በደሴ → ወልድያ → ማይጨው → ገደፈና፤ ፯. መንዝ ማማ ሞላሌ ደዋ ዮሐንስ (900 ዓመታት በላይ ያስቈጠረ) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፥ ሞላሌ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ሞላሌ → ደዋ፤ ፰. ዣት ደብረ ፀሐይ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ጅሩ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → በደብረ ብርሃን በኩል → ጅሩ ፥ እነዋሪ → ዣት፤ ወይም ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በሙከጡሪ (መርሐ ቤቴ መስመር) → ለሚ → ጅሩ ፥ እነዋሪ፤ ፱. ዘንስር ደብረ ተድላ ዮሐንስ ማዕከላ ለጐንደር፤ /ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱና ዋነኛው፤ በጎንደር ከተማ የማኅሌተ ጽጌ ቁመት ወደ ግምጃ ቤት ማርያም ከመዛወሩ በፊት በብቸኝነት የጎንደርና የመላው ኢትዮጵያ ሊቃውንት የማኅሌተ ጽጌን ቁመት ለመቆም የሚተሙት ታላቅ ደብር/፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አራዳ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በቡሬ /በሞጣ/ መስመር → ባህር ዳር → ወረታ → ጎንደር ከተማ፡፡ ወይም ከመቀለ /አኵሱም/ → ሽሬ → በሊማሊሞ (በሁመራ ዳንሻ) → ጎንደር ከተማ፤ ወይም ከደሴ → ወልድያ → ደብረ ታቦር → ወረታ → ጎንደር ከተማ፤ ፲. ሞያሌ ደጋ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ሞያሌ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. → ሞያሌ፤ ፲፩. ደምበጫ አጠገብ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ ደምበጫ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → /በባህር ዳር መስመር/ ደምበጫ፤ ፲፪. ቦኮሙራ ወልደ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ.ን፤ አድራሻ፤ ሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት፥ ሚሻ ወረዳ፥ ቦኮሙራ ቀበሌ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ስልጤ → በኮሙራ፤ ፲፫. ናዝሬት(አዳማ) ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ምሥራቅ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ናዝሬት(አዳማ)፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → በደብረ ዘይት (በፈጣን መንገድ) → ናዝሬት (አዳማ) ከተማ፤ ፲፬. ደሴ ዩኒቨርሲቲ ደብረ ነጎድጓድ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ደሴ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ደሴ ከተማ፤ ፲፭. መቱ ደብረ ሳሌም ወነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፤ (በ1915 ዓ.ም. የተመሠረተ) አድራሻ፤ ም.ወለጋ ሃገረ ስብከት፥ መቱ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ወለጋ/መቱ፤ ፲፮. ጨንቻ ዶርዜ አይራ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ጋሞ ጎፋ ሃገረ ስብከት ፥ ጨንቻ ወረዳ፥ ዶርዜ አይራ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ወለጋ/መቱ፤ ፲፯. ፎገራ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት ፥ ፎገራ ወረዳ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በቡሬ /በሞጣ/ መስመር → ባህር ዳር → ወረታ → ፎገራ፡፡ ወይም ከመቀለ /አኵሱም/ → ሽሬ → በሊማሊሞ (በሁመራ ዳንሻ) → ፎገራ፤

ጥር  3 የደብረ_ሊባኖስ_ገዳምን_የመሠረቱና_በስማቸው_የተሠየመላቸው እና የእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳምን_ጸበል_ያፈለቁ የታላቁ አባት  አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ  በዓለ ዕረፍት ነው ። #ጥር ፫፤ #የአቡነ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ_በዓለ_ዕረፍት_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፲፩ ገዳማትና አድባራት (ከታች)፡፡ #በአ.አ. #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት ቀድሞ በቅዳሴና በውዳሴ ታቦተ ሕጋቸው ሲከበር የቆየው የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ታቦተ ሕጋቸው #ዓርብ_ጥር 3/2015 ዓ.ም. ዐምስተኛ ጊዜ_ታቦተ_ሕጋቸው_ወጥቶ_ይከብራል፡፡ (ሁላችሁም እንድትገኙ ገዳሟ ጥሪዋን አስተላልፋላች)፡፡ አባ ሊባኖስ #የደብረ_ሊባኖስ_ገዳምን_የመሠረቱና_በስማቸው_የተሠየመላቸው፤ ፠ ቅዱስ ላሊበላ ከ11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱን በስማቸው ያነፀላቸው፡፡ ፠ #ከደረቅ_ዐለት_ላይ_ውሃ_እያፈለቁ_ድውያንን_የሚፈውሱ_ተአምረኛ_አባት ፠ በኤርትራ አካለ ጉዛይ ገዳመ መጣዕ፣ በአኵሱም ከተማ አጠገብ፣ በላስታ ላሊበላ፣ ደብረ ወርቅ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፣ እንዲሁም ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ በአ.አ. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ገዳም ክብረ በዓል የሚከበርላቸው። ፠ አባታቸው አብርሃም እናታቸው ንግሥት ሊድሯቸው ሲሉ መመነን በመፈለጋቸው መልአክ በሌሊት መጥቶ ወደ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡ ፠ አባ ጳኩሚስም ሥርዐተ ገዳምን፥ አስኬማ መላእክትን፥ ቅናተ ዮሐንስን አስተማሯቸው፤ አመነኮሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡ ፠ ቀድሞ የመራቸው መልአክ ከአባ ጳኩሚስ ‹‹ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድሎህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአኵሱም ተቀመጡ፡፡ ፠ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው (ቀድሞ የዋልድባን ገዳም ባስፋፉ አባቶች የተመሠረተችውን #የእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳምን እስፋፍተው፡፡) ተመልሰው ወደ አኵሱም ሄዱ፡፡ ፠ በአኵሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ፥ ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአኵሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል ‹‹ተራ ውሃ ነው›› ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጥጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ ‹‹አምላከ አባ ሊባኖስ›› ብሎ አመሰገነ፡፡ (ስዕላቸው የሚገልጸው ይህንን ተአምር ነው፡፡) ፠ ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው ‹‹ምትሃት ነው የሚያሳየው›› ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡ ፠ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአኵሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ፤ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው ‹‹አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን›› ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡ አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡ ፠ ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ (የአሁኗ ደብረ ሊባኖስ) መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው ‹‹ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ (አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኮሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል›› አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን ‹‹ደብረ ሊባኖስ›› ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡ ፠ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አኵሱም ወሰዳቸው፡፡ ከዚያም ‹‹ታሪክ ወደምትሠራበት ዕጣ ክፍልህ ወደሆነው ቦታ አደርስሃለሁ›› አላቸውና ወደ ኤርትራ አካለ ጉዛይ አውራጃ ልዩ ስሙ መጣዕ ወደተባለው ቦታ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም አባታችን ድውያንን እየፈወሱ፣ ለምፃሞችን እያዳኑ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ወንጌልን እየሰበኩ ‹‹ሊባኖስ ዘመጣዕ›› የሚባለውን ትልቁን ገዳማቸውን መሠረቱ፡፡ በወቅቱ የነበረው አፄ ገብረ መስቀልም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን አሠራላቸው፡፡ ፠ ቅዱስ ላሊበላ 23 ዓመት ሙሉ ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶች ውስጥ አንደኛውን በአባ ሊባኖስ ስም ሰይሞላቸዋል፡፡ አፄ ገብረ መስቀል ያሠራላቸው ሌላኛው ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ የሚታወቁት አባታችን እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን ላይ ብርሃንን አብርተዋል፡፡ ፠+፠ በመጨረሻም ጥቅምት 2 ቀን ተፀንሰው ፤ ፠+፠ ሐምሌ 3 ቀን ተወለደው፤ ፠+፠ በ140 ዓመታቸው ጥር 3 ቀን በክብር ዐርፈዋል፡፡ ፠+፠ ቅዳሴ ቤታቸው ደግሞ ሐምሌ 3 ነው፡፡ ይኸውም ለመጀመሪያ ጊዜ በዐፄ ገብረ መስቀል ጊዜ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ የተመረቀበት ዕለት ነው፡፡ * እኛም ለክብረ በዓሉ የሚሆነውን ከዋይዜማው ጀምሮ ሙሉውን ሥርዐተ ማኅሌት እነሆ ብለናል፡፡ #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም ፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡ ፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው ጠበሏን አፍልቀው ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡ ፠ በ197 ዓ.ም.  አንድ ምዕመን ለአቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር  እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡ ፠ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ይመስገን፨

#ጥር ፫፤ #የአቡነ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ_በዓለ_ዕረፍት_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፲፩ ገዳማትና አድባራት፡፡ (አባ ሊባኖስ በሃገራችን ላይ 80 ገዳማትን መሥርተዋል) በ79 ገዳማትና አድባራት ላይ ሲከበሩ ዐበይቶቹ የሚከተሉት ናቸው፤ #በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ እንጦጦ፤ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ ጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (ከመርካቶ) → ሽሮ ሜዳ → እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት፡፡ #ለቅምሻ_በአጭሩ፤ #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም ፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ደግሞ ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡ ፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው፥ ጠበሏን አፍልቀው፥ ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡ ፠ በ1967 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡ ፠ ባለውለታዋን ዘንግታ የቆየችው እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳምም ከ በኋላ በዕለተ እሑድ ጥር 3/2012 ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ ታቦተ ሕጉን አውጥታ አክብራለች፨ ፪. አያት ጣፎ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ን፡፡ (በድርብነት ይከበራል) አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አያት 2 ኮንዶሚንየም ትራንስፖርት፤ ከመገናኛ → አያት(በሲኤምሲ) አደባባይ ወደ ጣፎ በሚወስደው መንገድ ወይም ከመገናኛ በኮተቤ ጣፎ /አባ ኪሮስ ጋር ወርደው/ በባጃጅ (በታክሲ) ያገኙታል፡፡ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፱ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ደብረ ወርቅ ገዳመ መጣዕ አቡነ ሊባኖስ፤ (በ523 ዓ.ም. በጻድቁ በአቡነ ሊባኖስ የተገደመና በአፄ ገብረ መስቀል የታነጸ፥ ገደል ወገብ ላይ የታነፀና የሚያስደንቅ፡፡) (የጻድቁ የከበረ አጽም የሚገኝበት፥ ሙት ያስነሳበት፥ ዕውር ያበራበት ገዳም ነው) አድራሻ፤ ደቡብ ኤርትራ፥ አካለ ጉዛይ አውራጃ፥ ሃም ታርካ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ (በአውሮፕላን) → ኤርትራ → አካለ ጉዛይ → ሃም ታርካ፡፡ ፪. አኵሱም አጠገብ የሚገኝ አባ ሊባኖስ፤ (ጻድቁ የዋሻ በዓት ሠርተው የጸለየበት፥ 7ት ዓይነት ጠበል ያፈለቀበት፤ አንዲት እናት ውኃ ነው ብላ ብትዳፈር ልጇ ሞቶባት እንደ ኤልያስ ያስነሳበት፥ የአከባቢው ካህናት ቢያድሙበት እንደ ኤልያስ በዚህ አካባቢ ላይ ለ3ት ዓመት ዝናብ እንዳይዘንብ የከለከለበት ኋላ ደግሞ በይቅርታ ቢጠይቁት ዝናብ ያዘነበበት ነው) (ልጅ ያጡ የሚወልዱበት መታሻ ደንጊያ ያለበት፥ ከዐለት ላይ የሚፈልቅ ተአምረኛ ጠበል ያለበት) (ገዳሙ ዋሻና ለእኅቶች ደግሞ ክብ ሕንፃ ቤ/ን አለ) አድራሻ፤ አኵስም ሃገረ ስብከት ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ በጎንደር/በሽሬ/ → አኵስም → የ10 ብር ትራንስፖርት(የ2ሰዐት የእግር መንገድ) ወይም ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ በደሴ/ወልድያ/መቀለ/ → አኵስም → የ10 ብር ትራንስፖርት(የ2ሰዐት የእግር መንገድ) ፫. ተንቤን አምበራ አቡነ ሊባኖስ (በአፄ ገብረ መስቀል የታነፀ) አድራሻ፤ ትግራይ ትራንስፖርት፤ ከአኵሱም → ተንቤን ፬. ላስታ ላሊበላ ቤተ አባ ሊባኖስ (ቅዱስ ላሊበላ ለ23ት ዓመታት ካነጻቸው አንዱ፥ በላስታ ከሚገኙት 11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ አንዱ የኾነና ከ11ዱ ሙሉ ለሙሉ ከተራራ ላይ ተፈልፍሎ ባለመውጣቱ በአሠራሩ ልዩ የኾነ) አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ላስታ፥ ላሊበላ ከተማ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ በደሴ/በጋሸና/ → ላሊበላ ወይም ከአ.አ. (በአውሮፕላን) → ላሊበላ ወይም ከጎንደር (ባህር ዳር) /በወረታ/ /ደብረ ታቦር/ /ጋሸና/ → ላሊበላ ወይም ከመቀለ በወልድያ መስመር/ጋሸና/ → ላሊበላ ፭. ዛራ ሐሙሲት አካባቢ የሚገኘው አባ ሊባኖስ (ቅዱስ ላሊበላ ለ23ት ዓመታት ካነጻቸው አንዱ) አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት ትራንስፖርት፤ ከባህር ዳር /በጎንደር መስመር/ → ሐሙሲት ፮. ጎንደር ግራርጌ (ቆላ ድባ) ፈለገ ሕይወት አቡነ ሊባኖስ፤ (በአፄ ገብረ መስቀል እንደተመሠረተ የሚነገርለት፥ አጸዱ እጅግ በጣም የሚማርክ /ዕድሜ ጠገብና አርስ በእርሱ የገጠመ 4 ትላልቅ ወርካና 4 ጽድ የሚገኝበት፤ ወርካውን ፈልፍለው መነኰስ ይኖሩበት የነበረው ለምስክር ቆሞ የሚገኝበት፥ 1ዱ ጽድ በ1880 አካባቢ ወድቆ እስካሁን ዝናብና ፀሐይ እየፈራረቀበት ሳይበሰብስ የሚገኝበት)፤ ውሎ ቅዳሴ የሚቀደስበት፤ የአከባቢው ገበሬ እህሉን ወደ ጎታው ከቅዳሴ በኋላ የሚያስገባበት የበረከት ቃል ኪዳን የተሰጠው ምድር፡፡ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደንቢያ ወረዳ፥ ቆላ ድባ ከተማ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከጎንደር (አዘዞ) → ወደ ጎርጎራ መስመር (በደረስጌና በቆላ ድባ መሃል ላይ ያገኙታል) (በ25 ኪ.ሜ አስፓልቱ ዳር) ፯. በመንዝ ቀያ ሀገረ ገራዴ አባ ሊባኖስ አፅመ ቅዱሳን ዋሻ (ፈዋሽ ጠበልና አስገራሚ ዋሻ ያለበት)፡፡ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ፥ ዘመሮ ከተማ፥ በንዲ ቀበሌ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ዘመሮ → 9 ኪ.ሜ ያህል እንደተጓዙ በንዲ ቀበሌ (ከአዲስ አበባ 328 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ይገኛል) ፰. መንዝ ላሎ አንጀትላ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፥ ዘብር፥ ላሎ፥ አንጀትላ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ዘብር(247 ኪ.ሜ.) → የ2ት ሰዐት የእግር መንገድ → የአንጀትላ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፡፡ ፱. *** ነገር ግን የመሠረቱት፥ ለ40 ዓመታት በዓት ሠርተው የኖሩበትና፥ በስማቸው የሚጠራው ታላቁ ገዳም ደብረ ሊባኖስ ግን ባለፉት 10ር ዓመታት ውስጥ ገድላቸውን በግእዝና በአማርኛ ከማሳተም የዘለለ የሚጠበቅበትን ሥራ አልሠራም፡፡ (ያልጠቀስናቸውን አሳውቁን) /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/    #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com

