Ethio Words
Открыть в Telegram
863
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-830 дней
Архив постов
863
📝 እናሸንፋቸው!!!
ወደፊት ለመሄድ ስትሞክር ወደኋላ ለመጎተት አንተን ለማደናቀፍ ይተቹኋል, ይስቁብሀል, አይሆንም ብለው ሊያቆሙህ ይታገላሉ ያለህን በሙሉ እንደሌለህ አድርገው ያሳጡሀል ነገር ግን ሁሉም ምቀኛ ስለሆኑ አይደለም!
የሚወዱህም ሰዎች ከመንገድህ የሚያስቀሩህ አሉ እንዳትጎዳባቸው በመስጋት ነገር ግን አንድ ነገር ብቻ ልንገርህ እነዚህን ሁሉ አልፈህ የሄድክ ዕለት ድል ያንተ እና ያንተ ብቻ ትሆናለች!!!
ያኔ ወደኋላ ዞረህ የመጣህበትን መንገድ እያየህ ትገረማለህ ለሌሎችም ትልቅ ትምህርት ትሆናለህ!
Join @ethiowords
863
📝 ደፋር መሆን አለብን!!!
ደፋር ሰው ማለት ፍርሀት የማይሰማው አይደለም ግን ከፍርሀቱ ጋር ፊት ለፊት የሚፋለም ነው' ይለናል ኔልሰን ማንዴላ።
ይሄን የምናነብ ሁላችንም ፍርሀታችንን ፊት ለፊት መጋፈጥ አለብን ምክንያቱም ፍርሀታችንን የምናስተናግድበት መንገድ የህይወት መዳረሻችንን በሁለት መንገድ ይወስነዋል።
1ኛው አዲስና አስገራሚ የህይወት አጋጣሚዎችን እናጣጥማለን
2ኛ ምንም ሳንሞክር እንደፈራን እናልፋለን
Join @ethiowords
863
📝 ከራስህጋ ተወዳደር!
በህይወት ሩጫ ውስጥ የሚያሸንፈው ቀድሞ የደረሰ ብቻ አይደለም ውድድሩን የጨረሰም ነው። የግድ በዙሪያችን ካሉ ሰዎች ቀድመን ወይም እኩል መድረስ አለብኝ ብለን ራሳችንን ማስጨነቅ የለብንም።
ራሳችንን ካወዳደርን አይቀር ከሰዎች ጋር ሳይሆን ከትላንቱ ማንነታችን ጋር መሆን አለበት። ስኬት የሚለካው በራስ መነፅር እንጂ ከሌሎች ጋር ባለን ንፅፅር አይደለም።
Join @ethiowords
863
📝 ዋጋ ክፈል!
የምትፈልገውን ህይወት ለመኖር መጀመርያ የሚያስፈልገውን ዋጋ መስጠት መቻል አለብህ ፤ ዋጋ ያልተከፈለበትን እቃ መውሰድ እንደማትችል ሁሉ ዋጋ ያልከፈልክበትም ስኬት ያንተ ሊሆን አይችልም!!!
Join @ethiowords
863
📝 ከራስህ ጋር ብቻ!
በህይወት ሩጫ ውስጥ የሚያሸንፈው ቀድሞ የደረሰ ብቻ አይደለም ውድድሩን የጨረሰም ነው። የግድ በዙሪያችን ካሉ ሰዎች ቀድመን ወይም እኩል መድረስ አለብኝ ብለን ራሳችንን ማስጨነቅ የለብንም።
ራሳችንን ካወዳደርን አይቀር ከሰዎች ጋር ሳይሆን ከትላንቱ ማንነታችን ጋር መሆን አለበት። ስኬት የሚለካው በራስ መነፅር እንጂ ከሌሎች ጋር ባለን ንፅፅር አይደለም።
Join @ethiowords
863
📝 አስተውል!
የምታደርጋቸውን እያንዳንዶቹን ነገሮች ስታከናውን በማስተዋል ይሁን ለምንድን እንደምታደርጋቸው እወቅ ፣ ከአፍህም ለሚወጡት ቃላት ተጠንቀቅላቸው !
ምክንያቱም አንዴ ከአንተ ያመለጠን ነገር መልሰህ ልትጠግነው አትችልም ይሄን በማድረጌ ማን ምን ይጎዳል ብለህ ስታስተውል ግን ላንተም ከፀፀት የፀዳህ ለሌሎችም እረፍት የምትሰጥ ሰው ትሆናለህ!
Join @ethiowords
863
📝 መልካም እንሁን!
በተቻለህ አቅም ሁሉ ለሰዎች መልካም ሁን ምን አይነት ሁኔታ ላይ እንዳሉ አታውቅም እና አትክፋባቸው!
ክፋ ለመሆን የተፈጠረ ሰው የለም ሁኔታዎች ግን ሰዎችን ይቀያይሯቸዋል ! የእኛ ጥሩ መሆን ግን በእነዚያ ሰዎች ህይወት ላይ የሚፈጥረው ተፅዕኖ ቀላል አይደለም !
ስለዚህ በተገኘህበት ቦታ ሁሉ የጥሩነት ምሳሌ ሁን ፤ ሁኔታዎች አይገድቡህ የበላያቸው ሆነህ አስደንግጣቸው !!!
Join @ethiowords
863
📝 እንዳትፈራ!
ለምንድነው የምትፈራው ? ምን ላለማጣትስ ብለህ ነው ከመንገድህ የቆምኸው? ማድረግ የምትፈልገውን ነገር ላለማድረግ ምን ገደበህ?
አለም ላይ የተሰጠህ እድሜ በሙሉ ያንተ ውድ ስጦታ ነው ! እያንዳንዷን ግዜህን በፈለግኸው መንገድ ልትጠቀምባት ተፈቅዶልኋል የምታደርገውን ማወቅ ያንተ ድርሻ ነው!
ብትከስር እንኳን መነሳት ትችላለህ ብትወድቅም ድጋሚ ከፍ ማለትህ አይቀርም ስለዚህ ወንድሜ ባታደርገውም የሚሆነው መሆኑ አይቀርምና ወደፊት መራመድን አትፍራ !
Join @ethiowords
863
📝 ከሰው አትጠብቅ !!
ለችግርህ ጊዜ የራቁህ ለስኬትህ ዙሪያህን ቢከቡህ አትደነቅ፤ በከባዱ ጊዜህ ትዝም ያላልከቸው በምርጡ ጊዜ ፍቅር በፍቅር ቢሆኑ እንዳይገርምህ።
የዛሬም ሺ አመት ሰዎች እንደዚህ ነበሩ፤ ዛሬም ነገም እንዲህ ናቸው። ስለዚህ ከሰው ምንም አጠብቅ! ከፈጣሪህ ቀጥሎ ራስህን እመነው! ራስን እንደመጠራጠር ህልም ገዳይ ነገር የለም!
Join @ethiowords
863
📝 በፈጣሪህ ተደገፍ!
ህይወትህን የሚቀይረው ከሰው ጠብቀህ የምታገኘው ነገር አይደለም፤ ፀጋው፣ ስጦታው፣ ቸርነቱ ከማያልቀው ከፈጣሪህ ከምታገኘው በረከት ነው ህይወትህ የሚቀየረው።
ወዳጄ በጭራሽ ከሰው እንዳጠብቅ፤ ሰው ማለት ሸንበቆ ነው የሆነ ቀን መቀንጠሱ አይቀርም! ከፈጣሪ ቀጥሎ ራስህን እመነው!!!
Join @ethiowords
863
📝 ከሰው መጠበቅ አቁም!
ልብህን የሚሰብረው ከሰዎች ብዙ መጠበቅ ነው፤ ስለዚህ ከሰዎች ብዙ አጠብቅ። እህቴ የሚከፋሽ ሌሎች የሚያደርጉልሽን ጠብቀሽ ስላላገኘሽ ነው።
ከሰው መጠበቁን አቁመን ደስታችንን ከአላህ እና ከራሳችን ልብ ውስጥ ማግኘት ነው ያለብን፤ ያኔ አንዱን ቀን ደስ ብሎን ሌላኛውን ቀን አይከፋንም ምክንያቱም ደስታችን ሌሎች ላይ ጥገኛ አይደለም።
Join @ethiowords
863
📝 ምረጥ እና ወስን!
ሁለት አማራጮች ፊትህ ቁጭ ተደርገው የቱን መወሰን እንዳለብህ ግራ የሚገባህ ጊዜ አለ አይደል የቱን ልስራ ? ምን ልማር ? ማንን ላግባ ? መቼስ ይሁን ? የትኛውን ትምህርት ላጥና ...?
ብዙ ከከባድ እስከ ቀላል የሆኑ ምርጫዎች ይቀርቡልሃል እናም አንድ ነገር ብቻ ልምከርህ ራስህን ብዙ አታስጨንቅ ዱአ አድርግ ጌታህን ጠይቅ ከዛም በደንብ ትኩረት አድርገህ አስተውል ጥቅሙንም ጉዳቱንም ዝርዝር አድርገህ እይ ከዛ ቶሎ ወስን የሚመጣው ነገር ካለው በላይ አያስፈራህ !!!
Join @ethiowords
863
📝 አታመንታ!
ቁጭ ብለህ እንዲህ ባደርግ እንዲህ ቢሆን አትበል! አድርገው! ወደ ተግባር ግባ! ወዳጄ ባህሩ ላይ ማፍጠጥ አያሻግርህም ተነስተህ ጀልባውን መቅዘፍ አለብህ።
ከአልጋህ ተነስ፣ ስፖርቱን ስራ፣ መፅሀፉን አንብብ፣ በጊዜህ ወደ ስራህ ግባ ፤ ወዳጄ የተግባር ሰው ካልሆንክ በሀሳብ መንሳፈፍ ነው ስራህ! ዳይ ተነስ!
Join @ethiowords
863
📝 እሄንንም ታልፈዋለህ!
"ፈጣሪ ስጦታ ሊሰጥህ ሲል የስጦታው መሸፈኛ ችግር ነው፤ ትልቁ የፈጣሪ ስጦታ ሊሰጥህ ሲል በትልቅ ችግር ተጠቅልሎ ይደርስሀል" ይለናል ደራሲ ኖርማል ቪንሰንት ፔል።
አሁን የገጠመህ ችግር የማይታለፍ ቢመስልም ብዙ ስጦታዎች ይዞ እንደሚመጣ አትጠራጠር!!!
Join @ethiowords
863
📝 ሁሉም ለበጎ ነው
ፈጣሪ በነገሮች በሁኔታዎች ነው የሚያናግርህ፤ በጆሮህ መጥቶ እንዲህ አድርግ አይልህም፤ በህይወት እየሆነ ያለው ነገር በሙሉ ለምክንያት ነው።
ንቁ ሆነህ በህይወትህ የሚሆነውን ሁሉ ማስተዋል አለብህ! ደግሞ አትርሳ ተማሪ ካለ አስተማሪ የትም ቦታ አለ!!!
Join @ethiowords
863
ታገስ!!!
የምትፈልገው ነገር ለመሳካት ረጅም ጊዜ ሊወስድ ይችላል ግን ተስፋ መቁረጥ የለብህም፤ ምክንያቱም ጊዜው እንደሆነ መሄዱ አይቀርም።
ጥቂቶች ስኬታማም ደስተኛም የሚሆኑት የተለዩ ስለሆኑ ወይ እድለኛ ሆነው አይደለም፤ ላመኑበት ጉዳይ በፅናት እና በትዕግስት ስለሚቆሙ ነው። አንተም ለዚህ አታንስም ወዳጄ ታገስ!
Join @ethiowords
863
ነገሮችን በቀና እይ!!!
ከምንም ነገር በላይ ሰው ላይ አትክፋ መልካም ሁን ሲያሸንፉ ስታይ አይንህ ደም አይልበስ ተደሰት ጠይቃቸው እንዴት አድርጋችሁ አሳካችውት በላቸው እንጂ ፈጣሪ ለእነርሱ አደላ አትበል ሌሎች ቀድመው ማሸነፍ ስለቻሉ አንተ ወድቀህ የቀረህ አይምሰልህ ከቀደሙህ ተምረህ የባሰ ከፍ እንድትል ነው ከእነርሱ ኋላ ያለኸው ስለዚህ ወዳጄ የሰዎችን ስኬት ከማኮሰስ እና በመቀደምህ ከማዘን እንኳን ተሳካላቸው እኔስ ከእነርሱ ምን ልማር በል!
Join @ethiowords
863
እባክዎን ለተመረቁ ጓደኞችዎ ወይም ቤተሰቦችዎ ቻናላችንን ያካፍሉ። ቻናላችንን ከተቀላቀሉ በየቀኑ የምንለጥፋቸውን የ0 አመት ስራዎች ሊያገኙ ይችላሉ
https://t.me/+fojMriihIxFiZWM8