ru
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Открыть в Telegram
1 474
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-2130 дней
Архив постов
ባለስልጣኑ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት 3,511 የመንገድ መብራት ፖሎች ጥገና አከናወነ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን በ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በተለያዩ ምክንያቶች ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሳይሰጡ የቆዩ በቁጥር 3,511 የመንገድ መብራት ፖሎችን በመጠገን እንዲበሩ በማድረግ ከዕቅዱ በላይ አከናውኗል፡፡ ባለስልጣኑ ባከናወነው ሰፊ የመንገድ መብራት ጥገና ስራ ህብረተሰቡ ለረጅም ጊዜ ጥያቄ ሲያነሳባቸው የነበሩ መንገዶችን በጥናት በመለየት ማብራት ችሏል፡፡ በመንገድ መብራቶቹ ላይ ያሉ ብልሽቶችንና ያልተሟሉ መሰረተ-ልማቶችን በመለየትና በመፍታት ተገቢውን የመንገድ መብራት አገልግሎት እንዲሰጡ ከተደረጉ በርካታ መንገዶች ውስጥ ከዋሺንግተን አደባባይ- ቡልጋሪያ፣ ከአራራት- ኮተቤ-ካራ ፣ ከመገናኛ ደራርቱ ህንፃ- ሃያ አራት፣ ከመንዲዳ- የሺ ደበሌ፣ ከሽሮ ሜዳ -ቁስቋም፣ ከአቡነ ጴጥሮስ- ፓስተር - ዊንጌት-አስኮ-ሳንሱሲ፣ ከራስ ደስታ -ቀጨኔና ሌሎችም መንገዶች ተጠቃሾች ናቸው ፡፡ በተጨማሪም ባለስልጣኑ በሩብ ዓመቱ 12 የቦርድ ጥገና፣ 254 ሶዲየም ላምፖችን መቀየር፣ 284 ፖሎች ጥገና ፣ 3,750 ፖሎችን አሁናዊ ሁኔታ በፍተሻ መለየትና ማረጋገጥ እንዲሁም በአንደኛና ሁለተኛ ዙር የኮሪደር ልማት የለሙ የመንገድ መብራትን አሁናዊ ሁኔታ ለማረጋገጥ በየዕለቱ የምሽት ቅኝት ስራዎች ለማከናወን አቅዶ አብዛኛውን መፈፀም ችሏል ፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

አዲስ አበባን ውብ፣ ጽዱና ለኑሮ ምቹ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ሳር ቤት - ጀርመን አደባባይ - ጋርመንት ፉሪ የኮሪደር ልማት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ See less

ብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል ኃላፊ አደም ፍራህ ስለ ሳር ቤት-ጀርመን አደባባይ-ጋርመንት እና ፉሪ አካባቢ የኮሪደር ልማት ሥራ የሰጡት ማብራሪያ… See more

ከሳርቤት - ጀርመን አደባባይ- ጋርመነት ፉሪ የሚዘልቀው የኮሪደር ልማት ምን አካቷል? ከሳርቤት - ጀርመን አደባባይ- ጋርመነት ፉሪ የሚዘልቀው የኮሪደር ልማት ምን አካቷል? 👉 በሁለተኛ ዙር ከተጀመረው 6ኛዉና ከካዛንቺስ ኮሪደር ቀጥሎ በዲናዋ ሁለተኛው ረጅሙ እና ሰፋ ያለ አካባቢ የሚሸፍን ነዉ 👉 ከ589 ሄክታር በላይ ቦታ የለማበት ነው 👉 እስከ 60 ሜትር የሚሰፋ 16.5 ኪ.ሜ አስፓልት መንገድ ( በተጨማሪ 3 .5 ኪ. ሜ የውስጥ ለውስጥ መንገድ) አለው ፣ 👉 33 ኪ.ሜ የእግረኛ መንገድ ፣ 👉 13.3 ኪ.ሜ የሳይክል መንገድ ፣ 👉 21 የተለያዩ ፕላዛዎች ፣ 👉ክረምት ከበጋ ፣ በቀን እና በምሽት አገልግሎት የሚሰጡ 20 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ 👉 20 የልጆች መጫወቻ ቦታዎች ፣ 👉 5.2 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ፣ 👉 20 የመኪና ማቆሚያ ቦታና ተርሚናሎች ፣ 1 የመኪና ቻርጂንግ ስቴሽን ፣ 👉 በግለሰቦች እና በመንግስት የተገነቡ 1,107 የንግድ ቤቶች ፣ 👉 50.5 ሄክታር ስፋት ያላቸዉ አረንጓዴ ቦታዎች ፣ 👉 40 የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች ፣ 👉 38 የታክሲና አውቶቡስ ቤይ ፣ 👉 13 ካፌዎች እና 1 ሬስቶራንት እንዲሁም 👉 ከ 1 ሄክታር በላይ የነርሰሪ ቦታን በዉስጡ አካትቶ ይዟል ጥቅምት 15/ 2018 ዓ. ም #አዲስሚዲያኔትዎርክ #PMOEthiopia #Ethiopia #addisababa

ዛሬም የረዳን ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን ! ከሳርቤት - ጀርመን አደባባይ- ጋርመነት ፉሪ የሚዘልቀውን የኮሪደር ልማት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባላት በተገኙበት መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ። ሕዝባችንን በታማኝነት፣ በቅንነት ለማገልገል የገባነውን ቃል ቆጥረን እየተገበርን እንገኛለን። የተሰሩት መሰረተ ልማቶች ከተማችንን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት፣ ለዜጎቻችን ሰፊ የስራ ዕድል የፈጠረ እንዲሁም ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ መሰረታዊ የሆነ ለዉጥ ማምጣት በሚያስችል መልኩ የተሰራ ነው። በልማቱ ከመሬት በላይ ከሚታየው እኩል ከመሬት በታች ጭምር የተሰሩ በርካታ ስራዎች የከተማችንን አገልግሎት የሚያሳልጥ፣ በዘላቂነት ስማርት ሲቲ ለማድረግ የሰነቅነዉን ራዕይ ለማሳካት የሚያስችል መሰረታዊ ስራ የተሰራበት፣ ሰፊ የስራ ዕድል የተፈጠረበት ሲሆን፤ ለቱሪዝም ዘርፉ ተጨማሪ እሴት፤ የስበት ማዕከል የሆኑ ፅዳት፣ ውበት፣ አገልግሎትን ያጣመሩ ስራዎችም በስፋት ተሰርተውበታል ። ይህ የኮሪደር ልማት በሁለተኛ ዙር ከጀመርነው 6ኛዉና ከካዛንቺስ ኮሪደር ቀጥሎ በከተማችን ሁለተኛው ረጅሙ እና ሰፋ ያለ አካባቢ የሚሸፍነው ሲሆን ከ589 ሄክታር በላይ ቦታ የለማበት ነው። • እስከ 60 ሜትር የሚሰፋ 16.5 ኪ.ሜ አስፓልት መንገድ ( በተጨማሪ 3 .5 ኪ. ሜ የውስጥ ለውስጥ መንገድ) አለው ፣ • 33 ኪ.ሜ የእግረኛ መንገድ ፣ • 13.3 ኪ.ሜ የሳይክል መንገድ ፣ • 21 የተለያዩ ፕላዛዎች ፣ • ክረምት ከበጋ ፣ በቀን እና በምሽት አገልግሎት የሚሰጡ 20 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ • 20 የልጆች መጫወቻ ቦታዎች ፣ • 5.2 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ፣ • 20 የመኪና ማቆሚያ ቦታና ተርሚናሎች ፣ 1 የመኪና ቻርጂንግ ስቴሽን ፣ • በግለሰቦች እና በመንግስት የተገነቡ 1,107 የንግድ ቤቶች ፣ • 50.5 ሄክታር ስፋት ያላቸዉ አረንጓዴ ቦታዎች ፣ • 40 የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች ፣ • 38 የታክሲና አውቶቡስ ቤይ ፣ • 13 ካፌዎች እና 1 ሬስቶራንት እንዲሁም ከ 1 ሄክታር በላይ የነርሰሪ ቦታን በዉስጡ አካትቶ ይዟል ። ይህንን ለከተማችን ተጨማሪ ድምቀት ፣ ለዜጎቻችን መጠነ ሰፊ የስራ እድል እና የእውቀት ሽግግር የፈጠረን ፣ ለነዋሪዎቿ ደግም ምቾትን ያጎናፀፈውን ግዙፍ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በታለመለት ጊዜ በጥራት እና በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ላደረጋችሁ ፣ ከመደበኛ ስራችሁ ጎን ለጎን ሌት ተቀን ለለፋችሁ በየደረጃዉ ያላችሁ የከተማችን አመራሮች፣ ባለሞያዎች፣ እንዲሁም በልማት ስራው ሁልጊዜም የዘወትር ድጋፍ እና ትብብሩ ላልተለየን የአካባቢው ነዋሪ ማህበረሰብ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ከብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን የተጠናቀቀውን የሳር ቤት-ጀርመን አደባባይ-ጋርመንት እና ፉሪ አካባቢ የኮሪደር ልማት ሥራ ጎብኝተናል። 589 ሄክታር በላይ የሚሸፍነው ከባቢ ከካዛንቺስ ቀጥሎ ሰፊው የልማት ስፍራ ሆኗል። ፕሮጀክቱ 16.5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ፣ የ3 ኪሎ ሜትር ተጨማሪ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ብሎም 33 ኪሎ ሜትር የተዘረጋ የእግረኛ መንገድ አካትቷል። የፕላዛዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ የሕፃናት መጫወቻዎች እና 5.2 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራ ተከናውኗል። የመኪና ማቆሚያዎች፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ኃይል መሙያ ስፍራዎች፣ በግል እና የመንግሥት ተቋማት የተገቡ 1107 ሱቆች በልማት ሥራው የተሠሩ ናቸው። የኮሪደር ልማቱ 50.5 ሄክታር አረንጓዴ ሥፍራ፣ የሕዝብ መጸዳጃዎች፣ 13.3 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መጋለቢያ መንገድ፣ 38 የአውቶቡስ እና ታክሲ መጫኛ-ማውረጃዎችን አካትቷል። እንደዚህ ያሉት ሀገራዊ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ሥራዎች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን ከማሳደግ ባሻገር የትራፊክ እንቅስቃሴን በማሻሻል፣ ማኅበራዊ መስተጋብርን በማጠንከር ደማቅ ለእንቅስቃሴ ምቹ እና ዘላቂነት ያላቸው የከተማ ሥፍራዎች በመፍጠር ረገድ ዐቢይ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ Together with members of the Prosperity Party Executive Committee, we visited the completed corridor development project extending from Sar Bet to German Square, the Garment Factory, and the Furi area. Covering more than 589 hectares, it stands as the second largest and widest site after Kazanchis. The project includes the construction of 16.5 km of asphalt roads, an additional 3 km of internal roads, and pedestrian walkways stretching a total of 33 km. It features plazas, sports facilities, children’s playgrounds, and 5.2 km of riverbank development. In addition, there are parking areas and terminals, an electric car charging station, and 1,107 shops built by both private and government entities. The development also encompasses 50.5 hectares of green spaces, public toilets, 13.3 km of bicycle lanes, and 38 taxi and bus bays. Our national corridor development projects like this one are playing a vital role in boosting local economic activity, improving mobility, and enhancing social interaction by creating vibrant, accessible, and sustainable urban spaces.

ከብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን የተጠናቀቀውን የሳር ቤት-ጀርመን አደባባይ-ጋርመንት እና ፉሪ አካባቢ የኮሪደር ልማት ሥራ ጎብኝተናል። 589 ሄክታር በላይ የሚሸፍነው ከባቢ ከካዛንቺስ ቀጥሎ ሰፊው የልማት ስፍራ ሆኗል። ፕሮጀክቱ 16.5 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ፣ የ3 ኪሎ ሜትር ተጨማሪ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ብሎም 33 ኪሎ ሜትር የተዘረጋ የእግረኛ መንገድ አካትቷል። የፕላዛዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ የሕፃናት መጫወቻዎች እና 5.2 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራ ተከናውኗል። የመኪና ማቆሚያዎች፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ኃይል መሙያ ስፍራዎች፣ በግል እና የመንግሥት ተቋማት የተገቡ 1107 ሱቆች በልማት ሥራው የተሠሩ ናቸው። የኮሪደር ልማቱ 50.5 ሄክታር አረንጓዴ ሥፍራ፣ የሕዝብ መጸዳጃዎች፣ 13.3 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መጋለቢያ መንገድ፣ 38 የአውቶቡስ እና ታክሲ መጫኛ-ማውረጃዎችን አካትቷል። እንደዚህ ያሉት ሀገራዊ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ሥራዎች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን ከማሳደግ ባሻገር የትራፊክ እንቅስቃሴን በማሻሻል፣ ማኅበራዊ መስተጋብርን በማጠንከር ደማቅ ለእንቅስቃሴ ምቹ እና ዘላቂነት ያላቸው የከተማ ሥፍራዎች በመፍጠር ረገድ ዐቢይ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛሉ።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ምልከታ በኮይሻ’ #EBC #ebcdotstream #PMAbiy #Ethiopia ‘የሚኒስትሮች ምክር ቤት ምልከታ በኮይሻ’…

የቦሌ ክ/ከተማ አመራሮች በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የልምድ ልውውጥና ጉብኝት አካሄዱ፡፡ ***************** ጥቅምት 14-2018ዓም የቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌትነት አይናለም፣ የአስተባባሪ ኮሚቴ አባላትን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ አስተዳደር 'አዲስን እንደ አዲስ' በሚል እየተሰራ ያለውን የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ መንደርን አስመልክቶ ጉብኝትና የልምድ ልውውጥ አድርገዋል:: የአመራር ውህደትና ቁርጠኝነትን በመላበስ 'አዲስን እንደ አዲስ' በሚል መርህ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን የገለፁት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ የቦሌ ክ/ከተማ አመራሮች ከኛ ጋ ልምድ ለመቅሰም መርጠውን በመምጣታቸው እናመሰግናለን ብለዋል:: የቦሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌትነት አይናለም፣ የአዲስ ከተማ አመራሮች ተሞክሮ ለማካፈል ላሳዩት ቀናነትና ፈቃደኝነት ምስጋና አቅርበው የተወሰዱ ልምዶችን አዳብሮ እና እሴት ጨምሮ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ስንቅ የሚሆን ስራዎችን መመልከት ችለናል ሲሉ ተናግረዋል:: በክፍለ ከተማው አዲስን እንደ አዲስ በሚል መነሻነት እየተሰሩ ካሉ የልማት ስራዎች መካከል በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ህዝቡን ያሳተፈ የአካባቢ ልማት ስርዓትን በመስራት ክፍለ ከተማውን ፅዱ፣ ውብና ማራኪ እንዲሁም ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ አመርቂ ስራ መሰራቱን የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን ኮርሜ አስረድተዋል:: የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ደመቀ ዋኘው በበኩላቸው አመራርን አቀናጅተን ህዝብን አስተባብረን 7/24 መርህን ተከትለን በመስራታችን ተጨባጭ ወደ ውጤት እያስመዘገብን እንገኛለን ሲሉ ገልጸዋል:: የቦሌ ክ/ከተማ አመራሮች አዲስ ከተማ በውጤት ጎዳና ላይ እንደሚገኝ ባደረግነው ጉብኝት አረጋግጠዋል ሲሉ ተናግረዋል:: ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የባህር በርን ጨምሮ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ስብራቶችን ለመጠገን ከባለድርሻዎች ጋር በትጋት ይሰራል - ብልፅግና ፓርቲ የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የባህር በርን ጨምሮ ቀሪ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ስብራቶችን ለመጠገን ከባለድርሻ አካላት ጋር በትጋት ይሰራል አለ። የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ እንዳሉት፤ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮችና የፓርቲ አጀንዳዎች ላይ መክሮ አቅጣጫ አስቀምጧል። የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና የማረጋገጥ ራዕይን ሰንቆ ወደ ተግባር የገባው ፓርቲው ባለፉት ዓመታት ለህዝብ ቃል የገባውን በውጤታማነት እየፈጸመ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያን ቀሪ ስብራቶች ለመጠገን ከባለድርሻ አካላት ጋር በትጋት እንደሚሰራ ተናግረው፤ ብሔራዊ ጥቅምን ማዕከል ያደረጉ የተሟላ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንደሚወጣ ገልፀዋል። ባለፉት ዓመታት በተሠሩ የልማት ስራዎች ኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ውጤት መምጣቱን ገልጸው፤ ለአብነትም ባለፈው ዓመት የ9 ነጥብ 2 በመቶ እድገት መመዝገቡን ተናግረዋል። የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር እየተረጋገጠ መሆኑን ሥራ አስፈጻሚው መገምገሙን ጠቅሰው፤ በዚህም ኢኮኖሚው ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪና ዘመናዊ አገልግሎት እየተሸጋገረ ይገኛል ብለዋል። በገቢ ማሰባሰብ፣ በወጪ ንግድ እና በተኪ ምርት አመርቂ ውጤት መመዝገቡን በማንሳት አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱ ፈጣን ብቻ ሳይሆን አካታች፣ ጥራት ያለውና የህዝቡን ኑሮ በተጨባጭ እያሻሻለ መሆኑን ጠቅሰዋል። የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን በተጀመሩ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸው፤ በሰው ተኮር ስራዎችም በርካታ አቅመ ደካማ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። በቀጣይም ተረጂነትን የማስወገድ፣ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለማሟላት በቂ ፈንድ የመያዝ እንዲሁም ብሔራዊ የመጠባበቂያ ክምችትን በራስ አቅም የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የሰላም እና የፖለቲካ ጉዳዮችን መገምገሙን በማንሳት ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የበኩሉን ሚና ለመወጣት ቁርጠኛ መሆኑን ማረጋገጡን ጠቅሰዋል። መጪው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተአማኒ፣ ግልጽና አሳታፊ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ ፓርቲው የድርሻውን እንደሚወጣም ገልጸዋል። ውስን የሰላምና ፀጥታ ችግር የነበረባቸውን አካባቢዎችን ለማረጋጋት መንግስትና ህዝብ በጋራ በሰሩት ስራ ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። የፖለቲካ ጥያቄ ያለው ማንኛውም አካል ጥያቄውን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ምህዳር መፈጠሩን ገልጸው፤ ፓርቲውና የሚመራው መንግስት ሁልጊዜም በራቸው ለሰላም ክፍት ነው ብለዋል። በስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ስብሰባ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድረግ የተቀመጠው አቅጣጫ ወደ ተጨባጭ ተግባር መግባቱን ተገምግሟል ነው ያሉት። በዚህም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የማስፋትና የዲጂታላይዜሽን ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን አመልክተው፤ እስካሁንም 16 ማዕከላት ተገንብተው አገልግሎት እየሠጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። በመሶብ ማዕከላት የህዝቡ እርካታ ወደ 95 መቶ መድረሱን ገልጸው፤ ማዕከላቱን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ 100 ለማድረስ እንዲሰራ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አቅጣጫ ማስቀመጡን ተናግረዋል። ብልፅግና ፓርቲ ጠንካራ መንግስትና ሀገር ለመገንባት የያዘውን ግብ ለማሳካት የአመራርና አባላቱን አቅም የሚያጎለብቱ የተለያዩ ተግባራትን እንዳከናወነ መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል። አመራርና አባላቱ በተሠጣቸው ተልዕኮ ልክ በየደረጃው የመገምገም ስራ ሲሠራ መቆየቱን አስታውሰው፤ በምዘናው መሠረት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡት እውቅና መሰጠቱን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የተሰጣቸውን ሀገራዊና የፓርቲ ተልዕኮ በአግባቡ ባልተወጡ አመራሮች ላይ የተለያዩ ርምጃዎችን መወሰዱን ተናግረው፤ ፓርቲው ህዝብና ሀገርን ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራችውን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager