ru
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Открыть в Telegram
1 474
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-2130 дней
Архив постов
መንግሥት የኢትዮጵያን ታላቅነት ለመመለስ እያደረገ ያለውን ጥረት ከማድነቅ ባለፈ አይቀሬዉን የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ በጋራ እንሠራለን" የዉይይቱ ተሳታፊዎች በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሐሳብ ህዝባዊ ውይይት ተካሔዷል። በውይይት መድረኩ የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ፣ የብሄራዊ መረጃ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታጅር ገ/እግዚአብሔር፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ሃላፊ አቶ ጀማሉ ጀንበሩ እንዲሁም ሌሎች የክፍለ ከተማ አመራሮችና የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል:: መድረኩን የመሩት የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ በጠራ ሃሳብ እና እይታ የሚመራው የመደመር መንግሥት የበለፀገች፣የምትከበር፣ የምትፈራ- ጠንካራ ህብረብሄራዊት ሐገር ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ እየሰራ ይገኛል ብለዋል:: የብሄራዊ መረጃ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታጅር ገ/እግዚአብሔር በበኩላቸው ህዝቡ በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ተሳታፊ መሆኑና በልማት ስራዎች ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርግ ህዝባዊነትን የተላበሰ ሀገር ወዳድ ትዉልድ ነዉ ሲሉም ገልፀዋል። የእለቱን የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ሃላፊ አቶ ጀማሉ ጀንበሩ መንግሥት አገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል፣ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ ያከናወናቸውን ተግባራት ከነባራዊ ተጨባጭ እዉነታዎች ጋር በማዛመድ አቅርበዋል መንግሥት የኢትዮጵያን ታላቅነት ለመመለስ እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው ከመንግስት ጎን በመሰለፍ የማይቀረውን ብልፅግና እናረጋግጣለን ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጽያን የማንሰራራት ጉዞ እና የመዲናዋን ፈጣን እድገት ለማስቀጠል ቅንጅታዊ ስራዉ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በዛሬዉ የዉይይት መድረኩ ማረጋገጥ ተችሏል። በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ "የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ቱሪፋቶች!" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የህዝብ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በመደመር እሳቤ ሀገርን ወደ ተምሳሌት ለመቀየር የተሰራበት ሂደት፣ አርቆ በማሰብ የመፈፀም ብቃት እና በመስራት ሀገርን በኢኮኖሚ ሉዋላዊነቷ እንዲረጋገጥ የተሰራበት ሂደት እንዲሁም ሌሎች ጉዳዮች በዉይይቱ ተነስተዋል። በተለይም በትምህርት፣ በጤና፣ በከተማ ግብርና፣ በስራ እድል ፈጠራ፤ በሰው ተኮር ተግባር፣ በሌማት ቱሩፋት፣ በበጎ ተግባራት፣ በትራንስፓርት አገልግሎትና በመልካም አስተዳደር የተሰሩ ስራዎች ላይ ሰፊና ጥልቅ ዉይይት የተደረገባቸዉ ናቸዉ። በ ሃገር አቀፍም ሆነ በከተማ ደረጃ የተሠሩ ስራዎች ተጨባጭ ለዉጥ የታየባቸዉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችም የህዝብን እርካታ የሚያረጋግጡ እና ይህንኑ ስኬት ይበልጥ የሚያስቀጥሉ መሆናቸዉ ተነስቷል። ወደፊትም ዉስንነቶችን በጋራ በማረም የኢትዮጽያን የማንሰራራት ጉዞ እና የመዲናዋን ፈጣን እድገት ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ ስራዉ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በመድረኩ ማረጋገጥ ተችሏል። በውይይቱ የባህልና ስፓርት ሚኒስትር ወ/ሮ ሻዊት ሻንካ፣ የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ አስተባባሪ ሚኒስትር አቶ መለስ አለሙ፣ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት ም/ኃላፊ ና የፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አለምፀሀይ ሽፈራው ከነዋሪዎች ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የለሚ ኩራ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚልከንፋስ ስልክ ላፍቶ ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተደርጓል ውይይቱ ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረኮች ላይ ከነዋሪዎቻች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የተሰጠበት እና በቀሪ ስራዎች ላይም ጥልቅ ውይይት የተደረገበት ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ባለፉት 7 የለውጥ ዓመታት መንግስት በፈተናው ውስጥ ሆኖ ያስመዘገባቸው ስኬቶች የዜጎችን ህይወት ትርጉም ባለው መልኩ የቀየሩና ተጠቃሚነትም ያረጋገጡ መሆናቸውን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ያላት አቅም ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት የባንኩ ገዢ አሁን በተጀመረው የመደመር መንግስት አቅጣጫ ሀገሪቱ የዓለም የልማት ምሳሌ መሆን የምትችልበት ጊዜ እሩቅ አደይደለም ብለዋል። አያይዘውም መንግስትና ህዝብ በትብብር በመስራታቸው የተመዘገቡ ውጤቶችን የበለጠ አጠናከሮ ማስቀጠልና የቀጣይ እቅዶች ላይ ነዋሪውን አሳትፎ ማከናወን እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢፊዲሪ የሰላም ሚኒስትር ሚኒስትር አቶ መሐመድ እድሪስ የዴሞክራሲያዊ መንግስት ከህዝብ ጋር ያለው ቁርኝት የጎላ መሆኑን ጠቅሰው የዛሬውም ውይይት የዚህ አካልና ለህዝብ ጥያቄዎች ተጨባጭ መልሶችን ለመስጠት እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። በተለይም በባለፉት ጊዜያት በህዝቦች መካከል አንድነት እንዳይኖር በተሰሩ የጥላቻ ትርክቶች አሁን እያገጠመ ላለው ፈተና መነሻ መሆናቸውን ጠቅሰው መንግስት ሁሌም ለሰላም ያለው ቁርጠኝነት ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል። በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ከውሃና ከመብራት አኳያ ችግሩ የማመንጨትና የአቅርቦት ሳይሆን የሚታዩ የመሰረተ ልማት ውስንነቶች መሆናቸውን ጠቅሰው ይህንንም ለማስተካከል የተጀመሩ ስራዎች እንዳሉ ገልፀዋል። የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በአዲስ አበባ በ5ቱም መግቢያ በሮች ሸማቹን ከአምራቹ የሚያገናኙ የደላላን ሰንሰለት ያሳጠሩ ሁሉንም የምርት አይነቶች የያዙ የገበያ ማዕከላት በመኖራቸው የዋጋ ንረትን ለመከላከል ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑንም ገልፀዋል። በመድረኩ ክቡራን ሚኒስትሮች፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ ባለሀብቶችና ምሁራንን ጨምሮ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

"የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚልከንፋስ ስልክ ላፍቶ ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተደርጓል ውይይቱ ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረኮች ላይ ከነዋሪዎቻች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የተሰጠበት እና በቀሪ ስራዎች ላይም ጥልቅ ውይይት የተደረገበት ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ባለፉት 7 የለውጥ ዓመታት መንግስት በፈተናው ውስጥ ሆኖ ያስመዘገባቸው ስኬቶች የዜጎችን ህይወት ትርጉም ባለው መልኩ የቀየሩና ተጠቃሚነትም ያረጋገጡ መሆናቸውን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ያላት አቅም ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት የባንኩ ገዢ አሁን በተጀመረው የመደመር መንግስት አቅጣጫ ሀገሪቱ የዓለም የልማት ምሳሌ መሆን የምትችልበት ጊዜ እሩቅ አደይደለም ብለዋል። አያይዘውም መንግስትና ህዝብ በትብብር በመስራታቸው የተመዘገቡ ውጤቶችን የበለጠ አጠናከሮ ማስቀጠልና የቀጣይ እቅዶች ላይ ነዋሪውን አሳትፎ ማከናወን እንደሚገባ ተናግረዋል። የኢፊዲሪ የሰላም ሚኒስትር ሚኒስትር አቶ መሐመድ እድሪስ የዴሞክራሲያዊ መንግስት ከህዝብ ጋር ያለው ቁርኝት የጎላ መሆኑን ጠቅሰው የዛሬውም ውይይት የዚህ አካልና ለህዝብ ጥያቄዎች ተጨባጭ መልሶችን ለመስጠት እድል የሚሰጥ ነው ብለዋል። በተለይም በባለፉት ጊዜያት በህዝቦች መካከል አንድነት እንዳይኖር በተሰሩ የጥላቻ ትርክቶች አሁን እያገጠመ ላለው ፈተና መነሻ መሆናቸውን ጠቅሰው መንግስት ሁሌም ለሰላም ያለው ቁርጠኝነት ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል። በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ከውሃና ከመብራት አኳያ ችግሩ የማመንጨትና የአቅርቦት ሳይሆን የሚታዩ የመሰረተ ልማት ውስንነቶች መሆናቸውን ጠቅሰው ይህንንም ለማስተካከል የተጀመሩ ስራዎች እንዳሉ ገልፀዋል። የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በአዲስ አበባ በ5ቱም መግቢያ በሮች ሸማቹን ከአምራቹ የሚያገናኙ የደላላን ሰንሰለት ያሳጠሩ ሁሉንም የምርት አይነቶች የያዙ የገበያ ማዕከላት በመኖራቸው የዋጋ ንረትን ለመከላከል ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑንም ገልፀዋል። በመድረኩ ክቡራን ሚኒስትሮች፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ ባለሀብቶችና ምሁራንን ጨምሮ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች!" በሚል ርዕስ የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ከፌዴራልና ከአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አካሄዱ። "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች " በሚል ርዕስ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ከሃይማኖት አባቶች፣ ከአገር ሽማግሌዎች፣ ከወጣቶችና ሴቶች፣ ከንግዱ ማህበረሰብ፣ ከባለሀብቶችና ምሁራንን ጨምሮ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ከፌዴራልና ከአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በማህበረሰቡ የልማት እና መልካም አስተዳደር ተግባራት እንዲሁም በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙርያ ውይይት ተካሂዷል። በውየፌደራል ስራና ክህሎት ሚንስትር ሚኒስቴር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል መንግስት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት ዘርፈ ብዙ ስኬታማ ስራዎችን መስራት መቻሉንና ውይይቱ በዋናነት ያስፈለገው ማህበረሰቡ ሲያነሳቸው የቆዩ ጥያቄዎች በተሰጡ ምላሾች ፣ ህዝቡ መንግስት እየሰራ የሚገኘውን ተግባራት በምን መልኩ እንደሚገነዘብ በማወቅ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች በማድመጥ ጥያቄዎቹ የሚፈቱባቸዉ መንገዶች ላይ በጋራ ለመወያየት ያለመ መሆኑን በማንሳት ውይይቱ የበለፀገች ኢትዮጵያን በጠንካራ መሰረት ላይ ለመጣል ተጨማሪ አቅምን የሚፈጥር መሆኑን ገልፀዋል ። የፌዴራል ውሃና ኢነርጂ ሚንስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በበኩላቸው ጉባ ሀገሪቱን ወደ ብልፅግና ማሻገር የሚቻልባቸው ዘመን ተሻጋሪ ትልልቅ ብስራቶች የተሰሙበት መሆኑን በማንሳት መንግስት ከለውጡ ማግስት እንደ ሀገር የነበሩ ስብራቶችን በመጠገን ስኬቶችን ማስመዝገብ መቻሉን በማንሳት አሁንም ቀሪ ስራዎች መኖራቸውንና ከመድረኩ የተነሱ ጥያቄዎችን በየደረጃዉ ለመፍታት የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል። መንግስት ታች ማህበረሰቡ ድረስ ወርዶ ህዝቡን ማወያየቱ ለህዝቡ ያለውን ክብር ያሳየና ቃሉን በተግባር ለመፈፀሙ ማረጋገጫ መሆኑን የገለፁት የውይይቱ ተሳታፊዎች ከለውጡ ማግስት የተከናወኑ በርካታ ስራዎች መንግስት ትክክለኛ የህዝብ ውግንናን ያሳየበት፣ በዲፕሎማሲው ፣ በሰው ተኮር ስራዎች ፣ በቴክኖሎጂ ፣ በመሰረተ ልማት በሌሎች በርካታ ተግባራት ስኬታማ ስራዎች መሰራታቸውን በማንሳት የተሰሩ ስራዎችም በህዝቡ ዘንድ የወል ትርክትን ማስረፅ የቻሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የኢንደስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ በመድረኩ የተነሱ ሀሳቦች ለከተማ አስተዳደሩ ተጨማሪ አቅምን የሚፈጥሩ መሆናቸውን ጠቅሰው ከተማ አስተዳዱሩ መንግስት የቤት አቅርቦት ችግርን ለመፍታት ፣ የጤናውን ዘርፍ ለማሻሻል ፣ የኢንዱስትሪውን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ በመጥቀስ ከመድረኩ የተነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት የሚሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

በወንዝ ዳርቻ የመብራት መሰረተ-ልማት የስራ አፈፃፀም ላይ የመስክ ምልከታ ተደረገ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን የወንዝ ዳርቻ ልማትን ተከትሎ በመከናወን ላይ ያለውን የመብራት መሰረተ-ልማት ስራ ያለበትን አፈፃፀም ለመገምገም የሚያስችል የመስክ ላይ ምልከታ ተደረገ፡፡ በሳይት ምልከታው ላይ የባለስልጣኑ የግንባታ ዘርፍ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የስራ ተቋራጭ እና አማካሪ ተሳትፈዋል፡፡ ከቁስቋም መቀጠያ እስከ ፒኮክ መናፈሻ ባሉ ሰባት ሳይቶች ላይ ያለውን አጠቃላይ የፕሮጀክት እንቅስቃሴና የደረሰበትን አፈፃፀም በአካል ማየት ተችሏል፡፡ በተደረገው የመስክ ምልከታ ፕሮጀክቶቹ የደረሱበትን የአፈፃፀም ደረጃ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና ቀጣይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚገቡ ጉዳዮች ላይ የጋራ ግንዛቤ በመያዝና ፕሮጀክቱን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የጋራ ግብዓት መውሰድ አስችሏል፡፡ ዘመናዊ መብራት፤ ለብሩህ አዲስ አበባ! ህዳር 27/2018 ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

መንግሥታችን ሕዝብን ያዳምጣል፣ ከሕዝብ ለሚነሱ ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ይሰጣል። ዛሬ ከማለዳ አንስቶ ከነዋሪዎቻችን ጋር ሰፊ ውይይቶችን አካሂደናል። ውይይቶቹ በመዲናችን አዲስ አበባ በሚገኙ በሁሉም ክፍለ-ከተሞች በስፋት ተካሂደዋል። የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ ባለሀብቶችና ምሁራንን ጨምሮ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ተሳታፊ ሆነዋል። ከዚህ ቀደም በተለያዩ የሕዝብ መድረኮች ላይ ከነዋሪዎቻችን ለተነሱ ጥያቄዎች፣ ቅሬታዎች እና አስተያየቶች በተግባር የተሰጡ ምላሾች፣ እንዲሁም ቀሪ ሥራዎችን አስመልክቶ በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል። የከተማ አስተዳደራችን ከፍተኛ አመራሮችና ሚኒስትሮች መድረኮቹን በመምራት ከህዝብ የተነሱ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፤ የቤት ስራም ወስደዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በከተማችን በተለያዩ የልማት ሥራዎች አስደናቂ ስኬቶች የተመዘገቡት መንግሥትና ሕዝብ አንድ ሆነው በመቀናጀትና በመናበብ ሊፈጽሟቸው በመቻላቸው ነው። ዛሬም በመንግሥትና በሕዝብ ትብብር የተሰሩ በርካታ ሥራዎችን እና የተመዘገቡ ውጤቶችን ይበልጥ ለማጠናከር፣ እንዲሁም የሕዝብን ተሳትፎ ይበልጥ በሚያረጋግጡ ቀጣይ የጋራ ዕቅዶች ላይ እንደ ወትሮው ከነዋሪዎቻችን ጠቃሚ ግብዓት ያገኘንበት ፍሬያማ የውይይት መድረክ ነበር። ውድ ነዋሪዎቻችን፣ ለሰጣችሁን ገንቢ አስተያየት፣ ለነበራችሁ ከፍተኛ ተሳትፎ፣ ለሰጣችሁን ውድ ጊዜ በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም ከልብ አመሰግናለሁ። በቀጣይም ይበልጥ ተቀራርበን መሥራታችንን እንቀጥላለን። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

‎በነዋሪዎቿ ተሳትፎ ጽዱ የሆነች ውብ ከተማ አዲስ አበባ! ‎ ‎ብሎክን ማዕከል ያደረገ ሳምንታዊ የጽዳት ንቅናቄ በወረዳ 4 አስተዳደር ተካሄደ። ‎ ‎በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ብሎክን ማዕከል ያደረገ የበጋ ወራት የአንድ ማዕከል ሳምንታዊ የጽዳት ንቅናቄ በወረዳ 4 ተካሄደ። ‎ ‎በንቅናቄው የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ታከለ ደሲሳ፣የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማናዬ ጫኔ፣የጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በየነ ቱሉ፣የወረዳ 4 አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኤፍሬም መልካ፣የኃይማኖት አባቶች፣የሀገር ሽማግሌዎች፣የጸጥታ አካላትና የወረዳው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል። ‎ ‎የከተማ አስተዳደሩ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ታከለ ደሲሳ እንደገለጹት ቆሻሻ ሀብት መሆኑን በመረዳት በአግባቡ በአይነት ለይቶ መያዝ እንደሚገባና ለሽርክና ማህበራት ማስረከብ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው መዲናችን አዲስ አበባ ከተማ እንደስሟ ውብ፣ጽዱና ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ እየተከናወነ ባለው ተግባር ሁሉም አከባቢውን ዘወትር በማጽዳትና በማስዋብ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል። ‎ ‎የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማናዬ ጫኔ በበኩላቸው ሁሉም አከባቢውን ለኑሮ ምቹና ተስማሚ ለማድረግ በሚከናወነው ንቅናቄ በንቃት መሳተፍ እንደሚገባና ሞዴል መንደር መፍጠር እንደሚያስፈልግ ጠቁመው አከባቢን በጋራ ማጽዳት እንድነትንና አብሮነትን እንደሚያጎለብት ተናግረዋል። ‎ ‎የክፍለ ከተማው ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በየነ ቱሉ በመርሃ ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ እንደገለጹት ጽዳት የስልጣኔ መገለጫ መሆኑን በመረዳት ቆሻሻን በአግባቡ መያዝና ማስወገድ እንደሚገባና በህገ ወጥ መንገድ ቆሻሻ በሚያስወግዱ አካላት በወጣው ደንብ መሠረት እርምጃ መውሰድ ይገባል ብለዋል። ህዳር 27/2018 ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager