ru
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Открыть в Telegram
1 474
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-2130 дней
Архив постов
ዛሬ ከሰዓት በኋላ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ህብረት አፍሪካን በሚገባ የሚወክል ኮፕ 32 ለማዘጋጀት እንዴት ተቀራርበው መስራት እንደሚችሉ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር እና ከቡድናቸው ጋር ተወያይቻለሁ። በክቡር ማህሙድ አሊ የሱፍ መሪነት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን COP32ን የተሳካ ለማድረግ የኢትዮጵያ ቁልፍ አጋር ለመሆን ቁርጠኛ መሆናቸውን ተገንዝብያለው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነበራቸው ቆይታ በምስል

ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ኢትዮጵያን በመጎብኘትዎ እና የኢትዮጵያ እና ህንድን ግንኙነቶች እንዲጠናከሩ ለሚያደርጉት ጥረት ምስጋና አቀርባለሁ። ትስስራችንን ወደ ስትራቴጂያዊ ደረጃ ከፍ ለማድረግ የተወሰነው ውሳኔም በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ትብብራችን… See more

በመዲናችን አዲስ አበባ በቅርቡ ስራ ላይ የዋለው አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት በኤጀንሲው እየተካሄደ ያለውን ሪፎርም ወደተሟላ ደረጃና ወደ አዲስ ምእራፍ የሚያሸጋግር ነው- በም/ከንቲባ ማእረግ የአ… See more

የዲፕሎማሲ እና ታላቅነት ምሽት ለጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን መዐከል የተደረገ የክብር ግብዣ። #PMOEthiopia

ለህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በብሔራዊ ቤተመንግሥት ይፋዊ አቀባበል ሥነሥርዓት አድርገናል። ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ውይይት ካደረግን በኋላ ከልዑካን ቡድኖቻችን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደናል። በውይይታችን በኢትዮጵያ እና ህንድ መካከል እያደገ የመጣውን ትብብር እና የወል ቅድሚያዎች የሚያንፀባርቁ አዳዲስ የትብብር መስኮችን ቃኘተናል። በሁለቱ ሀገራት መካከል በጉምሩክ የጋራ አስተዳደር ድጋፍ፣ በኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዳታ ማዕከል ምስረታ የመግባቢያ ሥምምነቶችን እንዲሁም በአለምአቀፍ የሰላም ማስከበር ላይ ያለንን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እና የሚያጠናክረውን የተባበሩት መንግሥታት የሰላም ማስከበር ሥራ የመግባቢያ ሥምምነት የፊርማ ሥነሥርዓት ላይም ተገኝተናል። ህንድ የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ አጋር ስትሆን የዛሬዎቹ ውይይቶች እና ሥምምነቶችም ለጋራ ጥቅም በተለያዩ ዘርፎች ያሉንን ትብብሮች ለማስፋት ያለንን የጋራ ቁርጠኛ አቋም ያሳያሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲን ለይፋዊ ጉብኝት በመቀበሌ ደስታ ተሰምቶኛል። የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል እያደገ የመጣውን ትስስር የሚያመለክት ሲሆን ውይይቶቻችን በጋራ የቅድሚያ ጉዳዮቻችን ላይ ትብብሮቻችንን የበለጠ የምናጠናክርበት እንደሚሆን እምነቴ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ደረቅ ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም ዘርፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ተገለፀ። የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ በፕላስቲክ ጠርሙስ እና ኤሌክትሮክስ ተረፈ ምርት መልሶ መጠቀምና ኡደት ማድረግ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶችን ትምህርታዊ ጉብኝት አካሂዷል። በጉብኝቱ ላይም የኤጀንሲው አመራሮችን ጨምሮ የክ/ከተማ ፅዳት አሰተዳደር ፅ/ቤት ኃላፊዎች አስተባባሪዎች እና ቡድን መሪዎች የተገኙ ሲሆን አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኙትን ኢኬቲ ፕላስቲክ ውጤቶች እና ሄፍሊ የኤሌክትሮኒክስ ተረፈ ምርት መልሶ መጠቀምና ኡደት ማድረግ ድርጅቶችን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አሰተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኻኝ ዴሲሳ ደረቅ ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም ዘርፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ጠቁመው ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በተያዘው በጀት ዓመት 3 ወራት ብቻ ቆሻሻን ወደ ሀብት በመቀየር ከ515 ሚሊዮን ብር በላይ በዘርፉ የተሰማሩ ማህበራት ገቢ ማገኝት መቻላቸውን ተናግረዋል። አቶ ገዛኻኝ አክለውም ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ በመያዝና ወደ ሀብት በመቀየር የከተማዋን ፅዳት ከመጠበቅ ጎን ለጎን በዘርፉ ለበርካታ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል በመፍጠር ቆሻሻ ሀብት መሆኑን አብራርተዋል በዚህም የከተማዋ ነዋሪ ደረቅ ቆሻሻ በአግባቡ ከያዝነው የጤና ጠንቅ ሳይሆን የማያልቅ የገቢ ምንጭና ሀብት መሆኑን ተገንዝቦ በተለይ ከምንጩ በአይነት መለየት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት ዋና ዳይሬክተሩ አሳስበዋል የጉብኝቱ ዋና ዓላማም በፕላስቲክ ጠርሙስ እና ኤሌክትሮኒክስ ተረፈ ምርት መልሶ መጠቀምና ኡደት ማድረግ ዘርፍ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው በማስቻል ዘርፉን የበለጠ ለማሳደግና ተነሳሽነትን ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ተገልፅዋል። የኢኬቲ ም/ ስራ አስኪያጅ አቶ ዳንኤል በበኩላቸው በደረቅ ቆሻሻ መልሶ መጠቀም ዘርፍ ከተሰማሩ ማህበራት በመሰብሰብ ወደ መልሶ መጠቀምና ኡደት ማድረግ ላይ በማዋል ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ በማቅረብ ብዙ ስራዎች እየተሰራ መሆኑን ለተሳታፊዎቹ አስረድተዋል። ያለንን የገበያ ፍላጎትና የማሽን አቅም ያህል ግብአቱን እያገኝን አይደለም ያሉት ም/ ስራ አስኪያጁ ከሚመለከተው ዘርፍ ጋር ያለማንም ጣልቃ ገብነት /ደላላ/ በቀጥታ ተገናኝተን ለመስራት አመቺ ሁኔታ ቢፈጠር ሁላችንንም የሚጠቅም ሀብት ነው ብለዋል። ጎብኝዎቹ በበኩላቸው ቆሻሻ ሀብት መሆኑኑን በተግባር መመልከታቸው ልምድ እንደቀሰሙ ገልፀው ይህን ጉብኝት ላዘጋጀው ለኤጀንሲው ምስጋና አቅርበዋል። ታህሳስ 7/ 2018 ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

