cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

Gimba Media Network

#በዚ_ቻናል_ያዘጋጀንላቹ_ፕሮግራሞች ። ➠ ዜናዎች ➠ መዝናኛዎች ➠ አስገራሚ ታሪኮች ➠ ስለ ጤናዎ አዳዲስ መረጃዎች ➠ የቢዝነስ አሳቦች ሀሳብ፣አስተያየት፣ጥቆማ ከስር ባለው ሊንክ ይጻፉልን👇👇👇 https://t.me/GimbaChat

Больше
Рекламные посты
3 945
Подписчики
-324 часа
-267 дней
-14330 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

በልደታ ፍ/ቤት በድጋሚ መዝሙር ተዘመረ❗️❗️ ችሎቱ ተቋርጧል❗️❗️                                                                                                               ፍርድ ቤቱ ዛሬ ሲያየው የነበረውን የእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋን መዝገብ አቋርጦ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ።                                                                                                                                           ጋዜጠኞቹ ጎበዜ ሲሳይ፣ መስከረም አበራ ፣ ዳዊት በጋሻውና ገነት አስማማውን ጨምሮ በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ የተከሰሱ 24 በአማራ ጉዳይ ላይ የሚሰሩ ሰዎች ዛሬ ሃምሌ 25/2015 የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት የቀረቡ ሲሆን ውጥረት የበዛበት ችሎቱም ሳይጠናቀቅ መቋረጡን ሮሃ በችሎት ተገኝታ ተከታትላለች።                                                                                    ችሎቱ ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው "የምስክሮች ጥበቃ ሊደረግ ይገባል ወይስ አይገባም" በሚለው ክርክር  ላይ ውሳኔ ለመስጠትና የተከሳሾች አቤቱታ ላይ ብይን ለመስጠት ነበር። ነገር ግን ጠዋት 4:00 በችሎት አዳራሽ የተገኙ የተከሳሽ ቤተሰቦችና ታዳሚዎች እንዳይገቡ በፖሊስ  ታግደው ጋዜጠኞች ብቻ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡ ሆኖም  ዳኞቹ ከተሰየሙ በኋላ የተከሳሽ ጠበቆች ችሎቱ በዝግ መካሄደ የለበትም በሚል ተከራርክረው ዳግም ቤተሰቦችና ታዳሚያን ወደ ችሎት እንዲገቡ ተፈቅዷል፡፡ በችሎቱም የዳኞች መለዋወጥ በፍርድ ሂደቱ ላይ እንዳንተማመን አድርጎናል ሲሉ ተከሳሾች ቅሬታ አቅርበዋል፡፡በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ቀን ጀምሮ ዳኞች እየተቀያየሩ መሆናቸውን በማንሳት "የመሃል ዳኛው አቶ ረቡማ ተፈራ ብቻ ሳይቀያየሩ እየዳኙን እንደሆነ ነው የምናምነው በዚህም ደግሞ ዳኛው ከመንግስት ገለልተኛ ናቸው ብለን አናምንም" ብለዋል፡፡ ነገር ግን ተከሳሾቹ ይህንን አቤቱታቸውን በዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ በኩል እያሰሙ በነበረበት ወቅት የመሃል ዳኛው አቶ ረቡማ ለማስቆም ጥረት አድርገዋል፡፡"አቤቱታችሁን በፅሁፍ አስገቡ እንጂ ማንበብ አትችሉም" የሚል ምላሽም ነው የሰጡት፡፡ ሆኖም ተከሳሾቹ "አቤቱታችንን የአማራ ህዝብ ፣ የኢትዮጵያ ህዝብና ሚዲያዎች እንዲሰሙልን ስለምንፈልግ ህጋዊ መብታችንን ተጠቅመን አቤቱታችንን እናቀርባለን" በሚል ከወንበራቸው በመነሳት ሁሉም እጃቸውን አውጥተው እንደቆሙ ሮሃ ተመልክታለች፡፡ በዚህም ተከሳሽ ዮርዳኖስ አለሜ "የአማራ ህዝብ የግፍ እስረኞች ነን ስለዚህ ችሎቱ አቤቱታችንን ሊሰማን ይገባል ፣ እኛ እዚህ ፍርድ ቤት የቀረብነው ህጻናት አርደን ፣ ሴቶችን ደፍረን ፣ ሰው ገድለን አይደለም ፤ ለአማራ ህዝብ ስለታገልንና ድምጽ ስለሆንን እንጂ" ሲል አቤቱታውን አሰምቷል፡፡ጋዜጠኛ መስከረም አበራ "ትንሹን የመደመጥ መብታችንን ፍርድ ቤቱ ሊያከብርልን ይገባል፣ ችሎቱ አቤቱታችንን በቃል እንዳናሰማ የሚፈልግበትን ምክንያት ያሳውቀን" ስትል ጠይቃለች፡፡ መስከረም አክላም "ፍርዱና ዳኝነቱ የኢትዮጵያ ህዝብና የአማራ ህዝብ ነው ። ስለዚህ አቤቱታችንን በቃል እንድናሰማ ሊፈቀድልን ይገባል" ስትል ጠይቃለች፡፡ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው በበኩላቸው ፍርድ ቤቱ አዞ እስካሁን ያልተተገብሩ ውሳኔዎች እንዳሉ አንስተዋል፡፡ በተጨማሪም ረዳት ፕሮፌሰሩ "ቂሊንጦ ላሉ ታራሚዎች ቤተሰብ በሳምንት አራት ቀን ነው ምግብ እንዲያስገባ የሚፈቀድለት ፣ በተቀሩት ቀናቶች የሚቀርበው የመንግስት ምግብ ነው ፤ እኛ ደግሞ አማራ ክልል ላይ ህዝብ እየጨፈጨፈ ያለን መንግስት አምነን፣ ያቀረበልንን ምግብ አንበላም" ብለዋል፡፡ አክለውም "እኛ የታስርነው የኦሮሞ ብልጽግና አማራ ላይ የሚያደርሰውን  ግፍ በመቃወም ነው፤  ስለዚህ አገዛዙን በሚደግፍ የኦህዴድ ዳኛ አንዳኝም" ሲሉ ተደምጠዋ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ፡፡ ባጠቃላይ 24ቱም ተከሳሾች የመሃል ዳኛው አቶ ረቡማ አማራ ጠል በመሆናቸው እንዲነሱልን እንፈልጋለን የሚለውን አቤቱታቸውን በምክንያት እንዲያቀርቡ ሲጠይቁ በመከልከላቸው ከቆሙበት አንቀመጥም ብለዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም አቤቱታው እንዲነበብ አልፈቅድም በሚል ችሎቱን አቋርጧል፡፡ የመሃል ዳኛውም ስሜታዊ ሲሆኑ የታዩ ሲሆን የግራና ቀኝ ዳኛዎችም ሲያረጓጓቸው ታይተዋል፡፡ሆኖም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ብይን ለመስጠትና አቤቱታ ለማዳመጥ ተቀጥሮ የነብረው ችሎት ከመቋረጡ በፊት የተለያዩ ውሳኔዎች ተላልፈዋል፡፡ በዚህም መስከረም አበራ ልጇን ለማግኘት ያቀረበችው አቤቱታ ፣ ጋዜጠኛ ገነት አስማማው ቤተሰቦቿ እንዲጠይቋት ያቀረበችው ጥያቄ ፣ እና ከንብረት ጋር በተያያዘ በቀረቡ አቤቱታዎች ላይ እንዲፈጸሙ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡   ፋና ፣ ኢቢሲ ፣ አሚኮ እና ዋልታ ከዚህ ቀደም በተከሳሾች ላይ ያስተላለፏቸውን ዶክመንተሪዎች ከቋታቸው  ማውረዳቸውን ያሳወቁ ሲሆን ኦቢኤን ግን መልስ አልሰጠም፡፡ የዛሬው ውጥረት የሞላበትና ከባድ ክርክር የተደረገበት ችሎት ተቋርጦ የግራ ዳኛው ለጥቅምት 15/2016 ዓ.ም ምህረት ማለትም ሶስት ወር ገደማ ለሚፈጅ ጊዜ ቀጣይ ቀጠሮ ሲሰጡ ተካሶቹ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል፡፡በዚህም ተከሳሾቹ " በእሳት ለነደደው ቤተ_ እምነቴ፣                                                                                            ለተደፈረችው ምስኪኗ እህቴ ፣ በግፍ ለታረደው ወንድሜ ፣                                                                                                       ባጭር ለተቀጨው ለህጻኑ ልጄ፣ አላፈገፍግም ወደኋላ!"                                                                                                             የሚለውን መዝሙር ሲዝምሩና ሲያጨበጭቡ ታዳሚውም በጭብጨባ አጅቧቸዋል፡፡በፍርድ ቤቱ ዙሪያም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የታጠቀ የፌደራል ፖሊስ ተሰማርቶ ታይቷል፡፡ ይህ ©ጊምባ ሚድያ ኒትዎርክ የተሰኘ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።⬇️ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች ጆይን👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork
Показать все...
Gimba Media Network

#በዚ_ቻናል_ያዘጋጀንላቹ_ፕሮግራሞች ። ➠ ዜናዎች ➠ መዝናኛዎች ➠ አስገራሚ ታሪኮች ➠ ስለ ጤናዎ አዳዲስ መረጃዎች ➠ የቢዝነስ አሳቦች ሀሳብ፣አስተያየት፣ጥቆማ ከስር ባለው ሊንክ ይጻፉልን👇👇👇

https://t.me/GimbaChat

Фото недоступноПоказать в Telegram
Фото недоступноПоказать в Telegram
ሰበር ዜና! በዚህ ውድቅት ሌሊት በቆቦ ከተማ ዙሪያ ጦርነት ተከፍቷል።      አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ ሀምሌ 24/2015 ዓ/ም_አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ሀምሌ 24/2015 ከእኩለ ለሊት 6:30 ጀምሮ በቆቦ ከተማ ዙሪያ ልዩ ስሙ ካራይላ አከባቢ ከባድ የሆነ ውጊያ እየተካሄደ ስለመሆኑ ተገልጧል። የምስራቅ አማራ ፋኖዎች ከዙ 23 እስከ መድፍ ከታጠቀው  ከመከላከያ ጦር ጋር በከፍተኛ ውጊያ ላይ መሆናቸው ታውቋል። በዚህ ውድቅት ለሊት ከምሽግ ምሽግ እየዘለሉ በጠላት ኃይል ላይ የማያዳግም እርምጃ እየወሰዱ ነው ተብሏል። አካባቢው በተኩስ እሩምታ እየተናወጠ ነው። ምንጭ_አማራ ድምጽ ሚዲያ ይህ ©ጊምባ ሚድያ ኒትዎርክ የተሰኘ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።⬇️ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች ጆይን👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork
Показать все...
''አናጨው አጋጨው እንደነጋዴ ጨው!'' አለ ያገሬ ሰው! << መንግስት ከጠሸሸ እኛም ተከትለን መጠሸሽ አለብን ወይ ? ምን እየተካሄደ ነው? ይሄ እብደትና በገዛ ህዝብ ላይ ጦርነት የመክፈት አስነዋሪ ተግባር እዚህ ላይ ሊቆም ይገባል! ደማችንን ባፈሱት ፣ አብረውን በተዋደቁት በወንዶሞቻችን ላይ አንተኩስም! >> የሚል አቋም እየያዙ ያሉት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ቁጥር ፥ ከተራ ወታደሮች እስከ ከፍተኛ ባለማእረግ ድረስ በየጊዜው እየጨመረ ነው። ይህን ተከትሎም ''እንኳን ዘንቦብሽ እንደውም ጤዛ ነሽ'' የሆነው ተቋም ወደመከፋፈልና መካረር እያመራ ይገኛል! እብሪተኛው ቡድን ይህን ለመቅረፍ እንደመፍትሄ አድርጎት የሰነበተው '' በማንነት እየመረጡ ማሰርን '' እልፍ ሲልም እርምጃ መውሰድን ቢሆንም ፤ አሁን ግን በማንነት አማራ የሆኑት ብቻ ሳይሆን ደቡብን ጨምሮ ከበርካታ ኢትዮጵያውያን ህዝቦች የወጡ የሰራዊቱ አባላቶች '' የመንግስትን እብደት ተከትለን አናብድም!'' እያሉ ይገኛሉ። ከሰራዊቱ ያገኙትን አጋጣሚ ተጠቅመው የሚኮበልሉት ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ መጥቷል! በግዳጅ ላይ ሆነው ''የተሰጠንን ተልእኮ አንፈፅምም!'' የሚሉትም እየተበራከቱ ይገኛሉ! ዛሬ ወደ ራያ የተላከው የመንግስት ሀይል መካከል የተፈጠረው ሁነትም ከዚሁ ጋር የሚያያዝ ነው። ምናልባትም በቅርብ ቀናት በሰራዊቱ ውስጥ ጎልቶ የሚወጣ አንዳች ሁነት ልንመልከት እንደምንችል በቀላሉ መገመት አያዳግትም! መልካም ለሊት! ይህ ©ጊምባ ሚድያ ኒትዎርክ የተሰኘ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።⬇️ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች ጆይን👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork
Показать все...
Gimba Media Network

