ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 381 подписчиков, занимая 5 582 место в категории Религия и духовность и 2 194 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 381 подписчиков.

Согласно последним данным от 09 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 38, а за последние 24 часа — -1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 21.91%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.42% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 370 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 449 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 25.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 10 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 381
Подписчики
-124 часа
-67 дней
+3830 день
Архив постов
፠##፠ ሰላም ለከ #ሚናስ_ኅሩይ፥ ዘታዕካ ሰማይ፥ ዘኀረየከ አዶናይ፨ (አዶናይ አምላክ በሰማይ አዳራሽ የመረጠህ ሚናስ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን) በገባሬ ተዓምርነቱ የሚታወቀው ወጣቱ ሰማዕት ቅዱስ ሚና
+1
፠##፠ ሰላም ለከ #ሚናስ_ኅሩይ፥ ዘታዕካ ሰማይ፥ ዘኀረየከ አዶናይ፨ (አዶናይ አምላክ በሰማይ አዳራሽ የመረጠህ ሚናስ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን) በገባሬ ተዓምርነቱ የሚታወቀው ወጣቱ ሰማዕት ቅዱስ ሚናስ ዛሬ ኅዳር 15 በዓለ ዕረፍቱ ነው፨ **በኢትዮጵያ በአተር ቆሎ ብዙ ገቢረ ተዓምራት የሚያደርገው ገዳሞቹ ደቡብ ጎንደር ከባሕር ዳር ከተማ አጠገብ (ከአቡነ ሐራ ድንግል አቅራቢያ) እንዲሁም በደቡብ ሸዋ ጢያ ላይ ይገኛሉ፨ **በአ.አ. መርካቶ ራጉኤል ጋር ማኅበሩን የሚጠጡ አሉ፤ በሕመም የምትሰቃዩ ማኅበሩን ፈልጋችሁ የአተር ዝክሩን ቅመሱ፥ በእርግጠኝነት ትፈወሳላችሁ፨ **በግብፅ ግን በጣም ታዋቂ ሰማዕት ነው፨ ፠##፠ እንዲሁም፤ ዛሬ የቅዱስ ቂርቆስም በዓለ ልደቱ ነው፨ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ https://t.me/medihanaelem

ተወከፍ ጸሎተነ ውስተ ኑኃ ሰማይ፤ ከመ መዐዛ ሠናይ ሊቀ መላእክት፡፡ (ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል እንደ መልካም መዓዛ ጸሎታችንን በሰማይ ተቀበል፡፡)
ተወከፍ ጸሎተነ ውስተ ኑኃ ሰማይ፤ ከመ መዐዛ ሠናይ ሊቀ መላእክት፡፡ (ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል እንደ መልካም መዓዛ ጸሎታችንን በሰማይ ተቀበል፡፡)

#ጸሎተ_ምሕላ_ከኅዳር_15 - 17፡፡ ፠፠፠ በአጠቃላይ ስለ ሃገራችን ሰላም በመላው ዓለም የምንገኝ ምዕመናን ከሰኞ እስከ ረቡዕ (ከኅዳር 15 - 17/2012 ዓ.ም.) ማለዳ ከጸሎተ ኪዳን ጋር ጸሎተ ምሕላ እንድናደርግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል።

፠፠፠ ለቡ (ልዩ ማስታወሻ!!!) (N.B.) ፠ በዘመነ ዮሐንስም ሆነ በሌሎቹ 3ት ዘመናት፤ ማለትም (#ሁልጊዜም_በየዓመቱ_የገና_ጾም_የሚገባው_ኅዳር_15_ነው)፤ ፠ አንዳንድ ዓይናማ የጕባኤ መምህራን በዘመነ ዮሐንስ ኅዳር 14 ነው ጾሙ የሚገባው ይላሉ፤ ነገር ግን ቅዱስ ሲኖዶስ ከዚህ በፊት በጥቅምት 17/1980 ዓ.ም. በ4ቱም ዘመናት (ዘመነ ዮሐንስን ጨምሮ) የጾሙ መግቢያ ኅዳር 15 እንዲሆን ስለደነገገ፤ እንደ ቤተ ክርስቲያናችን ደግሞ የጾምን ሥርዐት ፥ ሰዐት፥ መግቢያና መውጫ ውሳኔ የሚያስተላልፍ ቅዱስ ሲኖዶስ ስለሆነ ጾሙ የሚገባው ኅዳር 15 ፤ ቅበላው ኅዳር 14 ነው፡፡

#ጾመ_ነቢያት_ (#የገና_ጾም_) የ2012 ዓ.ም. የገና (የነቢያት) ጾም፤ ፠#ቅበላው_እሑድ_ኅዳር_14_ድረስ_ብቻ_ነው_፤ ፠ #ጾሙ_ሰኞ_ኅዳር_15_ይጀምራል_!! ላልሰሙት Share/like በማድረግ ይተተባበሩ፡፡ ፠ ከ7ቱ አጽዋማት (ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ፍልሠታ፣ ጾመ ሐዋርያት፣ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌ ና ጾመ ገሃድ) መካከል አንዱ ነው፡፡ ፠ ኅዳር 15 ቀን ተጀምሮ እስከ ልደት ለአርባ ሦስት ቀናት የሚጾም ጾም ነው፡፡ ፠ ይህንን ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ብዙ ቅዱሳን ጾመውታል፤ በዚህም ምክንያት የሚከተሉት ስያሜዎች አሉት፡፡ እነርሱም፤ † ፩. #ጾመ_አዳም_፤ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገት ከተባረረ በኋላ; በፈጸመው በደል አዝኖ ፥ ተክዞ፤ አለቀሰ (እንባ ቢያልቅበት እዥ እስከሚያፈስ፤ እዥ ቢያልቅበት ደም በዓይኑ እስከሚፈስና ዓይኑ ይቡስ ወይም ደረቅ እስከሚሆን ድረስ አለቀሰ) ፥ ጾመ፣ ጸለየ፡፡ ከልብ የሆነ ጸጸቱን፣ ዕንባውን፣ በራሱ መፍረዱንም እግዚአብሔር አይቶ ተስፋ ድኅነት ሰጠው፡፡ ‹‹ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ፣ በደጅህ ድኼ፣ በዕፀ መስቀል ተሰቅዬ፣ ሞቼ አድንሃለሁ፡፡›› የሚል ነው፡፡ /ገላ. ፬፥፬፣ መጽ.ቀሌምንጦስ/ ስለዚህ ጾሙ የተሰጠው ተስፋ ፥ የተቆጠረው ሱባኤ ስለተፈጸመበት ‹‹ጾመ አዳም›› ይባላል፡፡ † ፪. #ጾመ_ነቢያት_፤ ነቢያትም የምሥጢረ ሥጋዌ ነገር ተገለጦ ስለታያቸው፣ ክርስቶስ ለሰው ልጅ የሚከፍለውን የፍቅር ዋጋ በትንቢት ተመልክተው ጾመውታልና ጾመ ነቢያት ይባላል፡፡ ይህ ጾም ከአባታችን አዳም እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ድረስ የተነሱ አበውና እናቶች: ድኅነትንና ረድኤትን ሲሹ የጾሙት ጾም ነው:: በተለይ አባታችን አዳም: ቅዱስ ሙሴ: ቅዱስ ኤልያስ፣ ቅዱስ ዳንኤል ና ቅዱስ ዳዊት በጾማቸው የተመሰከረላቸው ቅዱሳን ናቸው:: (ዘዳ 9:19, ነገ. 19:8, ዳን. 9:3፣ መዝ. 68:10, 108:24) ቅዱሳን ነቢያት በጭንቅ በመከራ ሆነው የጾሙት ጾም ወደ መንበረ ጸባኦት ደርሶ: ወልድን ከዙፋኑ ስቦታል:: ለሞትም አብቅቶታል:: † ፫. #ጾመ_ሐዋርያት_፤ ሐዋርያት ‹‹ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብራለን፣ ልደትን ምን ሥራ ሠርተን እናከብረዋለን?›› ብለው ከልደተ ክርስቶስ በፊት ያሉትን ፵፫ ዕለታት ጾመዋልና፡፡ † ፬. #ጾመ_ማርያም_፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ቅድስናዋን አይቶ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ወልደ አምላክን ያለ ሰስሎተ ድንግልና በግብረ መንፈስ ቅዱስ ጸንሳ እንደምትወልደው ቢነግራትም የትሕትና እናት ናትና ‹‹ምን ሠርቼ የሰማይና ምድርን ፈጣሪ እችለዋለሁ?›› ብላ ጌታን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማለችና ‹‹ጾመ ማርያም›› ይባላል፡፡ † ፭. #ጾመ_ፊልጶስ_፤ ሐዋርያው ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ እያስተማረ ሳለ በሰማዕትነት ሲሞት፤ አስክሬኑ ከደቀመዛሙርቱ ስለተሰወረ፤ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስክሬን እንዲገለጽላቸው ከኅዳር ፲፮ ጀምረው ጾመው በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስክሬን ተመልሶላቸዋል፤ ነገር ግን አስከሬኑ ቢመለስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል፡፡ † ፮. #ጾመ_ስብከት_፤ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት፥ የሰው ልጆች ተስፋ የተመሰከረበት፥ የምስራች የተነገረበት ስለሆነ ጾመ ስብከትም ይባላል፡፡ † ፯. #ጾመ_ልደት_፤ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት ስለሆነ ‹‹ጾመ ልደት›› ይባላል፡፡ ጾምን ትእዛዝ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን የፍቅርና የበረከት ምንጭ በመሆኑ ጭምር ደስ እያለን ብንጾመው የቅዱሳኑ በረከት ያድርብናል፡፡ ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት በአጭሩ የተዘጋጀ፡፡ https://t.me/medihanaelem የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡

ኅዳር ፲፫፤ እንኳን ለቅዱስ እግዚአብሔር አብና ለእልፍ አእላፋት፥ ትዕልፊት አእላፋት (ለቅዱሳን መላእክት በዓለ ሢመት)፤ በሰላምና በጤና አደረሰን፤ አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ (ከእልፍ አእላፋት አለቃ
+8
ኅዳር ፲፫፤ እንኳን ለቅዱስ እግዚአብሔር አብና ለእልፍ አእላፋት፥ ትዕልፊት አእላፋት (ለቅዱሳን መላእክት በዓለ ሢመት)፤ በሰላምና በጤና አደረሰን፤ አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ (ከእልፍ አእላፋት አለቃዎች ስሞች በጥቂቱ)፡፡ ጸሎትነ ትብጻሕ (ሰላም ለክሙ) ለመላእክተ ምሕረት፤ ፨ ሚካኤል ወገብርኤል፥ ፨ ሱራፌል ወኪሩቤል/፬ቱ እንስሳ/፥ ፨ ዑር(ራ)ኤል ወሩፋኤል /፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ/፥ ፨ ሱርያል ወፋኑኤል፥ ፨ አፍኒን ወራጕኤል፥ ፨ ሳቁኤል ወአቅናኤል፥ ፨ ብርናኤል ወሱባኤል፥ ፨ ፍናኤል ወሰላታኤል፥ ፨ ሰዳካኤል ወኤልናኤል፥ ፨ አናንኤል ወኢየሩማኤል፥ ፨ ግርማኤል ወድርማኤል ፥ ፨ ድማህኤል ወአድማኤል፥ ፨ ሙራኤል /ምናቴር አብያቴር/፥ ፨ ሱታ(ስቱ)ኤል ወሱርያል፤ ……. ፎቶዎቹ፤ ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ቦታዎች ጥቂቶቹ፤ …. 1. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (መስቀሉ የሚገኝበት)፤ 2. ጠዳ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (ጎንደር፤ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ)፤ 3. ጎርዶማ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን (በሰሜን ሸዋ)፤ 4. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (አዲስ አበባ)፤ 5. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) 6. ቦሌ ቡኒ ደብረ ቤቴል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፫፡፡ Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ለምን እንፈተናለን፤ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋ
+1
#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፫፡፡ Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ለምን እንፈተናለን፤ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋቸው፤ …. ……እንዳያመልጣችሁ፤ በሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ በብዙ ጕባኤያት ላይ ያልተዳሰሱ ርዕሶች የሚዳሰሱበት ጕባኤ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ፤ #ደግመን_እንላለን_ይህ_ትምህርት_በፍጹም_እንዳያመልጣችሁ!!!!! ለ፬ ተከታታይ ሳምንታት፤ ትምህርቱ ተከታታይነት ስላለው መቅረትና ማርፈድ አይመከርም!!፡፡ (፻፶፪ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ) ዐርብ ኅዳር ፲፪ ጀምሮ ከ፲፪-፪ ሰዓት አሁንም በድጋሚ እንላለን ለሕይወታችን ወሳኝና በብዙ የትምህርት ጕባኤያት ላይ የማይዳሰሱ ትምህርቶች ስለሆኑ እንዳያመልጣችሁ!!!! የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡

በመዲና ከተማችን የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል የሚከብርባቸው ገዳማትና አድባራትን እንጠቁማችሁ፡፡ /ፎቷቸውን ያልለጠፍናቸውና ስማቸውን ያልጠቀስናቸውን እንድትልኩልን በሊቀ መልአኩ ስም እንጠይቃለን) 1) *የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (ሾላ፤ መገናኛ) 2) *አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል /ጭቁኑ/፤ ፈረንሳይ 3) *ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል (አዲሱ ሚካኤል)፤ አውቶብስ ተራ 4) *ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል፤ /ቦሌ/ 5) *ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ /ላፍቶ/ 6) *ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል፤ (መካኒሣ) 7) *ኮተቤ ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል /ሳጠራው/ (ቀድሞ ኮተቤ አሁን ሲምሲ) 8) *ደብረ ምሕረት ሚካኤል (ቀድሞ ወህኒ ቤት ሚካኤል) 9) *መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል 10) *ገነተ አምባ ቅዱስ ሚካኤል 11) *ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል 12) *ካራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና 24ቱ ካህናተ ሰማይ 13) *ሐያት ጨፌ ኢያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (በ1980ዓ.ም ጽላቱ ከነ ድርሳናቱ ተቀብሮ የተገኘበት) 14) *መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም /ኋላ ወቅድስት አርሴማ በሚል እየተጠራ የሚገኝ/፤ (በቀጨኔ በአዲሱ ገበያና በእንጦጦ መሃል ጉብታ ላይ የሚገኝ) እንዲሁም በድርብነት 15) *እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት 16) *መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (ስድስትኪሎ) 17) *ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ (መስቀል አደባባይ) 18) *ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ቤ.ክ (ኋላ ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል በሚል እየተጠራ የሚገኘው)፤ (ኢምግሬሽን አጠገብ) 19) *ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ (ኋላ ወመካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም በሚል እየተጠራ የሚገኝ)

እንኳን ለቅድስት ሐና በዓለ ዕረፍት አደረሳችሁ፡፡ ፎቶዎቹ፤ በአ.አ. የሚገኙ የቅድስት ሐና አብያ ክርስቲያናት ፠ ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤ/ክ ፠ ኮተቤ መካነ ቀረዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤ/ክ እንዲ
+4
እንኳን ለቅድስት ሐና በዓለ ዕረፍት አደረሳችሁ፡፡ ፎቶዎቹ፤ በአ.አ. የሚገኙ የቅድስት ሐና አብያ ክርስቲያናት ፠ ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤ/ክ ፠ ኮተቤ መካነ ቀረዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤ/ክ እንዲሁም፡ ፠ ደብረ ንግስት መንዝ ቅድስት ሐና::

ኅዳር ፲፪፤ ቅዱስ ሚካኤል በእልፍ አእላፍ መላእክት ላይ የተሾመበትና እስራኤልን የመራበት ክብረ በዓል ነው፡፡ #በዓለ_ሢመቱ_፥#ወበዓለ_መራኄ_ፍኖቱ_ለቅዱስ_ሚካኤል_ሊቀ_መላእክት_፨ ኅዳር ፲፪ ለሰው ወገን የሚያዝንና የሚራራ፥ በእግዚአብሔር የጌትነት ዙፋን ፊት ሁልጊዜ ለምስጋና የሚቆም፥ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ፥ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመቱና እስራኤላውያንን በባሕረ ኤርትራ ያሸገረበት በዓል ነው፡፡ (እንኳን አደረሳችሁ) ፠ #፩ በዓለ ሢመቱ፤ ሚካኤል ማለት ማን እንደ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ከሌሎች መላእክት ጋር በእለተ እሑድ ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የተፈጠረ ሲሆን፤ እርሱም መጀመሪያ ከ100ው ነገደ መላእክት የ10ሩ ነገደ መላእክት (የኃይላት) አለቃቸው ነበር፤ በተጨማሪም ከሳጥናኤል ውድቀት በኋላ የኃይላት አለቅነቱን እንደያዘ የአጋእዝትን ነገድም (ሳጥናኤል/ሰማልያል/) ይመራቸው የነበሩትን 10 ነገዶችም በአለቅነት ደርቦ አለቃ ኾኗል፤ እንዲሁም በዛሬው ዕለት ለ100ውም(99ኙም) ነገደ መላእክት (ለእልፍ አእላፋት መላእክት) አለቃቸውም ቅዱስ ሚካኤል ኾኖ የተሾመበት ዕለት ነው፡፡ ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር ያሰኘውም ይኸው ነው፡፡ ቅ/ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 (ከበዓለ ሢመቱ) ጀምሮ እስከ ኅዳር 13 (የአእላፍ መላእክት) በዓል ድረስ ከአምላኩ ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረትን የሚለምንበት ዕለታት ናቸው፡፡ ፠#፪ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት እየመራቸው ማውጣቱን የሚዘከርበት በዓል ነው፡፡ ይህም የሆነው ያዕቆብ በረሃብ 70 ኹኖ ወደ ግብፅ ከወረደ በኋላ ከ215 ዓመታት (አብርሃም ወደ ግብፅ በተሰደደ ከ430 ዓመታት) በኋላ፤ የዮሴፍን ዝና ያልሰማ፥ ዮሴፍን የማያውቅ ፈርዖን በግብፅ ነገሠ፡፡ እስራኤል ከእኛ ይልቅ በዝተዋል ጠላቶቻችን ቢነሱብን ከጣለቶቻችን ጋር ተደርበው ያጠፉናል በማለት አገዛዝ አጸናባቸው፥ ፍርድ አጓደለባቸው፡፡ የእስራኤል ሴቶች ልጅ ሲወልዱ ወንድ ከሆነ እንዲገደል በማድረግ መከራ አጸናባቸው፡፡ ለ215 ዓመታት በግብፅ በባርነት ከቆዩ በኋላ ከዕብራውያን ወገን የሆነችው ራሔል ጭቃ እያቦካች ምጥ በያዛት ጊዜ ከሥራዋ እንዲያሳርፏት ጠየቀች፤ ግብጻውያን ግን የሕፃናቱ ደም ጡቡን ያጠነክራል ርገጭ አሏት፡፡ ከማሕፀኗ የወጡ ሁለት መንትያ ልጆቿን እያየች ከጭቃ ጋር ረገጠች፤ ራሔልም መሪር ልቅሶን አለቀሰች፤ ስለ ልጆቿም መጽናናትን እንቢ አለች፡፡ የእስራኤል ንጉሥ ሆይ የሆነብንን እይ ስትል ራሷን ይዛ ታለቅስ ጀመር ፥ እንባዋንም ወደ ሰማይ ንጉሥ ወደ እግዚአብሔር ረጨች፡፡ የራሔል እንባዋ የሕዝበ እስራኤልን ሁሉ ጩኸት ፥ እሮሮ ይዛ ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰች፡፡ “. . . ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች የሉምና ስለ ልጆቿ መጽናናት እንቢ አለች” /ኤር 31፥5፤ ማቴ 2፥17/ እንዲል፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን አስነሳና፤ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል መሪነት፤ 10 ተዓምራትን በምድረ ግብፅ በ11ኛ ተዓምር ደግሞ በኅዳር 12 (ፈርዖንን ከነሠራዊቱ በኤርትራ ባሕር አስጥሞ) ወደ ተስፋይቱ ምድረ መራቸው፡፡ ባሕረ ኤርትራን እስራኤላውያን እንደተሻገሩም የእስራኤል ልጆች የሙሴ የአሮን እኅት ማርያም ከበሮ እየመታች ‹‹ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ ፤ እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው እያሉ፡፡›› ጠላታቸውን የመታላቸውን ፥ እነሱንም በተአምራቱ ያሻገራቸውን ፥ ከጠላታቸው እጅ ያዳናቸውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ከዚህ በኋላ መጋቤ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው ፥ መና ከሰማይ እያወረደላቸው ፥ ውሃ ከጭንጫ እያፈለቀላቸው ፥ ቀኑን በደመና ፥ ሌቱን በብርሃን መርቷቸው አርባ ዘመን ተጕዘው የቃል ኪዳን አገራቸው ምድረ ርስት ከነዓንን (የዛሬዋ ኢየሩሳሌምን) ወርሰዋል፡፡ /ዘጸ. 15/ ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም እስራኤልን በሚመራበት ጊዜ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እስራኤልን ይረዳቸው ነበር፡፡ ከጠላቶቻቸው ጋር ሲዋጉም ሰልፉን ይመራ የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ለምሳሌ እስራኤላውያን ከኢያሪኮ አጠገብ በነበሩበት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ኢያሱን አነጋግሮታል፡፡ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ቀና ብሎ ሲመለከት የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ አንድ ሰው ከፊቱ ቆሞ አየ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ በመሆኔ መጥቻለሁ” ብሎታል /ኢያሱ 5፥13-15/፡፡ ይህ የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ ከኢያሱ ፊት ለፊት የቆመው መልአክ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል (እንዲሁም መልአኩ ቅዱስ ራጕኤል) ነው፡፡ ይህን ለአብነት አነሣን እጅ እስራኤል በሚበድሉበት ጊዜ ሁሉ ወደ እግዚአብሔር የሚማልድላቸው ይህ ታላቅ መልአክ መጋቤ ብሉይ ቅ/ሚካኤል ነበር፤ እግዚአብሔር አምላክ በእደ መልአኩ ይጠብቀን፤ ከበዓሉ ረድኤት ፥ በረከት ይክፈለን፤ አሜን፨ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ https://t.me/medihanaelem

#ለኅዳር_ጽዮን_ጕዞ_ወደ_መጠቆሚያ_ማርያም_፡፡ (የሰ/ትቤታችን አባላት፣ 30 የሚጠጉ የሰ/ትቤት ተዋካዮች፣ የአጥቢያችን ምዕመናንና ሕዝበ ክርስቲያንን በአንድነት የሚያሳትፍ ጕዞ) ፠የጕዞ ቀናት፤ ቅዳ
+1
#ለኅዳር_ጽዮን_ጕዞ_ወደ_መጠቆሚያ_ማርያም_፡፡ (የሰ/ትቤታችን አባላት፣ 30 የሚጠጉ የሰ/ትቤት ተዋካዮች፣ የአጥቢያችን ምዕመናንና ሕዝበ ክርስቲያንን በአንድነት የሚያሳትፍ ጕዞ) ፠የጕዞ ቀናት፤ ቅዳሜና እኁድ (ከኅዳር 20-21) 2012 ዓ.ም. ፠ለመመዝገብ፤ የሰ/ትቤታችን ልማት ክፍል፣ ትምህርት ክፍል ወይም መዝሙርና ኪነ ጥበባት ክፍል እንዲሁም በ0910 61 72 58 ወይም 0902 50 39 54 ብለው ይደውሉ፡፡ ፠የጕዞ ዋጋ፤ 250 ብር (ምግብን ጨምሮ) ፠የመመዝገቢያ ቀናት፤ እስከ ኅዳር 17/2012 ዓ.ም. /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#ጸሎተ_ምሕላ_፡፡ ስለ ጸሎተ ምሕላው ለጠየቃችሁን፡፡ ባለፈው ሳምንት በተጠቃጠሉብን አብያተ ክርስቲያናትና በተሰዉ ምዕመናን ዙሪያ ቅዱስ ሲኖዶስ ኅዳር 4/2012ዓ.ም. አስቸኳ ስብሰባ አድርጎ የሚከተ
#ጸሎተ_ምሕላ_፡፡ ስለ ጸሎተ ምሕላው ለጠየቃችሁን፡፡ ባለፈው ሳምንት በተጠቃጠሉብን አብያተ ክርስቲያናትና በተሰዉ ምዕመናን ዙሪያ ቅዱስ ሲኖዶስ ኅዳር 4/2012ዓ.ም. አስቸኳ ስብሰባ አድርጎ የሚከተሉትን 3ት ውሳኔዎች አሳልፏል፤ ፠1ኛ) በተፈጠሩትና እየተፈጠሩ ባሉ ጥቃቶች ዙርያ ከክልሉ መንግሥት ምክር ቤት (ጨፌ ኦሮሚያ) ጋር በአስቸኳይ መነጋገር እና መፍትሔ ማምጣት፡፡ ፠2ኛ) ከእስልምና ምክር ቤት (መጅሊስ) ጋር እየተፈጠሩ ባሉ ግጭቶች ምክንያት በምእመናን እና በአብያተ ክርስቲያናት ላይ እየደረሰ ስላለው ቃጠሎ በመነጋገር ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት፤ ፠3ኛ) ጸሎተ ምሕላ በመላው አብያተ ክርስቲያናት ከሰኞ እስከ ረቡዕ (ከ8 - 10/03/2012 ዓ.ም) ጠዋት እንዲደረስ፤ እንዲሁም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ደግሞ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የምሕላ ጸሎት እንዲደረ ወስኗል፡፡ ****** ምዕመዕናን ሆይ ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያናችን የበላይ አካል ስለሆነ፤ የሚወስናቸውን ውሳኔዎች ተቀብሎ መፈጸም እንጂ፤ ለምን እንዲህ ሆነ፤ እንዲህ ቢሆንስ፤ እንዲያ ቢሆንስ፤ እያሉ መከራከር አይገባም፤ ቅዱስ ሲኖዶስ ካስፈለገ ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በተመለከተ አዲስ ሥርዐት መደንገግ ካስፈለግም የበፊቱን ሥርዐት ማስተካከል ብሎም መሻር ይችላል፤ የአባቶች የሐዋርያት ሥልጣንን ይዟልና፤ በቀልምድ በፌዝም የምናወራ ሰዎች እንጠንቀቅ፤ ኀጢአትም ነውና!!!፡፡

ኅዳር ፱፤ የሠለስቱ ምዕት (318ቱ ሊቃውንት) ክብረ በዓል ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያኑ ፎቶ፤ ሐመረ ኖኅ ሠለስቱ ምዕት ቤ.ክ፤ በሃገራችን በሠለስቱ ምዕት (በ318ቱ ሊቃውንት ስም) ብቸኛ የሆነውና በአሁኑ ሰዐት ከ4ቱ የመጻሕፍት ጕበኤያት በኢትዮጵያ ደረከጃ የመጻሕፍተ መነኰሳት ዋና ማስመስከሪያ የሆነ ነው፡፡ ፠ በሃገራችን በሠለስቱ ምዕት (በ318ቱ ሊቃውንት ስም) ብቸኛ የሆነውና ከ311 ዓመታት በፊት በአፄ ቴዎፍሎስ (ስመ መንግሥት አጽራር ሰገድ) ታንጾ የነበረ ሲኾን ንጉሡ ሲያንጹትም የሠለስቱ ምዕት የአእላፍ መላእክትና የነቢያት ቤተ ከርስቲያን አድርገው ነው፤ ድርቡሽ ጎንደርን ከ130 ዓመታት በፊት በወረረ ጊዜ ጠፍ ኹኖ ቆይቶ በ2007 ዓ.ም. ቤተ ክርስቲያኑ ድጋሚ ተሠርቶ፤ እነሆ ዘንድሮ ለ6ኛ ጊዜ ተከብሮ ውሏል፡፡ ፠ ይህ ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ጕባኤ ቤትም ሲኖረው፤ ቀድሞ የ4ቱ ጕባኤያት ዋና ማስመስከሪያ ኹኖ ቆይቷል፤ ከአፄ ኀይለ ሥላሴ ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ ደረጃ የመጻሕፍተ መነኰሳት ዋና ማስመስከሪያ ኹኖ ይገኛል፡፡ ፠ ፎቶ ላይ የምትመለከቱት የሠለስቱ ምዕት የመጻሕፍተ መነኰሳት ጕባኤ ቤት ከዋናውና ከጥንቱ የመጻሕፍተ መነኰሳት ጕባኤ ማሄጃ ብራና መጻሕፍት ጋር በእሳት አደጋ በተቃጠለበት ወቅት፤ በጎንደር የሚገኙ፤ በኢትዮጵያ ደረጃ ዋና የመጻሕፍተ ብሉያት ምስክር መምህር ዘዐቢየ እግዚዕ ኪዳነ ምሕረት (መምህር ኤልያስ)፤ በኢትዮጵያ ደረጃ ዋና የመጻሕፍተ ሐዲሳት ምስክር መምህር ዘግምጃ ቤት ማርያም (ሊቀ ማዕማራን ወመጋቤ ሐዲስ ወልደ ሰንበት ባይነሳኝ)፤ በኢትዮጵያ ደረጃ ዋና የመጻሕፍተ ሊቃውንት ምስክር መምህር ዘመንበረ መንግሥት መድኀኔ ዓለም (ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ) በአንድ ላይ ሁነው፤ ፠ በኢትዮጵያ ደረጃ ዋና የመጻሕፍተ መነኰሳት መምህር ዘሠለስቱ ምዕት የሆኑትን (መጋቤ ምሥጢር ወመጋቤ ምክር መምህር ተሾመ ታደሰን)ና ቀደ መዛሙርቶቻቸውን ሲያጽናኑ የሚያሳይ ነው፡፡

፬ቱ (ዐርባዕቱ) እንሰሳ ወይም ኪሩቤል፨ ፎቶው፤ ከ1500 ዓመታት በፊት በንጉሥ ካሌብ የተፈለፈለው የዐርባዕቱ እንሳሳ (ኪሩቤል) ቤተ ክርስቲያን፡፡
+5
፬ቱ (ዐርባዕቱ) እንሰሳ ወይም ኪሩቤል፨ ፎቶው፤ ከ1500 ዓመታት በፊት በንጉሥ ካሌብ የተፈለፈለው የዐርባዕቱ እንሳሳ (ኪሩቤል) ቤተ ክርስቲያን፡፡