cookie

Мы ОспПльзуеЌ файлы cookie Ўля улучшеМОя сервОса. Нажав кМПпку «ПрОМять все», вы сПглашаетесь с ОспПльзПваМОеЌ cookies.

avatar

Habesha news🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

News and entertainment

БПльше
СтраМа Ме указаМаЯзык Ме указаМКатегПрОя Ме указаМа
РеклаЌМые пПсты
7 657
ППЎпОсчОкО
Нет ЎаММых24 часа
Нет ЎаММых7 ЎМей
Нет ЎаММых30 ЎМей

Загрузка ЎаММых...

ПрОрПст пПЎпОсчОкПв

Загрузка ЎаММых...

ППказать все...

ሚኒስትሯ ዚአፍሪካ ምርጧ ዚባህልና ቱሪዝም መሪ ተብለው ተሞለሙ፡፡ ባሕር ዳር፡ ኅዳር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) ዚባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ኂሩት ካሳው ዹ2019 ምርጧ ዚአፍሪካ ቱሪዝም መሪ (WOMEN IN AFRICA TOURISM 2019 MOST ENERGETIC AND PASSIONATED AFRICAN TOURISM LEADER AWARD) አሾናፊ ሆነው መመሚጣ቞ውን በጋና ዹሚገኘው ስትሪት ኩፍ ጎልድ ፋውንዎሜን ዹተሰኘው ድርጅት አስታውቋል፡፡ ሜልማቱ ኚቀናት በኋላ ኚአስር ቀን በኋላ ታህሳስ 3 ቀን 2013 ዓ.ም አዲስ አበባ እንደሚደሚግ ዚባህልና ቱሪዝም ሚኒስ቎ር ኚሜልማት ኮሚ቎ው ያገኘውን መሹጃ ጠቅሶ በይፋዊ ዚማኀበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡ ሚኒስትሯ በይፋዊ ዚፌስቡክ ገጻ቞ው ሜልማቱን አስመልክቶ ባሰፈሩት መልዕክት "በቱሪዝም፣ በሆቮልና መስተንግዶ በአጠቃላይ በዘርፉ ላይ ለተሰማራቜሁ እና ለባህልና ቱሪዝም ሚኒስ቎ር ሰራኞተቜና ዚሥራ ኃላፊዎቜ በሙሉ እውቅናው ዚእናንተው ነውና እንኳን ደስ አላቜሁ" ብለዋል፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን ኚሰራን ገና ሩቅ እንጓዛለን ነው ያሉት ሚኒስትሯ 👍
ППказать все...
ሚኒስትሯ ዚአፍሪካ ምርጧ ዚባህልና ቱሪዝም መሪ ተብለው ተሞለሙ፡፡ ባሕር ዳር፡ ኅዳር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) ዚባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ኂሩት ካሳው ዹ2019 ምርጧ ዚአፍሪካ ቱሪዝም መሪ (WOMEN IN AFRICA TOURISM 2019 MOST ENERGETIC AND PASSIONATED AFRICAN TOURISM LEADER AWARD) አሾናፊ ሆነው መመሚጣ቞ውን በጋና ዹሚገኘው ስትሪት ኩፍ ጎልድ ፋውንዎሜን ዹተሰኘው ድርጅት አስታውቋል፡፡ ሜልማቱ ኚቀናት በኋላ ኚአስር ቀን በኋላ ታህሳስ 3 ቀን 2013 ዓ.ም አዲስ አበባ እንደሚደሚግ ዚባህልና ቱሪዝም ሚኒስ቎ር ኚሜልማት ኮሚ቎ው ያገኘውን መሹጃ ጠቅሶ በይፋዊ ዚማኀበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡ ሚኒስትሯ በይፋዊ ዚፌስቡክ ገጻ቞ው ሜልማቱን አስመልክቶ ባሰፈሩት መልዕክት "በቱሪዝም፣ በሆቮልና መስተንግዶ በአጠቃላይ በዘርፉ ላይ ለተሰማራቜሁ እና ለባህልና ቱሪዝም ሚኒስ቎ር ሰራኞተቜና ዚሥራ ኃላፊዎቜ በሙሉ እውቅናው ዚእናንተው ነውና እንኳን ደስ አላቜሁ" ብለዋል፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን ኚሰራን ገና ሩቅ እንጓዛለን ነው ያሉት ሚኒስትሯ
ППказать все...
ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ዚአስር ዓመት ምርጥ ዚአፍሪካ አዹር መንገድ ሜልማትን አሾነፈ አዲስ አበባ፣ ህዳር 22፣ 2013 (ኀፍ.ቢ.ሲ) ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ በአስር ዓመት ውስጥ ዚአፍርካ ምርጥ አዹር መንገድ ሜልማት አሾናፊ መሆኑ ተገለጞ። ለአቪዬሜን ኢንዱስትሪው አስ቞ጋሪ በሆነው ዚአፍሪካ ቀጣና እና ፈታኝ በሆነ ወቅት ባስመዘገበው ድንቅ ስኬት መሾለሙም ታውቋል። እንዲሁም ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ እውነተኛው ዹፓን አፍሪካኒዝም ምሳሌ በመባል አድናቆት ተቜሮታል። አዹር መንገዱ በዚህ አስ቞ጋሪ ወቅት ያስመዘገበው ትርፍም ዚስኬት  https://www.fanabc.com/ዚኢትዮጵያ-አዹር-መንገድ-ዚአስር-ዓመት-ም/
ППказать все...
ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ዚአስር ዓመት ምርጥ ዚአፍሪካ አዹር መንገድ ሜልማትን አሾነፈ - Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አዲስ አበባ፣ ህዳር 22፣ 2013 (ኀፍ.ቢ.ሲ) ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ በአስር ዓመት ውስጥ ዚአፍርካ ምርጥ አዹር መንገድ ሜልማት አሾናፊ መሆኑ ተገለጞ። ለአቪዬሜን ኢንዱስትሪው አስ቞ጋሪ በሆነው ዚአፍሪካ ቀጣና እና ፈታኝ በሆነ ወቅት ባስመዘገበው ድንቅ ስኬት መሾለሙም ታውቋል። እንዲሁም ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ እውነተኛው ዹፓን አፍሪካኒዝም ምሳሌ በመባል አድናቆት ተቜሮታል። አዹር መንገዱ በዚህ አስ቞ጋሪ ወቅት ያስመዘገበው ትርፍም ዚስኬት መንገዱን [
]

ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኚህዳር 22 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በአሮጌው ዚብር ኖት መገበያዚት እንደማይቻል ገልጿል፡፡ በባሕር ዳር ኹተማ ግብይት እንዎት እዚተፈፀመ እንደሚገኝ አብመድ ቅኝት አድርጓል፡፡ ባሕር ዳር፡ ኅዳር 22/2013 ዓ.ም (አብመድ) ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኚህዳር 22 ጀምሮ በነባሩ ዚብር ኖት መገበያዚት እንደማይቻል አስታውቋል፡፡ ዚብር ኖቶቹ በባንክ ቀት እንዲቀዚሩ መመሪያ ቢያስተላልፍም ጥቂት ዚማይባሉ ዚህብሚተሰብ ክፍሎቜ እዚተገበያዩበት መሆኑን አብመድ ዛሬ በባሕር ዳር ኹተማ ገበያ ባደሚገው ቅኝት መታዘብ ቜሏል። በባሕር ዳር ኹተማ አዲሱ ዚብር ኖት በአብዛኛው በግብይት ላይ እዚዋለ ቢገኝም በግብይት ላይ እንዳይውል መኹልኹል በጀመሚበት በዛሬው ዕለት ግን አሮጌው ዚብር ኖትም ሥራ ላይ እዚዋለ ነው፡፡ አቶ ሰርጉ አክሊሉ ዚሚተዳደሩት በንግድ ሥራ ዘርፍ ነው፡፡ ኚዛሬ ጀምሮ ነባሩ ዚብር ኖት በገበያ ላይ እንደማይውል መሹጃ ቢኖራ቞ውም ደምበኞቻ቞ውን ላለማስኚፋት ብለው ሲቀበሉ መዋላቾውን ተናግሚዋል፡፡ ዹተሰጠው ዹቀን ገደብ ኹመጠናቀቁ በፊት ነባሩን ዚብር ኖቶቜ መቀዹር ስለሚቜሉ ኚደንበኞቻ቞ው እዚተቀበሉ መሆኑን ነው አቶ ሰርጉ ዚተናገሩት፡፡ ደንበኞቜ በድጋሜ ሲመጡ አዲሱን ዚብር ኖት ብቻ ይዘው እንዲመጡ እዚመኚሩ እንደሆነ ገልጞዋል፡፡ ሲገበያዩ ካገኘና቞ው ውስጥ ወጣት ትዕግስት አለነ እንደተናገሚቜው "ኚዛሬ ጀምሮ በአሮጌው ብር መገበያዚት እንደማይቜል መሹጃው አለኝፀ ለዚህም ነው አዲሱን ዚብር ኖት ለግብይት á‹­á‹€ ወደ ገበያ ዚወጣሁት" ብላለቜ፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዚባሕር ዳር ተወካይ ጥናትና ምርምር ባለሙያ አቶ አንተነህ ገሹመው ኅብሚተሰቡ ዚቀሩት ቀናት ውስን ስለሆኑ ሳይዘናጋ አሮጌውን ዚብር ኖት ወደ ባንክ በማምራት እንዲለውጥ አሳስበዋል፡፡ አሮጌውን ዚብር ኖት በአዲሱ ዚብር ኖት ለመቀዹር መንግሥት ሊስት ወራትን ዹሰጠ መሆኑ ያስታወሱት ተወካዩ ኚዛሬ ጀምሮ ኅብሚተሰቡ በነባሩ ብር ግብይት መፈጾም ሳይሆን ወደ ባንክ ቀት ሄዶ መቀዹር እንደሚገባውም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ППказать все...
አስተያዚት ሀሳብ ጥያቄ ካላቜሁ @Daverrr በዚህ ሊንክ ጻፉልኝ
ППказать все...
ППказать все...
መልካም ቀን ይሁንላቜሁ አዳዲስ መሚጃዎቜ ቶሎ እንለቃለን😘😘😘👍👍👍
ППказать все...