ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 335 подписчиков, занимая 5 641 место в категории Религия и духовность и 2 191 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 335 подписчиков.

Согласно последним данным от 15 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -80, а за последние 24 часа — -1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 22.23%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 10.47% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 409 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 605 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 22.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 16 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 335
Подписчики
-124 часа
-117 дней
-8030 день
Архив постов
መድኀኔዓለም "የአማልክት አምላክ የአጋዕዝትም ጌታ የጽኑዓን ጌታቸው መላእክትና ሊቃነ መላእክት የሚሰግዱለት እርሱ ነው።" ሠለስቱ ምእት https://t.me/finotehiwott
+9
መድኀኔዓለም "የአማልክት አምላክ የአጋዕዝትም ጌታ የጽኑዓን ጌታቸው መላእክትና ሊቃነ መላእክት የሚሰግዱለት እርሱ ነው።" ሠለስቱ ምእት https://t.me/finotehiwott

🎓🎓🎓 የተማሪዎች ምርቃት #5_ቀን_ቀረው 🎓🎓🎓 " ኅየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ " {"በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ"} (መዝ 44:16) በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነ
🎓🎓🎓 የተማሪዎች ምርቃት #5_ቀን_ቀረው  🎓🎓🎓 " ኅየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ " {"በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ"} (መዝ 44:16)      በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትምህርታቸውን  ተከታትለው  ያጠናቀቁ እና በሀገረ ስብከት በብሔራዊ ደረጃ ምዘና ተደርጎላቸው ያለፉ  #የ4ኛ , #የ8ኛ እና #የ10ኛ ክፍል #ከ11_000 በላይ ተማሪዎች ብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ፤ አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፤ የተመራቂ ተማሪ ወላጆች እንዲሁም ምዕመናን/ት በተገኙበት የምርቃት መርሐ ግብር ይከናወናል!!! 🎓🗓 #ጥቅምት_30_2018_ዓ_ም      🎓 🕰 #ከቀኑ_5_30_ጀምሮ            🎓  🏢 #በሚሊኒየም_አዳራሽ አይቀርም!!! ኑ ተማሪዎቻችን በጋራ እንመርቅ!!!   የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓

ሥርዐተ ማኅሌት ዘጥቅምት ፳፯ በዓለ መድኀኔዓለም ወመብዓ ጽዮን ✤ ልዩ አዋጅ ዘጥቅምት መድኀኔዓለም ✤ የጥቅምት መድኀኔዓለም የማኅሌቱ ሥርዐት ‹‹የመልክአ መድኀኔዓለምን›› እና ‹‹የመልክአ መስቀልን
+5
ሥርዐተ ማኅሌት ዘጥቅምት ፳፯ በዓለ መድኀኔዓለም ወመብዓ ጽዮን ✤ ልዩ አዋጅ ዘጥቅምት መድኀኔዓለም የጥቅምት መድኀኔዓለም የማኅሌቱ ሥርዐት ‹‹የመልክአ መድኀኔዓለምን›› እና ‹‹የመልክአ መስቀልን›› የሚከተል ነው፡፡ ‹‹የመልክአ መድኀኔዓለም››ን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ‹ዘአዲስ አበባ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም የሚለውን እንዲከተሉ፤ ‹‹የመልክአ መስቀል››ን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ‹ዘጎንደር መንበረ መንግሥት መድኀኔዓለም›› የሚለውን እንዲከተሉ እናሳስባለን፡፡ ✤ መልካም በዓል ✤ https://t.me/finotehiwott

ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን፤ (ስብስብ 3)፤ የ114 ዓመታት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ የልጅ ኢያሱ ደብር፤ ለዛቲ ቤት ሣረራ ኢያሱ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት፤ ወፈጸመታ ንግሥት ዘውዲቱ፡፡ (ይህችን ደብረ ሰላምን በመጀመሪያ አቤቶ ኢያሱ /አልጋ ወራሽ ልጅ ኢያሱ/ (ክፍለ ያዕቆብ) በሐምሌ 26 ቀን 1903 ዓ.ም. መሠረታት፤ ንግሥት ዘውዲቱ አሁን ያለውን ሕንፃው ቤ.ክ ጥቅምት 27 ቀን 1913 ዓ.ም አስፈጸመችው፡፡) የሰላም አምላክ የፍቅር ጌታ መድኀኔዓለም ያደረባት ደብረ ሰላም ብዙ ነገሮች አሏት፤ የብዙ ሊቃውንት መፍለቂያ፤ የላይ ቤት አቋቋም፣ የተክሌ ዝማሜና የሸዋና የራሱ የደብሩ ቀለም እንደ ወንዝ የሚፈስባት፤ ታሪካዊ ቅርሶችን የያዘ ቤተ መዘክር (Museum)ና ቤተ መጻሕፍት የሚገኙበት፤ ደብሩን አገልግለው ወደ ሌላ ደብር የሚዛወሩ ካህናት ኹሌም በዓይናቸው የደብሩ ፍቅር ውልብ የሚልባቸው፤ ምዕመናኑ በአጸዱና በግርማ ሞገሱ ኹሌም የሚደነቁበት፤ ስዕለት ሰሚ ታቦታት ያሉበት፤ 4ት የሚጠጉ ፈዋሽ ጠበሎች የሚገኙበት፡፡ #አጽዶቹ ሳይቀሩ በቁጥር በ72 አርድዕት ቅዱሳን አምሳያ የተተከሉበት። በጣሊያን ወረራ ወቅት እንኳን አንድም ቀን አገልጎሎት ያልቋረጠበት፤ 365 ቀን በሰዓታቱ፣ በማኅሌቱ፣ በመቅደሱ ያለ ማቋረጥ የምስጋና ወንዝ የሚፈስበት፤ ሁልጊዜ ወር በገባ ከ፩ አስከ ፯ ምሕላ የሚደርስበት። አረጋውያኑ ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት በአዘቦት ቀን ለቅዳሴ እና ለጸሎት የሚገኙበት፤ የስውራን ቅዱሳን አባቶች መናሐሪያ የሆነ፤ ከጥንት ዘመን እስከ ዛሬ መዐዛ ቅዳሴ የተሰኘው የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ቅዳሴ በወርኃ ጽጌ በብቸኝነት የሚቀድስበት ደብር #ፍጹም መንፈስ ቅዱስ የረበበት ታላቅ እና ልዩ ደብር ነው፡፡ ✣ ለደብረ ሰላም ይደልዋ ስብሐት፤ እስመ በውስቴታ ኀደረ መድኀኔዓለም፤ በደብረ ሰላም በውስጧ መድኀኔዓለም ስላደረ ምስጋና ይገባታል፡፡

በአዲስ አበባ የመድኀኔ ዓለም ክብረ በዓል ያለባቸው አብያተ ክርስቲያናት #ጥቂቶቹን እንጠቁማችሁ፤ (ስብስብ 2) 👉 በየአካባቢያችሁ ያሉትን የመድኀኔዓለም አድባራት በአስተያየት መስጫው ላይ አስቀምጡልን፤ ያሏችሁንም ፎቶዎች አጋሩን። 1) ደብረ ቀራንዮ መድኀኔዓለም ቤ.ክ፤ በአዲስ አበባ ከተመሠረተ ከ1826 ዓ.ም ጀምሮ ፍልሰት ሳያጋጥመው በመቆየቱ፤ የመጀመሪያው የአዲስ አበባ ቤ.ክ፡፡ (በመሃል ፍልሰት እያጋጠማቸው እንጂ በአዲስ አበባ ከ1600 ዓመታት በፊት ደብረ ኤረር፣ የካ ዋሻ ተክለሃይማኖትና /ኋላ የካ ሚካኤል/ በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን፤ እንዲሁም እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት በአልአሜዳ ዘመነ መንግሥት መመሥረታቸውን ልብ ይሏል) 2) ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉኀን ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን (ታሪኩን በሰፊው በቀጣዩ ፖስት ይልከቱ) 3) ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔዓለም፤ (ታቦተ ሕጉ ባይወጣም በሰዐታትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡)፤ 6 ኪሎ 4) አቃቂ ጋራው መድኀኔዓለም፤ 5) ረቢ መካነ ጎልጎታ መድኀኔዓለም፤ረጲ 6) መንበረ ሕይወት መድኀኔዓለም፤ አቃቂ ክ/ከተማ 7) ደብረ ቅዱስ ደብረ ቀራሜሎስ ካራአሎ መድኀኔዓለም ወአቡነ ገሪማ፤ የካ ክ/ከተማ 8) መካነ ሰላም መድኀኔ ዓለም፤  የካ ክ/ከተማ 9) ቦሌ ቡልቡላ ደብረ ገነት መድኀኔ ዓለም፤ቦሌ ቡልቡላ 10) ድልበር መድኀኔዓለም፤ ጉለሌ (ቶታል) 11) ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኀኒት መድኀኔዓለም ቤ.ክ  ልደታ ሜክሲኮ 12) ደብረ ሳሌም ቦሌ መድኀኔዓለም ወቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤተ ክርስቲያን 13) ምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኀኔዓም ቤተክርስቲያን፤ቀበና 14) አያት መድኃኔዓለም፤ አያት 15) ደብረ ኢያሪኮ መድኀኔዓለም፤ደቡባዊ አ.አ 16) ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን፤ የመድኀኔዓለም  ታቦት በድርብት ይገኛል፡፡  17) ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብት ይገኛል ፡፡  ጎተራ 18) የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ወኢሉጣ ቤ.ክ የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብት ይገኛል፤ ለገሃር 19) ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ፤ የመድኀኔዓለም  ታቦት በድርብት ይገኛል፡፡  20) ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብነት ይገኛል) 21) መንበረ ንግሥት ቊስቋም ማርያም ቤ.ክ (የመድኀኔዓለምና የመብዓ ጽዮን ታቦት በድርብነት ይገኛል) 22) ኮተቤ(ሲምሲ) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ.፤ (የመድኀኔዓለም ታቦት በድርብነት ይገኛል)

እንኳን ለቸሩ አምላካችን #ለመድኀኔዓለም ክብረ በዓል (ለመጋቢት 27 ጥንተ ስቅለት ልዋጭ በዓል) እና #ለአቡነ_መብዓ_ጽዮን ክብረ በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ፡፡ በመላው ሀገራችን ከሚገኙ የመድኀኔዓለም ገዳማትና አድባራት #በጣም #ጥቂቶቹ፤ (በየአካባቢያችሁ ያሉትን የመድኀኔዓለም አድባራት በአስተያየት መስጫው ላይ አስቀምጡልን) 1) ዋልድባ አብረንታት መድኀኔዓለም ገዳም 2) ኤልሻማ ደብረ ማኅቶት መድኀኔዓለም (ከ1,455 ዓመታት በፊት የታነጸ፤ ደቡብ ወሎ፤ ጃማ 3) ላሊበላ ቤተ መድኀኔዓለም 4) ጎንደር መንበረ መንግሥት መድኀኔዓለም 5) መንዳባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም፤ ጣና 6) ሽረ እንዳሥላሴ መድኀኔዓለም ወመስቀል ክብራ 7) ቆላድባ መድኀኔዓለም፤ ጎንደር ከተማ አጠገብ 8) ጨነቅ ዋሻ መድኀኔዓለም፤ በቅዱስ ላሊበላ በዋሻ ውስጥ እንደገና ፎቅ ተደርጎ የተፈለፈለ፤ በሰሜን ተራሮች (በራስ ደጀን) እግር ሥር የሚገኝ፤ በፓርክ ክልል ውስጥ በመኾኑ በብዙ ኢትዮጵያውያን የማይታወቅ፤ ነገር ግን ብዙ ተዓምራትን የሚያደርግ እጅጉን ፈዋሽ የኾነ ጠበል የሚገኝበት፡፡ 9) መናገሻ ጋራ መድኀኔዓለም፤ ግማደ መስቀሉ ያረፈበት፤ ቅዳሴ ቤቱን ታላቁ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ቀድሞ የልደታ ቤ.ክ) በአካል በመገኘት በመስቀሉ የባረከው፤ በድርሳነ ራጕኤል ላይ የተገለጸና ቅዱስ ራጕኤል የማይለየው፤ በአረማዊው ግራኝ ወረራ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ ካህናቱን መነኮሳቱንና ምዕመናኑን እንደያዘ በምድር ውስጥ ገብቶ የተሰወረበት በሥጋ ዕረፍተ ሞት ያልተገቱ ሥውራን ግሩማን አበው የሚኖሩበት "ዛቲ ይእቲ አምባ ማርያም መካነ ክብሮሙ ወጸሎቶሙ ለቅዱሳን ወለነገሥታተ ኢትዮጵያ በሐ በልዋ ተሳለምዋ ጊሱ ሐቤሃ ኢትርሐቁ እምኔሐ" ብለው አበው ያወደሷት የጸሎት የአርምሞና የትኅርምት ቦታ፡፡ 10) ገዳመ አባ ጽጌ ድንግል (መድኀኔዓለም ቤ.ክ)፤ ማኅሌተ ጽጌ የተደረሰበት ወሎ፤ ወግዲ፤ ወለቃ ወንዝ አጠገብ፤ የበረሃው ዕንቊ ገዳም፤ አባ ጽጌ ድንግል የፈለፈሉት ባለ 3 መቅደስ እጅግ ሰፊ ዋሻ ቤ.ክ፡፡ 11) ዋሻ መድኃኔ ዓለም አቡነ ሙሴ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም 12) አርብዓሐራ ምስካበ ቅዱሳን መድኀኔዓለም ገዳም፤ ደመ ክርስቶስን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል የተቀበለበትን የብርሃን ጽዋ የሚያጥኑ ቅዱሳን እና የሌሎችን ቅዱሳንን አጽም በንሥር አሞራ የተመሰለ የጌታ መልአክ በቀስተ ደመና ተከብቦ በቀን የሚያመጣበት፤ እልፍ ታሪክና ብዙ፥ የብዙም ገቢረ ተአምራት የሚፈጸሙበት፤ ለተፈቀደላቸውና እንደሚገባ ሆነው በቦታው ላይ በበጎ ኅሊና ለሚጸልዩ ምዕመናን ሥውራኑ እየተገለጡ ጥያቄያቸውን የሚመልሱበት፤ ግርማ ያለው ክቡር ንዑድ የ40ዎቹ ቅዱሳን ሰማእታት መካነ ጸሎት የአቡነ ሐራ ግብፃዊ የቃልኪዳን ሥፍራ 13) ጨጨሆ መድኀኔዓለም፤ ወሎና ጎንደር ድንበር ላይ 14) በደሌ ደብረ ሣህል መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን፤ ከ100 ዓመት በላይን ያስቈጠረ ጥንታዊ ቤ.ክ. 15) ደሴ ደብረ መድኀኒት መድኃኔዓለም፤ በ3ወር ከ14ቀን ተሠርቶ የተጠናቀቀ፤ በ1905 በንጉሥ ሚካኤል የተሠራ 16) ሬማ መድኀኔዓለም፥ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ገዳም፤ በ1414ዓ.ም በአቡነ ኖብ የተመሰረተ፤ የእናታችን ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ አጽሟ የሚገኝበት፤ ጣና ሐይቅ 16) ወዘም ባሕታዊ መድኃኔዓለም፣ ፍቼ አጠገብ ሰሜን ሸዋ 17) ደጀን አበ ብዙኃን አብርሃም ወመድኃኔዓለም፤ ደጀን ጎጃም 18) አርባምንጭ ደብረ መድኃኒት መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን፤ አርባ ምንጭ ከተማ 19) ቦራራ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን 20) ደብረ ቀራንዮ መድኀኔዓለም ወቅዱስ ላሊበላ ቤ.ክ፤ ጎንደር 21) ጌቴ ሴማኔ ፈረስ ቤት መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን፣ ደብረ ማርቆስ 22) ወልዲያ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም፡፡ 23) መቅደላ መድኀኔዓለም 24) ባሕር ዳር ድባንቄ መድኄኔዓለም 25) አዴት መድኃኔዓለም 26) አዲስ አምባ መድኃኔዓለም፤ ከ1600 ዓመት በላይ ዕድሜ ያለው በግብፃዊው ጻድቅ አቡነ ሙሴ የተፈለፈለ የዋሻ ገዳም 27) ወንጪት መድኃኔዓለም፤ በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግስት ተመስርቶ እስካሁን ድረስ ነብር በቤተ መቅደሱ እየኖረ በሚጠብቀው፤ በታላቁ ወይን እንጨት ቅዱስ ሚካኤል ገዳም ውስጥ የተሰራ 28) መቀለ ደብረ መድኀኒት መድኃኔዓለም 29) አድግራት መድኃኔዓለም ወቅድስት ሥላሴ ወቅዱስ ቂርቆስ ገዳም፤ ብዙ ድንቅ ታሪክ ያለው 30) ደባርቅ መድኃኔዓለም 31) የሽረት መድኃኔዓለም እጅግ ተደንቀውና ተደምመው ምስጋናዎ ኢምንት ሆናብዎት የሚመለሱበት 32) ኮሶ በር መድኃኔዓለም 33) ሐረር መድኃኔዓለም 34) ምስካበ ቅዱሳን ጻድቃኔ ዋሻ መድኃኔዓለም ገዳም 34) እመኪና መድኃኔዓለም ገዳም፤ በመናኔው ጻድቅ ንጉሥ በአጼ ካሌብ ልጅ፥ በጻድቁ ንጉሥ በአጼ ገብረ መስቀል፥ በ6ኛው መ.ክ.ዘ. የተመሰረተ ታሪካዊ ገዳም 35) በሬ አገር መድኃኔዓለም ገዳም፤ 1000 ሜትር ፍልፍል ዋሻ ገዳም 36) ተከዜ መድኃኔዓለም ገዳም፤ በ11ኛው መ.ክ.ዘ. የላስታ ንጉሥ ቅዱስ ገብረ ማርያም /ታላቁ ሐርቤይ/ ደቀ መዝሙር፤ እንደነ ነቢዩ ኤልያስና ወንጌላዊው ቅ.ዮሐንስም ሞትን ሳያይ እስከ ምጽዓተ ሐሳዊ መሲህ /ዳግም ምጽአተ ክርስቶስ ዋዜማ/ ድረስ የተሰወረው፤ ጻድቁ አቡነ ሐዋርያ ክርስቶስ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን ከሰማይ ተቀብሎ የመሰረተው፤ ንዑድ ክቡር የሆነ መካነ ጸሎት ወአርምሞ ወትኅርምት 37) ደብረ ታቦር መድኃኔዓለም 38) ናዝሬት መድኃኔዓለም 39) ምስካበ ቅዱሳ ዋሻ መድኃኔዓለም፤ ሰላ ደንጋይ፤ ጻድቃኔ አካባቢ) 40) ሰቃ መድኃኔ ዓለም፤ ለሚ፤ እንሳሮ 41) ገነተ ቅዱሳን ዋሻ መድኃኔዓለም አንድነት ገዳም ደብረ ማርቆስ አካባቢ፤ 42) ጅፋ መድኃኔዓለም፤ ደቡብ ወሎ ዞን ተንታ ወረዳ፤ በዱሮው አጠራር መረሂመኖ፤ ከታች ተንታ ቅዱስ ሚካኤል 10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ፤ ጥንታዊ ቤ.ክ. 43) ኦቦራ ዓለምገና ደብረ ገሊላ መድኃኔዓለም፤ ባሌ 44) ጎባ ደብረ ገነት መድኃኔዓለም፤ ባሌ 45) አዳባ መድኃኔዓለም፤ ባሌ 46) ዙላ መድኃኔዓለም፤ ባሌ

ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፪ኛ ዙር ዓመት፤ ፬ኛ ሳምንት፥ዘጥቅምት ፳፫) በዓለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት፡፡ ✤፠ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤ ፠  ማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት
+4
ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፪ኛ ዙር ዓመት፤ ፬ኛ ሳምንት፥ዘጥቅምት ፳፫) በዓለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት፡፡ ✤፠ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤ ፠  ማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል ዑራኤል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን፤ የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን(የሸዋን) የተከተለ ነው፤  የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ እያሳሰብን፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡

#ጥቅምት_20_በዓለ_ልደቱ_ለኤልሳዕ_ነቢይ #በዓሉ_በእንጦጦ_ራጉኤል_ይከብራል። ኤልሳዕ የስሙ ትርጒም “እግዚአብሔር ደኅንነት ነው” ማለት ነው፡፡ነቢዩ ኤልሳዕ እጅግ ባለጠጋ የሆነ ሰው ነበር። ከዕለታት በአንደኛ ዕለት በ12 ጥማድ በሬ ሲያርስ ቴስቢያዊው ነቢዩ ኤልያስ ተከተለኝ አለው ምንም ሳያቅማማ ሀብት ንብረቱን ትቶ ተከተለው፤ ኤልያስ በእሳት ሰረገላ ከማረጉ በፊት ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ ይለዋል ባንተ ላይ ያደረ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እጥፍ ድርብ ሆኖ ይደርብኝ ይለዋል፤ እንደ ቃሉ ሆነለት ተደረገለት፤ ኤልያስ አንድ ሙት ሲያስነሳ ኤልሳዕ ሁለት ሙት አስነስቷል፤ ኤልያስ አንድ ጊዜ ባህር ሲከፍል ኤልሳዕ ሁለት ጊዜ ባህር ከፍሏል። የኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ሆኖ አድሮበት ለረጅም ጊዜ እግዚአብሔርን አገለገለ፣ ብዙ ተአምራትንም አደረገ፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ወደ ኢያሪኮ ከተማ በሚገባበት ጊዜ በከተማዋ የሚኖሩ ሰዎች ነቢዩ ኤልሳዕ ወደ እነርሱ እንደመጣ ባዩ ጊዜ “የዚች ከተማ ኑሮ መልካም ነው ውኃው ግን ክፉ ነው ምድሪቱም ፍሬዋን ትጨነግፋለች” አሉት፡፡ የኢያሪኮ ከተማ ሰዎች ይህን ልመና ለኤልሳዕ ያቀረቡት እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ነገርን ሁሉ መለወጥ እንደሚችል ይታመኑ ስለነበር ነው፡፡ ነቢዩ ኤልሳዕ የሰዎቹን ችግር ከተረዳ በኋላ የከተማውን ሰዎች አዲስ ማሰሮ እና ጨው እንዲያመጡለት አዘዘ፡፡ ሰዎቹም ኤልሳዕ እንዳዘዛቸው አደረጉ፡፡ አዲስ ማሰሮ በውስጡ ጨው አድርገው አመጡለት፤ ነቢዩ ኤልሳዕ ወደ ውሃው ምንጭ ወደ አለበት ስፍራ መጥቶ ጨው ጣለበት እና “እግዚብሔር እንዲህ ይላል ይህን ውኃ ፈውሼዋለሁ ከዚህም በኋላ ሞትና ጭንገፉ አይሆንበትም” ብሎ ለከተማው ሰዎች ተናገረ፡፡ ኤልሳዕም እንደ ተናገረው ውኃው እስከ ዛሬ ድረስ ተፈውሶአል፡፡ የኢያሪኮ ከተማ ሰዎች ከዛ ጊዜ ጀምሮ ንጹሕ ውሃ መጠጣት ጀመሩ፡፡ የምድሪቱንም ፍሬ ተመገቡ፡፡ እግዚአብሔር በነቢዩ አልሳዕ ድንቅ ነገር ሰለአደረገላቸው ዘወትር ያመሰግኑ ነበር፡፡ እምቤታችንን የኤልሳዕ ጋን ይላታል ኤልሳዕ የመረረውን ውኃ እንዳጣፈጠ እመቤታችንም ይህን መራራ ዓለም ጌታን በመውለዷ አጣፍጣዋለች። ኤልያስ አንድ ሙት ሲያስነሳ ኤልሳዕ ሁለት ሙት አስነስቷል፤ ኤልያስ አንድ ጊዜ ባህር ሲከፍል ኤልሳዕ ሁለት ጊዜ ባህር ከፍሏል። እምቤታችንን የኤልሳዕ ጋን ይላታል ኤልሳዕ የመረረውን ውኃ እንዳጣፈጠ እመቤታችንም ይህን መራራ ዓለም ጌታን በመውለዷ አጣፍጣዋለች፤ የዚህ ነቢይ ድንቅ ታሪኩ 2ኛ ነገስት19 ላይ በስፋት ተጽፏል ጥቅምት 20 ልደቱ ሲሆን ሰኔ 20 ቀን ደግሞ በዓለ እረፍቱ ነው። /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ • Facebook 👉 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 https://t.me/finotehiwott • YouTube 👉 https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w