ማንነትን በመቀያየርና የተለያየ ስም በመጠቀም በሁለት ቦታዎች ለመገልግል የሞከረች ግለሰብ በቁጥጥር ስረ መዋሏን የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ። እንደ ኤጀንሲ ገለጻ ማንነትን በመቀያየር እና የተለያየ ስም በመጠቀም በሁለት የተለያዩ ቦታዎች መታወቂያ ለማውጣት ጥረት ያደረገች የውጭ ሀገር ዜግነት ያላት ግለሠብ በቁጥጥር ስር ውላ ጉዳዩ በህግ እየተጣራ እንደሚገኝ አመልክቷል። ‎ግለሰቧ በአ/ከ/ክ/ከ ወረዳ 6 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ቅጽ ላይ ስም አማረች ያለው ሰመረ በሚል ስም ተመዘገበች ሲሆን በሌላ በኩል በኮ/ቀ/ክ/ከ ወረዳ 9 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት በድጅታል መታወቂያ ምዝገባ ላይ ታደለች አሰፋ በርሔ በሚል መጠሪያ ስም ተመዝግባ ተገኝታለች ብሏል፡፡ ‎አሜሪካዊ ዜግነት ያለት ይህች ግለሰብ መታወቂያ ለማውጣት በመጣችበት ሰዓት በህግ ቁጥጥር ስር እንድትውል መደረጉን የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤትን በመጥቀስ ኤጀንሲው አስታውቋል፡፡ ኤጀንሲው ከዚህ ጋር አያይዞም ህገወጥነትን ለመከላከል በቁርጠኝት እየሰራን መሆኑን ገልጾ ህብረተሰቡ ከጎኑ በመቆም እና ማንኛውንም ህገ ወጥ እንቅስቃሴ ሲመለከት ጥቆማ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪውን አስተላልፋል፡፡ ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ በኤጀንሲው ነጻ የስልክ መስመር 7533 ይደውሉ። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ከፈረንሳይ በኮሎኔል ኢማኑኤል ዱካር የተመሩ ልኡካን ቡድን ጋር በጋራ መስራት በሚቻልበት ዙሪያ ላይ ውይይት ተካሄደ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አህመድ መሐመድ የልዑካን ቡድኑ በተለይም ከኮሚሽኑ ጋር በጋራና በትብብር ለመስራት ላሳዩት ቀና ትብብር አመሰግነው ይህም ትብብር በመዲናችንን የቅድመ አደጋ መከላከል ለማጠናከርና የስጋት ተጋላጭነት ለመቀነስና ለመቋቋም ለሚከናወኑ ስራዎች ምንቋ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል። የፈረሳይ የEURE ዲፓርትመንት ኮሎሬል ኢማኑኤል ዱካር በበኩላቸው አንደገለፁት በአደጋ ምላሽ፣ አደጋ ቅነሳ ፣ ቴክኖሎጂ በማዘመን ፣ በአቅም ግንባታ ስልጠና እና በአብሮነት ለመስራት የሚያስችል የጋራ ልምድ ልውውጥ በማድረግ በትብብር እንደሚሰሩ ተናግረዋል። እንዲሁም የልኡካን ቡድኑ አባል የሆኑት ኮሎሬል ባልዴን ሌፎት ከVAL D'ois ዲፓርትመንት እንደገለጹት አደጋዎችን የመከላከልና የማስተዳደር፣በአደጋ ስጋት ቅነሳ፣ በአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ተናግረዋል። የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የየዘርፋ አመራሮች በውይይቱ ላይ በመሳተፍ ኮሚሽኑ አሁን በጀመራቸው የከተማዋ ኢኒሸቲቮችና እየተከናወኑ ባሉ የአደጋ የመከላከል፣ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ፣ ቴክኖሎጂን የማዘመን ስራዎች ላይ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የአስቸኳይ ጊዜ አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል ስራ ምን እንደሚመስል የኮሚሽኑ ተሞክሮዎችን አቅርበዋል። በመጨረሻም ልዑካን ቡዱን የኮሚሽኑን #939 የመረጃ ማዕከልን እንዲሁም በእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር በአራዳ ቅርጫፍ የአምቡላንስ ስምሪትን፣ የፋየር መኪናዎችን፣ የተለያዩ ማሺነሪዎችን፣ የአደጋ ፈጣን ምላሽ የስታንዳርድ አፈጻጸሞችን በጉብኝት በርካታ ልምዶች ማየት ችለዋል። የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን Fire and Disaster Risk Management Commission ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager