cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ESAT (ኢሳት🇪🇹)®

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot 🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Больше
Рекламные посты
246 752
Подписчики
+1924 часа
-1967 дней
-62430 дней
Время активного постинга

Загрузка данных...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Анализ публикаций
ПостыПросмотры
Поделились
Динамика просмотров
01
230 ኢትዮጵያውያን ከኦማን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ‼️ ወደ ሀገር ቤት የተመለሱት ዜጎች ሁሉም ወንዶች መሆናቸው ተገልጿል፡፡ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡ ከሚያዝያ 29 ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ከኦማን ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ 460 ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡ በኦማን የሚገኙ 1 ሺህ 590 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር ለመመለስ መታቀዱ የሚታወስ ነው። @Esat_tv1 @Esat_tv1
23 9605Loading...
02
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ግንባታን አስጀመሩ‼️ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ይህ ታሪካዊ ክስተት የኢትዮጵያ አዲስ የፈጠራና ከፍተኛ የኢኮኖሚ ልማት ጅማሮን የሚያበስር ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ ባለፈም የኢኮኖሚ ፈጠራን በማራመድ፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማብቃትና ዘላቂነትን በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ይሆናል ነው ያሉት። የኢኮኖሚ ፈጠራን በማራመድ ረገድ ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ የማዕዘን ድንጋይ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አንስተዋል፡፡ @Esat_tv1 @Esat_tv1
32 1343Loading...
03
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ። https://t.me/Poppycarmarket ☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን
30 2421Loading...
04
የቤንዚን የችርቻሮ መሸጫ ላይ ጭማሪ ተደረገ‼️ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ ከግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ/ም ለሊት 6፡00 ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ ያለው የነጭ ናፍጣ ፣ የኬሮሲን ፣ የአይሮፕላን ነዳጅ ፣ የቀላል ጥቁር ናፍጣና የከባድ ጥቁር ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት እንደሚቀጥል አሳውቋል። በዚህ መሰረት ፦ - ነጭ ናፍጣ ብር 79.75 በሊትር - ኬሮሲን ብር 79.75 በሊትር - የአውሮፕላን ነዳጅ ብር 70.83 በሊትር - ቀላል ጥቁር ናፍጣ ብር 62.36 በሊትር - ከባድ ጥቁር ናፍጣ ብር 61.16 በሊትር ሆኖ ባለበት ይቀጥላል። የቤንዚን ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደርጎ በሊትር 78 ብር 67 ሳንቲም ገብቷል። @Esat_tv1 @Esat_tv1
44 21555Loading...
05
የእስራኤል ጦር በጋዛ እና ግብጽ መካከል ያለውን ወሳኝ ማቋረጫ በመቆጣጠር ወደ ራፋ ከተማ እየገሰገሰ ነው ተብሏል‼️ አለምአቀፍ አደራዳሪዎች፣ እስራኤል እና ሀማስ ተኩስ ለማቆም እንዲስማሙ ጥረት እያደረጉ ባለበት ወቅት የእስራኤል ጦር በጋዛ እና ግብጽ መካከል ያለውን ወሳኝ ማቋረጫ በመቆጣጠር ወደ ራፋ ከተማ እየገሰገሰ ነው ተብሏል። ሀማስ፣ እስራኤል ጥቃት በመክፈት በካይሮ እየተካሄደ ባለው የተኩስ አቁም ድርድር ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረች ነው ሲል ከሷል። @Esat_tv1 @Esat_tv1
46 18410Loading...
06
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ። https://t.me/Poppycarmarket ☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን
39 0482Loading...
07
[CREATINE MONOHYADRATE ] ጡንቻን ለመገንባት እና ጉልበት ለማግኘት፤ ለሰውነትዎ የሚያስፈልገውን ይስጡት! ጥንካሬ፣ብርታት እና ፈጣን የሰዉነት ጥገና ያስፈልገኛል ብለዉ ካሰቡ ክሬቲን ይገባዎታል 👨🏾‍⚕️የዘርፉ ባለሙያዎች ጥናት እንደሚያሳየዉ ክሬቲን የሚጠቀሙ አትሌቶች እና ስፓርተኞች 23 % የተሻለ አፈጻጸም እና ጥገና ያሳያሉ!🏃‍♂️ ለነፃ የምክር አገልግሎት እና የተሟላ መረጃ ወደ ጥሪ ማእከላችን ይደውሉልን። አድራሻችን;- ሆሳዕና ጮራሞ ሕንፃ 1 ፎቅ የቤት ቁጥር 07 ጎራ በማለት የሚፈልጉትን ያገኛሉ። ☎️ +251966114766 ☎️ ☎️ 9369 ላይ ይደውሉ   ☎️
41 1353Loading...
08
ቦሌ አየር መንገዱ ይቅርታ ጠየቀ‼️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET154 ዛሬ ሚያዝያ 29፣ 2016 ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ በአውሮፕላን ውስጥ ጭስ የታየ ቢሆንም አውሮፕላኑ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ በተመደበለት የመንገደኞች ማስተናገጃ በር ያለ ምንም እክል በመቆም መንገዶኞቻችንን ከአውሮፕላን ላይ ደህንነታቸው እንደተጠበቀ ወርደዋል። በአሁኑ ሰአት የክስተቱ መንስኤ በመጣራት ላይ ያለ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው ክስተት ውድ ደንበኞቹን ይቅርታ ጠይቋል፡፡ @Esat_tv1 @Esat_tv1
48 91529Loading...
09
ታግታ የተወሰደችው የ2 ዓመት ከ8 ወር ህፃን በተደረገ የተቀናጀ ክትትል በሦስት ቀናት ውስጥ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ * ታግታ የተወሰደችው የ2 ዓመት ከ8 ወር ህፃን የአዲስ አበባ ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃ አገልግሎት ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ጠንካራ ክትትል በሦስት ቀናት ውስጥ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።  የ2 ዓመት ከ8 ወር ዕድሜ ያላት አቢጊያ ዳንኤል የተባለችው ህፃን የታገተችው በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሳርቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ተወስዳ እንደነበር ተጠቅሷል። ቸርነት ጥላሁን የተባለው ተጠርጣሪ ከቤተሰቡ ጋር በነበረው ቅርበት ሕፃን አቢጊያን በተለያዩ ቦታዎች እየወሰደ በማዝናናት እንደ ቤተሰቡ አባል ያጫውታት እንደነበረና ከአምስት ወር በላይ ከቤተሰቡ ጋር በትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪነት የነበረው ቅርርብ ወንጀሉን በቀላሉ ለመፈፀም ምቹ ሁኔታን እንደፈጠረለትም ነው ፖሊስ የገለፀው። ግለሰቡ ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ/ም ከምሽቱ 12 ስዓት ተኩል ገደማ ወደ ህፃኗ ወላጆች መኖሪያ ቤት በመሄድና "እናቷ አምጣት ብላኛለች" ብሎ ለቤት ሰራተኛዋ ከነገረ በኋላ ሕፃኗን ወስዶ በማገት ገንዘብ እንዲሰጠው ከወላጆቿ ጋር ሲደራደር መቆየቱን ፖሊስ ገልጿል። ተጠርጣሪው 150ሺህ የአሜሪካን ዶላር እንዲሰጠው በመጠየቅ ገንዘቡን ማግኘት ካልቻለ ሕፃኗን በህይወት እንደማያገኟት ሲዝት እንደነበረ የህፃን አቢጊያ ወላጅ እናት ለፖሊስ በሰጠችው ቃል ማስረዳቷም ነው ፖሊስ የጠቀሰው፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ህፃኗን ለማስመለስና ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ቀንና ለሊት ክትትል ሲያደርግ ቆይቶ በተደረገው ክትትልም ትናንት ሚያዚያ 28 ቀን 2016 ዓ/ም በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አለም ሰላም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተጠርጣሪው ተከራይቶ በሚኖርበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለሶስት ቀናት ያህል ታግታ የቆየችው ህፃን አቢጊያ ዳንኤል  ልትገኝ መቻሏን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። ህፃናት ልጆች ለእንደዚህ አይነት ወንጀል ተጋላጭ እንዳይሆኑ እንዲጠብቋቸው አደራ የተሰጣቸው ግለሰቦችም ሆኑ ሞግዚቶችና ወላጆች  ነገሮችን በጥርጣሬ በማጤንና የማረጋገጥ ሃላፊነታቸውን በመወጣት አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።
49 02314Loading...
10
Media files
44 6375Loading...
11
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ ባወጣው መግለጫ "የህወሓት ኃይሎች" ከሱዳን ጦር ጎን በቅጥረኝነት ተሰልፈው ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ጋር እየተዋጉ ነው መባሉን አስተባብሏል‼️ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ባለፈው ቅዳሜ የህወሓት ኃይሎች ከሱዳን ጦር እና ተባባሪ ሚሊሻዎች ጋር ሆነው እየተዋጉት እንደሆነ ማረጋገጡን መግለጹን ተከትሎ ነው። የሱዳን ጦርነት ከተጀመረበት ከሚያዝያ 2023 ወዲህ የሱዳን ጦር የውጭ ቅጥረኞችን እርዳታ እየፈለገ ነው የሚል ክስ ያቀረበው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ጦር፣ በጦርነት ወቅት ተገድለው የተገኙ ቅጥረኞችን መመዝገቡን ጠቅሷል። የህወሓት ኃይሎች ከሱዳን ጦር ጎን ተሰልፈው እየተዋጉ ነው የሚለውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች "መሰረተቢስ ክስ" በጽኑ እንደሚያወግዝ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ገልጿል። @Esat_tv1 @Esat_tv1
53 0205Loading...
12
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ። https://t.me/Poppycarmarket ☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን
31 2081Loading...
13
የኢትዮጵያ ሰራተኞች እየተከፈላቸው ባለዉ ደመወዝ ክፍያ ኑሮን መቋቋም ባለመቻላቸው ለችግር መጋለጣቸውን ኢሰማኮ አስታወቀ‼️ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን የኢትዮጵያ ሰራተኞች እየተከፈላቸው ባለዉ ደመወዝ ክፍያ ኑሮን መቋቋም ባለመቻላቸው ለችግር መጋለጣቸውን በመግለፅ ይህን አስመልክቶ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ያቀረብኩት ጥያቄ ትኩረት ሳይሰጠዉ ቀርቷል ብለዋል። ማህበሩ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅርበው ምላሽ አላገኙም ካሏቸዉ ጥያቄዎች ዉስጥ "ሠራተኞች አሁን እየተከፈላቸው ባለው የደመወዝ ክፍያ የኑሮ ዉድነቱን በፍጹም መቋቋም ያልቻሉ በመሆኑ ደመወዝ የገቢ የሥራ ግብር እንዲቀነስ ላቀረብነዉ ጥያቄ መንግሥት ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው ብሏል። ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል የሚወስን የደመወዝ ቦርድ እንዲቋቋም በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ የተደነገገ ቢሆንም የደመወዝ ቦርድ ማቋቋሚያ ደንብ በሚንስትሮች ምክር ቤት ባለመውጣቱ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ያልተገባ መሆኑን ነዉ ማህበሩ ያስታወቀው። በጦርነት ዘላቂ መፍትሒ ስለማይመጣ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ግጭትና ጦርነት ቆሞ በዉይይት ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ ሁሉም ወገኖች በድርድር እንዲፈቱ የጠየቀው ኢሰማኮ ለጉዳዩ አፅንኦት ይሰጠዉ ብሏል በመግለጫው። @Esat_tv1 @Esat_tv1
55 38142Loading...
14
የእስራኤል ካቢኔ የኳታሩ የቴሌቪዥን ጣቢያ አልጀዚራ ቢሮ እንዲዘጋ ወሰነ‼️ የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ ካቢኔው በእስራኤል የሚገኘው የአልጀዚራ ቴሌቪዥን ጣቢያ ቢሮ እንዲዘጋ በሙሉ ድምጽ ማጽደቁን አስታውቋል። ውሳኔው የቴሌቪዥን ጣቢያውን የስርጭት ቁሳቁሶች መውረስ እና የተቋሙን ድረገጽ መዝጋት ያካትታል ተብሏል። እስራኤል ከዚህ ቀደም በጋዜጠኞች ላይ በተናጠል ካሳለፈችው እገዳ ውጭ የውጭ የመገናኛ ብዙሃን እንዲዘጋ ስትወስን አልጀዚራ የመጀመሪያው ይሆናል። @Esat_tv1 @Esat_tv1
49 9767Loading...
15
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ። https://t.me/Poppycarmarket ☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን
30 1182Loading...
16
[CREATINE MONOHYADRATE ] ጡንቻን ለመገንባት እና ጉልበት ለማግኘት፤ ለሰውነትዎ የሚያስፈልገውን ይስጡት! በፆም ወቅት የሚወሰድ! ጥንካሬ፣ብርታት እና ፈጣን የሰዉነት ጥገና ያስፈልገኛል ብለዉ ካሰቡ ክሬቲን ይገባዎታል 👨🏾‍⚕️የዘርፉ ባለሙያዎች ጥናት እንደሚያሳየዉ ክሬቲን የሚጠቀሙ አትሌቶች እና ስፓርተኞች 23 % የተሻለ አፈጻጸም እና ጥገና ያሳያሉ!🏃‍♂️ ለነፃ የምክር አገልግሎት እና የተሟላ መረጃ ወደ ጥሪ ማእከላችን ይደውሉልን ☎️9369 ☎️ አድራሻ📍 አዳማ - ፖስታ ቤት ሶሬቲ ህንፃ ፊትለፊት ጀርመን ሲቲ ሞል 1ኛ ፎቅ ሱቅ ቁጥር 110 ☎️ +251966113766 ☎️ Join https://t.me/+RCaZ_Ka6SOrlz0u5
45 8844Loading...
17
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ። https://t.me/Poppycarmarket ☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን
10Loading...
18
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች ማዕድ አጋሩ‼️ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአረጋዊያን እና ለአቅመ ደካሞች ማዕድ አጋርተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ለአረጋዊያን እና ለአቅመ ደካሞች የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ ማጋራታቸውን ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡ @Esat_tv1 @Esat_tv1
63 75516Loading...
19
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ። https://t.me/Poppycarmarket ☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን
38 3460Loading...
20
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 907 ቤቶችን ለነዋሪዎች አስተላለፈ‼️ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ለኑሮ አመቺ ያልነበሩ አፍርሰን በአጭር ጊዜ መልሰን የገነባናቸውን እና ያደስናቸውን 907 ቤቶች እንኳን ለትንሳኤ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ብለን ለነዋሪዎች አስተላልፈናል ብለዋል። በተጨማሪም አዳዲስ ግንባታዎችን በዛሬው ዕለት እንዳስጀመሩ ነው የገለጹት፡፡ አርጅተው በመፍረስ ላይ የነበሩ ጎስቋላ ቤቶችን አፍርሰን ለዘመናዊ አኗኗር አመቺ በሆነ መልክ በነበሩበት ቦታ ላይ መልሰን የገነባነው በርካታ ልበቀና ባለሃብቶችን በማስተባበር ነው ብለዋል ከንቲባዋ። የከተማ አስተዳደሩን ጥሪ በመቀበል ለወገኖች በመድረስ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለተወጡ የከተማዋ ባለሃብቶች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ነዋሪዎች እድሉ ተጠቃሚ ስለሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉት ከንቲባዋ ፥ ማህበራዊ ፍትህ የነገሰባት አዲስ አበባን የመገንባቱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። @Esat_tv1 @Esat_tv1
57 85817Loading...
21
የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ (Diversity Visa) 2025 አሸናፊዎች ነገ ይፋ ተደረገ‼️ DV 2025 ሞልታቹ የነበራቹ ውጤቱ ተለቋል ወደ ቀጣይ ሂደት ማለፍ አለማለፋቹን የተሰጣቹን"Confirmation Number" እያስገባቹ ማየት ትችላላችሁ ውጤቱን ለማየት በዚህ ሊንክ ይግቡ https://dvprogram.state.gov/ESC/CheckStatus.aspx @Esat_tv1 @Esat_tv1
21 995169Loading...
22
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ። https://t.me/Poppycarmarket ☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን
32 9562Loading...
23
ቅርጫ አልተከለከለም‼️ አ/አ ከተማ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ በዘንድሮዉ ዓመት የሚከበረዉን የትንሳኤ በአል አስመልክቶ ህብረተሰቡ በየቤቱ በእርድ መልክ የሚጠቀመዉን እና በየአካባቢዉ የቁም እንስሳትን ቅርጫ በማረድ የሚከፋፈለዉን ተከልክሏል በሚል በማህበራዊ ሚዲያዉ ሀሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል። በመሆኑም ከዚህ ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ክልከላ ያልተደረገ ሲሆን በየአካባቢዉ በህገ ወጥ መንገድ እርድ በመፈፀም ለሆቴሎች እና ለስጋ ቤቶች በማከፋፈል ተግባር ላይ የሚገኙ አካላት የቁም እንስሳቱ ጤንነት ባልተረጋገጠበት ሁኔታ የከተማዉን ነዋሪ ጤንነት ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል። የከተማችን ነዋሪ በአላትን ሽፋን በማድረግ ጤንነቱ ያልተረጋገጠ እንስሳት አርዶ ማከፋ ፈል በጤና ላይ የሚያደርሰዉን ጉዳት ግምት ዉስጥ በማስገባት በህገወጥ እርድ የሚሰ ማሩ አካላት በሚደረገዉ ቁጥጥር ተባባሪ እንዲሆን መልክታችንን እናስተላልፋለን። @Esat_tv1 @Esat_tv1
61 53585Loading...
24
ቅርጫ እንወርሳለን ፉከራ ሀገር የላችሁም ዓይነት ትዕቢት ነው። ለመሆኑ ለፋሲካ የሚታረደውን ሁሉ ቄራ ለማስተናገድ አቅም አለው?‼️ 🗣 ስናፍቅሽ አዲስ - ለድሬ ቲዩብ የአዲስ አበባ ፀጥታ ቢሮ ሰጠው የተባለውን መግለጫ ሰማሁት። የመንግስት ሰዎች መንግስታቸው አልወድቅ ብሏቸው የተቸገሩ ይመስላሉ። መልካም ኀሳብ ሲያነሱ ለዘለዓለም እንድንጠላው አድርገው ነው። መልእክቱን ያስተላለፉት ባለሥልጣን ንግግር ትህትና የለውም። ወቅቱን የጠበቀ ነው የሚል እምነትም የለኝም። መንግስትና ህዝብን የሚያናክስ ቃላት የሞሉበት እንደሆነም አምናለሁ። ልክ ነው፤ ህገ ወጥ እርድ ለጤናም ለኢኮኖሚም ጎጂ ነው። ያንን ለማስቆም ግን ባህል እና ልማድ ብሎ ነገር የለም ብሎ ማህበራዊ እሴት ላይ ከመዛት ባይጀመሩ ጥሩ ነው። ዛሬ እኮ መንግስት ስጋ ቤቶችን እንኳን ተቆጣጥሮ ከሉካንዳ ቤት ጀርባ የሚደረግ እርድን መቆጣጠርና ማስቆም አልቻለም። የፋሲካ በዓል ሊከበር ቀናት ሲቀሩት በማህበር በሬ የገዙ ሰዎች ለእርዱ ቀን ሲጠባበቁ በሚዲያ ብቅ ብሎ "የሚታረድ በሬ ውረስ" ቅስቀሳ ማህበራዊ ቀውስ እንጂ ስልጣኔ አያመጣም። እንዲህ ያሉ አሰራሮች በጥናት፣ ያሉንን የማረጃ ቦታዎች የማስተናገድ አቅም በማጤን ማህበረሰቡን አወያይቶ በመፍታት እንጂ በግብታዊነት የሚደረግ አይደለም። ከምመለከተው ነገር ብልፅግና እሱን መስለው በህዝብ ዘንድ እንዲተፋ የሚያድርጉ ንግግር አላዋቂ የስራ ኃላፊዎች እየበዙበት ነው። የሰሞኑን የእርድ ጉዳይ ዛቻም የህዝበ ክርስቲያኑን ልብ የሚጎዳ "ምን ታመጣላችሁ?" ድምፅ ያለው መመሪያ ነው። በግ በእኛ ባህልና አኗኗር በምን ስሌት ነው ቄራ ወስደን የምናርደው? በፋሲካ ማግስት በሬ ወይም ስጋ ንጠቅ ያልነውን የፀጥታ አካል ለምን ዓይነት ብልሹ አሰራር አሳልፈን እየሰጠነው መሆኑንስ ተረድተናል? ይተገበራል፣ አይተገበርም ከሚለው ይልቅ ይህንን መመሪያ ተገን አድርጎ በየቅርጫው ማውደልደል የሚፈልግ ደንብ አስከባሪ ነኝ ባይ እና በፀጥታ አስከባሪነት ስም የግል ጥቅሙን የሚያጋብስ ህገ ወጥ የሚፈጥረውን ችግር እና ገንዘብ ንጥቂያ አስቡት። ያ በመንግስትና በህዝብ መካከል ቁርሾ ማኖር ነው። የሚሆን ሀሳብን በማይሆንን ንግግር ተጠልቶ እንዲታሰብ ማድረግ በእራሱ አስቂኝ ነው። ቅርጫ ማህበራዊ እሴት ነው። ጤንነቱ ያልተረጋገጠ እርድን መቆጣጠር መንግስታዊ ኃላፊነት ነው። ይሄንን ለማስታረቅ ብዙ መሰራት ያለባቸው ስራዎች አሉ። ፆም ፍቺ ላይ ለስጋ ቤት እንኳን ለማቅረብ አቅም የሌላቸው ቄራዎች ይዘን ብዙ ሺህ ከብት በአንድ ጠዋት ስለማድረስ መናገርም ትዝብት ውስጥ ይጥላል። አቅም እስኪኖረኝ ፆም አትፈቱም ከሆነም መናገር ነው። በእርግጥ ይሄ የግለሰብ ሀሳብ ሊሆን ይችላል። መንግስት በዚህ መጠን ያብዳል ብዬ አላስብምና። @Esat_tv1 @Esat_tv1
58 21752Loading...
25
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ-ግብረ ኃይል የትንሣዔ በዓል በሰላም እንዲከበር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ‼️ ሕዝበ ክርስቲያኑ የትንሣዔ በዓልን በሰላም እንዲያከብር በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ ከተማ አሥተዳደሮች ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ወደ ተግባር መግባቱን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታወቀ፡፡ ሕዝቡም የአካባቢውን ሰላምና ደኅንነት የሚያውኩ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ከጋራ ግብረ-ኃይሉ ጎን እንዲቆም ተጠይቋል፡፡ ግብረ-ኃይሉ ለመላው የክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞቱን ገልጿል፡፡ @Esat_tv1 @Esat_tv1
54 6212Loading...
26
በአቃቂ የገበያ ማዕከል ትናንት ምሽት በደረሰ የእሳት አደጋ 16 ንግድ  ሱቆች ወደሙ ‼️ ሚያዚያ 24 ቀን2016  ዓ.ም ምሽት 3:10 ሰዓት ላይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ  ወረዳ 03 አቃቂ የገበያ  ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ 16 የንግድ ሱቆች ሙሉ በሙሉና በከፊል መውደማቸውን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል። የእሳት አደጋዉን  ለመቆጣጠር አምስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ ሁለት የዉሀ  ቦቴ  የተሰማራ ሲሆን እሳቱ ወደገበያ ማዕከሉ ተስፋፎቶ በሰዉና በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነትና ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አደጋዉን ለመቆጣጠር ሁለት ሰዓት ፈጅቷል። በአደጋ መቆጣጠሩ ሂደት የፌደራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በሰው  ላይ የደረሰ ጉዳት  የለም። አቃቂ የገበያ ማዕከል ትንሹ መርካቶ እየተባለ የሚጠራ የገበያ ማዕከል ሲሆን ገበያ ማዕከሉ በከተማ ደረጃ ለእሳት አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ ከተለዩ አንዱ ነው። በገበያ ማዕከሉ በተደጋጋሚ የእሳት አደጋ እያጋጠመ በንብረት ላይ ጉዳት ሲደርስ መቆየቱንም አቶ ንጋቱ ጨምረው ነግረውናል።ኮሚሽኑ ገበያ ማዕከሉ ለአደጋ የተጋለጠባቸዉን ዝርዝር ጉዳዮችን የመፍትሄ ሀሳቦችን አካቶ ለገበያ ማዕከሉ ማህበራትና ለሚመለከታቸዉ አካላት ከዚህ ቀደም ያቀረበ ቢሆንም የማስተካከያ እርምጃዎች አልተወሰዱም። በመሆኑም በቀጣይ መሰል አደጋዎች እንዳያጋጥሙ መፍትሄ መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ኮሚሽኑ አሳስቧል። @Esat_tv1 @Esat_tv1
51 93112Loading...
27
በአዲስ አበባ ከተማ የወጣው የመሬት ሊዝ  ጨረታ ተራዘመ‼️ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በአራዳ ክፍለ ከተማ  ፤ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም አካባቢ በኮሪደር ልማት ምክንያት የፀዱ ቦታዎችን ጨምሮ በሌሎችም ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች የተዘጋጁ ቦታዎችን በጨረታ አወዳድሮ በሊዝ ለማስተላለፍ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል። በዚህም ከሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 24/2016 ዓ/ም ድረስ የጨረታ ሰነድ ሽያጭ ሲከናወን ቆይቷል። ነገር ግን የጨረታ ሰነድ ሽያጩ ከ28 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 09/09/2016 ዓ/ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት መራዘሙ ተነግሯል። ተጫራቾች ፦ - የጨረታ መልስ ማቅረቢያ ሰነድ፣ - ሲፒኦ፣ - የግንባታ አቅም ማሳያ ማስረጃ፣ - ሰነዱን ለመግዛት በቴሌ ብር የከፈሉበት ስሊፕ - ሌሎች መያያዝ ያለባቸዉ እና በተጫራቾች መመሪያ ላይ የተገለጹትን በመጨመር የጨረታ ሰነዶችን በኤንቨሎፕ በማሸግ ግንቦት 09/2016 ዓ/ም ከቀኑ 11፡30 ሰዓት ድረስ ለም ሆቴል አከባቢ ኤም ኤ (MA) ህንፃ ላይ በሚገኘው የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው ተብሏል። ጨረታው ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግንቦት 12/2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ ለተከታታይ 9 የስራ ቀናት በቦሌ ክ/ከተማ አስተደዳር አዳራሽ  እንደሚከፈት ተገልጿል። @Esat_tv1 @Esat_tv1
50 6398Loading...
28
ባለፉት ዘጠኛ ወራት 374.20 ቢሊዮን ብር ገቢ ተሰብስቧል‼️ 23ሺ ግብር ከፋዮች በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ዘዴ ክፍያ መፈጸም ችለዋል። የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት 9 ወራት 374.20 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን የሚኒስቴር መ/ቤቱ ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ የ9 ወራት ሪፖርቱን ባቀረቡበት ወቅት ገልፀዋል። መስሪያ ቤቱ 391.34 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ የነበረ ሲሆን፤ የዕቅዱን 95.62 በመቶ ማሳካት እንደቻለ ገልጿል። ከነዚህ ውስጥ 23,071 ግብር ከፋዮች በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ዘዴ ክፍያ መፈጸም መቻላቸውም ተገልጿል። የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት በመስራት ባለፉት 9 ወራት የቴሌ ብር ሥርዓትን ለቀረጥና ታክስ አሰባሰቡ በሥራ ላይ ማዋል በመቻሉ 7,130 ግብር ከፋዮች በቴሌ ብር በኩል ክፍያቸውን እንደፈፀሙ ተነግሯል። በተያየዘ የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ዘዴን ለማሳለጥ የታቀፉ የንግድ ባንኮች ቁጥር 21 እንዲደርስ የተደረገ መሆኑን ሲጠቆም የተቀሩት ባንኮችንም ወደ ሥርዓቱ ለማስገባት ሥራዎች እየተሰራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። @Esat_tv1 @Esat_tv1
57 51514Loading...
230 ኢትዮጵያውያን ከኦማን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ‼️ ወደ ሀገር ቤት የተመለሱት ዜጎች ሁሉም ወንዶች መሆናቸው ተገልጿል፡፡ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡ ከሚያዝያ 29 ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ከኦማን ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ 460 ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡ በኦማን የሚገኙ 1 ሺህ 590 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር ለመመለስ መታቀዱ የሚታወስ ነው። @Esat_tv1 @Esat_tv1
Показать все...
ሼር/share
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ግንባታን አስጀመሩ‼️ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ይህ ታሪካዊ ክስተት የኢትዮጵያ አዲስ የፈጠራና ከፍተኛ የኢኮኖሚ ልማት ጅማሮን የሚያበስር ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ ባለፈም የኢኮኖሚ ፈጠራን በማራመድ፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማብቃትና ዘላቂነትን በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ይሆናል ነው ያሉት። የኢኮኖሚ ፈጠራን በማራመድ ረገድ ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ የማዕዘን ድንጋይ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አንስተዋል፡፡ @Esat_tv1 @Esat_tv1
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ። https://t.me/Poppycarmarket ☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
የቤንዚን የችርቻሮ መሸጫ ላይ ጭማሪ ተደረገ‼️ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ ከግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ/ም ለሊት 6፡00 ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ ያለው የነጭ ናፍጣ ፣ የኬሮሲን ፣ የአይሮፕላን ነዳጅ ፣ የቀላል ጥቁር ናፍጣና የከባድ ጥቁር ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት እንደሚቀጥል አሳውቋል። በዚህ መሰረት ፦ - ነጭ ናፍጣ ብር 79.75 በሊትር - ኬሮሲን ብር 79.75 በሊትር - የአውሮፕላን ነዳጅ ብር 70.83 በሊትር - ቀላል ጥቁር ናፍጣ ብር 62.36 በሊትር - ከባድ ጥቁር ናፍጣ ብር 61.16 በሊትር ሆኖ ባለበት ይቀጥላል። የቤንዚን ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደርጎ በሊትር 78 ብር 67 ሳንቲም ገብቷል። @Esat_tv1 @Esat_tv1
Показать все...
ሼር/share
Фото недоступноПоказать в Telegram
የእስራኤል ጦር በጋዛ እና ግብጽ መካከል ያለውን ወሳኝ ማቋረጫ በመቆጣጠር ወደ ራፋ ከተማ እየገሰገሰ ነው ተብሏል‼️ አለምአቀፍ አደራዳሪዎች፣ እስራኤል እና ሀማስ ተኩስ ለማቆም እንዲስማሙ ጥረት እያደረጉ ባለበት ወቅት የእስራኤል ጦር በጋዛ እና ግብጽ መካከል ያለውን ወሳኝ ማቋረጫ በመቆጣጠር ወደ ራፋ ከተማ እየገሰገሰ ነው ተብሏል። ሀማስ፣ እስራኤል ጥቃት በመክፈት በካይሮ እየተካሄደ ባለው የተኩስ አቁም ድርድር ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረች ነው ሲል ከሷል። @Esat_tv1 @Esat_tv1
Показать все...
ሼር/share
Фото недоступноПоказать в Telegram
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ። https://t.me/Poppycarmarket ☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
[CREATINE MONOHYADRATE ] ጡንቻን ለመገንባት እና ጉልበት ለማግኘት፤ ለሰውነትዎ የሚያስፈልገውን ይስጡት! ጥንካሬ፣ብርታት እና ፈጣን የሰዉነት ጥገና ያስፈልገኛል ብለዉ ካሰቡ ክሬቲን ይገባዎታል 👨🏾‍⚕️የዘርፉ ባለሙያዎች ጥናት እንደሚያሳየዉ ክሬቲን የሚጠቀሙ አትሌቶች እና ስፓርተኞች 23 % የተሻለ አፈጻጸም እና ጥገና ያሳያሉ!🏃‍♂️ ለነፃ የምክር አገልግሎት እና የተሟላ መረጃ ወደ ጥሪ ማእከላችን ይደውሉልን። አድራሻችን;- ሆሳዕና ጮራሞ ሕንፃ 1 ፎቅ የቤት ቁጥር 07 ጎራ በማለት የሚፈልጉትን ያገኛሉ። ☎️ +251966114766 ☎️ ☎️ 9369 ላይ ይደውሉ   ☎️
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
ቦሌ አየር መንገዱ ይቅርታ ጠየቀ‼️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET154 ዛሬ ሚያዝያ 29፣ 2016 ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ በአውሮፕላን ውስጥ ጭስ የታየ ቢሆንም አውሮፕላኑ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ በተመደበለት የመንገደኞች ማስተናገጃ በር ያለ ምንም እክል በመቆም መንገዶኞቻችንን ከአውሮፕላን ላይ ደህንነታቸው እንደተጠበቀ ወርደዋል። በአሁኑ ሰአት የክስተቱ መንስኤ በመጣራት ላይ ያለ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው ክስተት ውድ ደንበኞቹን ይቅርታ ጠይቋል፡፡ @Esat_tv1 @Esat_tv1
Показать все...
ሼር/share
ታግታ የተወሰደችው የ2 ዓመት ከ8 ወር ህፃን በተደረገ የተቀናጀ ክትትል በሦስት ቀናት ውስጥ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ * ታግታ የተወሰደችው የ2 ዓመት ከ8 ወር ህፃን የአዲስ አበባ ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃ አገልግሎት ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ጠንካራ ክትትል በሦስት ቀናት ውስጥ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።  የ2 ዓመት ከ8 ወር ዕድሜ ያላት አቢጊያ ዳንኤል የተባለችው ህፃን የታገተችው በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሳርቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ተወስዳ እንደነበር ተጠቅሷል። ቸርነት ጥላሁን የተባለው ተጠርጣሪ ከቤተሰቡ ጋር በነበረው ቅርበት ሕፃን አቢጊያን በተለያዩ ቦታዎች እየወሰደ በማዝናናት እንደ ቤተሰቡ አባል ያጫውታት እንደነበረና ከአምስት ወር በላይ ከቤተሰቡ ጋር በትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪነት የነበረው ቅርርብ ወንጀሉን በቀላሉ ለመፈፀም ምቹ ሁኔታን እንደፈጠረለትም ነው ፖሊስ የገለፀው። ግለሰቡ ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ/ም ከምሽቱ 12 ስዓት ተኩል ገደማ ወደ ህፃኗ ወላጆች መኖሪያ ቤት በመሄድና "እናቷ አምጣት ብላኛለች" ብሎ ለቤት ሰራተኛዋ ከነገረ በኋላ ሕፃኗን ወስዶ በማገት ገንዘብ እንዲሰጠው ከወላጆቿ ጋር ሲደራደር መቆየቱን ፖሊስ ገልጿል። ተጠርጣሪው 150ሺህ የአሜሪካን ዶላር እንዲሰጠው በመጠየቅ ገንዘቡን ማግኘት ካልቻለ ሕፃኗን በህይወት እንደማያገኟት ሲዝት እንደነበረ የህፃን አቢጊያ ወላጅ እናት ለፖሊስ በሰጠችው ቃል ማስረዳቷም ነው ፖሊስ የጠቀሰው፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ህፃኗን ለማስመለስና ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ቀንና ለሊት ክትትል ሲያደርግ ቆይቶ በተደረገው ክትትልም ትናንት ሚያዚያ 28 ቀን 2016 ዓ/ም በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አለም ሰላም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተጠርጣሪው ተከራይቶ በሚኖርበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለሶስት ቀናት ያህል ታግታ የቆየችው ህፃን አቢጊያ ዳንኤል  ልትገኝ መቻሏን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። ህፃናት ልጆች ለእንደዚህ አይነት ወንጀል ተጋላጭ እንዳይሆኑ እንዲጠብቋቸው አደራ የተሰጣቸው ግለሰቦችም ሆኑ ሞግዚቶችና ወላጆች  ነገሮችን በጥርጣሬ በማጤንና የማረጋገጥ ሃላፊነታቸውን በመወጣት አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።
Показать все...