ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 369 подписчиков, занимая 5 633 место в категории Религия и духовность и 2 187 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 369 подписчиков.

Согласно последним данным от 19 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -46, а за последние 24 часа — 37, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 22.37%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 7.87% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 438 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 210 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 22.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 20 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 369
Подписчики
+3724 часа
+367 дней
-4630 день
Архив постов
የበዓለ ገብርኤል ፎቶ ማስታወሻ ፣ በቀጨኔ ደብረሰላም መድኀኔዓለም  ። ሐምሌ 2016 ዓ.ም

"#የሞተ_ሰውስ_አረፈ_ነገር_ግን_ነፍሱ_ታርፍ_ዘንድ_ተዝካር_አውጣለት " ሲራክ 38፥23 በሰንበት ትምህርት ቤታችን እያገለገሉ በሥጋ የተለዩንን ወንድም እህቶቻችን ሐምሌ 21 ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀ
"#የሞተ_ሰውስ_አረፈ_ነገር_ግን_ነፍሱ_ታርፍ_ዘንድ_ተዝካር_አውጣለት " ሲራክ 38፥23 በሰንበት ትምህርት ቤታችን እያገለገሉ በሥጋ የተለዩንን ወንድም እህቶቻችን ሐምሌ 21 ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ የምናሰብ ስለሆነ ሁላችንም ተገኝተን እንዘክራቸው።

#በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በመላው_ዓለም_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፳፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በአዲስ_አበባ_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፲፫) #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ካዛንቺስ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ካዛንቺስ፡፡ ፪. ኤረር በር ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ዑራኤል፡፡ አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ኤረር በር፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ→ ኤረር በር፤ ፫. አዲስ ሰፈር አንፎ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ዑራኤል፣ መጥምቁ ዮሐንስና ልደታ ለማርያም፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አዲስ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → አንፎ፡፡ ፬. ፉሪ ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ፉሪ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → ፉሪ፡፡ ፭. ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም መካነ ብርሃን ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ አድራሻ፤ ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጎፋ ካምፕ → ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #እንዲሁም_በድርብነት_፤ ፮. ድልበር መካነ ጎልጎታ መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ቶታል/ድል በር/ (ጎጃም በር)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → አዲሱ ገበያ → ቶታል፡፡ ፯. አስኮ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለምና ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንየ ክፍለ ከተማ፥ አዲስ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ /ከአቡነ ጴጥሮስ/ → አስኮ፡፡ ፰. አውግስታ ደብረ ጽዮን ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አውግስታ ሸሚዝ ፋብሪካ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → አውግስታ ሸሚዝ ፋብሪካ፡፡ ፱. ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ታቦት ማደርያ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → ታቦት ማደርያ፡፡ ፲. ቱሉ አቦ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፤ ቅዱስ ዑራኤልና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቱሉ አቦ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → አቃቂ → ቱሉ አቦ፡፡ ፲፩. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚከኤል፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ፡፡ ፲፪. ላፍቶ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለምና መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ላፍቶ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መካኒሳ → ላፍቶ፡፡ ፲፫. ሐመረ ወርቅ ማርያምና አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፮ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩ መንዝ ዕመጓ ደብረ ቆጵሮስ ኢየሱስ ቅዱስ ዑርኤል ገዳም፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መንዝ፡፡ ፪. ግሸን ቅዱስ ዑርኤል፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ግሸን ደብረ ከርቤ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ግሸን፡፡ ፫. ጎንደር ደብረ ኀይል ቅዱስ ዑርኤል ወበዓታ፤ አድራሻ፤ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፬. ደብረ ታቦር አንቀፀ አድህኖ ቅዱስ ዑርኤል፤ አድራሻ፤ ደ. ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ታቦር ከተማ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ታቦር፡፡ ፭. የወልዲያ ቅዱስ ዑርኤል ፤ አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ወልዲያ ከተማ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ወልዲያ ፡፡ ፮. ደብረ ብርሃን ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል ፤ አድራሻ፤ ሰ. ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ብርሃን ከተማ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #ከኢትዮጵያ_ውጭ_የሚከበርባቸው_ #፫ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ጀርመን ደብረ ኃይል ቅዱስ ዑርኤል ወቅዱስ ያሬድ፤ አድራሻ፤ ጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ፪. ደብረ ብርሃን ቅዱስ ዑርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አሜሪካ ሜንሶታ ፫. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አሜሪካ ሎሳንጀለስ ካሊፎርኒያ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Angeles #ቅዱሳን_መላእክት #ክብረ_በዓላት #Feasts

እንኳን #ለብርሃን_መልአክ_ከሣቴ_ምሥጢር_ለሆነው #ቅዱስ_ዑርኤል_ሊቀ_መልአክ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ #ሐምሌ ፳፪፤ #በዓለ_ቅዱስ_ዑራ(ር)ኤል_ቅዳሴ_ቤቱ_የሚከበርበትና (ሐምሌ ፳፩ ደግሞ ለዕዝራ ጽዋዕ ልቡና ያጠጣበት ነው፡፡) #ዑራኤል ማለት “ብርሃነ እግዚአብሔር” ማለት ነው። “ዑራኤል ሥዩም ላዕለ ኵሎሙ ብርሃናት፤ #ዑራኤል በብርሃናት ላይ ሁሉ የተሾመ ነው” እንዲሁም “ዑራኤል አሐዱ እመላእክት ቅዱሳን እስመ ዘረዓም ወዘረዓድ፤ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ ዑራኤል በመብረቅና በነጎድጓድ የተሾመ ነው” እንዲል፡፡ (ሄኖክ ፮፥፪) ከሊቃነ መላእክት አንዱ መሆኑንና ፍርሃት ረዓድ ላለባቸው ረዳታቸው እንደሆነ የመላእክትን ነገር የተናገረ ሄኖክ ነግሮናል፡፡ “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል” በማለት ነቢዩ ዳዊት እንደተናገረ እግዚአብሔርን በሚፈሩና በሚያከብሩት ሰዎች ጭንቀት ጊዜ በመካከላቸው እየተገኘ ያጽናናቸዋል። (መዝ.፴፫፥፯) ምሥጢር ይገልጥላቸዋል፤ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይጠብቃቸዋል። #ቅዱስ_ዑራኤል ምሥጢር ገላጭ ነው። ምሥጢር ማናገር #የመንፈስ_ቅዱስ ሥራ ቢሆንም የተሠወረውን መግለጥ፣ በአዲስ ቋንቋ ማናገር ለመላእክት የተሰጠ ጸጋቸው መሆኑም ግልጽ ነው። በዚህ ሀብትነትም የተወደደ ሥራ ለሚሠሩና እንዲያውቁ ለተፈቀደላቸው ሁሉ #ቅዱስ_ዑራኤል ምሥጢር ይገልጣል፤ #ለዕዝራ_ሱቱዔል የሆነለትም እንዲህ ነው። #መልአኩ_ዑራኤል “አፍህን ክፈት፤ እኔም የማጠጣህን ጠጣ” … ብሎ አእምሮ ለብዎውን ገልጦለታል። (ዕዝ.ሱት. ፲፫፥፴፰) የዚህን ተአምር መታሰቢያ ሐምሌ ፳፪ በየዓመቱ ቤተ ክርስቲያናችን ታከብራለች። ለሄኖክም ምሥጢረ ሰማይንና ዕውቀትንም ሁሉ የገለጠለት እርሱ እንደሆነ በመጽሐፈ ሄኖክ ተጽፏል። (ሄኖክ ፳፰፥፲፫) አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ልቡናውን ያበራለት ይህ መልአክ እንደሆነ ገዳሙ ባሳተመው ገድሉ ላይ ተጽፏል። በዚህ አገልግሎቱም ሊቃውንቱ #ከሣቴ_ምሥጢር ይሉታል። አፋቸውን ከፍተው የምስጋና ቃል ለሚናገሩ ሁሉ ክብርና ጥበቃን ከመላእክት እንደሚቀበሉ ከላይ በተመዘገበው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ለዕዝራ ሱቱዔል የተደረገለትን መረዳት ይገባል። ዕዝራ ለረጅም ወራት እግዚአብሔርን ደጅ ጸንቶ ነበር። የነገሩትን የማይረሳ እግዚአብሔር መልአኩን ላከለት፤ የሰማዩን ምሥጢርም ዐወቀ። ይህ መልአክ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ግብጽ ተራሮች በተሰደደች ጊዜ በመካከላቸው ሁኖ መንገድ ይመራቸው እንደነበር በድርሳነ ዑራኤል ተገልጿል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ አደባባይ ደሙን በፈቃዱ ሲያፈስም በጽዋዕ የተቀበለው መልአክ እርሱ መሆኑን በዕለተ ዓርብ በሚነበበው ግብረ ሕማም ተጽፏል። ሐምሌ ፳፪ ከሚታሰበው በዓሉ በተጨማሪም ፤ በሊቀ መላእክትነት የተሾመበትን በማሰብ ጥር ፳፪ ቀን፣ ከጌታችን የፈሰሰውን ደም በጽዋዕ የተቀበለበትን ቀን በማሰብ መጋቢት ፳፯ ቀን ይከበራል። የሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን! #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Angeles #ቅዱሳን_መላእክት #ክብረ_በዓላት #Feasts

#በመዲናችን_በአዲስ_አበባ__የቅዱስ_ገብርኤል_ በዓል_የሚከበሩባቸው #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩) ፠ (መ.መ.ገ.) መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ በ1889 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ፠ አስኮ ቅዱስ ገብርኤል፤ ፠ ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል፤ ፠ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል) ፭) ፠ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ፠ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል በ.ክ. ፠ ደብረ ገነት ፉሪ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት አርሴማና አቡነ አዳም ቤ.ክ. ፲) ፠ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፲፭) ፠ ደብረ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ጋራ ኦዳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አንቆርጫ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፳፠ አቃቂ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቦሌ ሃራብሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቦሌ ቡልቡላ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፳፭) ፠ ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ (የቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. በድርብነት በውስጥ አለ) ፠ ቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ቦሌ መንበረ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ ገሊላ አማኑኤል ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፴) ፠ ጀሞ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ.ክ. ፠ አቃቂ ጃቲ መካነ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ የካ አባዶ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኮልፌ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤል ፴፭) ፠ ኮልፌ ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ. (አዲሱ ሚካኤል) (በድርብነት ይከብራል) ፠ ካራ ቆሬ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ድልበር መካነ ጎልጎታ መድኀኔዓለም (በድርብነት ይከብራል) ፠ አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ (አዲስ ሰፈር) ፵)፠ ደብረ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም ስር የሚገኘው ሙት አንሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ መንበረ ልዑል ገብርኤልና ማርያም ቤ.ክ.፤ ፠ አየርጤና ደብረ ብሥራት ገብርኤልና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ. ፠ ቱሉ ዲምቱ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቀበና ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅ/ገብርኤል ቤ.ክ. ፵፭) ፠ መጠሊ ደብረ አሮን ፍልፍል ዋሻ ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ.ክ. ፠ ቂሊንጦ ደብረ ብሥራት ገብርኤልና ማርያም፤ ፠ ደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)፡፡ ፠ አንቀጸ ምሕረት (ራስ ካሣ) ቅዱስ ሚካኤል፤ (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ ዕንቊ ልደታ ለማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል) ፶) ፠ ቦሌ ቡልቡላ ድብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም፤ (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል) ፠ ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ይከብራል) ፠ ፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል) ፶፬) ፠ ብሥራተ ወንጌል ቅድስተ ማርያም ቤ.ክ.፤ (በድርብነት ይከብራል) #በሃገራችንና_በዓለም_አቀፍ__በዓላቸው_የሚከበሩባቸው_ጥንታውያን #፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩) ዘብር ቅዱስ ገብርኤል (መንዝ ሰ ሸዋ) ፪) ወይቅን ቅዱስ ገብርኤል (ቆላ ተንቤን) ፫) ክብራን ገብርኤል (ጣና ጎጃም) ፬) ቦሎ ገብርኤል (መርሐ ቤቴ) ፭) ጎንደር አቡን ቤት ገብርኤል ፭) ደሴ ገብርኤል ፮) ናዝሬት ገብርኤል ፯) ቁልቢ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ፰) ባሕር ዳር ዐባይ ማዶ ገብርኤል ፱) ሐዋሳ ገብርኤል ፲) ድሬደዋ ሳባ ገብርኤል #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Angeles #ቅዱሳን_መላእክት #ክብረ_በዓላት #Feasts