የታኅሳስ ገብርኤል ክብረ በዓል በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም 🛑 በፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት/ቤት አባላት የቀረበ https://youtube.com/watch?v=OBIHHnxzZ1E&si=5k8TGzGx1dCuLbHI

እንኳን አደረሳችኁ ! #ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ #ጌና_እና_ልደት ጌና እና ልደት ዋዜማና ክብረ በዓል /የተለያዩ ቀናት/ ቢኾኑም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን ጌና ልደትን እየተካ እንጠቀምበታለን፤ ነገር ግን ይህ ሊስተካከል ይገባዋል፡፡ ልዩነት ስላለውም የኢትዮጵያ ብርሃን የተባለው አፈ ጳዝዮን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለጌናና ለልደት ለ2ቱም በዓላት ለየብቻቸው በመጽሐፈ ምሥጢር ድርሰት ደርሶላቸዋል፡፡ #ጌና፤ የልደት በዓል ዋዜማ ቀን ሲኾን በዚህ ቀን ‹‹በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ›› የተባለለትን ‹‹የገና ጨዋታ›› እንጫወታለን፤ የምንጫወትበት የኳሱ ስያሜ ‹‹ሩር›› ሲባል ስያሜውን ያገኘው፤ ሰብዓ ሰገል እልፍ እልፍ ሠራዊት አስከትለው የተወለደውን አይሁድ ንጉሥ ፍለጋ ወደ ንጉሡ ሔሮድስ ደርሰው ነበርና፤ ሔሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ፈልጎና በውስጡ ሸሽጎ ለሰብዓ ሰገል ሂዱ ሕፃኑን ፈልጉ ስታገኙትም ንገሩኝ ብሎ ሰድዷቸዋል፤ ነገር ግን በዚያው ሳይነግሩኝ እንዳይሄዱ በማለት እነርሱ ሳያውቁ ‹‹ሩር›› የተባለ ሰላይ በመሃላቸው አስገብቶ ነበርና ሰብዓ ሰገልን ይመራቸው የነበረው ኰከብ ተሠውሮባቸዋል፤ ሰብዓ ሰገል ሠራዊታቸውን ቢያጣሩ ከመሃከላቸው የተቀላቀለ ሩር የተባለ የሔሮድስን ሰላይ አገኙ ይህንንም ሰላይ የሰብዓ ሰገል ሠራዊት አንገቱን በሰይፍ ቀልተውታልና ያን ለማስታወስ ዛሬ በገና ጨዋታ ላይ ሩር የተባለው ኳስ የሔሮድስ ሰላይን ‹‹ሩር›› እንዲያስታውስ አባቶች ሥርዐትን ሠሩ፡፡ #ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ #‹‹ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ::›› /#ቅዱስ_ያሬድ/ ጌታችን ለሰው ልጆች ብሎ፤ የሰው ልጆች ፍቅር አገብሮት ንጽሕትና ቅድስት ከኾነች ከእመቤታችን ያለ ወንድ ዘር በመጋቢት 29 ተጸንሶ ታኅሣሥ 29 በ1ዓ.ም. (ዓለም ከተፈጠረ፥ ዘመን ከተቈጠረ በ5,500 ዓመት) በበረት ተወልደ፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው፤ ወሰነውም በሌሊት መንጋቸውን የሚጠብቁ እረኞች ነበሩ፡፡ መልአኩ መጥቶ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹እነሆ! ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና፡፡ ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ›› አላቸው፡፡ ሉቃ2፡10-12፡፡ ከመለአኩም ጋራ ሠራዊተ መላእክት መጥተው ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዕጓለ እመሕያው /ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ/›› አሉ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ እረኞቹ እርስ በርሳቸው ‹‹እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ፣ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ›› ተባባሉና ፈጥነው መጡ፡፡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ፡፡ አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ፤ የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሯቸው ነገር አደነቁ፤ የብርሃን እናቱ እመ አምላክ ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር፡፡ ሉቃ 2፡13-19፡፡ መላእክትም ሰማይ መንበሩ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆኑለት አምላክ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በጎል ተኝቶ በጨርቅ ተጠቅልሎ አይተውት ደስ ብሏቸው ወደ ሰማይ ቢያርጉ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በዕሪና ከመንበሩ አይተውት ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት›› ብለው አመስግነውት