cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

አብሰራ ገብርኤል ለማርያም

እኔ #በእግዚአብሔር_ፊት የምቆመው #ገብርኤል_ነኝ በቻናላናችን የሚሰጡ ነገሮች መንፈሳዊ ትምህርቶች መንፈሳዊ ምክሮች መንፈሳዊ መዝሙር መንፈሳዊ ጥያቄዎች መንፈሳዊ ስዕልዎች በየለቱ ስንክሳር አስተያየት ካላቹ 👇👇👇 https://t.me/Enatemareyam21 https://t.me/Enatemareyam21

Больше
Рекламные посты
2 989
Подписчики
+424 часа
+327 дней
+1930 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

[ ስንክሳር ሰኔ - ፳፪ - ] .mp34.33 MB
Фото недоступноПоказать в Telegram
🕊 [ † እንኳን ለቅዱሱ አባታችን የዋህ ዻውሊ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ] †  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † 🕊  †  ቅዱስ ዻውሎስ የዋህ  †  🕊 † በ፬ [ 4 ] ኛው መቶ ክ/ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ግብፅ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ቅዱሱ ስሙ ዻውሎስ ቢሆንም ብዙ ጊዜ የሚጠራው "የዋህ ዻውሊ" በሚል ነው:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :- የዋህ ዻውሊ ከሕጻንነቱ ጀምሮ መጻሕፍትን የተማረ: ግን ደግሞ ትዕቢት: ቁጣና ቂምን የማያውቅ ገራገር ሰው ነው:: እድሜው ለአካለ መጠን ሲደርስ ቤተሰቦቹ ሚስት አግባ አሉት:: እርሱ ባያስብበትም ወገኖቹን ላለማሳዘን አገባ:: እንዳለመታደል ሆኖ ግን ያገባት ሴት በጣም ቆንጆ በዚያም ላይ ክፉ ነበረች:: የዋህ ዻውሊ ክፋቷን ሁሉ ታግሶ ለበርካታ ዓመታት አብሮ ኖረ:: ልጆችንም አፈሩ:: አሁንም ግን እርሷ ከክፋቷ ልትታገስ አልቻለችም:: ይባስ ብሎ ዻውሊ በሌለበት ከሌሎች ወንዶች ጋር ትዘሙት ያዘች:: የዋሁ ሰው ይሕንኑ ያውቃል ግን የእግዚአብሔርን ሥራ ዝም ብሎ በተስፋ ይጠብቅ ነበር:: ለነገሩስ እሱ ያርሳል: ይቆፍራል: ነዳያንን ያበላል: እንግዳ ይቀበላል እንጂ ክፋትን ለማሰብ ጊዜ አልነበረውም:: አንድ ቀን ግን ለሥራ ወደ በርሃ ወጥቶ አንድ ግሩም ዜና ሰማ:: "አባ እንጦንስ ምንኩስና የሚባል ሕይወተ መላእክትን ጀምሯል: ደቀ መዛሙርትንም ይቀበላል" አሉት:: ግን ሚስትና ልጆች አሉትና ምን ያደርጋል? የዋህ ዻውሊ ሙሉ ቀን ሢሠራ ውሎ ወደ ቤቱ ሲመለስ ግን የጠበቀው ሌላ ነው:: ሚስቱ በራሱ መኝታ ላይ ከአገልጋይ እረኛው ጋር ራቁታቸውን አገኛቸው:: ልብ በሉልኝ በትክሻው ሞፈርና ምሳር: መጥረቢያም ይዟል:: እርሱ ግን ክፉን አላሰበም:: ጥሩ ልብስ አንስቶ ሁለቱንም አለበሳቸው:: እንዲሕም አላቸው:- "ከዚሕ በሁዋላ እኔ አልመለስም:: ሀብት ንብረቴን ውረሱ: በደስታም ኑሩ:: የልጆቼን ነገር ግን አደራ" ብሏቸው ተነሳ:: በእጁ ምንም አልያዘም:: በትከሻው ያለችውን ብጣሽ ጨርቅ ይዞ ወደ በርሀ ተጉዋዘ:: አባ እንጦንስም ተቀብለው አስተምረው አመነኮሱት:: ከዚያች ቀን ጀምሮ ራስን ዝቅ በማድረግ: በመታዘዝ አገለገለ:: ጾም: ጸሎትና ስግደቱንማ ማን ቆጥሮት:: እያለ እያለ ከብቅዐት ማዕርግ ደረሰ:: ምዕመናንም ሆነ መነኮሳት ሊጠይቁት ሲመጡ የእያንዳንዱ ኃጢአት በግንባራቸው ተጽፎ ይመለከት ነበርና ስለነሱ ሲያለቅስ ቅንድቡ ተላጠ:: ሰውነቱም አለቀ:: አንድ ቀን ጋኔን የያዘውን ሰው ፈውስ ብለው አመጡለት:: እርሱ ግን በአጋንንት ላይ ሥልጣን እያለው በትሕትና ተጠግቶ ጋኔኑን "አባ እንጦንስን ከምጠራብህ ቀስ ብለህ ውጣ" አለው:: ጋኔኑ ግን የፈራው መስሎት በትዕቢት "እንጦንስ ማነው?" አለው:: ያን ጊዜ የዋህ ዻውሊ እንደ እሳት ከጋለ ድንጋይ ላይ ቁሞ "ሕያው እግዚአብሔር ምስክሬ ነው:: ይሕ ጋኔን ካልወጣ አልወርድም" አለ:: ወዲያው በዘንዶ አምሳል ከሴትዮዋ ወጥቶ እየጮኸ ወደ ቀይ ባሕር ገባ:: ቅዱስ ዻውሊ የዋሕም እንዲሕ በቅድስና ተመላልሶ በዚሕች ቀን በመልካም ሽምግልና ዐርፏል:: " የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር: ደስታ: ሰላም: ትእግስት: ቸርነት: በጐነት: እምነት: የውሃት: ራስን መግዛት ነው:: እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም:: የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ::" [ገላ.፭፥፳፪] (5:22) 🕊 [ † ሰኔ ፳፪ [ 22 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. ቅዱስ አባ ዻውሊ የዋሕ ፪. ቅዱሳን ወክቡራን ቆዝሞስና ድምያኖስ [ ሰማዕታት ] ፫. ቅድስት ቴዎዳዳ ሰማዕት [ እናታቸው ] ፬. አንቲቆስ: ዮንዲኖስና አብራንዮስ [ ሰማዕታት ] [ †  ወርኀዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት ፪. ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ፫. ቅዱስ ደቅስዮስ [ የእመቤታችን ወዳጅ ] ፬. አባ እንጦንዮስ [ አበ መነኮሳት ] [ † አምላካችን ከቅዱስ ዻውሊ የውሃትን: ትእግስትን : በጐነትን : ጸጋ በረከትን ይክፈለን:: አሜን:: † ] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
Показать все...
00:31
Видео недоступноПоказать в Telegram
               †                [ ከርኵሰቱ ያልጠራ ትውልድ አለ ] " አባቱን የሚረግም ፥ እናቱንም የማይባርክ ትውልድ አለ። ለራሱ ንጹሕ የሆነ የሚመስለው ከርኵሰቱ ያልጠራ ትውልድ አለ። ከፍ ከፍ ያሉ ዓይኖች ያሉት ፥ ሽፋሽፍቶቹም ወደ ላይ የሚያዩ ትውልድ አለ።" [ ምሳ.፴፥፲፩]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
Показать все...
2.20 MB
1
[ + መንፈሳዊ ድካም + ].mp36.51 MB
Фото недоступноПоказать в Telegram
💛 ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 🕊     ም ክ ረ     ቅ ዱ ሳ ን     🕊 ▷  " የድካም ዓይነቶችና መፍትሔው !  " [    " ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ "    ] [                        🕊                        ] ----------------------------------------------- ❝ ፊትህን ከእኔ አትሰውር ፥ ተቈጥተህ ከባሪያህ ፈቀቅ አትበል ፤ ረዳት ሁነኝ ፥ አትጣለኝም ፥ የመድኃኒቴም አምላክ ሆይ ፥ አትተውኝ። ❞ [  መዝ . ፳፯ ፥ ፱  ] ❝ ምንም እንኳ የማልጠቅምና ሀጢያተኛ ብሆንም ያለማቋረጥ ደጆችህን አንኳኳለሁ፡፡ ❞ [  ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ  ] 🕊                        💖                     🕊                              👇
Показать все...
1
Фото недоступноПоказать в Telegram
1
asasibi.mp36.69 MB
Фото недоступноПоказать в Telegram
1
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.