cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

SEER SUNESIS // PARADISE CHURCH ✝️

Рекламные посты
7 786
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

ወጣቶች ዛሬ ልምከራችሁ 🥸🥸🥸 ከህይወቴ እና ከተረዳሁት ሕይወታችሁን አጥብቃችሁ ጠብቁ እናንተ የአብርሃም ዘሮች የነብያት ልጆች ናችሁ (ሐዋ 3:25) በሕይወታችሁ ሁሉ ማስቀደም ያለባቹን ነገር ሁሉ አስቀድሙ ጊዜ እና ሕይወት አንድ ናቸው ሁለቱም ይሞታሉ... ያኖራሉም አለማስተዋል ጊዜን ሲገድል ማስተዋል ደግሞ ትልቅ ሕይወትን ትሰጣለች:: አሁን ባለው ሕይወቴ ምንድን ነው የሚያስፈልገኝ ብላችሁ ቁጭ ብላችሁ ጠይቁ... ታውቃላችሁ ከ Relationship ገንዘብ እንደሚበልጥ? ከ Relationship እንደተማሪ ለቤተሰብ መገዛት እና መታዘዝ እንደሚበልጥ? ስትኖሩ እና ስትተጉ ለከፍታ እንጂ ለውድቀት አትትጉ... እንደሰራተኛ የት መድረስ ምን ማግኘት አለብኝ ለሚለው ትጉ እንደ ተማሪ ደግሞ እናት እና አባቴን እንዴት አድርጌ ላስደስታቸው ለደቂቃ እነርሱን ማሳዘን አልፈልግም ብላችሁ ምን አልባት በትምህርት ውጤታችሁ እንኳን ቢያዝኑባችሁ እና ምንም ለውጥ ማምጣት ቢያቅታችሁ በግልፅ ንግሯቸው ይህ ትምህርት ከበደኝ ባጠናም ምንም ባደርግ ብትሏቸው ታውቃላችሁ በብዙ ነገር እንደሚረዷችሁ እነርሱም በጣም ነው ደስ የሚላቸው... እንዲሁም ያዘዙአችሁን ብቻ ሳይሆን ያላዘዟቹን በማድረግ አስደስቷቸው ስለሚገባቸው! ለሚጠቅማችሁ ነገር ኑሩ እንጂ Television የሳለላቹን ውሸት አምናችሁ ለዛ አትኑሩ መንፈስ ቅዱስ ያሳያቹን Vision እርሱን እመኑት ለርሱ ኑሩ "የእኛ TELEVISION... VISION ነው":: ይህን ካደረጋችሁ አምናለው ትልቅ ቦታ ጋር 🫡
Показать все...
28👍 14🔥 8🕊 4 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
Deliverance Prayer
Показать все...
54🔥 4🥰 4👍 3
1ኛ ዮሐንስ 2 ¹ ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ² እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ። ³ ትእዛዛቱንም ብንጠብቅ በዚህ እንዳወቅነው እናውቃለን። ⁴ አውቄዋለሁ የሚል ትእዛዛቱንም የማይጠብቅ ውሸተኛ ነው እውነትም በእርሱ ውስጥ የለም። ⁵ ቃሉን ግን የሚጠብቅ ሁሉ በእርሱ የእግዚአብሔር ፍቅር በእውነት ተፈጽሞአል። በእርሱ እንዳለን በዚህ እናውቃለን፤ ⁶ በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደ ተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል። ⁷ ወንድሞች ሆይ፥ ከመጀመሪያ የነበረቻችሁ አሮጌ ትእዛዝ እንጂ የምጽፍላችሁ አዲስ ትእዛዝ አይደለችም፤ አሮጌይቱ ትእዛዝ የሰማችኋት ቃል ናት። ⁸ ዳግመኛ አዲስ ትእዛዝን እጽፍላችኋለሁ፥ ይህም ነገር በእርሱ በእናንተም እውነተኛ ነው፤ ጨለማው ያልፋልና እውነተኛውም ብርሃን አሁን ይበራል። ⁹ በብርሃን አለሁ የሚል ወንድሙንም የሚጠላ እስከ አሁን በጨለማ አለ። ¹⁰ ወንድሙንም የሚወድ በብርሃን ይኖራል ማሰናከያም የለበትም፤ ¹¹ ወንድሙን የሚጠላ ግን በጨለማ አለ፥ በጨለማም ይመላለሳል፥ የሚሄድበትንም አያውቅም፥ ጨለማው ዓይኖቹን አሳውሮታልና። ¹² ልጆች ሆይ፥ ኃጢአታችሁ ስለ ስሙ ተሰርዮላችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ¹³ አባቶች ሆይ፥ ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ጎበዞች ሆይ፥ ክፉውን አሸንፋችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ልጆች ሆይ፥ አብን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ¹⁴ አባቶች ሆይ፥ ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ጐበዞች ሆይ፥ ብርቱዎች ስለ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም ቃል በእናንተ ስለሚኖር ክፉውንም ስለ አሸነፋችሁ እጽፍላችኋለሁ። ¹⁵-¹⁶ ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም። ¹⁷ ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል። ¹⁸ ልጆች ሆይ፥ መጨረሻው ሰዓት ነው፥ የክርስቶስም ተቃዋሚ ይመጣ ዘንድ እንደ ሰማችሁ አሁን እንኳ ብዙዎች የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ተነሥተዋል፤ ስለዚህም መጨረሻው ሰዓት እንደ ሆነ እናውቃለን። ¹⁹ ከእኛ ዘንድ ወጡ፥ ዳሩ ግን ከእኛ ወገን አልነበሩም፤ ከእኛ ወገንስ ቢሆኑ ከእኛ ጋር ጸንተው በኖሩ ነበር፤ ነገር ግን ሁሉ ከእኛ ወገን እንዳልሆኑ ይገለጡ ዘንድ ወጡ። ²⁰ እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም ታውቃላችሁ። ²¹ እውነትን የምታውቁ ስለ ሆናችሁ፥ ውሸትም ሁሉ ከእውነት እንዳልሆነ ስለምታውቁ እንጂ እውነትን ስለማታውቁ አልጽፍላችሁም። ²² ክርስቶስ አይደለም ብሎ ኢየሱስን ከሚክድ በቀር ውሸተኛው ማን ነው? አብንና ወልድን የሚክድ ይህ የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው። ²³ ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ እንኳ የለውም፤ በወልድ የሚታመን አብ ደግሞ አለው። ²⁴ እናንተስ ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ጸንቶ ይኑር። ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ቢኖር፥ እናንተ ደግሞ በወልድና በአብ ትኖራላችሁ። ²⁵ እርሱም የሰጠን ተስፋ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው። ²⁶ ስለሚያስቱአችሁ ሰዎች ይህን ጽፌላችኋለሁ። ²⁷ እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ። ²⁸ አሁንም፥ ልጆች ሆይ፥ በሚገለጥበት ጊዜ እምነት እንዲሆንልን በመምጣቱም በእርሱ ፊት እንዳናፍር በእርሱ ኑሩ።
Показать все...
24👍 8🥰 2
Показать все...
Log in to Facebook

Log in to Facebook to start sharing and connecting with your friends, family and people you know.

ኢሳይያስ 53 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል? ² በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል፤ መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም። ³ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም። ⁴ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። ⁵ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። ⁶ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ። ⁷ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። ⁸ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ? ⁹ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ፤ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም ነበር። ¹⁰ እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል። ¹¹ ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሸከማል። ¹² ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።
Показать все...
18👍 5🔥 5
Фото недоступноПоказать в Telegram
🔥እንኳን ደስ አላችሁ በሐዋሳና በዙሪያዋ ያላችሁ!! 🔥ታህሳስ 5 እና 6 አርብ(9:30 ጀምሮ) እና ቅዳሜ(ጥዋት 3:00 ጀምሮ) በሐዋሳ ከተማ ታላቅ ትንቢታዊ Conference እና Prophetic School ተዘጋጅቶዋል። 🔥አገልጋይ ነብይ ፊልሞን እና ሌሎች ዘማሪዎች 🔥አንድ ሰው በትንሹ 10 ሰው ይዞ መምጣት አለበት።በዛ ቀን ከባድ ክብር ይገለጣል ሐዋሳዎች እስካገለግላችሁ ቸኩያለው SHARE💫 SHARE💫 SHARE💫     👇👇👇👇👇👇👇👇👇         @Prophetfilimiracle1
Показать все...
👍 4
01:18
Видео недоступноПоказать в Telegram
በኢየሱስ ስም እፀልያለሁ 🔥 #ARCMICHAEL https://www.facebook.com/ProphetSunesisOfficial?mibextid=ZbWKwL 👆👆👆
Показать все...
13.52 MB
34🔥 8👍 3
Фото недоступноПоказать в Telegram
12👍 3🔥 2
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.