በጣዕም ላይ ጣዕም፤ በጸጋ ላይ ጸጋ ተጨምሮላቸው ደስ ብሏቸዋል፡፡ ልደቱን ይሹታልና፤ መላእክትም ብቻ አይደሉም እንስሳትም አራዊትም ደስ ብሏቸዋል፡፡ #ይህም_ሊታወቅ_አንድ_ባሕታዊ_በቋራ_/_ኋላ_ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም/_ቋርፍ_ሲምስ_ቶራ_ሚዳቋ_ዮም_ተወልደ_ መድኀኔ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ከሣቴ_ብርሃን፡፡ እያለች ስትዘል አይቷል። በጌታችን በልደቱ የባሕር ውኃ ወተትና ማር ተራሮች እንጀራ እንጨቶችም የበረከት ፍሬ ሆነዋል፡፡ ልደቱንም በኮከብ ተረድተው ሰብአ ሰገል (የጥበብ ሰዎች) ስማቸውም ማንቱሲማር፣ ሜልኩ በዲዳስፋ የተባሉ የፋርስ ነገሥታት ከገነት የተገኘ ወርቅ፣ ዕጣን ከርቤ አምጥተው ገብረውለታል፡፡ /ዘኅ 20፡17፡፡ ‹‹ሰው ሆይ! ፈጽመህ ደስ ይበልህ፣ እግዚአብሔር ዓለሙን ወዶታልና አንድ ልጁንም የሚያምንበት ሁሉ እስከ ዘለዓለም ፈጽሞ ይድን ዘንድ አሳልፎ ሰጥቷልና ልዑል ክንዱን ሰደደልን፡፡›› ‹‹በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፤ ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ፤ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት፡፡ የማይታወቅ ተገለጠ፣ የማይታይ ታየ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ፡፡›› ‹‹ከቅድስት ሥለሴ አንዱ ወልድ መዋረዳችንን አይቶ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ባሕርዩን ዝቅ አደረገና መጥቶ በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀርም እንደ እኛ ሰው ሆነ፡፡ ነቢያት ትንቢት እንደተናገሩለት በቤተልሔም ተወለደ፤ ፈጽሞ አዳነን፣ ወገኖቹም አደረገን፡፡›› ይህችም ዕለት፤  ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ብሎ ትንቢት የተናገረላት ናት፡- ‹‹እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅ ትወልዳለች፣ ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች፣ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ /ት.ኢሳ. 7፥14/ **ነቢይ ሕዝቅኤል ‹‹እግዚአብሔርም አለኝ ‹ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች፣ አትከፈትም፣ የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር››› አለ፡፡ **ነቢዩ ዳንኤልም ‹‹ሌሊት በራእይ አየሁ ‹እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ፤ ዘመኑን ወደሚያስረጅ ደረሰ፣ ከፊቱም አቀረቡት፣ የዘላለም አገዛዝ፣ ጌትነት፣ መንግሥት ተሰጠው፡፡ ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል፤ አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው፤ መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው››› አለ፡፡ **ዳግመኛም ኢሳይያስ ‹‹እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጠልኝ›› አለ፡፡ አሁንም ደግሞ ‹‹አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ›› አለ፡፡ ሁለተኛም ‹‹በእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፣ ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል›› አለ፡፡ ዳግመኛም ‹‹ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው፣ ስሙም ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ይባላል›› አለ፡፡ **ነቢዩ ኤርምያስም ስለ እግዚአብሔር ‹‹በዚያን ወራት ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ፣ በምድርም የቀና ፍርድን ያደርጋል፣ እግዚአብሔርም ያመኑትን ያድናቸዋል›› አለ፡፡ **ኤልሳም ‹‹እግዚአብሔር ከሰማይ ይወርዳል፣ በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ ዕውነትን ያስተምራቸዋል፡፡ ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆኑ ወገኖች በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል›› አለ፡፡ **ናሆምም ‹‹እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል፣ ልብሱም እንደልብሴ ነው›› አለ፡፡