cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

𝙳𝚒𝚟𝚒𝚗𝚎 𝙿𝚘𝚠𝚎𝚛 𝙶𝚘𝚜𝚙𝚎𝚕 𝙼𝚒𝚗𝚒𝚜𝚝𝚛𝚢

🔥🔥 🇪🇹🔥🔥 ሰው #ከድነት ከጎደለ #ራሱን ይዞ ይጎላል #ከተልዕኮ ከጎደለ ግን #ትውልድን ይዞ ይጎላል🌍 #ሞት_ራሱ_ሞቷል፡፡ #አሰተያየት_ካለዎት

Больше
Рекламные посты
480
Подписчики
Нет данных24 часа
-57 дноК
-930 дноК

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

#የኮንሶ_መጽሐፍ_ቅዱስ_ሥርጭቱ_የትርጉሙና_የሕትመት_ሥራው_ተጠናቀቀ በቅርቡ የትርጉሙና የሕትመት ሥራው ተጠናቆ ከውጭ ሀገር ተጓጉዞ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው የኮንሶ መጽሐፍ ቅዱስ በቀጣይ ጥቂት ሳምንታት ውስጥ የምረቃ ሥነ ስርዓቱ ተከናውኖ ሥርጭቱ በይፋ ይጀመራል ተባለ። የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር እንዳስታወቀው ከውጭ ሀገር ተጓጉዞ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው የኮንሶ መጽሐፍ ቅዱስ የኮንሶ ዞን ዋና ከተማ ወደሆነችው ካራት ከተማ የተጓዘ ሲሆን እስካሁን ድረስ ለትርጉም ሥራው ካወጣው ወጪ በተጨማሪ ለሕትመቱ፥ ለመርከብ ማጓጓዣና ለሌሎች ተያያዥ ወጪዎች የወጣውን ተጨማሪ የገንዘብ ወጪ ሙሉ በሙሉ ሸፍኗል። ማኅበሩ ‘ይህችን ቀን ለማየት ለ18 ዓመታት በጸሎትና በትእግሥት ስትጠባበቁ ለቆያችሁ የኮንሶ ክርስቲያኖችና ምእመናን እንዲሁም አብያተ ክርስቲያናት እንኳን ደስ አላችሁ’ ብሏል። በዚህ ሥራ ውስጥ ደከመን፥ ሰለቸን ሳይሉ ለተሳተፉ የትርጉም ሠራተኞችና ሥራውን በመደገፍ ለውጤት ላበቁ አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም ለማኅበሩ የትርጉም ክፍል ሠራተኞች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቱን የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ አስተላልፏል፡፡ #ለበለጠ_መረጃ EGBCC ይከታተሉን፡፡ ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!
Показать все...
⚠️⚠️⚠️⚠️ ይሄን ሰሞን በከተማችን የተለያዩ ቦታዎች ራስን ማጥፋት በዝቷል። በተለይ በአፍላው እድሜ በሚገኙ ወጣቶች ዘንድ ራስን ማጥፋት በጣም እየጨመረ ነው። እባካችሁ ራሴን ላጠፋ ነው ወይም መሮኛል ብሎ ለፖሰተ ሰው ብታቁትም ባታውቁትም አብሮነታችሁን ድጋፋችሁን አሳዩ እንጂ ቀልድ አትቀልዱ። ለቀልድና ጨዋታ ብዙ የተሻለ ቦታ አለ። በቅርብ የምናቃቸው ሰዎች መሞታቸው ሲገለፅ የአብዛኛው ጓደኞቻቸው ምላሽ "እኔ መች ጠረጠርኩ... ደብሮኛል እያለኝ.. " ምናምንም በሚሉ ፀፀቶች የተሞላ ነው። በዙርያችሁ ላለ ሠው ሁሉ ትኩረት ስጡ! -------------------------------------------------------- በዓመት እስከ 800,000 ሰዎች ራሳቸውን እንደሚያጠፉ የWHO ሪፖርት ያመለክታል፡ ከዚህ ቁጥር በላይ ያሉ ሰዎች ደግሞ ራሳቸውን የማጥፋት ሙከራ ያደርጋሉ ። እድሜያቸው ከ 15 እስከ 29 ዓመት በሆኑ ወጣቶች ሁለተኛው ከፍተኛ ሞት የሚመዘገብበት ችግር ነው ፡ እንዲሁም 79% ያህሉ በዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሃገራት ላይ የሚስተዋል ነው ። ሰዎች ራሳቸውን ለማጥፋት መርዝ መጠጣት መታነቅ ፣የጦር መሳሪያ መጠቀም፣ በዋናነት ይጠቀማሉ ። አጋላጭ ሁኔታዎች ----------------------------------------------------------------- የተለያዩ የአዕምሮ ህመሞች በተለይም ድባቴ (Depression) ከፍተኛ የአልኮል መጠጥ ችግር ፣ከባድ አካላዊ ህመም ፣ የኢኮኖሚ ቀውስ፣ ጭንቀት፣ ድንገተኛ ግጭትና ብቸኝነት ዋና ዋና በአጋላጭ ችግሮች ናቸው ። እንዲሁም ቀደም ባለ ጊዜ ያልተሳካ ራስን የማጥፋት ሙከራ ከነበረ ዋነኛ አጋላጭ ችግር ሊፈጥር ሊሆን ይችላል ። መከላከያ መንገዶች ----------------------------------------------------------------- ራስን የማጥፋት ችግር በሚገባ መከላከል ይቻላል በተለይም ራስን ለማጥፋት የሚረዱ ምቹ ሁኔታዎችን መቀነስ፣ ተደጋጋሚ የሆነ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን በመገናኛ ብዙሃን በመስጠት፣ ትምህርት ቤቶችን መሰረት ያደረገ ማዕከል በማደራጀት ለመምህራን ለወላጆች እንዲሁም ለትምህርት ቤት ማህበረሰብ በቂ የቅድመ ጥንቃቄ መረጃና ትምህርት መስጠት እንዲሁም ለተማሪዎች የማማከር አገልግሎት ማመቻቸት፣ የአልኮል መጠጥ አጠቃቀም ላይ ጥንቃቄ ማድረግ ፣ የአእምሮ ህመሞችን ቶሎ መለየትና በቂ ህክምና ማድረግ እንዲሁም ተገቢውን ክትትል ማድረግ፣በቂ የሱስ ማገገሚያ ማዕከላትን ማቋቋም። ================================ ብዙ ሰዎች ህመማቸውን መከፋታቸውን የሚያወሩለት ወዳጅ አጥተው ሶሻል ሚዲያ ላይ ነው ሚገልፁት። እንዲህ አይነት ፖስቶችና መልእክቶች ስታዩ ረጋ ብላችሁ ምላሽ ስጡ። ቀልድ ነው ብላችሁ በምታላግጡበት ሰአት ያ ሰው ወደሞት እየቀረበ ይሆናል። በዚህ ርዕስ ሰፋ ያለ ፅሁፍ ይዤ እቀርባለሁ። ባላችሁበት የቴሌግራም ግሩፖች #share አድርጉ Cc @psychoet
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
ሰላም እንደምን አመሻችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ላልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች እያደረግን ያለነውን ጸሎት በዚህ ሳምንትም እንቀጥላለን፡ ፡ በሚቀጥሉት ቀናት ለቦዲ የሕዘዝብ ክፍል በየማለዳው እንጸልያለን፡፡ ብዙዎች የዚህ የጸሎት ንቅናቄ አካል ይሆኑ ዘንድ ሼር አድርጉልን ወደዚህ ገጽም ሰዎችን ይቀላቅሉ፡፡ የሕዝቡ ስም - ቦዲ የሕዝብ ብዛት - 13,000 ዋና ቋንቋ - ሚን ብዙ ተከታይ ያለው ሐይማኖት - የጎሳ እምነት ( 94.00 %) ክርስትና - 6.00% ወንጌላውያን ክርስቲያኖች - 3.85 % መጽሀፍ ቅዱስ- በከፊል ተተርጉሟል የእየሱስ ፊልም - አለ የተለያዩ የወንጌል መልዕክቶች በድምጽ ቅጂ - አለ
Показать все...
🔥 1
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 1፤ ሃሌ ሉያ። ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን አመስግኚ። 2፤ በሕይወቴ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤ በምኖርበት ዘመን ሁሉ ለአምላኬ እዘምራለሁ። 3፤ ማዳን በማይችሉ በሰው ልጆችና በአለቆች አትታመኑ። 4፤ ነፍሱ ትወጣለች ወደ መሬቱም ይመለሳል፤ ያን ጊዜ ምክሩ ሁሉ ይጠፋል። 5፤ የያዕቆብ አምላክ ረዳቱ የሆነ ተስፋውም በአምላኩ በእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምስጉን ነው፤        (መዝሙር 146) ✴️✴️ባለፍንበት ጎዳና ሁሉ በከፍታም በዝቅታም ከእኛ ጋር የነበረውን፤ ደግሞም በመጪውም ዘመን ብቸኛ መታመኛችን የሆነውን እርሱን እግዚአብሔርን በማስተዋል የምንደገፍበትና በሙሉ ልብ የምናመልክበት ዓመት ይሁንልን።✴️✴️ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼       2️⃣0️⃣1️⃣6️⃣            🌼  መልካም አዲስ ዓመት  🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 TRUE LOVE ❤️❤️❤️ ONE FAMILY 🤗🤗🤗 STRONG FELLOWSHIP💪💪🏿💪
Показать все...
👍 1🔥 1
መልካም አዲስ አመት ይሁንላችሁ! ውድ የDivine power Gospel Ministery ኢትዮጵያ ቤተሰቦች እንኳን ለ2016 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ፤ ያለፈውን አመት የእግዚአብሔርን አብሮነት፣ ረዳትነት ያያችሁት በሕይወታችሁ ሁሉ ጥበቃው የተገለጠበት ዓመት እንደነበር እምነታችን ነው፡፡ አዲሱ አመት በሕይወታችሁ እግዚአብሔር ዓላማውን የሚፈጽምበት፣ ከእርሱ ጋር በተልዕኮውተሳታፊ የምትሆኑበት እንዲሆን መልካም ምኞታችን ነው፡፡ በዚህ አገልግሎት ደግሞ የተቀበልነውን የወንጌል ተልዕኮ ስራ በጋራ በንቃት ምንወጣበት፣ ከቤተክርስቲያን እና ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር የእግዚአብሔርን መንግስት ስራ ለማስፋት በጋራ ምንቆምነት ነው የዚህ አካል እንደሆናችሁ ሁሉ አብረን እንድንተጋ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ መልካም አዲስ አመት !
Показать все...
ጌታ እኮ🥰 “ዳሩ ግን የስብከቱ ሼል በእኔ እንዲፈጸም አሕዛብም ሁሉ እንዲሰሙት፥ ጌታ በእኔ አጠገብ ቆሞ አበረታኝ፥ ከአንበሳ አፍም ዳንሁ።”   — 2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥17 TRUE LOVE❤️ ONE FAMILY🤗 STRONG FELLOWSHIP💪 Join us @divineService1040 @divineService1040 @divineService1040
Показать все...
🔥 2❤ 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
1.በወሎ ምድር የቤተክርስትያን ተከላ ንቅናቄ እንዲጀመር። 2. ከ 6,000 በላይ አዳዲስ የክርስቶስ አብያተክርስትያናት ይተከሉ ዘንድ። 3. ስድስት ሚልዮን ለሚጠጉት የወሎ የጠፉትን ነፍሳት የሚፈልጉ ስለመከሩ ግድ የሚላቸውን የመከሩን ሰራተኞች እግዚአብሄር አብ እንዲልክ (ማቴ9፥37) 4. በዛም ያሉት ሚሶናውያን ከመከሩ ብዛት አንጻር እጅግ ጥቂት ሚሶናውያን ቢሆኑም እግዚአብሄር የቤተክርስትያን ተከላ ንቅናቄን በወሎ ህዝብ መሃል በነሱ እንዲጀምር   በነዚህ ጉዳዮች ላይ ግድ ብሎን እንድንጸልይ ይሁን። አለበለዛ ዪሄ ሁሉ ሚልዮን ህዝብ ወደሲኦል ሲላክ ግድ አዪለንም ማለት ነው የሚሆንብን።
Показать все...
🥰 2🔥 1🤔 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱ ወዳሉበት ቀርቦ እንዲህ አላቸው፤ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጥቶኛል፤ ስለዚህ ሂዱና ሕዝቦችን ሁሉ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ አስተምሯቸው፤ እኔም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።” ማቴዎስ 28:18-20
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
"አንቺ ኢትዮጵያ እረፍትሽ ይምጣ! በምድራችን ላይ ጦር እና የጦር ወሬ ሰምተን መደንገጥ ካቆምን ቆየን፡፡ ሞት፣ ውድመት፣ እንባ ተለመዱ ምናልባት የቤታችንን በር ስላንንኳኩ መሰል በሩቅ የእነዚህ ስብራት አድማጭ የሆንን ሰዎች ለመናገር፣ እምቢ ለማለት ደነዘዝን፡፡ ወጣት ያለግዜው ሲሞት፣ እናት ስለልጆቿ ስታነባ፣ ቤተሰብ ሲበተን፣ ሕጻናት ያለ አሳደጊ ሲቀሩ አየን ተመለከተትን ዛሬም ግን ከአዙሪታችን መውጣት አልቻልንም፡፡ ምድራችን በንጹሃን ደም ጨቅይታለች በመበለቶች ዋይታ ፣ በሕጻናት ስቃይ እና ሰቆቃ ተሞልታለች ፡፡ ያለፉትን እረስተን ዛሬም ለሌላ እየተዘጋጀን፡፡ እውን ለምድራችን የእግዚአብሔር ሃሳብ ይሄ ነውን፣ ስለ ምድራችን የሰማነው የምንናፍቀው ተስፋ ይህ ነው? አይመስለኝም፡፡ ዛሬ ሙሉቀን በዜና አውታሮቻ ከ35 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በሚኖርበት የአማራ ሕዝብ ስላለው ግጭት ስንሰማ ውለናል፡፡ ይህ በእጅጉ በእግዚአብሔር ፊት ልጸልይበት እና ልናነባበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ በዚያ ያለ ሕዝብ ከዚህ የተሻለ እና የተለየ ተስፋ አለው፡፡ ሰላም፣ እረፍት፣ ልማት፣ መረጋጋት የሚገባው ሕዝብ በጦርነት ንጹሐን ሕይወታቸውን ሊያጡ ነጋሪት እየተጎሰመ ነው፡፡ እንደ ክርስቲያን ምላሻችን የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ እና የእግዚአብሔር ጣልቃ ገብነት እንዲመጣ አጥብቀን መጸለይ ነው፡፡ ዳግም ዋይታ አይሁን፣ ሞት ይብቃ፣ ሕጻናት ያለአሳዳጊ አይቅሩ፣ ቤተሰብ አይበተን በቃን ለምድራችን ኢትዮጵያ -  ለሰሜን፣ ለደቡብ ፣ ለምስራቅ ምዕራብ ሁሉ ሰላም ይሁን፣ ማረፍ ይሁን፡፡ ወንጌል ሊያስመልጠው ሚገባውን ሕዝብ በጦርነት አይጨርሰው፡፡ አንቺ ኢትዮጵያ እረፍትሽ ይምጣ! ሁላችን ስለ አማራ ክልል እንድንጽልይ ይሁን !! ስለ አማራ ክልል እጸልያለሁ! #እግዚእሔር ሆይ ጣልቃ ግባ፤ በቃ በለን!" ©AmaNuGeze
Показать все...