1 474
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-2130 дней
Архив постов
የመንግስት የጥሬ ገንዘብ አስተዳደርና አያያዝ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
የአዲስ አበባ ከተማ የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ለፅ/ቤቱ ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች የመንግስት የጥሬ ገንዘብ አስተዳደርና አያያዝ ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል።
ስልጠናው ለፅቤቱ ሰራተኞች መሰጠቱ በፋይናንስ ስርዓት ላይ ያላቸዉን እዉቀት ከማስፋት ባለፈ በቀጣይ የስራ ሂደት ላይ የራሱ የሆነ አቅም የሚፈጥር እንደሆነ በመድረኩ ላይ ተገልጿል።
አክስልጠናዉ በተለይም የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ከማድረግ አንፃር ፋይዳዉ የጎላ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን አንዳንድ በፋይናንስ ስርዓት ላይ የሚነሱ ክፍተቶችን በመለየትና በመፍታትና እንዲሁም ከስልጠናው የሚገኘዉን እዉቀት ወደ ተግባር ላይ በማዋል የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንዳለውም ተመላክቷል።
ለስራ አስኪያጅ ፅ/ ቤት ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች እየተሰጠ ያለው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዉ የመንግስት የገንዘብ ክፍያ፣የመንግስት የክፍያ መርሆች፣የበጀት አደረጃጀት ስርዓት ምንነት፣የተከፋይ ሂሳብ ምንነት፣ የሂሳብ ምዝገባ መነሻ፣የፋይናንስ ሀላፊነት ፣የሂሳብ ስራ ዑደት፣የሂሳብ አወቃቀር ስርዓት፣የሂሳብ አያያዝ ዘዴ፣የሂሳብ ሪፖርት አዘገጃጀት፣የኘሮግራም ምንነት እንዲሁም በሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ስልጠና ተሰጥቷል።
በመጨረሻም ከሰልጣኞች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ስልጠናዉ ተጠናቋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ቀጣይ የመንግስት ቁልፍ አቅጣጫዎች ውስጥ፡ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ማድረስ
በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተብለው ከተቀመጡ ቁልፍ ተግባራት አንዱ የሆነው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ትግበራ አሁን ላይ 28 ሚሊዮን ዜጎችን በማካተት በከፍተኛ አገራዊ ንቅናቄ እየተሠራ ነው።
በዚህም መሰረት በያዝነው ዓመት በመላው ሀገሪቱ ተደራሽነትን በማስፋት እና የብሔራዊ መታውቂያ ስርዓቱን በማጎልበት 40 ሚሊዮን ዜጎችን ለመመዝገብ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ኢትዮዽያ ከሁለት ዓመት በኋላ የሚካሄደውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን እንድታስተናግድ ብራዚል ውስጥ እየተካሄደ ባለው የዘንድሮ ስብሰባ ላይ ተመረጠች።
በአውሮፓውያኑ 2027 የሚደረገውን "ኮፕ32" ኢትዮጵያ እንድታስተናግድ የተመረጠችው ናይጄሪያን በመብለጥ ነው።
ኢትዮዽያ ባለፉት 6 ዓመታት በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ አመራር የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ ከ48 ቢሊዮን በላይ አገር በቀል ችግኞችን በመላዉ አገሪቱ የተከለች ሲሆን በተጨማሪም በወንዝ ዳርቻዎች ልማት ሰፋፊ የአካባቢ ጥበቃ ስራ እየከወነች እና ግዙፍ ታዳሽ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎችን እየገነባች ትገኛለች ።
ኢትዮዽያ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት ግንባታ በሰራቻቸዉ ሰፊ ስራዎች ለአብነት የምትጠቀስ እና ልምድ የሚቀሰምባት አገር ሆናለች ።
#COP32 ን ማስተናገድ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ልዑካንን ወደ አዲስ አበባ የሚስብ ሲሆን፣ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ተፅዕኖ ያጠናክራል።
በመዲናችን አዲስ አበባ ዘወትር እሮብ እና አርብ ሙሉ ቀናት በሁሉም ተቋማት የአገልግሎት መስጫ ቀናት መሆናቸውን ያውቃሉ?
ለአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት ተጠሪ በሆኑት እና የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በሚሰጡ 5 ተጠሪ ተቋማቶቻችን በየትኛው አገልግሎት ለማግኘት ፈልገዋል?
ዛሬ እለቱ እሮብ ነው! ቀኑ ደስ ይላል!ህዳር 3/ 2018 አ.ም።
ለጽ/ ቤታችን ተጠሪ የሆኑ 5ቱ ተቋማት መካከል አብዛኞቹ አገልግሎት አሰጣጣቸውን በዲጂታል ቴክኖሎጅ ያዘመኑ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት የሚሰጥባቸው ናቸው።
አምስቱን ተጠሪ ተቋማት እናስታውስዎ:-
1)- የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ
2)- የፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ
3)- የመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን
4)- የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
5)- የአዲስ አበባ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት እፕሬሽን ኮርዲኔሽን ፅ/ ቤት ናቸው።
በእነዚህ ተቋማት አገልግሎት ማግኘት የምትፈልጉ የከተማችን ነዋሪዎች ሙሉ አድራሻቸው እንደሚከተለው ቀርቧል።
1.የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ
ዋና ቢሮ አድራሻ፡- በአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 1 በተለምዶ ፒያሳ እሪ በከንቱ ዮናታን ቢቲ ህንጻ ከ7ኛ ፎቅ ጀምሮ
ነጻ የስልክ መስመር - 6199
ቴሌግራም፡- https://t.me/CGAACMA
ዩቲዩብ ፡- https://www.youtube.com/@aacma-bu4zt
ዌብሳይት፡- www.aacma.gov.et
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/profile.php?id=100064800963883
2.የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ
ዋና ቢሮ አድራሻ :- አዲሱ ገበያ ቱኒዝያ መንገድ ሸገር መናፈሻ ግቢ ውስጥ
ነጻ የስልክ መስመር - 7533
ዌብ ሳይት (website): https://www.aacrrsa.gov.et
የፌስቡክ (facebook): https://www.facebook.com/profile.php?id=100064083391686
ቴሌግራም (telegram): https://t.me/addisvaitalpress
ፖስታ ሳ.ቁ (Box No)፡ 20320
3. የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
ዋና ቢሮ አድራሻ ;-አራዳ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 10 አራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ፊትለፊት
ነጻ የስልክ መስመር :- 939
fdrmc1926@addisfire.gov.et
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/AADRMC1
4. የአዲስ አበባ ከተማ መብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን
የቢሮ አድራሻ:- አራዳ ክ/ ከተማ ወረዳ 1 በተለምዶ ፒያሳ እሪ በከንቱ አካባቢ ኤንሪኮ ኬክ ቤት ዝቅ ብሎ ዋስትና ንግድ ማዕከል 17ኛ ፎቅ
ስ.ቁ 0111127775
ፌስቡክ ገፅ:-https://www.facebook.com/profile.php?id=61565439308107
EMail; AAESAA@aaca.gov.et
Website:-https://aaesa.gov.et
5.አዲስ አበባ ኤሌክትሪክ ሪጅን ማስተባበሪያ ፅ/ ቤት
በመዲናችን 31 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን (ሰብስቴሽን ተገልጋዮች ይስተናገዳሉ።
[Facebook] http://www.facebook.com/EEUOfficial
[Telegram] https://t.me/eeuethiopia
[Website] http://www.eeu.gov.et
[YouTube] https://www.youtube.com/@EthiopianElectricUtility
[Tiwtter] https://x.com/EEUEthiopia
[TikTok] https://www.tiktok.com/@ethiopian.electri
[Whatsapp] https://www.whatsapp.com/channel/0029VbAAvBDE50UZXJlIl507
ዝቅ ብሎ የመዲናችንን ነዋሪዎች ማገልገል
የተቋማቶቻችን እሴት፣ክብርና ኩራታችንም ነው
ዝቅ ብሎ የመዲናችንን ነዋሪዎች ማገልገል
የተቋማቶቻችን እሴት፣ክብርና ኩራታችንም ነው!
ዛሬ እለቱ እሮብ ነው! ቀኑ ደስ ይላል!ህዳር 3/ 2018 አ.ም።
በመዲናችን ዘወትር እሮብ እና አርብ ሙሉ ቀናት በሁሉም ተቋማት የአገልግሎት መስጫ ቀናት መሆናቸውን ያውቃሉ?
ለአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት ተጠሪ በሆኑት እና የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በሚሰጡ 5 ተጠሪ ተቋማቶቻችን በየትኛው አገልግሎት ለማግኘት ፈልገዋል?
ለጽ/ ቤታችን ተጠሪ የሆኑ 5ቱ ተቋማት መካከል አብዛኞቹ አገልግሎት አሰጣጣቸውን በዲጂታል ቴክኖሎጅ ያዘመኑ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት የሚሰጥባቸው ናቸው።
አምስቱን ተጠሪ ተቋማት እናስታውስዎ:-
1)- የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ
2)- የፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ
3)- የመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን
4)- የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
5)- የአዲስ አበባ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት እፕሬሽን ኮርዲኔሽን ፅ/ ቤት ናቸው።
በእነዚህ ተቋማት አገልግሎት ማግኘት የምትፈልጉ የከተማችን ነዋሪዎች ሙሉ አድራሻቸውን በቀጣዩ ቪዲዮ ታገኘላችሁ።
እርስዎ ወደ ተቋማችን ይምጡ! እኛም በቅንነት፣ በታማኝነትና በትክክለኛው መንገድ ብቻ እናገለግለዎታለን!
በመዲናችን አዲስ አበባ በዲጂታል ቴክኖሎጅ እየተሰጠ ያለውን የነዋሪዎች የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ወደ ላቀና የተቀናጀ ዘመናዊ ስርአት ከፍ የሚያደርግ አዲስ ሲስተም ትግበራ በቅርቡ ይፋ ሊደረግ ነው።
በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዛሬው እለት በከተማችን የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት ረገድ እየተሰጠ ያለውን አገልግሎት በይበልጥ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ግልጽነት የተላበሰ እንዲሁም ተደራሽ የማድረግ አላማ ይዞ እየለማ ያለው አዲሱ ሲስተም የደረሰበትን ደረጃ ከጽ/ቤቱና ከኤጀንሲው አመራሮች ጋር በመሆን በዛሬው እለት ገምግመዋል።
በዚሁ መድረክ አዲሱን ሲስተም እያለማ ያለው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ባለሙያዎች ቡድን ባቀረቡት ገለጻ አዲሱ ሲስተም ቀደም ሲል አልፎ አልፎ ያጋጥም የነበረውን የአገልግሎት መቆራረጥ ችግር የሚቀርፍ፣ በሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በኩል የሚሰጡ አገልግሎቶችን በሌሎች ተቋማት ከሚሰጡ ወሳኝ አገልግሎቶች ጋር አቀናጅቶ ለመጠቀም የሚያስችል፣ነዋሪዎችም አገልግሎቶችን ካሉበት ቦታ ሆነው እንዲያገኙ የሚያስችል፣ ዘመናዊና ደህንነቱ የተጠበቀ እንደሆነ አብራርተዋል።
ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዚሁ ወቅት በከተማችን እየተሰጠ ያለው የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎቶች በሌሎች ተቋማት ዘንድ እንደ አብነት የሚጠቀስ እንደመሆኑ ይህንኑ አገልግሎት ከመዲናችን የስማርት ሲቲ ግንባታ ጋር የተዋኸደ፣ የተናበበና ዘመኑን በሚዋጅ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጅ መሠረተ ልማት ማሻሻያ ስራዎች የታገዘ፣ በየጊዜው እየላቀ እንዲሄድ እየተደረገ ባለው ጥረት የአዲሱ ሲስተም ትግበራ ከፍ ያለ ሚና እንዳለው አስምረውበታል።
አክለውም አዲሱ ሲስተም የከተማ አስተዳደሩ የአገልግሎት አሰጣጥ የመዲናዋን ሁለንተናዊ አድገትና ዘመናዊነት የደረሰበትን የእድገት ደረጃ የሚመጥን እንዲሆን ለማድረግ እየተካሄደ ባለው ጥረተ አብነታዊ ማሳያ በመሆኑ ሲስተሙ በአጭር ጊዜ ውስጥ በተያዘው እቅድ ወደ ትግበራ ለማስገባት በሁለቱ ተቋማት ለተከናወኑ ስራዎች ያላቸውን አድናቆትና ምስጋና ገልጸዋል። በቅርብ ቀናት ውስጥም የአዲሱን ሲስተም ትግበራ ይፋ ለማድረግ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እንዲጠናቀቁም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የከተማው አስተዳደር አመራሮች አቶ ጥራቱ በየነን በአዲስ አበባ የአመራርነት ቆይታቸዉ ለነበራቸዉ አስተዋፆ አመስግነዉ በሄዱበት መልካሙን ሁሉ በመመኘት በክብር ሸኝተዋል ።
እንዲሁም በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የስራ እና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ በመሆን የተሾሙት አቶ ሚሊዮን ማቲዎስን እንኳን ደህና መጡ ብለዋል ።
የመንገድ መብራቶችን የመጠገን ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
የአዲስ አበባ ከተማ መብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን በተለያዩ ምክንያቶች ረጅም ጊዜ አገልግሎት ሳይሰጡ የቆዩትንና ድንገተኛ ብልሽት ያጋጠማቸውን የመንገድ መብራቶች በየደረጀው በመፍታት የህብረተሰቡን የምሽት እንቅስቃሴ ምቹና ሰላማዊ የማድረግ ስራ አጠናክሮ ቀጥሏሰ፡፡
የጥገና ስራ ከተከናወነባቸው መንገዶች ውስጥ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ቀጠና 4 የቀጠለ ፣ ከኮካ አደባባይ- አብነት፣ ከሜክሲኮ-ሱዳን ኤምባሲ፣ ጎሮ የረር - ኡራኤል ቤ/ክ፣ ፈረንሳይ ጨፌና ሌሎች መንገዶችም ተጠቀሾች ሲሆኑ በመንገድ መብራቶቹ ላይ አጋጥሞ የነበረውን የብልሽት አይነት በመለየት የኮንታክተርና ሆልደር የመቀየር እና የመግጠም፣ የኬብል ዝርጋታ፣ የኤል.ኢዲ የመቀየርና ሌሎች ተያያዥ የጥገና ስራዎችን በማከናወን ወደ አገልግሎት የማስገባት ስራ አከናውኗል።
ባለስልጣኑ በከተማው በተለያዩ ምክንያቶች ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሳይሰጡ የቆዩ የመንገድ መብራቶች ላይ ያለውን የጥገና ስራ ተደራሽ ለማድረግ ቀንና ሌሊት በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
በመጨረሻም ህብረተሰቡ መሰረተ-ልማቱን ከስርቆትና ህገ-ወጥ ተግባር በመጠበቅ፤ ማንኛውንም ጥቆማና አስተያየት በባለስልጣኑ ነፃ መስመር 9101 በማሳወቅ የተለደውን የዜግነት ኃላፈነቱን እንዲወጣ ጥሪውን ያቀርባል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ ቤት የጥቅም ወር የስራ እንቅስቃሴን ያካተተውን የዜና መፅሄት በቀጣዩ ሊንክ በቴሌግራም ገፃችን ይከታተሉ።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