#በዚ_ቻናል_ያዘጋጀንላቹ_ፕሮግራሞች ። ➠ ዜናዎች ➠ መዝናኛዎች ➠ አስገራሚ ታሪኮች ➠ ስለ ጤናዎ አዳዲስ መረጃዎች ➠ የቢዝነስ አሳቦች ሀሳብ፣አስተያየት፣ጥቆማ ከስር ባለው ሊንክ ይጻፉልን👇👇👇

https://t.me/GimbaChat

Фото недоступноПоказать в Telegram
መረጃ|ወልድያ! በወልድያና አካባቢው ከንጋቱ 12 ሰዓት የጀመረው ውጊያ ተባብሶ መቀጠሉን ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመላክታል። ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ የጀመረው ውጊያ አድማሱን እያሰፋ ከጌሾበር እስከ ደቦት እና ወይንዬ ድረስ 6 ቀበሌዎችን ያካለለ ከፍተኛ ጦርነት እየተደረገ ይገኛል። በዚህም መሰረት ከወልድያ ወደ ጋሸና፣ ወደ ጎንደር እና ወደ ላሊበላ የሚወስዱ መንገዶች ተዘግተዋል። ስለደረሰው ጉዳት እስካሁን የታወቀ ነገር የለም። ➨ በተያየዘ ዜና ከ30 ደቂቃ በፊት በወልድያ በኩል አድርጎ ወደሳንቃ የሚጓዝ ከስድስት በላይ አይሱዙ እና ሁለት ኦራል የአብይ ሰራዊት አልፏል! ይህ ©ጊምባ ሚድያ ኒትዎርክ የተሰኘ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።⬇️ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች https://t.me/Amharaa
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
ይኸው ነው! ትናንት ብቻ ወደአስር የሚሆኑ አመራሮች ይፋዊ መልቀቂያቸውን በማህበራዊ ሚዲያ ለጥፈው አይቻለሁ ፣ አመራሩን ተከትለው የፖሊስና የፀጥታ ሀላፊዎችም ቀጠሉ ፣ አንዳንድ የፖሊስና የሚኒሻ አባላትም ''በዚህ ሰአትማ ከወገናችን ጎን ተሰልፈን እንሞታለን!'' እያሉ ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል። የብልጽግና አባላቶች ደግሞ በመንፈስ ከለቀቁ ቢቆይዩም አሁን ደግሞ ሰብሰብ እያሉ በአደባባይ እንደምታዩት ይፋዊ መልቀቂያ ማቅረባቸውን ቀጥለዋል! በርግጥ መልቀቂያም ሆነ ምንም ሳይሉ ፣ ሻንጣ ብቻ ይዘው የሚፈረጥጡት ''በተመላሽ'' አይቆጠሩም። Keep walking to the right way.👌 ➨ ይህ የጊሞባ ሚድያ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው መረጃዎችን ለማገኘት ጆይን በማለት ይቀላቀሉ👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork
Показать все...
ለኢትዮጵያውያን ዳቦ ማግኘት የሰማይን ያህል ቢርቃቸውም....! ጡሩምቤ ከሩሲያ ሲመለስ ፣ << ሩሲያ እኛ ስንዴ ኤክስፖርት ማድረግ መጀመራችንን በማስመልከት  ፣ ለ6ቱ የአፍሪካ ሀገራት በነፃ የምታቀርበውን ስንዴ ፣ ከእኛ እንድትገዛ የስምምነት ሰነድ ተፈራርመናል! >> አይልም ብዬ አልወራረድም! ይህ በእንዲህ እያለ ፣ የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ኤርትራ እና ሶማሊያን ጨምሮ ለስድስት የአፍሪካ አገሮች ስንዴ በነጻ ለማቅረብ ቃል ገብተዋል። ፕሬዝደንቱ ይኸን ቃል የገቡት የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጭምር በሚሳተፉበት የአፍሪካ ሩሲያ ጉባኤ በሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ሲጀመር ባሰሙት ንግግር ላይ ነው። ፑቲን በመክፈቻ ንግግራቸው  "በመጪዎቹ ሦስት እና አራት ወራት ከ25,000 እስከ 50,000 ቶን እህል በነጻ ለቡርኪና ፋሶ፣ ዚምባብዌ፣ ማሊ፣ ሶማሊያ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ እና ኤርትራ ለማቅረብ ዝግጁ እንሆናለን" ብለዋል። የፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን መንግሥት የዩክሬን እህል ለዓለም ገበያ እንዲቀርብ ይፈቅድ የነበረው ሥምምነት እንዲያበቃ በመወሰኑ ፣ አሜሪካን ጨምሮ ከምዕራባውያን ብርቱ ትችት ሲሰነዘርበት ቆይቷል። እስካሁን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በቱርክዬ አደራዳሪነት በተፈረመው ሥምምነት መሠረት 32.9 ሚሊዮን ቶን የምግብ እህል ከዩክሬን የእህል ጎተራዎች ለዓለም ገበያ ቀርቧል። '' የሩሲያን ውሳኔ ኃላፊነት የጎደለው ነው!'' ሲሉ የሚተቹት የምዕራቡ ዓለም ፖለቲከኞች '' በዚህ የሞስኮ ውሳኔ በደሐ አገሮች የሚኖሩ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ለረሐብ ይጋለጣሉ!'' ሲሉ ያስጠነቅቃሉ። ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ግን በሴንትፒተርስበርግ በመካሔድ ላይ በሚገኘው ስብሰባ በሥምምነቱ ከዓለም ገበያ ከቀረበው እህል ከ70 በመቶ በላይ የሚሆነው ከፍተኛ ገቢ ወይም ከአማካኝ በላይ ገቢ ላላቸው አገራት እንደቀረበ ተናግረዋል። ፑቲን እንዳሉት << ... እንደ ሱዳን ያሉ ደሐ አገሮች ከዩክሬን ወደቦች ከተላከው እህል የደረሳቸው ከ3 በመቶ በታች ነው። ምዕራባውያን አገሮች ደግሞ በአንድ በኩል የእህል እና የማዳበሪያ አቅርቦታችን እያስተጓጎሉ ነው። በሌላ በኩል አሁን በዓለም የምግብ ገበያ ለተፈጠረው ቀውስ ግብዝ ሆነው እኛን ይከሱናል! >> ሲሉ ተደምጠዋል። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስተር ከሳምንት በፊት ከዩክሬኑ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጋር በስልክ መነጋገራቸውን የገለፁ ሲሆን በውይይታቸውም ''የስንዴ አቅርቦት ጉዳይ !'' ዋነኛው እንደነበር ከዩክሬን በኩል የወጡት የመረጃ ምንጮች ይፋ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው! በነሲብ የሚመራው የሀገሪቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአለም አደባባይ መሳቂያ መሳለቂያ ከማድረግ አልፎ ሀገሪቷንና ህዝቦቿን ወደሚፈታተን የህልውና አጣብቂኝ ውስጥ እየከተታት እንደሚገኝ የአደባባይ ሀቅ ነው! ➨ ይህ የጊሞባ ሚድያ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው መረጃዎችን ለማገኘት ጆይን በማለት ይቀላቀሉ👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork
Показать все...
Gimba Media Network

#በዚ_ቻናል_ያዘጋጀንላቹ_ፕሮግራሞች ። ➠ ዜናዎች ➠ መዝናኛዎች ➠ አስገራሚ ታሪኮች ➠ ስለ ጤናዎ አዳዲስ መረጃዎች ➠ የቢዝነስ አሳቦች ሀሳብ፣አስተያየት፣ጥቆማ ከስር ባለው ሊንክ ይጻፉልን👇👇👇

https://t.me/GimbaChat

Фото недоступноПоказать в Telegram
ሰበር‼️ በሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ከተማ በዚህ ሰዓት ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እየተሰማ ይገኛል። ተኩሱ በድሽቃ ጭምር የታገዘ ነው ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል። ተኩሱ 04 ቀበሌ ምክር ቤቱ አካባቢ ነው ብለዋል። ቀን አካባቢ አስፋቸው በሚባል ቦታም ውጊያ ነበር፣ከባድ ጉዳት ደርሷል ብለዋል። Join ➨ @Gimbamedianetwork
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
ለማይበራ አምፖል ፣ ውሃ ለጠማው የውሃ ቆጣሪ የሚከፍለው ሰፊው ህዝብ ፣ ለማያየው ኢቲቪም እንዲከፍል ተወስኖበታል! ምናልባት አልፎ አልፎ አለምአቀፍ የሚዲያ አውታሮችን ለማሰስ ቴሌቪዥን ልመለከት እችላለሁ። EBCን ግን አይደለም ካየሁት ከቻናሎች ዝርዝር ከሰረዝኩ አመታት ተቆጥረዋል። ታዲያ! ተመልካች አልባውና የገዢዎቹ ጡሩምባ የሆነው EBC ከሰኔ ወር ጀምሮ የመብራት ክፍያ ጋር በየወሩ 10 ብር ''የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ'' እንዲከፈለው ማድረጉን ሰምተናል! በወር ጥቂት ቀን ለሚበራ መብራት እንከፍላለን ፣ መጥፋት ኃይል ''ቦግ እልም ሲጫወት'' ለሚያቃጥለው ቴሌቪዥንና መሰል የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ግን ''የስራችሁን ይስጣችሁ!'' ብለን እናልፋለን ፣ ለውሃ ጥፋትም እንዲሁ እንከፍላለን ፣ አንድ ቀን ካሳለፍን አፍንጫችንን ተይዘን ከቅጣት ጋር እንከፍላለን። ላልጠጣነው ውሃ ፣ ከጨለማና ከሻማ ግዢ ላላወጣን መጥፋት ሀይልስ ያው በተስፋ እንከፍላለን። እንዴት እንዴት ተደርጎ ላላየነውና ለማየት ለማንፈልገው ወደፊትም ለማናየው EBC ክፈሉ እንባላለን? ሠዎቹኮ በዚህ አያያዛቸው ፣ ይህን በቀን አንድ ጊዜ መመገብ ተስኖት በከፍተኛ የኑሮ ውድነትና ብስቁልና እየተሰቃየ የሚገኘውን ህዝብ ፣ ያለበትን ሸክምና ስቃይ ከማቃለል ይልቅ << የጣራና የግድግዳ ፣ የቴሌቪዥን ፣ .....ወዘተ ግብር ገብር >> እያሉ ሂደው ሂደው ፣ የቤት ቁሳቁሱን ከጨረሱ በኃላ '' ለምትተነፍሰው አየር ''Oxygen Tax'' ክፈል!'' ማለታቸው አይቀርም ! ''ተንቀናል!'' አለ መንጌ! join➨ @Gimbamedianetwork
Показать все...
የአብይ አህመድ ቀኝ እጅን ብርክ ብርክ ያሰኘው የምስራቅ አማራ ፋኖ ተጋድሎ!! << ከደቡብ እና ከምዕራብ እዝ ያመጣነው 2 ኮር ሰራዊት እንዴት በደቡብ ወሎ እና ሰሜን ወሎ ያለውን የፋኖ ታጣቂ መደምሰስ አቃተው? እንዴትስ በዚህ ደረጃ ሊዋጉን ቻሉ? >> ይህን ጠየቀው የሪፐብሊካን ጋርድ አዛዥ ጀነራል ብርሃኑ በቀለ ሰሞኑን በባህርዳር ከተማ ጀነራሎቹን ሰብስቦ በነበረበት ወቅት ነው! ጓዶች! 1 ኮር ማለት ከ 30 እስከ 50 ሺህ ወታደር ያቀፈ ማለት ነው! @Gimbamedianetwork
Показать все...
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.