ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 408 подписчиков, занимая 5 577 место в категории Религия и духовность и 2 192 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 408 подписчиков.

Согласно последним данным от 12 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 76, а за последние 24 часа — 7, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.12%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.38% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 871 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 446 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 23.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 13 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 408
Подписчики
+724 часа
+347 дней
+7630 день
Архив постов
ጥር 18 ዝርወተ አጽሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ በተለያዩ የሃገራችንና የዓለማችን ክፍሎች ተከብሮ ውሏል፤ በተለይ ግን በጎንደር ከተማ የሚገኘው ርዕሰ አድባራት አበራ ጊዮርጊስ እንደ ጥምቀት በዓል ወደ ባሕረ ጥምቀት በዋይዜማው ወጥቶ አድሮ ነው የሚመለሰው፤ እኛ ለዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኘው የደብረ ጽባሕ ቅዱስ ጊዮርጊስ የገበያ ቦታውን ባርኮ ሲመለስ የሚያሳየውን በፎቶ አቅርበንላችኋል /በፎቶ ላይየምታይዋቸው ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም ታላቁ አባት ናቸው/ ፡፡ የጎንደር አበራ ጊዮርጊስ ፎቶ ያላችሁ ላኩልን፡፡ /በነገራችን ላይ በጎንደር በጥር ወር የሚከበሩ በዓላት ወደ ጥምቀተ ባሕር በመውጣት የሚከበሩ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ጥር 18 አበራ ጊዮርጊስ፤ ጥር 21 ሎዛ ማርያም፣ ጥር 22 ቅዱስ ዑራኤል (በዓታ ያለው)፤ ጥር 25 ቅዱስ መርቆሬዎስ በተለይ በገጠሩ አካባቢ፡፡ እርሱ እንደ ንብ አውራ ፈረሱ እንደ አሞራ፤ ጊዮርጊስ፥ ጊዮርጊስ፥ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያን አደራ፡፡ ሰአል ለነ ጊዮርጊስ፤ ሰማዕተ ኢየሱስ ክርስቶስ፡፡ ዘሐረፀከ ዱድያኖስ፤ ወወገረከ ደብረ ይድራስ፤ ዘዘረወከ በነፋስ፡፡

5.18 ሥርዐተ ማኅሌት ዘጥር ፲፰ በዓለ ስባረ ዓፅሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ፡፡

አዲስ ቤተ ክርስቲያን ሲሰራ (ቅዳሴ ቤት ሲከበር) ወይም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ታንጾ ሲመረቅ የሚባለውን #ሥርዐተ_ማኅሌት እነሆ አቅርበንላችኋል፡፡ (ቤተ ክርስቲያኑ የቅዱስ ገብርኤል ከሆነ የሚቆመው ማኅሌት ከሌሎቹ ሁሉ ስለሚለይ የማኅሌቱን ጽሑፍ ያለ ሐረግ አዘጋጅተነዋል፡፡) #የሚመረቁ_አብያተ_ክርስቲያናትን_እንጠቁማችሁ #እናንተም_ጨምሩባቸው፤ #አዲስ_አበባ_ደብረ_በረከት_ቅዱስ_ገብርኤል፤ ካራቆሬ፤ አየር ጤና አጠገብ፤ ጅማ በር (ጥር 18 ስባረ ዓጽሙ ለጊዮርጊስ፤ ጥር 19 ቅዳሴ ቤቱ ለቅዱስ ገብርኤል) #መጠቆሚያ_ማርያም፤ ጊንጪ፤ በ1942ዓ.ም. የተመሠረተች፤ /ጥር 21 ይመረቃል/፤ #ሰንበት_ትምህርት_ቤታችን_ወደዚህች_ቤተ_ክርስቲያን_ለመሄድ_የምትፈልጉ_በምረቃዋ_ዋይዜማ_ጥር_20_ጀምሮ_ጉዞ_አዘጋጅቷል_/ #ሻምቡ_ከምቦልቻ_ማርያም፤ ሆሮ ጉድሩ፥ ወለጋ፤ /ጥር 21 ይመረቃል/ #ሻምቡ_ቃዎ_ጊዮርጊስ፤ ሆሮ ጉድሩ፥ ወለጋ፤ /ሚያዝያ 21 ይመረቃል/ #ተጎራ_ማርያም፥ መርሐ ቤቴ፥ ሰሜን ሸዋ /ጥር 21 ይመረቃል/ /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት/

በባሌ ሀገረ ስብከት ሮቤ ከተማ የሚገኘው የመ/መ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ረቡዕ ጥር 15 ቀን 2011 ዓ.ም. ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ላይ ለጊዜው ባልታወቀ መንስኤ መቃጠሉን መ/ር ያሬድ ገ/ማርያም የወረዳው ቤተ ክህነት ጸሐፊ ገለጹ፡፡ የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ቃለ ምዕዳን በሰጡበት ወቅት "ልጆቼ ሁሉም ፈቃደ እገግዚአብሔር ነው፤ ቃጠሎው ከምን እንደሆነ እግዚአብሔር ይመርምር" ብለዋል፡፡ ችግሩን ለመፍታት ክርስቲያንና ቀናነት ያላቸው ሙስሊም በአንድነት ተባብረዋል፡፡ #ጸልዩ_በእንተ_ሰላመ_ቤተ_ክርስቲያን_አሐቲ_ቅድስት_ጕባኤ_እንተ_ሐዋርያት_ርትዕት_በኀበ_እግዚአብሔር፡፡ (ሐዋርያት በሰበሰቧት በእግዚአብሔር ዘንድ ሰለቀናች፤ ክብርት ስለምትኾን አንዲት ቤተ ክርስቲያን ጸልዩ፡፡) #ጸልዩ_በእንተ_ሰላም_ፍጽምት_ወፍቅር_ተአምኁ_በበይናቲክሙ_በአምኃ_ቅድሳት፡፡ (ፍጽምት ስለምትኾን ሰላምና ፍቅር ጸልዩ፤ እርስ በእርሳችሁ በተለየች ሰላምታ እጅ ተነሳሱ፡፡) #አድኅነኒ_ወባልሐኒ_እምእዴሆሙ_ለደቂቀ_ነኪር_እለ_ከንቶ_ነበበ_አፉሆሙ_ወየማኖሙኒ_የማነ_ዐመፃ፡፡ (አድነኝ አፋቸውም ምናምን ከሚናገር ቀኛቸውም የሐሰት ቀኝ ከኾነ፤ ከባዕድ ልጆች እጅ አስጥለኝ፡፡) /#መዝ.፻፵፫፥፯/ ✤#በሐኪ_በሐኪ_ቤተ_ክርስቲያን_እምነ፤ #ግበሪ_ጸሎተነ_በእንቲአነ፤ #እምኀይለ_ጸላዒ_ወፀር_ዕቀቢ_ኪያነ፤ #ትንባሌኪ_የሃሉ_ምስሌነ፡፡ ✤‹‹#እግዚኦ በመዓትከ ኢትቅሰፈነ፥ ወበመቅሰፍትከ ኢትገስጸነ፡፡›› መዝ.ዳዊት

እንኳን ደስ አለን፤ በመዲናችን በአ.አ. የቤተ ክርስቲያን ቤተ መዘክሮቻችንን ቊጥር ወደ 9 ከፍ የሚያደርገውን ቤተ መዘክር (Museum) በጥንታዊቷ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም ጥር 4/2011ዓ.ም. በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ተመርቆ ለእይታ ክፍት ሆነ፡፡ በእለቱም ጥሪ የተደረገላቸው የመንግሥት ባለሥልጣናት ተገኝተዋል፡፡ በአዲስ አበባ የሚገኙ 9ኙ ቤተ መዘክሮቻችን የሚከተሉት ሲኾኑ እየሄዳችሁ ታዩ ዘንድ እንጋብዛለን፡፡ #የጠቅላይ ቤተ ክህነት መንበረ ፓትርያርክ ቤተ መዘክር(Museum) ፤ #እንጦጦ ደብረ ኀይል ቅዱስ ራጕኤል ወኤልያስ ቤተ መዘክር(Museum) ፤ #እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ማርያም ቤተ መዘክር(Museum) ፤ #ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ቤተ መዘክር(Museum) ፤ #መናገሻ ገተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ መዘክር(Museum) ፤ #ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል የአቡነ ቴዎፍሎስ መታሰበያ ቤተ መዘክር(Museum) ፤ #መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ መዘክር(Museum) ፤ #ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤተ መዘክር(Museum) ፤ #እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳማ ቤተ መዘክር(Museum) ፡፡ (ሰፋ ያለ ታሪካቸውን ግን አዲስ በጀመርነው ‹‹ገዳማትና አድባራት›› መርሐ ግብር ላይ ከቤተ ክርስቲያናቸው ታሪክ ጋራ አብረን እናቀርባለን፡፡) #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም፡፡ ይህች ገዳም ታሪኳ ከታላቁ ገዳማችን ዋልድባ (ገዳመ ዋሊ) ለ2ኛ ጊዜ መሥፋፋት (መመሥረት ጋር) የተያያዘ ታሪክ ያላት ናት፡፡ ይኸውም የሸዋ አባቶች ወደ ዋልድባ #በ485_ዓ_ም_በንጉሥ_አልአሜዳ_ዘመነ_መንግሥት_ባቀኑ_ጊዜ_ለ3_ወራት_የተሰባሰቡባት_ቦታ_ናት፡፡ እነዚህም አበው ከመኖሪያ ቀዬቸው (ቡልጋ/ምንጃር/……) ሁለት ታቦታትን (ታቦተ ኪዳነ ምሕረት ዘምሕረት አምባና፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለም ዘአብዬ ገዳምን) ይዘው ነበር፤ ይዘዋት በመጡት ታቦተ ኪዳነ ምሕረትም ገዳመ ሐመረ ኖኅን መሥረተዋል፡፡ የመድኀኔዓለም ታቦትን ደግሞ በታላቁ ገዳም በዋልድባ አኑረዋል፡፡ ይህች #ሐመረ_ኖኅ_፤ *በ500 ዓ.ም. በአባ ሊባኖስ የአንድነት ገዳም ሆና ተስፋፍታ ተቋቋመች፡፡ *በ9ኛ መቶ ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት የአክሱም ጽዮንን ቤተ መቅደስ ለማቃጠል ስትነሳ ንጉሡ አንበሣ ውድም ታቦተ ጽዮንን በምሥጢር በማስያዝ ወደ ሸዋ መጥተው በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነምሕረት ገዳም ታቦተ ጽዮንን አሳድረው ወደ ዝዋይ ደሴት ሲሄዱ ለገዳሟ ንዋየ ቅድሰት ስጦታ አበርክተዋል፤ ጠበሏን ተጠምቀው ቦታዋን መርቀው ሄደዋል፡፡ *በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከንጉሥ ላሊበላ ጋር ወደ ዝቋላ አምባ ሲመጡ በዚህች ገዳም በእንግድነት አድረው በጠበሏ ተጠምቀው ቦታውን ባርከዋል፡፡ *አፄ ዘርዓ ያዕቆብም ወደዚህች ገዳም መጥተው አቀማመጧንና የጠበሏን ፈዋሽነት ተመልክተዋል፤ ‹‹ዳሯ እሳት መሐሏ ገነት ይሁን›› ብለው ብዙ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ *አፄ ልብነ ድንግልም ወደ ገዳሟ መጥተው ተማህጽኖ አድርገው በጠበሏ ተጠምቀው ታቦተ ልደታንና ብዙ ንዋየ ቅድሳት ሰጥተው ሄደዋል፡፡ *በንግሥት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት ይህች ገዳም ሐመረ ኖኅ ኪዳነምህረት ገዳም ተብላ ተሰይማለች፤ አሁን ያለው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያንም ታንጿል፡፡ ***ይህች ቦታ ከታላቁ ገዳም ከዋልድባ ጋር አሁንም ግንኙነቷ እንደጠነከረ ነው፤ በዋልድባ ያሉ አባቶች ለተለያየ ጉዳይ ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ በዋነኛነት የሚያርፉባት ጥንተ ርስታቸውም ናት፡፡ ይህች ቦታ በርካት ቅዱሳን በኪደተ እግር የረገጧት በመኾኗ የብዙ መነኰሳት መጠጊያ ናት፡፡ ጠበሏም የአጋንንት ድል መንሻ፥ የሕሙማን መፈወሻ፥ የአእምሮ ማደሻ ናት፡፡ የእመቤታችንን ቃል ኪዳን ለማግኘትም በአዲስ አበባ ከሚገኙ ቦታዎች ብዙ ጊዜ ለሱባኤ ከሚመረጡ ቦታዎችም አንዷ ናት፡፡ **ወደዚህች ገዳም በየወሩ ለኪዳነ ምሕረት የሚጎርፈው ምዕመን ኈልቈ መሳፍርት ያልተገኘለትና በሃገራችን በየወሩ ምዕመናን በመሳለም ትልቁን ቊጥር ይዟል፡፡ የዓመታዊ ክብረ በዓሉንማ ምንን እንነግራችኋለን፡፡ (ከሽሮ ሜዳ ታክሲ ቦታው ድረስ ያደርስዎታል፡፡)

#ጥር_15_በ2ት_ዓመት_ከ9ኝ_ወሩ_ሰማዕትነትን_የተቀበለው_ቅዱስ_ቂርቆስ_በ3_ዓመት_ከ1_ወር_ከ3_ቀኑ_አንገቱን_በሰይፍ_ተቆርጦ_ሰማዕትነትን_የተቀበለበት_በዓለ_ዕረፍቱ_ነው፡፡ #ስምህ_በተጠራበት_ቤተ_መቅደስህ_በታነጸበት_ስዕልህ_ባለበት_ቦታ_ሁሉ_የሕፃናት_እልቂት_የከብት_በሽታ_የእህል_እጦት_ረሀብ_ቸነፈር_አይደርስም የሚል ቃልኪዳንም ጌታችን ገብቶለታል፡፡ #በገባለት ቃል ኪዳንም መሠረት በመዲናችን #በአዲስ_አበባ በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመን የሰው እልቂት የከበት በሽታ ገብቶ በነበረበት ወቅት የቂርቆስ ደብር #መካነ_ሰማዕት ሲተከል የሰውም በሽታ ርቋል፥ የከብት እልቂትም አቁሟል፡፡ #በጎንደር_ደብረ_መንክራት_ቅዱስ_ቂርቆስ_ቤክ_ደግሞ_#ጽዋ_ማስደፋት_ የሚል ሥርዐት አለ በዚህ ሥርዐትም የሰረቀውን ሰው ቅዱስ ቂርቆስ የሚያጋልጥበትና አሁንም ድረስ የሚታይ አስደናቂ ተዓምር ነው፡፡ የሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ አባቱ ቆዝሞስ (ስምዖን) እናቱ ኢየሉጣ ሲባሉ፤ የተወለደው በዘመነ ሰማዕታት በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በኅዳር 15 ቀን ነው፡፡ የትውልድ ሀገሩ በታችኛው እስያ ልዩ ስሙ አንጌቤን ይባላል፡፡ አንጌቤናይት ብጽዕት ኢየሉጣም ባሏ በሕይወት ባለ መኖሩ በመበለትነት ትኖር ነበር፤ በዘመኑ የነበረው መምለኬ ጣዖት የሆነው ንጉሥ እስክንድሮስ ቅድስት ኢየሉጣን ‹‹ለጣዖቴ ስገጂ›› ብሎ አስገደዳት፡፡ እርሷም ‹‹ሕፃኑ ልጄ መጥቶ ይመስክር›› ብላ ስትናገር ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ተጠራና ተጠየቀ፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ‹‹ለጣዖት አንሰግድም፣ ዘላለማዊ የሆነ የማይሻር አምላክ ስላለ ለእርሱ ነው የምንሰግደው›› ብሎ የአምላኩን ክብር በሕፃን አንደበቱ መሰከረ፡፡ ሕፃኑም ይህንን በመሰከረ ጊዜ ዕድሜው ገና ሁለት ዓመት ከዘጠኝ ወሩ ነበር፡፡ ንጉሡም እጅግ ተቆጥቶ 40 ጋን ውኃ የሚይዝ በርሜል አስጥዶ 40 ቀን ሙሉ እሳት አስነድዶ ቅንጭብ፣ ዘይት፣ ዝፍጥና ሌላም በእጅጉ የሚጎዱ ነገሮችን ("ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል) በውስጡ አስጨመረ፤ የእሳቱ ድምፅ እንደ ነጎድጓድ እስኪሰማ፥ ወላፈኑም እንደ ፀሐይ እስኪያንጸባርቅ ድረስ ሆነ፡፡ የፍላቱም ኃይል 14 ክንድ ያህል እየዘለለ ወጣ፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣን ወደዚያ እቶኑ እሳት እንዲከቷቸው አዘዘ፡፡ በዚያን ጊዜም 11,004 እስረኞች ከእስር ወጥተው እንዲያዩ ሹሙ አዘዘ፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም የፍላቱን ግርማ ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተጠብቆላት ያለውንም ዋጋ ትታ ልትክድ ፈለገች፡፡ ቅዱስ ቂርቆስም ይህን ባወቀ ጊዜ "እናቴ ሆይ ከብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ፤ ድንጋፄም አይደርብሽ" እያለ ከብሉይና ከሐዲስ እየጠቀሰ እንድትጸና አስተማራት፡፡ እናቴ ሆይ አናንያን አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳናቸው እግዚአብሔር እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ውስጥ ሊያድነን ይችላል፡፡ እናት ሆይ ከሚያልፈው ከዚህ ዓለም ጭንቅ ልታመልጭ በሚያልፈው በዘለዓለም እሳት ልትቀጭ ትሻለች፡፡ እናት ሆይ ይህን አትፈልጊ፤ ይቅርብሽ አሁን እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡... እያለ አብዝቶ መከራት፡፡ ነገርግን በዚህም ምክር እናቱን መመለስና ለሰማዕትነት ማዘጋቸት አልቻለም፡፡ ከዚህ በኋላ ቂርቆስ ዓይኖቹን ወደሰማይ አቅንቶ መጸለይ ጀመረ፡፡ "እግዚአብሔር ሆይ ይህች ባርያህ ከምትክድ ከሕይወት መፅሐፍ እኔን ፋቀኝ..." ብሎ ጸለየ፡፡ በዚያን ጊዜ ዲያብሎስ ከእርሷ ሸሽቶ ሄደ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ እንዲህ አለች፤ በመንግስተ ሰማያት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታህ ኃይል ሰጠኝ፡፡ የሚጠብቀንን ገድላችንን እንፈፅምና ድል እንነሣ" አለችው፡፡ የብረት ጋኑን ሲነድ ሳየው በምንጭ ላይ በዝቶ እንደሚወርድ ጠል ሁኖ አየዋለሁና፡፡ ቅዱሳንም ይህንን ሲነጋገሩ አንስተው ከብረት ጋኑ ውስጥ ጨመሯቸው፡፡ በውስጡም አንገትን የሚቆለምም ልብን የሚያጣምም ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርንም የሚበጥስ መሣሪያ ነበረበት፡፡ ወዲያውም የራማው ልዑል ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ ከሰማይ ወረደና የብረት ጋኑን እሳት ፈጽሞ አበረደው፡፡ ከቅዱሳንም አንዱን እንኳን ሳይነካው የብረት ጋን ማቃጠሉና መፍላቱ ፀጥ አለ፡፡ እንደ ውኃም ሆነ፡፡ ንጉሡም እሳቱ እንዳልጎዳቸው ሲያውቅ ከዚያ አውጥቶ፤ * በአፍና አፍንጫቸው መርዝ ከተተበት፣ ነገር ግን መርዙ ምንም አልጎዳቸውም እንዳውም ምግብ ሆነላቸው፡፡ * ጨውና በርበሬ በዐይናቸው አነደደበት፡፡ አሁንም ምንም አልነካቸውም፡፡ * አስራ አራት የተሳሉና የጋሉ ብረቶች፤ ሰባቱን በእናቱ አካል፥ ሰባቱን በቂርቆስ አካል ውስጥ (ከነዚሁም ሁለቱን በጆሮዎቹ፥ ሁለቱን በዓይኖቹ፥ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ፥ አንዱን በልቡ) ተከሉ፤ አሁንም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ፈወሳቸው፡፡ * በ4 ችንካሮች ላይ አስቀመጧቸው፤ መልአኩ ፈወሳቸው * የራስ ጠጕራቸውን ከቆዳቸው ጋር ገፈው በእሳት ውስጥ ጨመሩት፤ ቅዱስ ገብርኤል እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጥቶ ፈወሳቸው፡፡ * በመቃን ውስጥ ጨመረው በገመድ ሰቀሏቸው፤ መልአኩ አዳናቸው፡፡ (ሐምሌ 19 ቀን የምናከብረው ክብረ በዓል ከላይ ያሉትን ሁሉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ለቅዱስ ቂርቆስና ኢየሉጣ የተራዳበትን በማሰብ ነው፡፡) ንጉሡም በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ በብዙ ጭንቅና ሥቃይ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣን ለ3 ዓመታት አሠቃያቸው፡፡ እነርሱም መከራን እየተቀበሉ በከሀዲው ንጉሥ ፊት የአምላካቸውን ስም እየጠሩ መሰከሩ፡፡ በመጨረሻም ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ተጋድሎውን ፈጽሞ ጥር 15 ቀን በ3 ዓመት ከ1 ወር ከ3 ቀኑ አንገቱን በሰይፍ ተቆርጦ ሰማዕትነትን ተቀበለ፡፡ ሲሰየፍም ከአንገቱም ደም፣ ውኃና ወተት የወጣ ሲሆን ሦስት አክሊላትም ወርደውለታል፡፡ ሕፃኑም በምድር ላይ አልተቀበረም ይልቁንም ጌታችን በኤልያስ ሰረገላ ሥጋውን አሳርጎለታል፤ ሄሮድስ ላስፈጃቸው 144,000 የቤቴልሔም ሕፃናትም አለቃቸው ነው፡፡ እናቱ ቅድስት ኢየሉጣም በጥር 16 ቀን ሰማዕትቷን በክብር ፈጽማለች፡፡ በዚሁ ዕለት የቅዱስ ቂርቆስ ማኅበርተኞች የሆኑ 11,004 ሰዎች የጌታችንን ክብር እየመሰከሩ በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ (ምንጭ፤ የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰሌዳ መጽሔት፣ ከገድላት አንደበትና ዝክረ ቅዱሳን) /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

ከቃና ዘገሊላ በዓል ትውስታ፤ (በመንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም)

#ወጽአ_ወገብአ_ በሰላም_፡፡ ከጥምቀት ትውስታ፤ #ቂርቆሶች በዓሉን ስዕላዊ(ድራማዊ) በማድረግ ተክነውበታል፤ (ፎቶዎቹን ይመልከቱ) #መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅ/ጊዮርጊዮሶች እንደ አድዋ ባንዲራ የቅዱስ ጊዮርጊስ ምልክት ባላበት ባንዲራ በማሸብረቅ የሚደርስባቸው አልተገኘም፤ #የደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖትና የጽርሐ ጽዮን ጰራቅሊጦስ ወጎላ ሚካኤል ከሕፃን እስከ ጎልማሰ የሰ/ት/ቤቶችን ስብጥር በማሰለፍ ቀዳሚ ነበሩ #የኮተቤ ደብረ ጽባሕ (ሲምሲ) ሚካኤሎች በባህላዊ አከባበር የኢትዮጵያን የተለያዩ ባህላዊ የጥምቀት አከባበሮች በአንድ ቦታ ላይ ተሰብስበው የታዩበት ነበር፤ #ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለሞች በአጥቢያቸው ከሚገኙ ማኅበራት ጋራ በመተባበር በሀዲያና በስልጤ ያደረጉት ሐዋርያዊ ጉዞ ለሌላውም ልምድ የሚሆን ነው (በሌላ ዘገባ ሰሞኑን እንመለስበታለን)፡፡ #ጎንደሮች 17ት አውሮፕላን ተጓዥ በቀጥታ የተሳተፈበትን በዓል በልዩ ሁኔታ አክብረውታል፡፡ # በጥምቀት ሌሊት በጨረቃ ላይ የጌታን መጠመቅ የሚያሳይ ስዕል ታየ # በዐረብ ሃገራት በባሕሬን የጥምቀተ ባህሩ ታቦታት ሲጠጉት እንደ ዮርዳኖስ ሲሸሽ ታየ /እኛ ይህንን ጻፍን፤ ሌሎችንም በዘንድሮ ጥምቀት የተመለከታችሁትንና ያሰማችሁትን ልዩ ልዩ ነገሮች ጻፉ)

በቃና ዘገሊላ፤ ዘገሊላ ከብካብ ኮነ፨ ሥርዐተ ማኅሌት ዘጥር ፲፪፥ ዘቃና ገሊላ (የምትመለከቱት ፎቶ ጌታችን በቃና ዘገሊላ ተዓምራት ያደረገበት የዶኪማስ ቤት ነው።) በኔትወርክ ም/ት ዘግየታችን በመለጠፋችን ይቅርታ እንጠይቀለን፨