ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 381 подписчиков, занимая 5 584 место в категории Религия и духовность и 2 199 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 381 подписчиков.

Согласно последним данным от 03 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 21, а за последние 24 часа — -7, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 21.13%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.50% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 250 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 462 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 16.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 04 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 381
Подписчики
-724 часа
+117 дней
+2130 день
Архив постов
#ጥምቀት_በኢትዮጵያ፤ ፠ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠመቀው የንግሥት ሕንደኬ በጅሮንድ አቤላክ(ባኮስ) ‹‹እነሆ ውኃ አለ፣ ታድያ መጠመቅን ማን ይከለክለኛል?›› /የሐዋ. ፷፥፳፱-፴፮/ ብሎ በሐዋርያው ፊልጶስ በተጠመቀ ጊዜ ነው፡፡ ይህ ሥርዐት ግን ተስፋፍቶ የቀጠለው በነገሥታቱ በአብርሃ ወአጽብሐ (315-351ዓ.ም.) የቤተ መንግሥቱ ጃንደረባ በነበረውና ኋላ ጳጳስ በሆነው በፍሬምናጦስ(አባ ሰላማ) ዘመን ነው፡፡ በዓሉ ግን አሁን በምናከብረው ዓይነት ስዕላዊ በሆነ መልኩ መከበር የጀመረው ከማኅሌታዊው ቅዱስ ያሬድ ዜማ መስፋፋት ጋራ በአፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት (530-544ዓ.ም.) እንደሆነ ይነገራል፡፡ ፠ ገዳማቱና አድባራቱም በአቅራቢያቸው ወደሚገኙ የውኃ ምንጮች በተናጥል በመውረድ በዓለ ጥምቀትን ያከብሩ ነበር፡፡ ተቀራርበው የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ታቦታቸውን በአንድ ቦታ እንዲያሳድሩ ዐዋጅ የታወጀው፥ ትእዛዝ የተላለፈው በጻድቁና በጠቢቡ ንጉሥ ላልይብላ(1140-1180ዓ.ም.) ዘመነ መንግሥት ነው፡፡ በዚሁ ዘመን የነበሩት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአኵሱም በመቀለና በመርጡለ ማርያም ያሉ ጥምቀተ ባሕሮችን ባርከዋል፤ በአፄ ይኩኖ አምላክ ዘመን ደግሞ በአቡነ ተክለሃይማኖት አሳሳቢነት ሥርዐተ ጥምቀቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ዐዋጅ ታውጇል፡፡ እስከ አጼ ዘርዐ ያዕቆብ ድረስም ታቦታቱ ዕለቱን ጠዋት ወጥተው ማታ መለሱ ነበር፤ አፄ ዘርዐ ያዕቆብ ግን ታቦታቱ በዋዜማው ጥር 10 ከሰዐት በኋላ ወደ ትምቀተ ባሕር ወርደው እንዲያድሩ፤ አገሩንም በኪደተ እግር እንዲባርኩ፤ በሄዱበት መንገድም እንዳይመለሱ በዐዋጅ ወሰኑ፡፡ ቀጥሎም አፄ ናዖድ ሕዝቡ ታቦታቱን አጅቦ ወደ ጥምቀተ ባሕር እንዲሄድ በዐዋጅ አስነገሩ፡፡ ይህ ሥርዐትም እስካሁን ከኛ ዘንድ ደርሷል፡፡ በዘመናት ውስጥም የጥምቀት በዓል ሲከበርባቸው ከነበሩ ቦታዎች ዐበይቶቹን ለመጥቀስ ያህል፤ #በአኵሱም_የንግሥተ_ሳባ_መዋኛ_ ‹‹#ማይ_ሹም›› #በጎንደር_የአፄ_ፋሲል_መዋኛ_ገንዳ #በቅዱስ_ላሊበላ_የዮርዳኖስ_ወንዝ #በሸዋ_የአፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ_ፍርድ_መስጫ_አደባባይ #44ት #ታቦታት_የሚያድሩበት_የሸንኮራ_ሜዳ ‹‹#ኢራንቡቴ_ጥምቀተ_ባሕር›› #በአዲስ_አበባ_የጃንሆይ_ሜዳ_ (ጃንሜዳ) #በአዲስ_አበባ_የእንጦጦ_ማርያምና_ቅዱስ_ራጕኤል_ታቦት_ማደሪያ #ኀሙስ_ገበያ_ሜዳ ዐበይቶቹ ናቸው፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ኢራንቡቲ_ጥምቀተ_ባሕር (#ሸንኮራ_ወንዝ_ዳርቻ) ፥ ምንጃር፡፡ #41_ታቦታት_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_የሚወርዱበት፡፡ ከ600 ዓመታት በላይ ያስቈጠረው፤ በአፄ ዘርዐ ያዕቆብ የተጀመረውና ታሪክ፣ ባህል፣
#ኢራንቡቲ_ጥምቀተ_ባሕር (#ሸንኮራ_ወንዝ_ዳርቻ) ፥ ምንጃር፡፡ #41_ታቦታት_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_የሚወርዱበት፡፡ ከ600 ዓመታት በላይ ያስቈጠረው፤ በአፄ ዘርዐ ያዕቆብ የተጀመረውና ታሪክ፣ ባህል፣ እምነትና የሀገር ወግ የሚንጸባረቁበት፤ የኢራንቡቲ ጥምቀተ ባሕር እስከዛሬም ድረስ በሃገራችን በኢትዮጵያ የጥምቀት በዓል በደማቅ ከሚከበርባቸው ቦታዎች በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡ በበዓሉ ላይም እናቶች በእልልታ የታላቁን የደብረ ኤረር ተራርን አልፎ እስከሚያስተጋባ ድረስ ያደምቁታል፡፡ ከ41ዱ ታቦታት መካከል ጥቂቶቹ፤ ፠ ሸንኮራ ዮሐንስ ፠ ባልጪ አማኑኤል ፠ በሳ ሚካኤል ፠ ጅማ ገብርኤል ፠ ኢቲቻ ተክለ ሃይማኖት ፠ አረካ ዋርካ ይልፋታ ሥላሴ ፠ አክላል ኪዳነ ምህረት ፠ እንጆረራ አማኑኤል ፠ ወረቀት ሀገር ቅዱስ ጊዮርጊስ ፠ ውሪ ጊዮርጊስ …. ይገኙበታል፡፡ (ምንጭ፤ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም) #share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በከበሮ፡፡ #እግዚአብሔርን_በከበሮ_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ የቀደሙ ዓመታት የጥምቀት በዓል ማስታወሻዎች ፤ ከፍቶ ማሕደራችን! በፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አባላት
+6
ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በከበሮ፡፡ #እግዚአብሔርን_በከበሮ_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ የቀደሙ ዓመታት የጥምቀት በዓል ማስታወሻዎች ፤ ከፍቶ ማሕደራችን! በፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አባላት

ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በከበሮ፡፡ #እግዚአብሔርን_በከበሮ_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ የቀደሙ ዓመታት የጥምቀት በዓል ማስታወሻዎች ፤ ከፍቶ ማሕደራችን! በፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አባላት
+6
ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በከበሮ፡፡ #እግዚአብሔርን_በከበሮ_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ የቀደሙ ዓመታት የጥምቀት በዓል ማስታወሻዎች ፤ ከፍቶ ማሕደራችን! በፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አባላት

#ጥር_7_በዓለ_ሥላሴ_የሰናዖርን_ግንብ_ያፈራረሱበትና_ቋንቋ_የደባለቁበት_ዕለት፡፡ #የሰናዖርን_ግንብ እና #በቅድስት_ሥላሴ_የተሰየሙ_አድባራትና_ገዳማት ፤ከታች ያንብቡ ✤✤✤✤✤ “#ንዑ_ንረድ_ወንዝርዎ_ ከመ_ኢይሳምዑ_ነገሮሙ_አሐዱ_ምስለ_ካልኡ፤›› “ኑ ፥እንውረድ ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማ ቋንቋቸውን እንደባልቅባችው”ዘፍ 11፥7 #በባቢሎን የነበሩት በሰናዖር ሰፊ ሜዳ አግኝተው ‹ሳንሞት ስም ማስጠሪያ ግንብ እንገንባ› አገር እናቅና እስከ ሰማይ የመሚደርስ ግንብ እንስራ ተባባሉ ፤ማይ አይኀ በወረደ ጊዜ እንዳያጠፋን የምንጠጋበት ግንብ እንስራ ብለው ሥራ ጀመሩ ፤ አንድም ሞትን የሚያመጡብን ሥላሴ ናቸውና እርሱን ገለን ሞትንም እናጠፋለን ሲሉ፡፡ ✤ይህንን ግንብ #43 ዓመት ሰርተውታል ቁመቱም #5433 ከ2 ስንዝር ነው፤ በፀሐይም እያበሰሉ ይበሉ ጀምረው ነበር ፡፡ ✤ከዚያም ሆነው ጦር እየሰበቁ ይወረውሩ ጀመር ሰይጣን ከደመና በምትሀት ደም እየቀባ ይልክላቸዋል እነርሱም ደሙን እያዩ ‹‹ አሁን አብን ወጋነው አሁን ወልድን ወጋነው ….›› ይሉ ጀመር እግዚአብሔርም የሰናዖርን ግንብ ይጥልባችው ዝንድ ‹‹ንዑ ንረድ ወንዝርዎ ✤ ከመ ኢይሳምዑ ነገሮሙ አሐዱ ምስለ ካልኡ፤›› አሉ የአንዱን ቋንቋ አንዱ እንዳይሰማው ወርደን ቋንቋቸውን እንለያየው ፡፡ ሥላሴ ፍጥረት ሁሉ ቢጎዳ አይወዱምና #72_ቋንቋ አመጡባቸው፤ አንዱ እሣት አምጣ ሲለው አንዱ ውሃ ያመጣል አንዱ ጭቃ ሲል ደግም እንጨት ያመጣለታል፡፡ ✤ከዚያም ትተው ወረዱ ነገር ግን ግንቡን እንደ ጣዖት አርገው ማምልክ ሲጀምሩ ሥላሴ ጽኑ ነፋስ አስነስተው በትነውታል፡፡ #ምሥጢረ_ሥላሴን ሲያስረዳ ( “እግዚአብሔርም አለ” አንድነታቸውን ሲያጠይቅ ድግሞም ኑ እንውረድ አለ ፤ ሶስትነታቸውን ሲያጠይቅ፤) (ዘፍ 11) #ባቢሎን ማለት ዝርው (ዝሩት) ሲሆነ ቋንቋ እና በቦታ ስለተለያዩበት ስያሜውን አግኝቷል (እግዚአብሔር ቋንቋን በትኗልና፣ አህዛብንም በዓለም ሁሉ በትኗልና፡፡ ‹‹…ሥላሴ ሕጸበኒ ወአንጽሐኒ እምአበሳየ በሐሊበ ምሕረትከ ›› ሰይፈ ሥላሴ ዘዓርብ /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሰሌዳ መጽሔት / ✤✤✤✤✤ #share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ በቅድስት ሥላሴ የተሰየሙ ብዙ አድባራትና ገዳማት ቢኖሩም፤ የታሪክ ሙዳይ የኾኑ፥ ከዕድሜያቸው ብዛትና ከአመሠራረታቸው አንጻር በታሪክ አሻራ ላይ ያላቸው አስተዋጽዖ ከፍተኛ የኾኑ ፥ የታሪክ አሻራቸው ያንጸባረቀ፥ አሻራቸው የላቀ፥ እድሜያቸው የጎላ፤ 8ቱ ዐበይት ገዳማት (ቤ.ክ)፤ እንዲሁም በአ.አ. ክብረ በዓሉ የሚከበርባቸው አብያተ ክርስቲያናት፡፡ 1ኛ) #ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም፤ ከ2000ዓመታት በላይ ያስቈጠረ፤ የብዙ ቅዱሳን (የአባ ዓምደ ሥላሴ፣ የአባ ክፍለ ማርያም፣ የ7ቱ ዘሥላሴ፣ የአባ አርከ ሥሉስ ቅዱስ /የአርኬና የመልክዓ ቊርባን ደራሲ/፣ …….. ) መፍለቂያ፡፡ 2ኛ) #አሰቦት_ቅድስት_ሥላሴ፣ በ13ኛው ክ/ዘመን በታላቁ ጻድቅ በአቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ የተመሠረተ፡፡ 3ኛ) #ደብረ_ብርሃን_ሥላሴ_ሰሜን_ሸዋ_ደብረ_ብርሃን_ከተማ፤ በ14ኛው ክፍለ ዘመን በዓፄ ዘርዓያዕቆብ ዘመን የተመሠረተ፡፡ 4ኛ) #መካነ_ሥላሴ_ደቡብ_ወሎ_ወረኢሉ፤ በ1500ዓ.ም. በዓፄ ናዖድ የተመሠረተና በልጁ በዓፄ ልብነ ድንግል ሥራው የተጠናቀቀ፤ ባለ 16 መንበር በዕንቊና በወርቅ የታነጸ የነበረ፤ (ኋላ በግራኝ የፈረሰ፤ ጽላቱ በዓፄ ምኒልክ ወደ አዲስ አበባ የመጣ ቀድሞ መካነ ሥላሴ አሁን 4 ኪሎ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ በመባል የሚጠራው)፤ ደቡብ ወሎ ያለው መካነ ሥላሴ ግን ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር ነውና በቀድሞው ቅርጹ በባለ 16 መንበር ተደርጎ ካች አምና የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ በመገንባት ላይ ይገኛል፤ (ለሕንፀታ ቤቱ ኹላችንንም ያብቃን)፡፡ 5ኛ) #ደብረ_ብርሃን_ሥላሴ_ጎንደር_ከተማ፤ በጥር 26 ቀን 1683 ዓ.ም. በዓፄ አድያም ሰገድ የታነጸ፤ በጎንደር ከተማና ዙሪያ ከሚገኙ 44ቱ ታቦታተ ጎንደር በአሠራሩ ልዩ የኾነ፤ በ1880ዎቹ ድርቡሽ ጎንደር ከተማን ሲያጠፋ አብረው ከጠፉት 44ት አብያተ ክርስቲያናት በተዓምራት ሳይቃጣል የቀረ፤ የታላላቅ ሊቃወንት (የእነ ሊቁ ክፍለ ማርያም) መፍለቂያ፡፡ 6ኛ) #ናርጋ_ሥላሴ_ከጣና_ላይ_ገዳማት_አንዱና_ዋነኛው፡፡ 7ኛ) #ጨለቆት_ሥላሴ_ትግራይ፤ መቀለ አጠገብ፡፡ 8ኛ) #አዲስ_አበባ_መካነ_ሥላሴ_ ( #መንረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ በመባል እየተጠራ ያለ) (4 ኪሎ)፡፡ #በአዲስ_አበባ_የሚገኙ_የቅድስት_ሥላሴ_አብያተ_ክርስቲያናት (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ ጨምሩበት) 1ኛ. መካነ ሥላሴ (መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ.ክ.)፤ (4 ኪሎ) 2ኛ. መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ (ሽሮሜዳ) 3ኛ. መሪ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ሥላሴ (አያት መሪ) 4ኛ. ካራ አሎ ቅድስት ሥላሴ (ካራ አሎ ፥ አባዶ አጠገብ) 5ኛ. ጠሮ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ፤ (ኮልፌ ቀራንዮ) 6ኛ. ጀሞ ፈለገ ኮሬብ ቅድስት ሥላሴና ቅድስት ማርያም (ጀሞ) 7ኛ. ሰፈረ ገነት ቅድስት ሥላሴ (ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፥ ወረዳ 4) 8ኛ. ፈለገ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ (ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ) 9ኛ. ቂሊንጦ ቅድስት ሥላሴ (አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ፥ ወረዳ 9) 10ኛ. ኤረር ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ (ጎሮ ሰፈር፥ ወረዳ 9) 11ኛ. መሪ ቅድስት ሥላሴ (መሪ አያት፥ ወረዳ 13) እንዲሁም በድርብነት 12ኛ. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (የሥላሴ ታቦት በድርብነት ይከበራል) (አዲሱ ገበያ) /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሰሌዳ መጽሔት / #share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

#ጥር 6 በዓለ ግዝረት፥ ዕረገተ ኤልያስ ዕረፍተ ኖኅ፥ ልደተ ቅድስት አርሴማ፥ ዕረፍተ ዐቢይ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፥ አቡነ ኖኅኖኅ አባ ሙሴ ገዳማዊ፥ አባ ወርክያኖስ፥ ወአባ ሙሴ፡፡ —— #ግዝረተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ —— ፠ ጌታችን በተወለደ በ8ኛ ቀኑ ዕጉለ ማዕነቅ ይዞ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ ፠ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋ ግዝረትን ተቀበለ፣ ለአባቶች የተሰጠውን ቃልኪዳን ይፈጽም ዘንድ›› /ሮሜ.፲፭፥፰/፡፡ ፠ በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ በስምንተኛው ቀን እንደ ኦሪቱ ሥርዓት ግዝረት ይፈጸምለት ዘንድ ሕፃኑ ጌታችንን ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ሲገረዝ የሊቀ ካህን ልጅ ነው ብለው ሊገርዙት ወደ እርሱ መጡ፡፡ ጌታችን ግን ወደ ምድር የመጣው፡፡ ለትሕትና ነው እንጂ ለልዕልና አይደለምና ወሰዱት አለ /ትርጓሜ ወንጌለ ሉቃስ/፡፡ ፠ የእመቤታችን ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደመውጣቱ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ፡፡ እንዲሁ በተዘጋ ቤት መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እነዲሁ እንደፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ፡፡ ————- #ቅዱስ_ኤልያስ_በእሳት_ሰረገላ_ወደ_ብሔረ_ብፁዓን_ያረገበት_ዕለት_ነው፡፡ (የዚህን ቅዱስ ነቢይ ታሪክ በደንብ ያንቡብት ብዙ ትምህርት ይቀስሙበታል) **በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡ ✤ የሰማርያው ነቢይ ቴስቢያዊው ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ እናቱ ደግሞ ቶናህ(ቶና) ሲባሉ ሲወለድ መላእክት በእሳት ሰፋድል (መጠቅለያ መጐናጸፊያ) ጠቅልለውት ነው፡፡ የስሙ ትርጉምም ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ነው›› ማለት ነው፡፡ ** ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ? ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡ ✤ 1. ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ ሰማይ ዝናም ለዘር፥ ጠል ለመከር ከመስጠት እንዲከለከል ምድርም የተከሉባትን ✤ 2. አመጸኞች አክአብንና ኤልዛቤልን ምንነታቸውን ካሳወቀ በኋላ የዘጋውን ለመክፈት ወደ ፈጣሪው በመጸለይ ዝናም አዝንሟል፡፡ ✤ 3. በተፈጥሮ የማይመስላቸው በቋንቋም የማይግባባቸው እንኳን ለሰው ሥጋ ሊያመጡ ከሰው ሥጋ የሚነጥቁ አሞራዎች እንጀራና ሥጋ ለምግብ እንዲያመላልሱለት አደረገ 1ኛ ነገሥ. 17፥6-7፡፡ እነዚህ አሞራዎች ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ በጋ ከክረምት የለምንም እረፍት ኤልያስን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ እምነት ካለ ተአምር መሥራት አይገድም ይህንም ከኤልያስ ይማሯል፡፡ ✤ 4. ለአንዲት መበለት ዱቄትና ዘይት አበረከተ፤ ኤልያስ ቁራሽ እየለመነ ያደረገውን ተአምር ልብ ይሏል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 17፥16-24፡፡ ✤ 5. ዱቄትና ዘይት ያበረከተላት የሰራፕታዋ ሴት ልጇ /ኋላ ዮናስ ነቢይ የሆነው/ ቢሞት ከሞት አስነሳው 1ኛ ነገሥ. 17፥20-23 ✤ 6. ለብዙ ጊዜ በቤተ መንግሥት ተሰግስገው አክአብና ኤልዛቤልን በሐሰት ሲደልሉ፥ ግብዝ ሕብረተሰቡን ሲያታልሉ፥ ለፍቶ ያገኘው ገንዘቡን ሲሸልጉ፥ በኀጢአት ሊያስወጉ የነበሩ ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖትን በሕብረተሰቡ ፊት እስከ መምህራቸው ሰይጣን በቅሌት አከናንቦ ሲያስቅባቸው ውሏል፤ ሐሰቶች የነበሩትን 850 የሚጠጉ የጣዖት ካህናትንም ወደ ቂሶን ወንዝ አውርዶ ፈጅቷቸዋል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18 20 -29 ✤ 7. ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት ያቀረበው ንጹሕ መሥዋዕቱን ከሰማይ እሳት ወርዶ በሰው ፊት በላለት (ተቀበለለት) 1ኛ ነገሥ. 18፥30-40፡፡ በዚህም ማንነቱን በሰይጣንና በሰይጣን አቀንቃኞች ፊት አስመስክሯል፡፡ ✤ 8. እሳት ከሰማይ በማዝነም ሊጣሉት የመጡትን መምለኪያነ ጣኦት፥ ምሉአነ ኀጢአት፤ የሰይጣን ሠራዊት በሰው ደም የሰከሩ፥ በዲያብሎስ የሚመሩ ጠላቶቹን አጋይቷል 2ኛ ነገሥ 1 9-13 ✤ 9. ምግብና መጠጥ መልአክ ከሰማይ አመጣለት ያንን ተመግቦ ለአርባ ቀን ያለምንም ምግብና መጠጥ እስከ እግዚአብሔር ተራራ እስከ ኮሬብ ድረስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ተጉዟል 1ኛ ነገሥ. 19፥5-7፡፡ ✤ 10. በመጎናጸፊያው የዮርዳኖስን ባሕር ከፍሎ ከነ ደቀመዝሙሩ በደረቅ ተሻግሯል 2ኛ ነገሥ. 2፥11፡፡ ለደቀመዝሙሩም ሀብተ መንገፈስ ቅዱስን አድሎታል፡፡ ✤ 11. በትህትናው ‹‹ይበቃኛል፤ አሁንም አቤቱ እኔ ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ›› ብሎ እንዲሞት ለመነ፡፡ እግዚአብሔር ግን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ918 ዓመተ ዓለም ሳይሞት በሕይወቱ መራራውን ሞት ዕያየው በብርሃን ሠረገላ ወደሰማይ አሳርጎታል፡፡ 2ኛ ነገሥ. 2፥6-9 ✤ 12. እንደ አስፈላጊነቱ ከፈጣሪው ጋር ለብዙ ጊዜ ተነጋግሯል፡፡ ✤✤#ከአንድ እስከ አስራ አንድ ያደረጋቸውን ተአምራት የፈጸመለት ታማኝ ፈጣሪው ሰው በሆነበት ወራት በተራራ ከጓደኞቹ ጋር ብርሃነ መለኮቱን ገለጠለት ማቴ 17፥3፡፡ #ደመና_ደመና ….. #በሠረገላ_፤ ኤልያስ ኤልያስ ….. በሠረገላ፤ በእሳት ሠረገላ ….. በሠረገላ፤… ሰወረው ደመና ….. በሠረገላ፤ ኤልያስ ያረገው… በሠረገላ፤ በእሳት ሠረገላ…. በሠረገላ፤ በጾም በጸሎት ነው …. በሠረገላ፤ አይደለም በሌላ …. በሠረገላ፡፡ #ዳግመኛም ዛሬ የአባታችን ኖኅ መታሰቢው ነው፡፡ ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ …ኖኅም በትውልዱ ጻድቅ፥ ፍጹምም ሰው ነበር፡፡ ኖኅ አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፡፡ /ዘፍ. 6፥7/ #ዳግመኛም በዚህች ዕለት በበረሃ ስልሳ ዘመናት የኖረ የቅዱሳንን ልቡና ከማየቱ የተነሣ ያደነቀ፤ ፊቱም ተለውጦ እንደእሳት ፍሕም ሆነ፤ አባ ሙሴ በዓለ ዕረፍቱ ነው፡፡ ✤✤✤✤✤ ክብረ በዓሉ የሚከበርባቸው ቦታዎች #ለብቃ_ኢየሱስ/ሰሜን ሸዋ/፣ #በለስ_ዋሻ_ኢየሱስ /ተጉለትና ቡልጋ/፥ #በአ.አ. #ገነተ_ኢየሱስና_ገነተ_ማርያም ቤ/ክ፤ (ፈረንሳይ) #በአ.አ #ገዳመ_ኢየሱስ (ኮልፌ 18) #በልበሊት ኢየሱስ ——- #በአ.አ #እንጦጦ_ደብረ_ኀይል_ቅዱስ_ራጕኤልና_ኤልያስ (የኤልያስ ዕርገቱ) #በጎጃም_ደብረ_ኤልያስ ይከበራል፡፡ ክብረ በዓሉ የሚከበርባቸው ቦታዎች፤ (ተጨማሪ ካሉ ከነፎቷቸው ጨምሩበት) Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር በመዝሙር፡፡ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_አመስግኑት፡፡ መዝሙረ ዳዊት ፻፶ የ2012 ዓ.ም የከተራ እና የጥምቀት በዓል ፤ ከፍቶ ማሕደራችን፡፡

፠ ሰብሕዎ በቃለ ቀርን፤ ሰብሕዎ በመዝሙር ወበመሰንቆ፤ ሰብሕዎ በአውታር ወበዕንዚራ፡፡ (#እግዚአብሔርን_በመለከት_በነጋሪት_ድምፅ_አመስግኑት፤ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_በበገናና_በመሰንቆ_አመስግኑት፤
