ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 335 подписчиков, занимая 5 641 место в категории Религия и духовность и 2 191 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 335 подписчиков.

Согласно последним данным от 14 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -76, а за последние 24 часа — -1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 22.40%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 10.40% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 435 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 595 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 25.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 15 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 335
Подписчики
-124 часа
-67 дней
-7630 день
Архив постов
፮. ግብጽ እስክንድርያ ተክለ ሃይማኖት፤ ፯. ግብጽ እስክንድርያ አል አጋሚ ተክለ ሃይማኖት፤ ፰. ግብጽ እስሙናይ (እል መኖፊያ) ተክለ ሃይማኖት፤ ፱. ግብጽ ኤል ዛግዚክ ተክለ ሃይማኖት፤ ፲. ግብጽ ኤል ሙሐራቅ አስዩት ተክለ ሃይማኖት፤ ፲፩. ኬንያ ማሴኖ ተክለ ሃይማኖት (የግብጽ) ፲፪. ሎስ አንጀለስ ተክለ ሃይማኖት (የግብጽ) ፲፫. ኦታዋ ኦንታሪዮ ተክለ ሃይማኖት (የግብጽ) ፲፬. ብራምፕተን ኦንታርዮ ተክለ ሃይማኖት (የግብጽ) ፲፭. ፐርዝ አውስትራልያ ተክለ ሃይማኖት (የግብጽ) ፲፮. ሲድኒ አውስትራልያ ዳርዊን  ተክለ ሃይማኖት ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አዘዞ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ (ባሕር ዳር) → በጎንደር መስመር → ጎንደር ከተማ ሊገቡ ሲሉ አዘዞ ከተማ መግቢያ ላይ  ወደ ደንቢያ፥ ቆላ ድባ መታጠፊያ ላይ ያኙታል፡ ፬. ኤርትራ ሺምዛና ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፡፡ አድራሻ፤ ኤርትራ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → ኤርትራ → ሺምዛና፡፡ ፭. ኮራ ተክለ ሃይማኖት፤ (ጻድቁ የጸለዩበት) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት፥ ሰላሌ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከደብረ ሊባኖስ ገዳም ወደ ቆላው በእግር በመሄድ ያገኙታል፡፡ ፮. ወይንጌ(ዬ) ተክለ ሃይማኖት፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ደብረ ብርሃን፡፡ ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ መናኸሪያ → ደብረ ብርሃን ከተማ → በባጃጅ (በእግር) በመጓዝ ያገኙታል፡፡ ፯. አጆራ ተክለ ሃይማኖት፤ (አቡነ ተክለ ሃይማኖት በኢትዮጵያ በባለ መንታ ፏራቴነት ብቸኛ በሆነው አጆራ ላይ ከእጨጌ ዮሐንስና ከሌሎችም ደቀ መዛሙርቶቻቸው ጋር መቶሎሚ በቀፎ አድርጎ የወረወረበት፥ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ያዳናቸው ቦታ፡፡ ታሪክን ታሪክ ደግሞት 3ኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በቦታው ላይ ሱባኤ በመግባት በግራኝ መሐመድ ጊዜ ጠፍ ሆኖ የነበረውን ቤተ ክርስቲያንና ንዋያተ ቅድሳት ያገኙበት) አድራሻ፤ ደቡብ፥ ሌሾ፥ አጆራ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ አየር ጤና መናኸሪያ → ደቡብ (ሌሾ፥ አጆራ) ፰. ደብረ ገሪዛን (ገርዜን) ጕንዳጕንዶ ማርያም፤ (የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ/ክ ለብቻው አለ) አድራሻ፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት ፥ አዲግራት ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. → አዲግራት →  በእዳጋ ሐሙስ መስመር → ወደ አሲምባ የሚወሰደውን መንገድ በመተው ወደ ጕንዳጕንዶ በመሄድ ያገኙታል፡፡ ፱. አንጋራ ተክለ ሃይማኖት፤ (ከጣና ገዳማት አንዱ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጣና ደሴት ትራንስፖርት፤ ከአ. መርካቶ መናኸሪያ → ጎንደር → ጎርጎራ (ወይም ከባሕር ዳር) →  አንጋራ (በደንገል (በመርከብ /በጀልባ/) በመጓዝ ያገኙታል፤ ፲. አባ ጃሌ ተክለ ሃይማኖት፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ ትራንስፖርት፤ ከአ. መርካቶ መናኸሪያ → ጎንደር → ፒያሳ ፲፩. አደባባይ ተክለ ሃይማኖት፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ ትራንስፖርት፤ ከአ. መርካቶ መናኸሪያ → ጎንደር → አራዳ በሚል ታክሲ ፲፪. መቀለ ተክለ ሃይማኖት፤ አድራሻ፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ መቀለ ትራንስፖርት፤ ከአ. ጉርድ ሾላ መናኸሪያ → መቀለ ፲፫. ግሸና ተክለ ሃይማኖት፤ አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ግሸና ትራንስፖርት፤ ከጎንደር → ደቡብ ጎንደር (ደብረ ታቦር) → ግሸና ተክለ ሃይማኖት፡፡ ፲፬. ሚጣቅ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ አንኮበር፥ ሚጣቅ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ መናኸርያ → ደብረ ብርሃን ፥ በአንኮበር መስመር ሚጣቅ፡፡ ፲፭. ጎንድ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንድ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ መናኸርያ → በጎንደር መስመር ማክሰኚት → ጎንድ፡፡ ፲፮. ደብረ ድማኅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ (በ352 ዓ.ም. በአቡነ ሰላም ከሣቴ ብርሃን በታቦተ መድኃኔዓለምና ማርያም የተመሠረተ) አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ደላንታ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ መናኸርያ → ደሴ /ደላንታ/፡፡ ፲፯. ወላይታ ሶዶ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት 12 ዓመት ቆመው የጸለዩበት፤ ከሞተሎሜ ቤተ መንግሥት ዳሞት ተራራ ግርጌ የሚገኝ፤ የሀገረ ስብከቱ መንበረ ጵጵስና ያለበት፡፡ አድራሻ፤ ወላይታ ሀገረ ስብከት፥ ወላይታ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና መናኸርያ → ወላይታ፡፡ ፲፰. አኵስም ተክለ ሃይማኖት፤ (ከደብረ ጽዮን አኵስም አጥር ለአጥር የተያያዘ ቤ/ን) አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከጸለዩበት የአኵስም ጽዮን ቤ/ን አጠገብ የተሠራ፡፡ አድራሻ፤ አኵሰም ሀገረ ስብከት፥ አኵስም ከተማ፥ ጽዮን፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. → አኵስም፡፡ ፲፱. ጣራ ዋሻ ተክለ ሃይማኖት፤ አድራሻ፤ ማዕከላዋ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጣራ ገዳም፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ መናኸሪያ → በጎንድር መስመር (ጣራ ገዳም)፡፡ ፳. ጥዑመ ግራራ አጆራ ተክለ ሃይማኖት፤ (አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከእጨጌ ዮሐንስ ጋራ ሆነው በሞተለሜ ትእዛዝ በአጆራ ባለ 2ት ፏፏቴ በንብ ቀፎ የተወረወሩበትና ቅዱስ ሚካኤል ያዳናቸው) አድራሻ፤ ወላይታ ሶዶ ሀገረ ስብከት፥ ጣራ ገዳም፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና መናኸሪያ → ወላይታ /አጆራ/ → ጥዑመ ግራርያ፡፡ ፳፩. መርጠሉ ማርያም ደብረ ቢታንያ ተክለ ሃይማኖት (ደቡብ ወሎ፤ ንጉሥ አብርሃና አጽብሃ ከአባ ሰላማ ጋር በ333 ዓ.ም. የመርጡለ ማርያምን ገዳም ሲገድሙ ሱባኤ ከያዙባቸው አንዷ ተራራ) ፳፪. ቈየፃ ተክለ ሃይማኖት ፳፫. አንኮበር ተክለ ሃይማኖት (ሰሜን ሸዋ) ፳፬. ወግዲ ተክለ ሃይማኖት (ሰሜን ሸዋ) ፳፭. መንዝ ኮረብቲት ተክለሃይማኖት (ሰሜን ሸዋ) ፳፮. ራዛ ተክለ ሃይማኖት (ትግራይ) ፳፯. እምባይቶ ተክለ ሃይማኖት (ትግራይ) ፳፰. አራሮ ተክለ ሃይማኖት (ትግራይ) ፳፱. አፈር ባይኔ ተክለ ሃይማኖት ፴. ደጋ ዳሞት ተክለ ሃይማኖት (ምዕራብ ጎጃም) ፴፩. ባሕር ዳር ተክለ ሃይማኖት (ምዕተራብ ጎጃም፥ ባሕር ዳር ከተማ) ፴፪. ሰነቦ ተክለ ሃይማኖት (ምዕራብ ጎጃም) ፴፫. ቆላድባ ተክለ ሃይማኖት (ጎንደር፥ ደምቢያ፥ ቆላድባ) ፴፬. ደብረ ታቦር አንቀጸ አድኅኖ ዑራኤል ወተክለ ሃይማኖት (ደቡብ ጎንደር ) ፴፭. ሽና ተክለ ሃይማኖት ፴፮. ጉባ ላፍቶ ተክለ ሃይማኖት (ወሎ) ፴፯. ደሴ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (ሰሜን ወሎ፥ ደሴ) ፴፰. ዳቦት ተክለ ሃይማኖት ፴፱. የጁ ከረዩ ተክለ ሃይማኖት ፵. ጃናሞሬ ተክለ ሃይማኖት ፵፩. ገሬኖ ተክለ ሃይማኖት ፵፪. ቃሊቲ ገላን ጎሮ ተክለ ሃይማኖትና ኪሮስ ፵፫. ደብረ ዘይት (ቢፍቱ) ተክለ ሃይማኖት ፵፬. ሻሸመኔ ተክለ ሃይማኖት ፵፭. ሐዋሳ ተክለ ሃይማኖት ፵፮. ወንጂ ደብረ ፀሐይ ተክለ ሃይማኖት ፵፯. ሆሳዕና ደብረ ፀሐይ ተክለ ሃይማኖት ፵፰. አርባ ምንጭ ተክለ ሃይማኖት ፵፱. ሐረር ተክለሃይማኖት ፶. ጅግጅጋ ተክለ ሃይማኖት ፶፩. ባሌ ጎባ ደበረ ሰላም ተክለ ሃይማኖት ገዳም ፶፪. ወጠቅ ደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት፤ #ከኢትዮጵያ_ውጭ_የሚከበርባቸው_ #፲፯ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ኢየሩሳሌም ምስካበ ቅዱሳን ተክለ ሃይማኖት ገዳም (ኢየሩሳሌም፤ በአላዓዛር) ፪. ቨርጂኒያ ምሥራቀ ፀሐይ ተክለ ሃይማኖት (አሜሪካ) ፫. ብሪታንያ ሊቨርፑል መካነ ቅዱሳን ተክለ ሃይማኖት (እንግሊዝ) ፬. ስቶክሆልም ምዕራፈ ቅዱሳን ተክለ ሃይማኖት (ስዊዲን) ፭. ክላርክስተን ዳግማዊ ቁልቢ ደብረ ብሥራት ገብርኤልና ተክለ ሃይማኖት

የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን በዓለ ልደት የት ሊያከብሩ ዐስበዋል??? #በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በመላው_ዓለም_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፺፫ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ (በተለይም በድርብነት ያሉ በዓለ ልደቱን ላያከብሩ ስለሚችሉ ሲሄዱ አጣርተው ይሂዱ ) (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በአዲስ_አበባ_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፳፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩ ✣ ጥንታዊው በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ (ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዋሻ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም) /በአብርሐ ወአጽብሐ ዘመን በ‹‹ሐ›› ቅርጽ በልዩ አሠራር የታነጸ ፍልፍል ዋሻ፤ ከ1600 ዓመታት በላይ ያስቈጠረ፡፡/ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሾላ (መገናኛ) ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (4 ኪሎ) → ሾላ (መገናኛ) → የካ ሚካኤል → በእግር የ30 ደቂቃ መንገድ፤ ወይም ወደ ኮተቤ በአዲሱ መንገድ ሲሄዱ መንገድ ላይ ወርደው ተራራውን እንደወጡ ያገኙታል፡፡ ፪ ✣ደብረ አሚን ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ /ከዓመት እስከ ዓመት ከበዓለ ሃምሳ ውጭ እንደ ደብረ ሊባኖስ ውሎ ቅዳሴ የሚቀደስበት/ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ መርካቶ ተክለ ሃይማኖት፤ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (ከአውቶቡስ ተራ) → መርካቶ ተክለ ሃይማኖት ፫ ✣ መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል፥ አቡነ ተክለሃይማኖትና ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ በቀጨኔ በአዲሱ ገበያና በእንጦጦ መሃል ከደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ/ክ በላይ ጉብታው ላይ የሚገኝ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → ቀጨኔ(አዲሱ ገበያ) → የ20 ደቂቃ የእግር መንገድ፡፡ ፬ ✣ ሲ.ኤም.ሲ. መካነ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅድስት ልደታ፤ አድራሻ፤ የካ ክ/ከ፤ ሲ.ኤም.ሲ.፤ መሪ ሎቄ፤ ለገጅጃ ትራንስፖርት፤ ከመገናኛ ሲ.ኤም.ሲ. ፭ ✣ ኮልፌ ፊሊዶሮ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከ፥ ፊሊዶሮ፤ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → መርካቶ → ኮልፌ አጣና ተራ /ፊሊዶሮ/፡፡ ፮ ✣ ፍኖተ ሎዛ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ (በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከ፥ ብርጭቆ ኮንዶሚንየም ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ አረዳ → ብርጭቆ ፯ ✣ (ጀሞ) ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → ጀሞ ፰ ✣ ደብረ ቢታንያ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ፥ 5 ቊጥር (2 ቊጥር) ማዞርያ ትራንስፖርት፤ ከፒያሰ (መርካቶ)→ ሜክሲኮ → ንፋስ ስልክ ፱ ✣ ቦሌ ቡልቡላ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ሥላሴ ገዳም፤ (አስደናቂ ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ ቤሌ ክ/ከ፥ ቡልቡላ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (ከመገናኛ) → ሳሪስ አቦ → ቡልቡላ መድኀኔዓለም ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #እንዲሁም_በአንድነት_፤ ፲ ✣ መጠሊ ደብረ አሮን ፍልፍል ዋሻ ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ገላን ጉራ ገበሬ ማኅበር፥ መጠሊ፤ ታክሲ፤ ከቃሊቲ → ገላን፡፡ ፲፩ ✣ (ቀበና) ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሲግናል ዐደባባይ → ዐድዋ ድልድይ → ኮንጎ ሰፈር (ከበአታ ቤ/ን ፊት ለፊት)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ  → ካዛንቺስ (22) /በአዋሬ በኩል በሚሄዱት)፡፡ ፲፪ ✣ ቱሉዲምቱ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ/ክ፤ አድራሻ ፤አቃቂ ቃቲ ክፍለ ከተማ፥ ቱሊ ዲምቱ አደባባይ ወደ አለም ባንክ መንገድ ላይ ነዳይ ማደያ ጋር፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉ ዲምቱ → ዐደባባይ አለም ባንክ፡፡ ወይም ከቃሊቲ → ቱሊዲምቱ (አለም ባንል,ክ ነዳጅ ማደያው ጋር) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #እንዲሁም_በድርብነት_፤ ፲፫ ✣ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል፥ 24ቱ ካህናተ ሰማይና ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → የካ አባዶ፡፡ ፲፬ ✣ ቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኀኒት መድኀኔዓለም ቤ/ክ አድራሻ፤ ቤሌ ክ/ከ፥ ቡልቡላ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (ከመገናኛ)→ ሳሪስ አቦ → ቡልቡላ መድኀኔዓለም ፲፭ ✣ ገነተ ኢየሱስና ገነተ ማርያም (እናትና ልጇ) ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ፤ ታክሲ፤ ከ4(6) ኪሎ → ፈረንሳይ፡፡ ፲፮ ✣ ቤላ መጥምቀ መለከት ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ቤላ ፈረንሳይ ፓርክ፤ ታክሲ፤ ከ4 (6 ኪሎ) → ቤላ (ፈረንሳይ) ፲፯ ✣ ሰርጢ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከ፥ ሰርጢ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (ከመገናኛ) (ከመርካቶ)→ አቃቂ ፲፰ ✣ ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. አድራሻ፤ ኮለረፌ ቀራንዮ ክ/ከ፥ ቤተል ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → ቤተል/ዓለም ባንክ/ ፲፱ ✣ ኤ(የ)ረር በር መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤልና ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ጎሮ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ቦሌ) → ኤረር በር (ጎሮ)፡፡ ፳. ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሩፋኤልና ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ሩፋኤል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ጴጥሮስ ዐደባባይ) → ሩፋኤል፡፡ ወይም ከአዲሱ ገበያ/ቶታል/ →  በእግር ፳፩ ✣ ገዳመ ኢየሱስ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ሆላንድ ኤምባሲ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ  → መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ኮልፌ አጠና ተራ፡፡ ወይም ከጦር ኀይሎች → ኮልፌ (ቀለበት መንገዱ ላይ) ፳፪ ✣መሪ አያት ምሥራቀ ፀሐይ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክ/ከ፥ መሪ አያት ትራንስፖርት፤ ከመገናኛ → መሪ አያት ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፶፬ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ (፩-፫) ✣፫ቱ ደብረ ሊባኖሶች፥ ፪ቱ በእጨጌዎች የሚመሩ ፩. ደብረ ጽላልሽ (ዞረሬ) አቲሣ ተክለ ሃይማኖት፡፡ (#ጻድቁ_የተወለዱበት) አድራሻ፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት፥ ጽላልሽ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. → በደብረ ብርሃን መንገድ አሌልቱ ከተማ ላይ በመታጠፍ ያገኙታል፡፡ ፪. ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ (የበርካታ ቅዱሳን መፍለቂያና አጽማቸው በክብር ያረፈበት) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት፥ ደብረ ሊባኖስ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ →  ደብረ ሊባኖስ (ገዳም) የሚል ትራንስፖርት ያገኛሉ፡፡ ወይም ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ →  ፍቼ(ባህር ዳር) በሚሄድ ትራንስፖርት  ደብረ ጽጌን እንዳለፉ ጫገል የምትባል መንደር ላይ ወርደው በታክሲ(በባጃጃ) (በእግር) በመጓዝ ያገኙታል፡፡ ፫. ጎንደር፥ አዘዞ ደብረ ሊባኖስ፤ የኢትዮጵያ ርዕሰ መዲና ከ300 ዓመታት በላይ ጎንደር ላይ በነበረበት ወቅት ዳግማዊት ደብረ ሊባኖስ ሆኖ በእጨጌ እየተመራ የቆየ ታላቅ ገዳም፡፡

#ታኅሣሥ_23 #ቅድመ_ልደተ_ክርስቶስ_በ1080 #ቅዱስ_ዳዊት_አረፈ ፠ እግዚአብሔር እንደ ልቤ ብሎ የጠራው ፤ በዚህም ልበ አምላክ ተብሎ የሚጠራ፤ ፠ 10 አውታር ባለው በገና የሚያመሰግን፤ መዘምር፤ ፠ ከ15ቱ ነቢያት አንዱ፤ ፠ 40 ዓመታት እሥራኤልን የገዛ፤ አምላኩ ኪዳንን የሰጠው፤ ፠ የዋህ፣ ደግ፣ ትሁትና ርህሩህ (በየዋህነቱ ከሙሴ ጋር፤ በደግነቱ ከአብርሃም ጋር የሚነጻጸር) ፠ ኃይል የሆነ (በኃያልነቱ ከሶምሶን ጋር የሚነጻጸር) ፠ ጀግና (ከጀግንነቱ የተነሣ ዳዊት መጣ ሲባል ደንግጦና ፈርቶ የሚሞት የነበረ) ፠ አስተዋይና ብልህ መሪ (በርካታ አስተዋዮችና ብልህ መሪዎች በሥሩ የነበሩት) ፠ መዝሙሩ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ዕለት ዕለት የሚጸለይ (አንድ ክርስቲያን ግዴታ በየቀኑ ሊጸልየው የሚገባ ጸሎት ተብሎ በፍትሐ ነገሥት የተደነገገ) ፠ ከደረሰው መዝሙር የተውጣጡ ምስባኮች ከዓመት ዓመት በቅዳሴ ጊዜ በዜማ ጭምር የሚባሉለት ፠ የንስሐ አባት (ቶሎ ብሎ ንስሐ በመግባት ከፈጣሪው ጋር የሚታረቅ) * ትውልዱ ከእሥራኤልና እንዲሁም ከሞዓባውያን ወገን ከሆነችው ከደገኛይቱ ሩት ነው * እሥራኤልን በንግሥና መመምራት ከሳዖል ቀጥሎ ሁለተኛ ነው፡፡ (ነገር ግን የሳዖል መንግሥት የይንቆሽ ስለሆነ ዳዊት የመጀመሪያው የእሥራኤል ንጉሥ በመባል ይታወቃል)፤ * ገና በወጣትነት በእረኛ እጅ በፈጣሪው መራጭነት በጠንካራው እምነቱ ወደ ጦር ሜዳ በመጓዝ በግዝፍነቱና በጀግንነቱ ተወዳዳሪ የጠፋለት የዕብራውያንን ልብ እንደሰም ያቀለጠ፥ ንጉሣቸው ሳዖልንም ያሸበረና ያስደነገጠ፤ መምለኬ ጣዖት፥ መዝግበ ኃጢአት ፥ ትዕቢትን የተሞላ ፥ የጣዖት ድልብ ቁመቱ ስድስት ክንድ ከስንዝር የሚሆን ረአይታዊ ጎልያድን በፈጣሪው ኃይል በወንጭፍ ደንጊያ ግንባሩን መቶ ገርስሶ በመጣል ቸብቸቦውን በሰይፍ በመገንጠል እያንዳንዱ ዕብራውያንን ከጎልያድ ሰይፍ ታድጓል፡፡ (መዝ 151) ዳዊት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከጦር ሜዳ ሳይለይ አያሌ ዘመናት አሳልፏል፡፡ * የእስራኤል ሴቶችም ‹‹ሳዖል ሺህ ገደለ፤ ዳዊት ዕልፍ ገደለ /ጎልያድ የእልፍ ያህል ነውና/ እያሉ በመዝፈናቸው በሳዖል ልብ ቅንዐት አደረ፡፡ * በሽፍትነት በረሀ ለበረሀ በመንከራተት ብዙ ዘመን ካሳለፈ በኋላ ሳዖል ሲሞት መሪነቱን ይዟል፤ ነገር ግን እሥራኤልን ለመምራት የተመረጠው ገና ሳዖል በሕይወት እያለ በእግዚአብሔር ትዕዛዝ በሳሙኤል ቀባዒነት ነው፡፡ * ከጀግንነቱ የተነሣ ዳዊት መጣ ሲባል ደንግጦ እና ፈርቶ የሞተም እንዳለ ታሪክ ይነግረናል፡፤ 1ኛ ሳሙ 25፥1-39፡፡ ነገር ግን ዳዊት እንደ ጀግንነቱ ሁሉ ጨቃኝ አይደለም ርህራሄም የተሞላ መሪ ነበር ከአንዴም ሁለቴ ሳዖልን መግደል ሲችል ራርቶ የመረጠውን እግዚብሔርን ፈርቶ ትቶታል፡፡ * ዳዊት ትልቅ ኃጢአት የሠራው የጦር ጀግናው የኦርዮን ሚስቱን ከመቀማቱም ባሻገር በጦር ሜዳ ለጠላት ጦር አሳልፈው ሰጥተው ወደኋላ እንዲያፈገፍጉ ለእስራኤል በመምከር ኦርዮን ባልተረዳው ነገር ተደብድቦ እንዲሞት አስደርጓል፡፡ በዚህም እግዚአብሔርንም ሆነ የጦር መሪው ኢዮአብን አሳዝኗል፡፡ በዚህም እግዚአብሔር እውነተኛ ፈራጅ በመሆኑ በዳዊት ላይ ከበድ ያለ መከራና ኃዘን አምጥቶበታል፡፡ ለአነብነትም፤ 1ኛ) አምኖን የገዛ እኅቱን ከክብር አሳንሶ አዋረደ ፤ ዳዊት የሰው ሚስት በግፍ ደፍሮ ነበርና፤ 2ኛ) በዚህ ምክንያት አቤሴሎም ወንድሙ አምኖንን ገደለ ፤ ዳዊት ኦርዮንን በግፍ አስገድሎ ነበርና፤ 3ኛ) አቤሴሎም የዳዊትን መንግሥት ገልብጦ የአባቱን እቁባት ሁሉ በአደባባይ አረከሰ፤ ዳዊት የኦርዮንን ሚስት በድብቅ ተገናኝቷታልና እንዲሁም ዳዊት የሳዖልን መንግሥት አስቸግሮ ነበርና፤ 4ኛ) አቤሴሎም በአባቱ የጦር አበጋዞች ተደብድቦ ሞተ፤ በዚህም ዳዊት እጅግ አዝኖ ነበር፡፡ 5ኛ) አዶንያስም በአባቱ ላይ መፈንቅል አድርጎ ለጊዜው ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ ነገር ግን ከላይ የተዘረዘሩት 5ት ሐዘኖች ቢገጥሙትም ዳዊት በለመደው የንስሐ ልቅሶ ችግሩን አስተካክሎ ወደ ፈጣሪው ተጠግቷል፡፡ * ኃጢአቱን ይቅር ያለው ፈጣሪው ግን ቤተ መቅደስን እንዳይሠራ በነቢይ አማካይነት ከልክሎታል፤ ዳዊትም ይህን የፈጣሪውን መመሪያ አልተጋፋም ሥራውን አቁሟል፡፡ የእግዚብሔር እንደራሴ ስለነበረ፡፡ •+++• ዳዊት እግዚአብሔር ለሰው ከሚሰጣቸው ልዩ ሐብታትም ባለቤት ነበር፡፡ እነርሱም፤ #1ኛ. ሀብተ ጥበብ ወአዕምሮ #2ኛ. ሀብተ ትንቢት #3ኛ. ሀብተ ኃይል (ገና በእረኝነት ግሩማን አራዊት ድብና አንበሳን ጉሮሯቸውን እያነቀ በመግደል ኋላም ግዙፍ ጎልያድን በአልባሌ መሣሪያ ገርስሶ በመጣል) #4ኛ. ሀብተ ምክር #5ኛ. ሀብተ ልቡና #6ኛ. ሀብተ ፈሪሃ እግዚአብሔር #7ኛ. ሀብተ ፈውስ #መዝሙረ_ዳዊት_፤ ፠151 መዝሙራት ሲኖሩት 88ቱ እርሱ የዘመራቸው ሲሆኑ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ ሌሎች የዘመሩትን ሲሆን የሌሎችንም መዝሙራት 10 አውታር ባለው በበገና ይዘምራቸው ስለነበረ 151ዱም የዳዊት መዝሙራት ተብለዋል፡፡ ፠ መዝሙረ ዳዊት ምሥጢራዊ ነገር ያለበት፥ በምሥጢሩ የጠለቀ፥ በትንቢታዊነቱ የረቀቀ፥ መንፈሳዊ ስብከት ፥ ትንቢታዊ ትምህርትን የተሞላ፥ ቊጥሩ አንድ ውስጡ ብዙ፥ የማይጠቅሰውና የማይናገረው የሌለ ዕፁብ ድንቅ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ ፠ መዝሙረ ዳዊት ባሕር ነው፤ አንድ ሰው ከጥልቅ ባሕር ገብቶ እንደ አቅሙ ትንሽ ዓሣ ይዞ ሊወጣ ይችላል፤ ፠ነቢዩ ዳዊት እግዚብሔር ብዙ የረቀቁ ትንቢቶችን ስለተናገረበት በፈጣሪው ዘንድ #የእግዚአብሔር_ልብ የመባል ልዩ ስያሜ ያገኘ ብቸኛ ሰው እንደነበር ዜና ነገሥት ይናገራል፡፡ /1ኛ ሳሙ 13፥14፣ የሐዋ ሥራ 13፥22/ ፠ ዳዊት በመዝሙሩ አምስቱን አዕማደ ምሥጢር መዝግቦ ያስነብበናል:: ፠ መዝሙረ ዳዊት ከተለያዩ መመዘኛዎች አንጻር በተለያዩ አከፋፈሎች ይከፈላል፡፡ #በቅዳሴ_ጊዜ_የዳዊት_መዝሙር_በዜማ_ይዜማል_ለምን? ** የዳዊት መዝሙር ለሌሎች የነቢያት መጻሕፍት ተለይቶ ቅድመ ወንጌል በዜማ እንዲሰበክ የተደረገበት ምክንያት፤ በርካታ ነገሮችን በወንጌል የተመዘገቡትን ስለያዘ ነው፡፡ በዚህም መዝሙረ ዳዊት ደረቅ ሐዲስ በመባል ይታወቃል፡፡ ** ስለ መዝሙረ ዳዊት ታላቁን ሊቅ ቅዱስ ያሬድን (በክስተተ አርያም፣ በመስተጋብዕ፣ …) ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫን (በመጽሐፈ ሰዐታቱ፣ በመዝሙረ ድንግል) ይጠይቁ፤ 151ዱን መዝሙር በቀጥታና በተዘዋዋሪ መንገድ በንባብ ብቻ ሳይሆን በጣዕማዊ ሰማያዊ ዜማ ከእግር እስከ ጫፍ ከጽንፍ አስመልክታ መልዕክቷን ወደ ፈጣሪዋ እንደታቀርብበት ለቤተ ልርስቲያናችን አስረክበዋልና፡፡ #ፎቶ_ላይ_ይምትመለከቱት_ቤ/ክ፤ ከ300 ዓመት በላይ የሆነውና  #በአድያም_ሰገድ #አፄ_ኢያሱ (1674-1698) የታነጸውን የቅዱስ ዳዊት ቤተ ክርስቲያን ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያኑ የሚገኘው #መተከል_ዞን_ዳዊት ቀበሌ ነው፡፡ (ወደ ቦታው ለመሄድ ከፈለጉ ከአዲስአበባ ተነስተው ፡ #በእንጅባራ አልፈው ፡ #ቻግኒና #ግልገል በለስንም ተሻግረው #ማንቡክ ወደምትባል ከዚያም #በላያ የሚባል አካባቢ ላይ ንጉሥ ዳዊት ቀበሌንና የቅዱሱን ደብር ያገኛሉ፡፡) /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

የታኅሣሥ ቅዱስ ገብርኤል የማታ ጉባዔ 🛑ቀጥታ ስርጭት ከቀጨኔ መድኃኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን https://www.youtube.com/live/SlHs4hCfmos?si=T9aBebf8f1rUAzJG

የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል ፥ ታኅሣሥ 19, 2018 ዓ.ም ፥ የማስታወሻ ፎቶ። /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

የታኅሣሥ ቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግሥ ቀጥታ ስርጭት ከቀጨኔ መድኃኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን https://www.youtube.com/live/WF_Nru_EkPc?si=0byLFbtFaR_KX7UB