+4
፠ ሰብሕዎ በቃለ ቀርን፤ ሰብሕዎ በመዝሙር ወበመሰንቆ፤ ሰብሕዎ በአውታር ወበዕንዚራ፡፡ (#እግዚአብሔርን_በመለከት_በነጋሪት_ድምፅ_አመስግኑት፤ #እግዚአብሔርን_በመዝሙር_በበገናና_በመሰንቆ_አመስግኑት፤ #እግዚአብሔርን_በአውታርና_እምቢልታ_አመስግኑት፡፡) መዝሙረ ዳዊት ፻፶ በፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሲሰጥ የነበረው# የበገና እና #የመሰንቆ ትምሕርት በዓለ ምርቃ እሑድ ጥር 2 ታኅሣሥ ወር 2013 ዓ.ም ተፈጸመ ፡፡ ፠ትምሕርቱ የተጀመረው ከወረርሽኙ አስቀድሞ ሲሆን በወረርሽኙ ምክንያት መሰንቆ እና በገናው ቤት ለቤት በመሰጠት በተለያዩ አማራጮች ት/ቱ ተሰቷል (Telegram) :: በመቀጠልም ተማሪዎቹን 7 ወር በማስልጠን ት/ቱ እንዲያልቅ ተደርጓል፡፡ ፠በበገና 11 ሴቶች ትምሕርቱን ሲያጠናቅቁ በመስንቆ ደግሞ 6 ወንድ እና 2 ሴቶች አጠናቀዋል፡፡ በምርቃቱም ላይ ታላላቅ ሊቃውንት( ሊቀ ጠበብት መዝገበ ጥበብ እና ቀሲስ ተስፋ ዘደብረሰላም ) ፣ ፣ የሕፃናቱ ቤተሰቦች እንዲሁም የሰንበት ት/ቤቱ ሰብሳቢ ዲያቆን ታምራት መሉነህ ተገኝተዋል ፡፡

#ጥር 4 ተዝካረ ፍልሰቱ #ለቅዱስ_ዮሐንስ_ሐዋርያ ፤ ዮሐንስ ወንጌላዊ ፤ ፍቁረ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ #በተለያዩ_ቅጽል_ስሞች_የሚጠራ፤ (100 አካባቢ ከሚጠጉ ስሞቹ ጥቂቶቹን /21ዱን ስሞች ከጽሑፍ በስተመጨረሻ ይመልከቱ) #ሰዓሊ_የኾነ፤ የጌታችንን ስነ ስቅለት የሳለ፡፡ #ከ81ዱ_የመጽሐፍ_ቅዱስ_ክፍሎች_5ቱንና_ሌሎች_መጻሕፍትንም_(ነገረ ማርያምን ..) የደረሰ፤ #ብዙ_ደቀ_መዛሙርትን_ያስተማረ፤ #share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ ጌታ እናቱንም እነሆ ልጅሽ ያላት እርሱን ደቀ መዝሙሩንም እነኋት እናትህ ያለው ነው፡፡ ✤ዮሐንስ ንጹሕ በአምሳለ ትጉሃን፤ (#ዮሐንስ_እንደ_መላእክት_ንጹሕ_ነው፤) ✤ዮሐንስ ድንግል ምክሐ ቅዱሳን፤ (#ዮሐንስ_ድንግል_የቅዱሳን_መመኪያ_ነው፤) ✤ዮሐንስ ስርግው በቀጸላ ሥን በሜላተ ብርሃን፤ (#ዮሐንስ_በብርሃን_መጐናጸፊያና_ሻሽ_የተጌጠ_ነው፤) ✤ዮሐንስ አርጋኖነ ዘቤተ ክርስቲያን፤ (#ዮሐንስ_የቤተ_ክርስቲያን_በገና_ነው፤) ✤ወበቃለ ቀርን ዘይኬልህ በኤፌሶን፥ ይስአል ለነ ስርየተ ለኀጥኣን፡፡ (#በኤፌሶን_ዐዋጅ_የሚናገር_ዮሐንስ_ኀጥኣን_ለምንሆን_ለኛ_ይቅርታን_ይለምንልን፡፡ /እመጽሐፈ ሰዐታት/ ፨ ‹‹ሰላም ለአፉከ ለዮሐንስ ዘሰዓሞ፤ ንጽሐ ኅሊናሁ ወልቡ ለዐይነ ፍትወትከ ሶበ አደሞ›› /መልክአ ኢየሱስ/ ፨ ሰላም ለሥዕልኪ ወለሥዕለ ወልድኪ ዘሰዓሞ፤ ዮሐንስ ርኄ ዮሐንስ ቀናንሞ፤ ለዝ ወልድኪ መሐሪ ኅሩመ በቀል ወተቀይሞ፤ ማርያም ሀብኒ በእዴኪ እንዘ ትጼውዒ ስሞ፤ ሥጋሁ ቅዱሰ ወክቡረ ደሞ፡፡ /መልክአ ሥዕል/ ፨#100_አካባቢ_ከሚጠጉ_ስሞቹ_ጥቂቶቹን_21ዱን_ስሞች_እነኾ፤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ዮሐንስ፤ ዮሐንስ #ፍቁረ እግዚእ፥ (የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ለጌታ በጣም ቀራቢ ከነበሩት ሦስት የምሥጢር ሐዋርያት (ጴጥሮስ ፣ ናያዕቆብ ) ዮሐንስ ቀዳሚዉ ነዉ፡፡ ጌታችን ምሥጢረ ተአምራትን በኢያኢሮስ ቤት ፣ ምሥጢረ መንግስትን (መለኮትን) በደብረ ታቦር፣ ምሥጢረ ምጽአትን በደብረ ዘይት ፣ ምሥጢረ ጸሎትን በጌቴ ሴማኒ ሲገልጽና ሲያሳይ አብሮ የተመለከተ በመሆኑና ለጌታ በጣም ቀራቢ በመሆኑና በወንጌልም ‹‹ጌታ ይወደዉ የነበረ ደቀ መዝሙር ››ተብሎ ስለ ተጠቀሰ የጌታ ወዳጅ ፍቁረ እግዚእ ይባላል፡፡ዮሐ 13፡ 23 ፡፡ ወልደ #ዘብድዮስ ፥ ዮሐንስ #ነባቤ መለኮት ፥ ዮሐንስ #ቦኦርኔጌስ ፥ ዮሐንስ #አብቀለምሲስ ፥ (ፍጥሞ በምትባል ደሴት ላይም ወደ ፊት የሚሆነዉን ነገር በራእይ ስለተገለጸለት በግሪክ ቋንቋ አቡቀለምሲስ ተብሏል፡፡ትጉሙም የራዕይ አባት ማለት ነዉ፡፡) ዮሐንስ #ወንጌላዊ ፥ ዮሐንስ #ድንግል ዮሐንስ #ታዎሎጎስ ቅዱስ ዮሐንስ ምሥጢረ ሥላሴንና ምሥጢረ ሥጋዌን አስፍቶ በመጻፉ (ታዎሎጎስ) ተብሏል፡፡ትርጉሙም ነባቤ መለኮት (የመለኮትን ነገር የሚናገር)ማለት ነዉ፡፡ 1. #ዮሐንስ_ብፁዕ (ብፁዕ ዮሐንስ) 2. ዮሐንስ ድንግል 3. #ዮሐንስ_ፍንው 4. #ዮሐንስ_ካህን 5. #ዮሐንስ_ኅሩይ 6. ዮሐንስ ሥርግው 7. #ዮሐንስ_ምዑዝ 8. ዮሐንስ ቅኑይ 9. #ዮሐንስ_ማኅቶት 10. ዮሐንስ ቤዛ ሰማይ 11. #ዮሐንስ_ክቡር 12. ዮሐንስ ጻድቅ 13. #ዮሐንስ_ረድእ 14. ዮሐንስ ማኅቶት 15. #ዮሐንስ_ድንግል 16. ዮሐንስ ንጹሕ 17. #ዮሐንስ_ለባዊ 18. ዮሐንስ መረግድ 19. #ዮሐንስ_ዕንቈ 20. ዮሐንስ መልአክ 21. #ዮሐንስ_ኪሩብ 22. #ቁጽረ ገጽ ቅዱስ ዮሐንስ እስከ መስቀል ድረስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለዉን መከራ በማየቱ ከዚያ ዕለት ጀምሮ 70 ዘመን ሙሉ ፊቱ በኅዘን የተቋጠረ በመሆኑ (ቁጽረ ገጽ) ሆኖ ኖሯል፡ ዓለምን ዞሮ ካስተማረ ቦኃላ በመጨረሻም ደቀ መዝሙሩ አብሮኮስን ከወንድሞችም ሌሎች ሁለትን መቆፈሪያ ይዘው ይከተሉት ዘንድ አዘዘ ፡፡ ጕድጓድም እንዲቆፍሩ አዘዘ ከዚያም ወረዶ ቆመ ልብሱንም አስወገድ የበፍታ ቀሚስ በቀር ሌላ አላረገም እየጸለየ ወደ ከተማም አሰናበታቸው በክርስቶስ ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ለሕዝብ ይነግሩአቸው ዘንድ አዘዘ ሁሉም እንደየ ስራው ጌታ እንደሚከፍላቸው ነገራቸው ካዛም እንዲህ አለ እኔ ከሁላችሁም ደም ንፁሕ ነኝ ከእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ ሳልነግራቹ የተውኩት ምንም ምን የለምና እናንተም ከእንግዲህ ከቶ ፊቴን አታዩኝም ፡፡ እጅና እግሮቹን ስመውት ትተውት ሄዱ ሲመለሱም ልብስና ጫማ እንጂ ምንም አላገኙም እግዚአብሔርንም አመሰገኑት ፡፡ዘጠና ዓመትም ኖረ፤ እንደባላሟሎቹ ሐዋርያት በመሰየፍ ሞትን አለቀመሰም፡፡ ስለ ድንግልናውና ስለንጽሕናው ይህ ሁሉ ሆነ፡፡ በዚህ በከበረ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን አሜን #share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ ✤✤✤✤በኢዲስ አበባ ማክበር ለምትፈልጉ✤✤✤✤ ✤✤✤✤✤#ደብረ_ነጐድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስና_መካነ_ጎልጎታ_ማርያም_ቤ_ክ_ማዕከላ_ለአዲስ_አበባ /መሐል አዲስ አበባ ከራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል አጠገብ የሚገኝ፤ ታቦተ ሕጉ ከኢየሩሳሌም የመጣና በአዲስ አበባ ብቸኛው የወልደ ነጐጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ./፤ (አዲስ አበባና በአካባቢዋ ያላችሁ በዚሁ ደብር እንድንገናኝ ይሁን) ✤✤ሥርዓተ ማኀሌቱን ከታች ይመልከቱ:: #ጥር 4 (#የሐዋርያው የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዓመታዊ ክብረ በዓል ፤ የአባ ናርዶስ ዘደብረ ቢዘን እረፍቱ ፡፡ የጊዮርጊስ፤ የሊቀ ጳጳሳት ማርቴና፤ የሰማዕት ታኦድራ፤ የአባ ሊቃኖስ፤ የቀውስጦስ መታሰቢያቸውም ነው፡፡) Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem